cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Berbir Mereja / በርብር መረጃ

Welcome back to our channel, where we bring you the latest updates and news from around the world.

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
5 798
مشترکین
-124 ساعت
+17 روز
+2030 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

Photo unavailableShow in Telegram
ዛሬ የሩሲያ ጦር ባወጣው ሰበር መግለጫ ክራይሚያ ላይ ዘግናኝ ጥቃት ለመፈጸም የተለቀቁ አምስት የአሜሪካ አታካምስ ሚሳኤል ስርዓቶች ኢላማቸውን ከመምታታቸው በፊት የሩሲያን ሰማይ ከጭልፊት ሳይቀር የሚጠብቀው ኤስ-400 አየር ላይ አቅፎ ወደ ከሰልነት መለወጡን ነው ይፋ ያደረገው። አዳዲስ አለማቀፍ ሰበር ዜናዎችን ለማግኘት በነዚህ አማራጮች ይጠቀሙ 👇👇👇 👉👉Telegram :- https://t.me/berbirmereja 👉👉Facebook--› https://www.facebook.com/berbirmereja/ 👉👉YouTube: -, https://youtube.com/@BerbirMereja
نمایش همه...
👍 3
Photo unavailableShow in Telegram
ፑቲን ቤጂንግ ገቡ‼️ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ለሁለት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት ቻይና ገብተዋል። ፕሬዝዳንት ፑቲን በቤጂንግ ከቻይናው አቻቸው ሺ ጂንፒንግ ጋር የተገናኙ ሲሆን፥ 75 አመት ያስቆጠረውን የሀገራቱን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ተስማምተዋል። ፑቲን በዩክሬን “ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ” ከመጀመራቸው ከቀናት አስቀድሞ በቤጂንግ ጉብኝት ሲያደርጉ ሀገራቱ “ገደብ የለሽ” ትብብር መመስረታቸውን ይፋ ማድረጋቸውን ሬውተርስ አስታውሷል። ፕሬዝዳንቱ ሩሲያን እስከ 2030 ለመምራት ተመርጠው ቃለ መሃላ ከፈጸሙ በኋላ በቻይና የመጀመሪያ የውጭ ሀገር ጉብኝታቸውን ማድረጋቸውም ለትብብሩ የሰጡትን ትኩረት ያሳያል ተብሏል። ከፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር ዛሬ በቤጂንግ ሲገናኙም የሀገራቱ ትብብር ጥቅምን ብቻ የሚያሳድድና ሆን ብሎ የሆነ አካልን ለመጉዳት ያለመ አለመሆኑን መናገራቸውን የሩሲያው አርአይኤ ኖቮስቲ የዜና ወኪልን ጠቅሶ አልአይን ዘግቧል። አዳዲስ አለማቀፍ ሰበር ዜናዎችን ለማግኘት በነዚህ አማራጮች ይጠቀሙ 👇👇👇 👉👉Telegram :- https://t.me/berbirmereja 👉👉Facebook--› https://www.facebook.com/berbirmereja/ 👉👉YouTube: -, https://youtube.com/@BerbirMereja
نمایش همه...
👍 1
የፌደራል መንግሥት በኤሌክትሪክ እና በውሃ አገልግሎት ላይ ቫት የሚጥል ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማ አቀረበ የኤሌክትሪክ እና የውሃ አገልግሎት በገደብ የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) እንዲከፈልባቸው የሚያደርግ ረቂቅ አዋጅ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀረበ። ከታክሱ ነጻ የሚሆኑት የገንዘብ ሚኒስቴር በሚያወጣው መመሪያ ከሚወሰን በታች የኤሌክትሪክ እና ውሃ ፍጆታ ያላቸው እንደሆኑ ተገልጿል። አዋጁ ሲጸድቅ ለሁለት አስርት ዓመታት በስራ ላይ ቆየውን የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ እና ከዛ በኋላ እሱን ለማሻሻል ሁለት ጊዜ የወጡትን የማሻሻያ አዋጆች ሙሉ በሙሉ የሚሽር ነው ተብሏል። “አነስተኛ ገቢ ያለው የህብረተሰብ ክፍል ያለበትን ወጪ ለማርገብ ሲባል” የኤሌክትሪክ እና የውሃ አገልግሎት ከታክሱ ነጻ ተደርገው እንደነበር ሲገለፅ ረቂቁ “የተጨማሪ እሴት ታክስ ከሚታይበት ጉድለት አንዱ እና ዋነኛው በርካታ ዕቃዎች እና አገልግሎቶች ከታክሱ ነጻ መደረጋቸው ነው” ይላል። በረቂቅ አዋጁ ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ በማድረግ የተሰጠውን “ልዩ መብት” እንደገና በመፈተሽ ማስተካከያዎች መደረጋቸውን ማብራሪያው ይገልጻል። ከታክስ ነጻ ተደርገው አሁን ታክስ እንዲከፈልባቸው ከተደረጉ አግልግሎቶች መካከል የውሃ እና ኤሌክትሪክ እንዲሁም የትራንስፖርት አገልግሎቶች ይገኙበታልም ተብሏል። በስራ ላይ ያለው አዋጅ የኤሌክትሪክ፣ የኬሮሲን [ናፍጣ] እና የውሃ እንዲሁም የትራንስፖርት አገልግሎትን ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ እንዲሆኑ እድርጎ ነበር። ይህን አዋጅ የሚሽረው አዲሱ ረቂቅ አዋጅ ግን የውሃ የኤሌክትሪክ፣ የውሃ እና የትራንስፖርት አገልግሎቶች በገደብ ታክስ እንዲከፈልባቸው አድርጓልም ነው የተባለው።(BBC Amharic) አዳዲስ አለማቀፍ ሰበር ዜናዎችን ለማግኘት በነዚህ አማራጮች ይጠቀሙ 👇👇👇 👉👉Telegram :- https://t.me/berbirmereja 👉👉Facebook--› https://www.facebook.com/berbirmereja/ 👉👉YouTube: -, https://youtube.com/@BerbirMereja
نمایش همه...
Berbir Mereja / በርብር መረጃ

