cookie

نحن نستخدم ملفات تعريف الارتباط لتحسين تجربة التصفح الخاصة بك. بالنقر على "قبول الكل"، أنت توافق على استخدام ملفات تعريف الارتباط.

avatar

Berbir Mereja / በርብር መረጃ

Welcome back to our channel, where we bring you the latest updates and news from around the world.

إظهار المزيد
مشاركات الإعلانات
5 798
المشتركون
-124 ساعات
+17 أيام
+2030 أيام

جاري تحميل البيانات...

معدل نمو المشترك

جاري تحميل البيانات...

Photo unavailableShow in Telegram
እስራኤል የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን “አሸባሪ ድርጅት” ብላ አወጀች !! በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የእስራኤል መንግስት ተወካይ " እስራኤል ከጋዛ ሰርጥ ከወጣች በኋላ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከሃማስ ጋር ሲተባበር እና ወንጀላቸውን ሲሸፍን ቆይቷል እናም የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እራሱ አሸባሪ ድርጅት ሆኗል" ሲሉ ተቋሙን አውግዘዋል። አዳዲስ አለማቀፍ ሰበር ዜናዎችን ለማግኘት በነዚህ አማራጮች ይጠቀሙ 👇👇👇 👉👉Telegram :- https://t.me/berbirmereja 👉👉Facebook--› https://www.facebook.com/berbirmereja/ 👉👉YouTube: -, https://youtube.com/@BerbirMereja
إظهار الكل...
👍 2😁 1
" አምባሳደሩ ንግግራቸው ሀገሪቷን እንዴት መምራት እንዳለብን ያልተጠየቀ ምክር ለመመምከር የሞከረ ነው " - መንግሥት የኢትዮጵያ መንግሥት በአሜሪካ አምባሳደር የተንጸባረቀው ሀሳብ " ሀሰተኛ እና ተቀባይነት የሌለው ነው " ብሎታል። በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ ትላንት አሜሪካ ስለ ኢትዮጵያ ያላትን ፖሊሲ በንግግር ማሰማታቸው ይታወሳል። ይህን በተመለከተ ዛሬ የኢትዮጵያ መንግሥት በውጭ ጉዳይ በኩል መግለጫ አውጥቷል። በዚህም የአምባሳደሩ ንግግር " በተረጋገጠ መረጃ ላይ ያልተመሰረተ ነው " ብሎታል። " በምርጫ ወደ ስልጣን የመጣን መንግስት እንጥላለን በሚል የሚንቀሳቀሱ፣ ንጹሃንን ከሚያግቱና ከሚያሸብሩ አካላት ጋር መንግስትን መጥቀሳቸውም ተገቢ አይደለም " ብሏል። ንግግራቸው " የኢትዮጵያ መንግስት ሀገሪቷን እንዴት መምራት እንዳለበት ያልተጠየቀ ምክር ለመመምከር የሞከረ ነው " በማለት ገልጾታል። " ከሁለቱ ሀገራት