Prosperity Party A.A - ብልፅግና
📈 تحلیل کانال تلگرام Prosperity Party A.A - ብልፅግና
کانال Prosperity Party A.A - ብልፅግና (@prosperityaddis) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 14 257 مشترک است و جایگاه 3 859 را در دسته سیاست و رتبه 2 376 را در منطقه أثيوبيا دارد.
📊 شاخصهای مخاطب و پویایی
از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 14 257 مشترک جذب کرده است.
بر اساس آخرین دادهها در تاریخ 12 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -2 877 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -23 بوده و همچنان دسترسی گستردهای حفظ شده است.
- وضعیت تأیید: تأیید نشده
- نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 6.45% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 3.99% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب میکند.
- دسترسی پستها: هر پست به طور میانگین 921 بازدید دریافت میکند. در اولین روز معمولاً 570 بازدید جمعآوری میشود.
- واکنشها و تعامل: مخاطبان بهطور فعال حمایت میکنند؛ میانگین واکنش به هر پست 0 است.
📝 توضیح و سیاست محتوایی
نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاههای شخصی توصیف میکند:
“የአዲስ አበባ ብልፅግና ፓርቲ ፅ/ቤት”
به لطف بهروزرسانیهای پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 13 ژوئیه, 2026)، کانال همواره بهروز و دارای دسترسی بالاست. تحلیلها نشان میدهد مخاطبان بهطور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته سیاست تبدیل کردهاند.
در حال بارگیری داده...
| تاریخ | رشد مشترکین | اشارات | کانالها | |
| 13 ژوئیه | 0 | |||
| 12 ژوئیه | 0 | |||
| 11 ژوئیه | 0 | |||
| 10 ژوئیه | 0 | |||
| 09 ژوئیه | 0 | |||
| 08 ژوئیه | 0 | |||
| 07 ژوئیه | 0 | |||
| 06 ژوئیه | 0 | |||
| 05 ژوئیه | 0 | |||
| 04 ژوئیه | 0 | |||
| 03 ژوئیه | 0 | |||
| 02 ژوئیه | 0 | |||
| 01 ژوئیه | 0 |
| 2 | በከተማችን ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ የከተማ አስተዳደራችን የ2019 በጀት 502. 27 ቢሊዮን ብር አድርገን አፅድቀናል።
በዚሁ መሰረት፡-
የበጀቱ 71 .53 % በዋናነት ለድህነት ቅነሳ፣ ለዘላቂ ልማት እና ለእድገት ተኮር ዘርፎች ( ለካፒታል ወጪ ) የሚውል ይሆናል።
ለአስተዳደራዊ ወጪ፡- ብር 142.97 ቢሊዮን ( 25.27%)
ለመጠባበቂያ ወጪ:- ብር 16.00 ቢሊዮን (3.18%) ሆኖ በሙሉ ድምፅ ፀድቋል።
የ2019 በጀት ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ152.26 ቢሊዮን ብር (43.5%) እድገት አለው።
በጀቱ የከተማዋን የልማት ፍላጎትና የአገልግሎት ደረጃ ይበልጥ ለማሳደግ ታሳቢ ተደርጎ የተመደበ ሲሆን ፣ የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎችን አጠናክሮ ለመቀጠል የሚውል ይሆናል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!