Welcome back to our channel, where we bring you the latest updates and news from around the world.

Photo unavailableShow in Telegram
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ቪኤአር (VAR) እንዲቀር በሚያደርግ ሐሳብ ላይ ድምፅ ሊሰጡ ነው ተባለ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች በሚቀጥለው ወር በሚካሄደው ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ቪኤአር (VAR) ይቅር ወይስ ይቀጥል የሚለውን በድምፅ ይወስናሉ ተብሏል። ቪኤአር (VAR) በእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ጥቅም ላይ መዋል የጀመረው በአውሮፓውያኑ 2019 ሲሆን ዓላማው በወሳኝ ውሳኔዎች ላይ ዳኞችን ማገዝ ቢሆንም በተለይ በዘንድሮው የውድድር ዓመት በርካታ አከራካሪ ውሳኔዎች ተሰጥተዉበታል ይባላል። ዎልቭስ ለፕሪሚዬር ሊጉ ባስገባው የመፍትሔ ሐሳብ መሠረት ቀሪዎቹ 20 ክለቦች በቪኤአር ዕጣ ፈንታ ላይ ድምፅ ለመስጠት በመጭው ሰኔ ይሰየማሉ። ክለቡ እንዳለው ምንም እንኳ "ቪኤአር ለበጎ ሥራ" ቢሆንም ጥቅም ላይ የዋለው "ያልታሰባበቸው በርካታ አሉታዊ ጎኖቹ በደጋፊዎች እና በእግር ኳስ መካከል ያለው ግንኙነት እንዲጠለሽ እያደረጉት ነው።" የዎልቭስ መግለጫ አክሎ እንደሚለው "የውሳኔን ትክክለኛነት ትንሽ ከፍ ለማድረግ በሚል የጨዋታው መንፈስ እየተነካ ነው።" በፕሪሚዬር ሊጉ ሕግ መሠረት ማንኛውም አዋጅ እንዲፀድቅ ሁለት ሶስተኛ ድምፅ ማግኘት አለበት። ይህ ማለት ከ20 ቡድኖች ቢያንስ 14 ቡድኖች ሊደግፉት ይገባል። አዳዲስ አለማቀፍ ሰበር ዜናዎችን ለማግኘት በነዚህ አማራጮች ይጠቀሙ 👇👇👇 👉👉Telegram :- https://t.me/berbirmereja 👉👉Facebook--› https://www.facebook.com/berbirmereja/ 👉👉YouTube: -, https://youtube.com/@BerbirMereja
نمایش همه...
👍 2
#የአሜሪካ_አቋም! " ግጭት የኢትዮጵያውያንን #ስቃይ_ከማባባስ ያለፈ መፍትሔ የለውም " - አሜሪካ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ አሜሪካ ስለ ኢትዮጵያ ያላትን ፖሊሲ በተመለከተ ምን አሉ ? - በትጥቅ ግጭት ውስጥ የገቡ አካላት፣ ግጭት አቁመው በንግግር ሰላምን ሊያሰፍኑና የሰብአዊ መብቶችን ማክበር አለባቸው። - የታጠቁ ቡድኖች ፖለቲካዊ ዓላማዎቻቸውን በአመፅ ለማሳካት እየገፉ ናቸው ፤ መንግስትም ይህን ለመከላከል የሚወስዳቸው ርምጃዎች፣ በፖለቲካ ምኅዳሩ ላይ የማይካድ ተጽእኖ አለው። ውይይትን ወደ ጎን ያለው ይህ አካሔድ የመብት ጥሰቶች እንዲቀጥሉ አድርጓል። - ሰላማዊ ዜጎች፣ በተለያዩ ኀይሎች ከሕግ ውጭ ግድያ፣ የዘፈቀደ እስራት፣ አስገዳጅ ስወራ፣ ከግጭት ጋራ የተያያዘ ጾታዊ ጥቃት እና ሌሎችም ጥቃቶች እየተፈጸሙባቸው መሆኑን የሚገልጹ ዘገባዎችን ማየቱ እጅግ ያሳዝናል። - የተፈጸሙ ጥፋቶች እውነተኛና ግልጽ የሽግግር ፍትሕ ሒደት በተከተለ የተጠያቂነት አሰራር በአስቸኳይ ሊፈቱ ይገባል። - ሽፍታዎች፣ የታጠቁ ቡድኖች፣ አንዳንዴም የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች፤ በህይወት የመኖር፣ የሰብዓዊ ክብርን፣ መከበርን በመሰሉ መብቶች ላይ ያለምንም ተጠያቂነት ጥሰቶች ይፈጽማሉ። - በጦርነት እና ግጭት ወቅት እንኳ የሰብዓዊ መብቶች ሊረሱ አይገባም። - ሁሉም ሀገር ራሱን የመከላከል ህጋዊ መብት አለው፤ ሆኖም ሀገራት ራሳቸውን የሚከላከሉበት መንገድ ያለምንም ጥርጥር የወደፊት ግጭቶችን አካሄድ የሚወስን ነው። - ሀገር የመከላከያ መንገዶቹ በዛሬው እና በወደፊቱ የማህብረሰብ ትስስር ላይ ይበልጡኑ ተጽዕኖ የሚያሳድር ነው። - የታጠቁ ወገኖች የፖለቲካ ግባቸውን ከውይይት ይልቅ በግጭት ለማሳካት ሲሞክሩ፤ ለሚፈጸሙ በደሎች ሁኔታዎች የተመቻቹ ይሆናሉ። - በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱት እራሳቸውን ' ፋኖ ' ብለው የሚጠሩ ታጣቂ ቡድኖች ንግግር / ድርድር አንቀበልም ማለታቸው እራሳቸውን ነው የሚጎዳቸው። በአማራ ያሉ በርካታ ሰዎች " የቆሙለት ዓላማ ፍትሃዊ ነው " የሚል እምነት/አላቸው ይህንኑ መከራከሪያቸውን ከግጭት ይልቅ በውይይት ማቅረብ አለባቸው። - በአማራ ክልል ውጊያዎች የሚቀጥሉ ከሆነ በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች እንዳለው በውጤቱ የሚሰቃዩት ሰላማዊ ሰዎች ናቸው።   - ህወሓት በኀይል ወሰን ለማስመለስ ከሚደረግ እንቅስቃሴ መቆጠብ አለበት። - የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ኃይሎች በድርድር ተስፋ ሳይቆርጡ መተማመን ለመገንባት የሰላም ውይይትን ሊቀጥሉ ይገባል። - ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በውስጣዊ ግጭቶች እየታመሰች ትገኛለች። - የኢትዮጵያ መንግስት የአገሪቱን ችግሮች በኀይል ለመፍታት ከሚያደርገው ጥረት መቆጠብ አለበት። በእስር ላይ የሚገኙ ቁልፍ የፖለቲካ ሰዎችን መፍታቱ ጠቃሚ ነው፤ ያን ተፈጻሚ ማድረግ ኢትዮጵያውያን የሚፈልጉትን የፖለቲካ ውይይት ሊያግዝ ይችላል። - ጊዜያዊ አገር አቀፍ የተኩስ አቁም ስምምነት ሊፈጸም ይገባል። - ሁሉም የታጠቁ ተዋናዮች፣ በመላ አገሪቱ አዲስ የሕዝብ መፈናቀልን ጨምሮ ለሰዎች ስቃይ ምክንያት ከመሆን መገታት አለባቸው። - የታጣቁ ኃይሎች ት/ቤቶችን፣ ጤና ተቋማትንና የውኃ መሠረተ ልማቶችን ዒላማ ማድረግ ማቆም አለባቸው። የተሟላና ያልተገደበ ሰብአዊ አቅርቦት ሊኖር ይገባል። ይህም ጊዜያዊ አገር አቀፍ የተኩስ አቁም ማድረግን ይጨምራል። - ግጭት የኢትዮጵያውያንን ሥቃይ ከማባባስ ያለፈ መፍትሔ የለውም። ውይይት ትኩረት ሊደረግበት ይገባል። - ምንም እንኳን ፍጹም ሊሆን ባይችልም፣ ሁሉም ወገኖች የአገራዊ ምክክሩን ዕድል ሊጠቀሙበት ይገባል። #USEmbassyAddisAbaba #VOA #EthiopiaInsider #tikvahethiopia አዳዲስ አለማቀፍ ሰበር ዜናዎችን ለማግኘት በነዚህ አማራጮች ይጠቀሙ 👇👇👇 👉👉Telegram :- https://t.me/berbirmereja 👉👉Facebook--› https://www.facebook.com/berbirmereja/ 👉👉YouTube: -, https://youtube.com/@BerbirMereja
نمایش همه...