ታሪካዊና ወዳጅነት ላይ ከተመሰረተው ግንኙነት የተቃረነ ነው " ሲልም አክሏል። መንግሥት በመግለጫው ላይ ፤ " የተፈጸመው ዲፕለማሲያዊ ስህተት ነው " ያለ ሲሆን በአዲስ አበባ ከሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ጋር በመስራት የተፈጠረውን ስህተት እንዲታረም እንደሚደርግ ገልጿል። ኢትዮጵያ የሰላምና የጸጥታ ጉዳዮችን ጨምሮ ከአሜሪካ ጋር ለመስራት ያላትን ዝግጁነትም ገልጿል። አዳዲስ አለማቀፍ ሰበር ዜናዎችን ለማግኘት በነዚህ አማራጮች ይጠቀሙ 👇👇👇 👉👉Telegram :- https://t.me/berbirmereja 👉👉Facebook--› https://www.facebook.com/berbirmereja/ 👉👉YouTube: -, https://youtube.com/@BerbirMereja
إظهار الكل...
👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
ዛሬ የሩሲያ ጦር ባወጣው ሰበር መግለጫ ክራይሚያ ላይ ዘግናኝ ጥቃት ለመፈጸም የተለቀቁ አምስት የአሜሪካ አታካምስ ሚሳኤል ስርዓቶች ኢላማቸውን ከመምታታቸው በፊት የሩሲያን ሰማይ ከጭልፊት ሳይቀር የሚጠብቀው ኤስ-400 አየር ላይ አቅፎ ወደ ከሰልነት መለወጡን ነው ይፋ ያደረገው። አዳዲስ አለማቀፍ ሰበር ዜናዎችን ለማግኘት በነዚህ አማራጮች ይጠቀሙ 👇👇👇 👉👉Telegram :- https://t.me/berbirmereja 👉👉Facebook--› https://www.facebook.com/berbirmereja/ 👉👉YouTube: -, https://youtube.com/@BerbirMereja
إظهار الكل...
👍 4👏 1
Photo unavailableShow in Telegram
ፑቲን ቤጂንግ ገቡ‼️ የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ለሁለት ቀናት ይፋዊ ጉብኝት ቻይና ገብተዋል። ፕሬዝዳንት ፑቲን በቤጂንግ ከቻይናው አቻቸው ሺ ጂንፒንግ ጋር የተገናኙ ሲሆን፥ 75 አመት ያስቆጠረውን የሀገራቱን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር ተስማምተዋል። ፑቲን በዩክሬን “ልዩ ወታደራዊ ዘመቻ” ከመጀመራቸው ከቀናት አስቀድሞ በቤጂንግ ጉብኝት ሲያደርጉ ሀገራቱ “ገደብ የለሽ” ትብብር መመስረታቸውን ይፋ ማድረጋቸውን ሬውተርስ አስታውሷል። ፕሬዝዳንቱ ሩሲያን እስከ 2030 ለመምራት ተመርጠው ቃለ መሃላ ከፈጸሙ በኋላ በቻይና የመጀመሪያ የውጭ ሀገር ጉብኝታቸውን ማድረጋቸውም ለትብብሩ የሰጡትን ትኩረት ያሳያል ተብሏል። ከፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ ጋር ዛሬ በቤጂንግ ሲገናኙም የሀገራቱ ትብብር ጥቅምን ብቻ የሚያሳድድና ሆን ብሎ የሆነ አካልን ለመጉዳት ያለመ አለመሆኑን መናገራቸውን የሩሲያው አርአይኤ ኖቮስቲ የዜና ወኪልን ጠቅሶ አልአይን ዘግቧል። አዳዲስ አለማቀፍ ሰበር ዜናዎችን ለማግኘት በነዚህ አማራጮች ይጠቀሙ 👇👇👇 👉👉Telegram :- https://t.me/berbirmereja 👉👉Facebook--› https://www.facebook.com/berbirmereja/ 👉👉YouTube: -, https://youtube.com/@BerbirMereja