፦ ከንቲባ አዳነች አቤቤ
#aa_prosperity | 504 |
| 3 | ቤት ልማትን በተመለከተ፡-
በመንግስት፣ በግል፣ በመንግስት እና በግል፣ በበጎ ፈቃደኞች እና በሌሎችም ፕሮግራሞች የቤት አቅርቦቱን ለማሳደግ ብርቱ ርብርብ ይደረጋል፡፡
በበጀት ብቻ ሳይሆን ተጨማሪ ፋይናንስ በማፈላለግም ርብርብ ይደረጋል፡፡ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ይፋ ካደረጉት እንደ ሀገር ከሚገነቡ 1 ነጥብ 5 ቤቶች ውስጥም ከተማችን ላቅ ያለ ድርሻ ይኖራታል፡፡
፦ ከንቲባ አዳነች አቤቤ
#aa_prosperity | 657 |
| 4 | ምርትና ምርታማነትን መጨመር፣ የግብይት ስርዓቱን ማሳለጥ፣ ህገወጥ ንግድን ስርዓት ማስያዝ በትኩረት እየተሰራ ነው፡፡
አምራቹን እና ሸማቹን ለማገናኘት በቀጣይም በትኩረት ይሰራል፡፡
በገበያ ማዕከላት፣ በትራንስፖርት እና በመሳሰሉት የሚደረጉ ድጎማዎችም ለገበያ መረጋጋቱ ጉልህ ሚና አላቸው፡፡
፦ ከንቲባ አዳነች አቤቤ
#aa_prosperity | 636 |
| 5 | بدون متن... | 630 |
| 6 | بدون متن... | 574 |
| 7 | የከተማችን ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ ሁለተኛ ቀን ውሎ በማካሄድ ላይ እንገኛለን ።
በዛሬ ማለዳው ክፍለ ጊዜ የአዲስ አበባ ከተማ ምክር ቤት የ5 ዓመት የህግ ማውጣት ሚና፣ የህዝብ ውክልና አፈፃፀም፣ የአስፈፃሚ አካላት ክትትልና ቁጥጥር አፈጻጸም ሪፖርትና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ተወያይተን አፅድቀናል።
በአሁኑ ሰአት የከተማችን ዋና ኦዲተር 107 የከተማዋ ተቋማት ላይ ያዘጋጀው ሪፓርት እየቀረበ ነው ። ውድ የከተማችን ነዋሪዎች ሁሉም አጀንዳዎች በአዲስ ሚድያ ኔትዎርክ ስርጭት እየተላለፈ ስለሆነ መከታተል ትችላላችሁ
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ | 417 |
| 8 | ያቀድናቸውን ስራዎች ሀላፊነት ተከፋፍለን በመረባረብ አልቀን ፈፅመናል፡፡ ከዕቅዱ አንፃር ስር ነቀል ለውጥ አምጥተናል፡፡ ነገር ግን ሀገራችን ካለመችው የብልፅግና ግብ እና ህዝባችን ካለው አዳጊ ፍላጎት አንፃር ብዙ ይቀረናል፡፡ የቀጣይ የቤት ስራ ነው፤
፦ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ
#aa_prosperity | 442 |
| 9 | بدون متن... | 471 |
| 10 | በሰለጠነ የውይይት ባህል እንመክራለን! ለሀገራዊ ችግሮቻችን ሀገራዊ መፍትሔ እንሰጣለን!
በጠረንጴዛ ዙሪያ ቁጭ ብሎ የመወያየት ባህል ባልነበረበት ዘመን ጭምር ኢትዮጵያዊያን በዛፎች ጥላ ስር ቁጭ ብለው በመምከር ችግሮቻቸውን የመፍታት እሴትን አዳብረዋል፡፡ የተጣላ ታርቋል፤ ቂም በቀልነት ተሽሮ ፍቅርና ይቅርታ ነግሷል፡፡
እንደ አለመታደል ሆኖ እነዚህ የኢትዮጵያዊያን የመደማመጥ እና የመከባበር ጥንታዊ እሴቶች ከዘመናዊው የውይይት ባህል ጋር ሳይሰናሰኑ፣ ተቋማዊም ሳይሆኑ ለዘመናት ሲሸረሸሩ ኖረዋል፡፡
ጥንታዊና ሀገራዊ እሴቶቻችን ከአካባቢያዊ ችግሮች መፍትሄነት ተሻግረው ሀገራዊ ችግሮችን የሚፈቱበትን አቅም ሳያጎለብቱ ይልቁንም በየጊዜው እየደበዘዙ መምጣታቸው የማይታበል ሀቅ ነው፡፡
ጥያቄ አለኝ የሚል ሁሉ ጠብመንጃ ማንሳትን እንደ ብቸኛ መፍትሄ የሚወስድበት ታሪካዊ ስብራት በመከሰቱ የሀገረ መንግስት ግንባታውም ሲያዘግም፣ አንዳንዴም ወደ ኋላ ሲመለስ መቆየቱም አይዘነጋም፡፡
የቂም በቀል ፖለቲካ ስር እንዲሰድ ከማድረግ ውጪ ችግሮችን በሀይል ለመፍታት የተደረጉ ጥረቶች ሁሉ መሰረታዊ ለውጥ አላመጡም፤ ሊያመጡም አይችሉም፡፡
በህዝባችን መካከል መጠራጠር እና መከፋፈል እየሰፋ፣ በአንፃሩ ደግሞ መደማመጥ እየቀነሰ የመጣው ለውይይት ባህል መዳበር የተፈጠሩ ዕድሎች ውስን ስለነበሩ ነው፡፡
የሀገራችንን ነባራዊ ሁኔታ በጥልቀት በመረዳት ብሩህ ነገዋን የተለመው ሀገራዊ ለውጡ ለውይይት ባህላችን መዳበር ጉልህ ሚና የሚጫዎቱ ተጨባጭ እርምጃዎችን ወስዷል፡፡
የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ እና መሰል የዴሞክራሲ ተቋማትን ነፃ፣ ገለልተኛ እና የኢትዮጵያን መልክ የሚያንፀባርቁ በማድረግ ለዴሞክራሲ ምህዳሩ መስፋት ፅኑ መሰረት ተጥሏል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ የምክክር ኮሚሽንን በማቋቋምም ሲንከባለሉ ለመጡ ችግሮች የጋራ መፍትሄ ለመስጠትና የጋራ ነገን በአብሮነት ለመገንባት ምቹ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል፡፡
በአራቱም ማዕዘን የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን፣ ዲያስፖራዎችም ጭምር ሀሳቦቻቸውን በነፃነት በማቅረብ ለብሔራዊ ምክክሩ ስኬታማነት የድርሻቸውን አበርክተዋል፡፡
በሁሉም የህብረተሰብ ክፍል የተነሱ ጥያቄዎችን እና ሀሳቦችን ጠቅለል አድርገው የያዙ፣ የጋራ መፍትሔን የሚፈልጉ 8 አንኳር አጀንዳዎች በብሔራዊ ምክክር ኮሚሽኑ የተቀረፁ ሲሆን ከአንድ ቀን በኋላ ሀምሌ 8 በመዲናችን በሚጀምረው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ ብሔራዊ መግባባት እንደሚደረስባቸው ይጠበቃል፡፡
ኢትዮጵያ የጀመረችው ለሀገራዊ ችግሮች ሀገራዊ መፍትሄ የመፈለግ አካሄድ ከትውልድ ትውልድ ሲሸጋገሩ የመጡ ስብራቶቻችንን በመጠገን ብሩህ ነገን የሚተልም ለአፍሪካዊያንም ተምሳሌታዊ እርምጃ ነው፡፡
ለአንድ ሀገራዊ ዓላማ የምንመክርበት፣ ተደማምጠን የምንግባባበት መልካም የስራ ሳምንት ይሁንልን!
በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት
#aa_prosperity | 556 |
| 11 | بدون متن... | 330 |
| 12 | بدون متن... | 531 |
| 13 | بدون متن... | 310 |
| 14 | ለትውልድ ግንባታው ልዩ ትኩረት ተሰጥቶታል!
መጪው ጊዜ የወጣቶች ነው፡፡ አሁን እየሰተራ ያለውን የዘላቂ ልማት ውጤትና ብልፅግናን የሚያጣጥሙት ወጣቶችና መጪው ትውልድ እንደሆነ ግልፅ ነው፡፡ በመሆኑም በየዓመቱ ወጣቶች በሃሳብ የበላይነትና በውይይት እንዲያምኑ ምክንያታዊ ወጣቶች እንዲሆኑ የጸረ ሰላም ሃይሎች መጠቀሚያ እንዳይሆኑ እና የሰላም ዘብ እንዲሆኑ፣ የመቻቻልና የመከባበር ባህልን እንዲያዳብሩ በየደረጃው ሰፋፊ ስራዎች ተከናውነዋል፡፡
በ114 የወጣት ስብዕና መገንቢያ ማዕከላት አገልግሎቶችን እንዲሰጡና አገልግሎቶች እንዲያሻሽሉ በማድረግ ወጣቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተደርጓል። የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች ቁጥር 495 የነበረ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት 2,581 ማድረስ ተችሏል።
በበጀት ዓመቱ ደረጃቸውን የጠበቁ 91 የስፖርት ማዘወተሪያ ስፍራዎች፣ ስፖርት ፓርክ፣ ብሔራዊ ጀግኖች ለሆኑ አትሌቶቻችን የአክብሮት ሀውልት ማቆምን ጨምሮ ብዙ ተግባራት ተከናውነዋል፡፡
በየደረጃው የማህበረሰብ አቀፍ ስፖርትን በትምህርት ቤት፤ በመኖሪያ እና መዝናኛ ቦታዎች እንዲሁም በስራ ቦታዎች በማስፋፋት ሁሉም ዜጎች በአካል እና በአእምሮ ጎልብተው ጤናማ እና አምራች እንዲሆኑ እና ማህበራዊ መስተጋብርን ለማጠናከር ርብርብ እየተደረገ ነው ነው፡፡
በአገራችንም ሆነ በከተማ ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ 5 አለም አቀፍ ውድድሮችን በማስተናገድ ከተማችንን የአለም አቀፍ ውድድሮች መዳረሻ ማድረግ ተችሏል፡፡
ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአዲስ አበባ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ ካቀረቡት ሪፖርት | 355 |
| 15 | بدون متن... | 452 |
| 16 | የቤት አቅርቦት በተለያዩ አማራጮች!