👍 4
00:20
Video unavailableShow in Telegram
ትራምፕ በቀጣይ የአሜሪካ ኘሬዚዳንት ሆነው ከተመረጡ የፍልስጤም ደጋፊ የሆኑ የእስራኤል ተቃዋሚዎችን ከዩኒቨርሲቲዎች ብቻ ሳይሆን ከአገረ አሜሪካ ጭምር ለማባረር ቃል ገብተዋል። " በተለይም ከሌላ አገር ወደ አሜሪካ መጥተህ ጂሃዲዝምን፣ ፀረ-አሜሪካኒዝምን ወይም ፀረ ሴማዊነትን በዩኒቨርሲቲዎቻችን ለማንፀባረቅ ከሞከርክ ወዲያውኑ ከአገራችን እናባርርሃለን" ሲሉ ዝተዋል። ይህንን የተመለከቱ የፖለቲካ ተንታኞች ሁኔታውን (ንግግራቸውን) " ብልጣ-ብልጡ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ያለ ተቀናቃኝ ወደ ስልጣን ለመመለስ የተጠቀሙበት የፖለቲካ አካሄድ ነው " ብለውታል። አዳዲስ አለማቀፍ ሰበር ዜናዎችን ለማግኘት በነዚህ አማራጮች ይጠቀሙ 👇👇👇 👉👉Telegram :- https://t.me/berbirmereja 👉👉Facebook--› https://www.facebook.com/berbirmereja/ 👉👉YouTube: -, https://youtube.com/@BerbirMereja
نمایش همه...
🌚 2👎 1
Photo unavailableShow in Telegram
በኢትዮጵያ ያሉ ሁሉም የታጠቁ ኃይሎች “ጊዜያዊ ሀገር አቀፍ የተኩስ ማቆም” እንዲያደርጉ የአሜሪካ አምባሳደር ጠየቁ በኢትዮጵያ ያሉ ሁሉም የታጠቁ ኃይሎች “ጊዜያዊ ሀገር አቀፍ የተኩስ ማቆም” እንዲያደርጉ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኢርቪን ማሲንጋ ጥሪ አቀረቡ። ታጣቂዎቹ ትምህርት ቤቶች፣ የጤና ተቋማትን እና የውሃ መሰረተ ልማቶችን ኢላማ ማድረጋቸውን እንዲያቆሙም አምባሳደሩ አሳስበዋል። በአምባሳደርነት ተሹመው ወደ ኢትዮጵያ ከመጡ ስምንት ወር የሞላቸው ማሲንጋ፤ ከእርሳቸው በፊት በነበሩ አምባሳደሮች ሲተገበር እምብዛም ያልታየውን ይፋዊ የፖሊሲ መልዕክት በዛሬው ዕለት አስደምጠዋል። አምባሳደሩ መልዕክታቸውን ለማስተላለፍ የመረጡት ታሪካዊው የአሜሪካን ግቢ፤ የንግግራቸው ማጠንጠኛ ከነበረው የሰብዓዊ መብት ጉዳይ ጋር ቁልፍ ተዛምዶ ያለው ነው። በአሁኑ ወቅት የየመን ማህበረሰብ ትምህርት ቤት አካል የሆነው የቀድሞው የአሜሪካ ቆንስላ ግቢ፤ በጣሊያን ወረራ ወቅት የየካቲት 12 ጭፍጨፋ ሲካሄድ 750 የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን ተሸሽገውበት የነበረ ነው። ማሲንጋ በንግግራቸው ወቅቱን ሲያስታውሱ፤ “በሺህዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ያለምንም ማስረጃ እና የህግ ሂደት “ኢላማ የተደረጉበት ነበር” ብለዋል። Via Ethiopiainsider አዳዲስ አለማቀፍ ሰበር ዜናዎችን ለማግኘት በነዚህ አማራጮች ይጠቀሙ 👇👇👇 👉👉Telegram :- https://t.me/berbirmereja 👉👉Facebook--› https://www.facebook.com/berbirmereja/ 👉👉YouTube: -, https://youtube.com/@BerbirMereja
نمایش همه...
👍 3🥴 1
نمایش همه...
ለየለት ሩሲያ በአሜሪካ ሚሳኤል ተመታች፤ቀዩ መስመር ተጣሰ፤አለምን ያራደ ጉድ መጣ፤እስራኤል በጋዛ ያልጠበቀችዉ መርዶ ደረሳት