إظهار الكل...
👍 3
የፌደራል መንግሥት በኤሌክትሪክ እና በውሃ አገልግሎት ላይ ቫት የሚጥል ረቂቅ አዋጅ ለፓርላማ አቀረበ የኤሌክትሪክ እና የውሃ አገልግሎት በገደብ የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) እንዲከፈልባቸው የሚያደርግ ረቂቅ አዋጅ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀረበ። ከታክሱ ነጻ የሚሆኑት የገንዘብ ሚኒስቴር በሚያወጣው መመሪያ ከሚወሰን በታች የኤሌክትሪክ እና ውሃ ፍጆታ ያላቸው እንደሆኑ ተገልጿል። አዋጁ ሲጸድቅ ለሁለት አስርት ዓመታት በስራ ላይ ቆየውን የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ እና ከዛ በኋላ እሱን ለማሻሻል ሁለት ጊዜ የወጡትን የማሻሻያ አዋጆች ሙሉ በሙሉ የሚሽር ነው ተብሏል። “አነስተኛ ገቢ ያለው የህብረተሰብ ክፍል ያለበትን ወጪ ለማርገብ ሲባል” የኤሌክትሪክ እና የውሃ አገልግሎት ከታክሱ ነጻ ተደርገው እንደነበር ሲገለፅ ረቂቁ “የተጨማሪ እሴት ታክስ ከሚታይበት ጉድለት አንዱ እና ዋነኛው በርካታ ዕቃዎች እና አገልግሎቶች ከታክሱ ነጻ መደረጋቸው ነው” ይላል። በረቂቅ አዋጁ ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ በማድረግ የተሰጠውን “ልዩ መብት” እንደገና በመፈተሽ ማስተካከያዎች መደረጋቸውን ማብራሪያው ይገልጻል። ከታክስ ነጻ ተደርገው አሁን ታክስ እንዲከፈልባቸው ከተደረጉ አግልግሎቶች መካከል የውሃ እና ኤሌክትሪክ እንዲሁም የትራንስፖርት አገልግሎቶች ይገኙበታልም ተብሏል። በስራ ላይ ያለው አዋጅ የኤሌክትሪክ፣ የኬሮሲን [ናፍጣ] እና የውሃ እንዲሁም የትራንስፖርት አገልግሎትን ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነጻ እንዲሆኑ እድርጎ ነበር። ይህን አዋጅ የሚሽረው አዲሱ ረቂቅ አዋጅ ግን የውሃ የኤሌክትሪክ፣ የውሃ እና የትራንስፖርት አገልግሎቶች በገደብ ታክስ እንዲከፈልባቸው አድርጓልም ነው የተባለው።(BBC Amharic) አዳዲስ አለማቀፍ ሰበር ዜናዎችን ለማግኘት በነዚህ አማራጮች ይጠቀሙ 👇👇👇 👉👉Telegram :- https://t.me/berbirmereja 👉👉Facebook--› https://www.facebook.com/berbirmereja/ 👉👉YouTube: -, https://youtube.com/@BerbirMereja
إظهار الكل...
Berbir Mereja / በርብር መረጃ