ቤት መሰረታዊ ፍላጐትና አንገብጋቢ የህዝብ ጥያቄ መሆኑን በመረዳት ባለፉት አምስት ዓመታት 496,971 ቤቶች የተገነቡ ሲሆን ፣ ከ26,563 የመንግስት ቤቶች ለልማት ተነሺዎች እና ለሌሎች ማስተላለፍ ተችሏል። ከ98 ሺህ በላይ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን በእጣ ለቆጣቢዎች ማስተላለፍ ተችሏል።
በበጀት ዓመቱም በተለያዩ የቤት ግንባታ አማራጮች /ሞዳሊቲዎች (በመንግስት፣ በሪል እስቴት አልሚዎች፣ በግል አልሚዎች፣ በህብረት ሥራ ማህበራት እና በበጎ ፈቃደኛ አልሚዎች) በድምሩ 179,516 ቤቶች ግንባታቸው እየተፋጠነ ይገኛል። ከነዚህም በመንግስት በጀት የሚገነቡ ቤቶች እቅድ 50,305 ሲሆን፣ አፈፃፀም በአማካኝ 30% በላይ ደርሷል።
ለረጅም አመታት በከተማዋ ላይ የነበረው የጋራ መኖሪያ ቤት የባንክ ብድር እዳ 62 ቢሊዮን ብር ከፍለናል፡፡ አሁንም ላይ 37 ቢሊዮን ብር ቀሪ እዳ ይቀረናል፡፡
ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአዲስ አበባ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ ካቀረቡት ሪፖርት
#aa_prosperity | 406 |
| 17 | بدون متن... | 387 |
| 18 | የተጀመሩ ተስፋ ሰጪና አበረታች ውጤቶችን በማስቀጠል በሚከተሉት የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ ርብርብ ይደረጋል!
1. በኢኮኖሚ መረጋጋት እና የኑሮ ውድነት ማቃለል
2. በሥራ ዕድል ፈጠራ እና ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች (MSEs)
3. በመሠረተ-ልማት ግንባታ፣ ጥገና፣ አስተዳደር እና ዘላቂነት
4. በከተማ ውበትና ፅዳት አስተዳደር
5. በትራንስፖርት እና የትራፊክ ፍሰት ማሻሻያ
6. ብልሹ አሰራርና ሌብነትን በመቀነስ በአገልግሎት አሰጣጥ ጥራት (Good Governance)
7. የማህበራዊ ልማትን በማጠናከር፡-
8. የከተማዋን ገቢ ማሳደግ እና የፋይናንስ አስተዳደር፣
9. አስተማማኝና ዘላቂ ሰላም እና ጸጥታን ማረጋገጥ
10. የከተማችን ነዋሪዎች አንገብጋቢ ጉዳይ የሆነውን የቤት ልማት ፕሮግራሞችን በግል ዘርፉ፣ በሕብረት ሥራ ማኅበራት፣ በመንግስትና በግል የአጋርነት ፕሮግራም በስፋት ተግባራዊ ይደረጋል።
11. የውሃ አቅርቦትና ሌሎች የተጀመሩ ሜጋ ኘሮጀክቶችን በተሟላ ሁኔታ ለማጠናቀቅ ይሰራል።
12. የመንገድ መሰረተ ልማትን ማስፋፋትና ኔትዎርኩን ማጠናከር ላይም ቅንጅታዊ ርብርብ ይደረጋል፡፡
ካቀድነው አንፃር አመርቂ ውጤት ቢመዘገብም፣ ጀመርን እንጂ አልጨረስንም፣ ገና ገና ብዙ ብዙ ይቀረናል፡፡ የሕዝባችን የልማት ፍላጐት በሚመጥንና ከብልፅግና ግባችን አንፃር በከፍተኛ የሥራ ትጋትና የጸና አቋም የጀመርነውን ልማት ከየትኛውም ጊዜ በላቀ ትጋት የምንረባረብ ይሆናል።
ክብርት ከንቲባ አዳነች አቤቤ በአዲስ አበባ ምክር ቤት 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ ላይ ካቀረቡት ሪፖርት
#aa_prosperity | 408 |
| 19 | بدون متن... | 448 |
| 20 | በ2018 በጀት ዓመት 350 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ ችለናል።
የገቢ መሰረትን በማስፋትና የሚሰበሰብ ገቢ ፍትሀዊነቱን በጠበቀ መልኩ እንዲሰበሰብ በማድረግ በሰፊው በመሰራቱ የ2ዐ18 ገቢ አሰባሰብ ከ2017 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት አንፃር በ 116.3 ቢሊዮን ብር ወይም 50 % እድገት አሳይቷል።
ግብር ከፋዮቻችንን ከልብ እናመሰግናለን!!
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
፦ ከንቲባ አዳነች አቤቤ
#aa_prosperity | 449 |