#berbirmereja #berbirnews #berbirnewstoday #ethiopiannews #ethiopia #ethiopiannewstoday #berbirethiopiannewsበየጊዜዉ ለሚለቀቁ ትኩስና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት ሰብስክራይብ ያድርጉ👉...

4
የደመወዝ ስኬል ማስተካከያ በየአራት ዓመቱ እየተጠና፣ ይወሰናል ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበው የፌደራል መንግስት ሰራተኞች ረቂቅ አዋጅ ከሚያስተዋውቃቸው ለውጦች ውስጥ አንዱ የደመወዝ ስኬል ማስተካከያ በምን ያህል ጊዜ እንደሚደረግ ማስቀመጡ ነው። በስራ ላይ ያለው አዋጅ የመንግስት ሰራተኞች የደመወዝ ስኬል “የመንግስትን የፋይናንስ አቅም፣ የህዝቡን አጠቃላይ የኑሮ ሁኔታ፣ የዋጋ ደረጃዎች እና አግባብነት ያላቸውን ሌሎች ሁኔታዎች ባገናዘበ መንገድ” እየተጠና እንደሚወሰን ይደነግጋል። ይሁንና አዋጁ “በየጊዜው እየተጠና የሚወሰን ይሆናል” እንዲሁም “አስፈላጊ ሆኖ” ሲገኝ የደመወዝ ስኬል ተጠንቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት እንደሚቀርብ ከመደንገግ ውጪ ይህ ጥናት በምን ያህል ጊዜ እንደሚደረግ አያስቀምጥም። አዲሱ ረቂቅ አዋጅ በአንጻሩ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን “የሥራ ደረጃ መነሻ ዝቅተኛ ደመወዝ እና ከፍተኛ ደመወዝ ጣሪያ በየአራት አመቱ አጥንቶ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት አቅርቦ” እንደሚያስወስን እንዲሁም አፈጻጸሙን እንደሚቆጣጠር ያስቀምጣል። ኮሚሽኑ የሚያደርገው የአበል ማስተካከያም በተመሳሳይ የጊዜ ገደብ ተቀምጦለታል። በረቂቅ አዋጁ፤ “የመንግስት ሠራተኛ ወጪን መሸፈን የሚያስችል ልዩ ልዩ የአበል አይነቶች እና የቀን ውሎ አበል ማስተካከያ በየሁለት አመት ኮሚሽኑ ይወስናል” ሲል በየስንት ጊዜው ማስተካከያ እንደሚደረግ ይወስናል። የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን የደመወዝ ስኬልን ለማስተካከል በየአራት ዓመቱ የሚያደርገውን ጥናት ለሚኒስትሮች ምክር ቤት ከማቅረቡ አስቀድሞ ግን ማረጋገጫ የመስጠት ኃላፊነት ያለው አዲስ ቦርድ በረቂቅ አዋጁ ተዋውቋል። አዳዲስ አለማቀፍ ሰበር ዜናዎችን ለማግኘት በነዚህ አማራጮች ይጠቀሙ 👇👇👇 👉👉Telegram :- https://t.me/berbirmereja 👉👉Facebook--› https://www.facebook.com/berbirmereja/ 👉👉YouTube: -, https://youtube.com/@BerbirMereja
نمایش همه...
Berbir Mereja / በርብር መረጃ

Welcome back to our channel, where we bring you the latest updates and news from around the world.

👍 1