Welcome back to our channel, where we bring you the latest updates and news from around the world.

Photo unavailableShow in Telegram
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች ቪኤአር (VAR) እንዲቀር በሚያደርግ ሐሳብ ላይ ድምፅ ሊሰጡ ነው ተባለ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች በሚቀጥለው ወር በሚካሄደው ጠቅላላ ጉባዔ ላይ ቪኤአር (VAR) ይቅር ወይስ ይቀጥል የሚለውን በድምፅ ይወስናሉ ተብሏል። ቪኤአር (VAR) በእንግሊዝ ፕሪሚዬር ሊግ ጥቅም ላይ መዋል የጀመረው በአውሮፓውያኑ 2019 ሲሆን ዓላማው በወሳኝ ውሳኔዎች ላይ ዳኞችን ማገዝ ቢሆንም በተለይ በዘንድሮው የውድድር ዓመት በርካታ አከራካሪ ውሳኔዎች ተሰጥተዉበታል ይባላል። ዎልቭስ ለፕሪሚዬር ሊጉ ባስገባው የመፍትሔ ሐሳብ መሠረት ቀሪዎቹ 20 ክለቦች በቪኤአር ዕጣ ፈንታ ላይ ድምፅ ለመስጠት በመጭው ሰኔ ይሰየማሉ። ክለቡ እንዳለው ምንም እንኳ "ቪኤአር ለበጎ ሥራ" ቢሆንም ጥቅም ላይ የዋለው "ያልታሰባበቸው በርካታ አሉታዊ ጎኖቹ በደጋፊዎች እና በእግር ኳስ መካከል ያለው ግንኙነት እንዲጠለሽ እያደረጉት ነው።" የዎልቭስ መግለጫ አክሎ እንደሚለው "የውሳኔን ትክክለኛነት ትንሽ ከፍ ለማድረግ በሚል የጨዋታው መንፈስ እየተነካ ነው።" በፕሪሚዬር ሊጉ ሕግ መሠረት ማንኛውም አዋጅ እንዲፀድቅ ሁለት ሶስተኛ ድምፅ ማግኘት አለበት። ይህ ማለት ከ20 ቡድኖች ቢያንስ 14 ቡድኖች ሊደግፉት ይገባል። አዳዲስ አለማቀፍ ሰበር ዜናዎችን ለማግኘት በነዚህ አማራጮች ይጠቀሙ 👇👇👇 👉👉Telegram :- https://t.me/berbirmereja 👉👉Facebook--› https://www.facebook.com/berbirmereja/ 👉👉YouTube: -, https://youtube.com/@BerbirMereja
إظهار الكل...
👍 2
#የአሜሪካ_አቋም! " ግጭት የኢትዮጵያውያንን #ስቃይ_ከማባባስ ያለፈ መፍትሔ የለውም " - አሜሪካ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኧርቪን ማሲንጋ አሜሪካ ስለ ኢትዮጵያ ያላትን ፖሊሲ በተመለከተ ምን አሉ ? - በትጥቅ ግጭት ውስጥ የገቡ አካላት፣ ግጭት አቁመው በንግግር ሰላምን ሊያሰፍኑና የሰብአዊ መብቶችን ማክበር አለባቸው። - የታጠቁ ቡድኖች ፖለቲካዊ ዓላማዎቻቸውን በአመፅ ለማሳካት እየገፉ ናቸው ፤ መንግስትም ይህን ለመከላከል የሚወስዳቸው ርምጃዎች፣ በፖለቲካ ምኅዳሩ ላይ የማይካድ ተጽእኖ አለው። ውይይትን ወደ ጎን ያለው ይህ አካሔድ የመብት ጥሰቶች እንዲቀጥሉ አድርጓል። - ሰላማዊ ዜጎች፣ በተለያዩ ኀይሎች ከሕግ ውጭ ግድያ፣ የዘፈቀደ እስራት፣ አስገዳጅ ስወራ፣ ከግጭት ጋራ የተያያዘ ጾታዊ ጥቃት እና ሌሎችም ጥቃቶች እየተፈጸሙባቸው መሆኑን የሚገልጹ ዘገባዎችን ማየቱ እጅግ ያሳዝናል። - የተፈጸሙ ጥፋቶች እውነተኛና ግልጽ የሽግግር ፍትሕ ሒደት በተከተለ የተጠያቂነት አሰራር በአስቸኳይ ሊፈቱ ይገባል። - ሽፍታዎች፣ የታጠቁ ቡድኖች፣ አንዳንዴም የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች፤ በህይወት የመኖር፣ የሰብዓዊ ክብርን፣ መከበርን በመሰሉ መብቶች ላይ ያለምንም ተጠያቂነት ጥሰቶች ይፈጽማሉ። - በጦርነት እና ግጭት ወቅት እንኳ የሰብዓዊ መብቶች ሊረሱ አይገባም። - ሁሉም ሀገር ራሱን የመከላከል ህጋዊ መብት አለው፤ ሆኖም ሀገራት ራሳቸውን የሚከላከሉበት መንገድ ያለምንም ጥርጥር የወደፊት ግጭቶችን አካሄድ የሚወስን ነው። - ሀገር የመከላከያ መንገዶቹ በዛሬው እና በወደፊቱ የማህብረሰብ ትስስር ላይ ይበልጡኑ ተጽዕኖ የሚያሳድር ነው። - የታጠቁ ወገኖች የፖለቲካ ግባቸውን ከውይይት ይልቅ በግጭት ለማሳካት ሲሞክሩ፤ ለሚፈጸሙ በደሎች ሁኔታዎች የተመቻቹ ይሆናሉ። - በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱት እራሳቸውን ' ፋኖ ' ብለው የሚጠሩ ታጣቂ ቡድኖች ንግግር / ድርድር አንቀበልም ማለታቸው እራሳቸውን ነው የሚጎዳቸው። በአማራ ያሉ በርካታ ሰዎች " የቆሙለት ዓላማ ፍትሃዊ ነው " የሚል እምነት/አላቸው ይህንኑ መከራከሪያቸውን ከግጭት ይልቅ በውይይት ማቅረብ አለባቸው። - በአማራ ክልል ውጊያዎች የሚቀጥሉ ከሆነ በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች እንዳለው በውጤቱ የሚሰቃዩት ሰላማዊ ሰዎች ናቸው።   - ህወሓት በኀይል ወሰን ለማስመለስ ከሚደረግ እንቅስቃሴ መቆጠብ አለበት። - የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት ኃይሎች በድርድር ተስፋ ሳይቆርጡ መተማመን ለመገንባት የሰላም ውይይትን ሊቀጥሉ ይገባል። - ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በውስጣዊ ግጭቶች እየታመሰች ትገኛለች። - የኢትዮጵያ መንግስት የአገሪቱን ችግሮች በኀይል ለመፍታት ከሚያደርገው ጥረት መቆጠብ አለበት። በእስር ላይ የሚገኙ ቁልፍ የፖለቲካ ሰዎችን መፍታቱ ጠቃሚ ነው፤ ያን ተፈጻሚ ማድረግ ኢትዮጵያውያን የሚፈልጉትን የፖለቲካ ውይይት ሊያግዝ ይችላል። - ጊዜያዊ አገር አቀፍ የተኩስ አቁም ስምምነት ሊፈጸም ይገባል። - ሁሉም የታጠቁ ተዋናዮች፣ በመላ አገሪቱ አዲስ የሕዝብ መፈናቀልን ጨምሮ ለሰዎች ስቃይ ምክንያት ከመሆን መገታት አለባቸው። - የታጣቁ ኃይሎች ት/ቤቶችን፣ ጤና ተቋማትንና የውኃ መሠረተ ልማቶችን ዒላማ ማድረግ ማቆም አለባቸው። የተሟላና ያልተገደበ ሰብአዊ አቅርቦት ሊኖር ይገባል። ይህም ጊዜያዊ አገር አቀፍ የተኩስ አቁም ማድረግን ይጨምራል። - ግጭት የኢትዮጵያውያንን ሥቃይ ከማባባስ ያለፈ መፍትሔ የለውም። ውይይት ትኩረት ሊደረግበት ይገባል። - ምንም እንኳን ፍጹም ሊሆን ባይችልም፣ ሁሉም ወገኖች የአገራዊ ምክክሩን ዕድል ሊጠቀሙበት ይገባል። #USEmbassyAddisAbaba #VOA #EthiopiaInsider #tikvahethiopia አዳዲስ አለማቀፍ ሰበር ዜናዎችን ለማግኘት በነዚህ አማራጮች ይጠቀሙ 👇👇👇 👉👉Telegram :- https://t.me/berbirmereja 👉👉Facebook--› https://www.facebook.com/berbirmereja/ 👉👉YouTube: -, https://youtube.com/@BerbirMereja
إظهار الكل...

👍 4
Photo unavailableShow in Telegram
00:20
Video unavailableShow in Telegram
ትራምፕ በቀጣይ የአሜሪካ ኘሬዚዳንት ሆነው ከተመረጡ የፍልስጤም ደጋፊ የሆኑ የእስራኤል ተቃዋሚዎችን ከዩኒቨርሲቲዎች ብቻ ሳይሆን ከአገረ አሜሪካ ጭምር ለማባረር ቃል ገብተዋል። " በተለይም ከሌላ አገር ወደ አሜሪካ መጥተህ ጂሃዲዝምን፣ ፀረ-አሜሪካኒዝምን ወይም ፀረ ሴማዊነትን በዩኒቨርሲቲዎቻችን ለማንፀባረቅ ከሞከርክ ወዲያውኑ ከአገራችን እናባርርሃለን" ሲሉ ዝተዋል። ይህንን የተመለከቱ የፖለቲካ ተንታኞች ሁኔታውን (ንግግራቸውን) " ብልጣ-ብልጡ የቀድሞው ፕሬዚዳንት ያለ ተቀናቃኝ ወደ ስልጣን ለመመለስ የተጠቀሙበት የፖለቲካ አካሄድ ነው " ብለውታል። አዳዲስ አለማቀፍ ሰበር ዜናዎችን ለማግኘት በነዚህ አማራጮች ይጠቀሙ 👇👇👇 👉👉Telegram :- https://t.me/berbirmereja 👉👉Facebook--› https://www.facebook.com/berbirmereja/ 👉👉YouTube: -, https://youtube.com/@BerbirMereja
إظهار الكل...
👎 3🌚 2
Photo unavailableShow in Telegram
በኢትዮጵያ ያሉ ሁሉም የታጠቁ ኃይሎች “ጊዜያዊ ሀገር አቀፍ የተኩስ ማቆም” እንዲያደርጉ የአሜሪካ አምባሳደር ጠየቁ በኢትዮጵያ ያሉ ሁሉም የታጠቁ ኃይሎች “ጊዜያዊ ሀገር አቀፍ የተኩስ ማቆም” እንዲያደርጉ በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኢርቪን ማሲንጋ ጥሪ አቀረቡ። ታጣቂዎቹ ትምህርት ቤቶች፣ የጤና ተቋማትን እና የውሃ መሰረተ ልማቶችን ኢላማ ማድረጋቸውን እንዲያቆሙም አምባሳደሩ አሳስበዋል። በአምባሳደርነት ተሹመው ወደ ኢትዮጵያ ከመጡ ስምንት ወር የሞላቸው ማሲንጋ፤ ከእርሳቸው በፊት በነበሩ አምባሳደሮች ሲተገበር እምብዛም ያልታየውን ይፋዊ የፖሊሲ መልዕክት በዛሬው ዕለት አስደምጠዋል። አምባሳደሩ መልዕክታቸውን ለማስተላለፍ የመረጡት ታሪካዊው የአሜሪካን ግቢ፤ የንግግራቸው ማጠንጠኛ ከነበረው የሰብዓዊ መብት ጉዳይ ጋር ቁልፍ ተዛምዶ ያለው ነው። በአሁኑ ወቅት የየመን ማህበረሰብ ትምህርት ቤት አካል የሆነው የቀድሞው የአሜሪካ ቆንስላ ግቢ፤ በጣሊያን ወረራ ወቅት የየካቲት 12 ጭፍጨፋ ሲካሄድ 750 የሚጠጉ ኢትዮጵያውያን ተሸሽገውበት የነበረ ነው። ማሲንጋ በንግግራቸው ወቅቱን ሲያስታውሱ፤ “በሺህዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ያለምንም ማስረጃ እና የህግ ሂደት “ኢላማ የተደረጉበት ነበር” ብለዋል። Via Ethiopiainsider አዳዲስ አለማቀፍ ሰበር ዜናዎችን ለማግኘት በነዚህ አማራጮች ይጠቀሙ 👇👇👇 👉👉Telegram :- https://t.me/berbirmereja 👉👉Facebook--› https://www.facebook.com/berbirmereja/ 👉👉YouTube: -, https://youtube.com/@BerbirMereja
إظهار الكل...
👍 3🥴 1