fa
Feedback
FMC Sport ፋና ስፖርት

FMC Sport ፋና ስፖርት

رفتن به کانال در Telegram

This is Fana Media Corporation’s (FMC) Sport official Telegram channel. For more updates please visit https://fanamc.com/amharic/

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام FMC Sport ፋና ስፖርት

کانال FMC Sport ፋና ስፖርት (@fmcsport) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 36 527 مشترک است و جایگاه 1 868 را در دسته ورزش و رتبه 905 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 36 527 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 17 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -537 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -5 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 6.97% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 3.44% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 2 548 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 256 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 4 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
This is Fana Media Corporation’s (FMC) Sport official Telegram channel. For more updates please visit https://fanamc.com/amharic/

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 18 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته ورزش تبدیل کرده‌اند.

36 527
مشترکین
-524 ساعت
-247 روز
-53730 روز
آرشیو پست ها
በዓለም ዋንጫ የጋሪ ሊንከርን ክብረ ወሰን የተጋራው ሃሪ ኬን… አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) እንግሊዛዊው የፊት መስመር ተጫዋች ሃሪ ኬን በዓለም ዋንጫ ውድድር በርካታ ግቦችን በማ
በዓለም ዋንጫ የጋሪ ሊንከርን ክብረ ወሰን የተጋራው ሃሪ ኬን… አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) እንግሊዛዊው የፊት መስመር ተጫዋች ሃሪ ኬን በዓለም ዋንጫ ውድድር በርካታ ግቦችን በማስቆጠር የሀገሩን ልጅ ጋሪ ሊንከር ክብረ ወሰን ተጋርቷል፡፡ በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታ ትናንት ምሽት እንግሊዝ ክሮሺን 4 ለ 2 ማሸነፏ ይታወቃል፡፡ እንግሊዛዊው የ32 ዓመቱ… https://www.fanamc.com/archives/316987

በዓለም ዋንጫ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ክብረወሰንን የተጋራው ሊዮ ሜሲ.. አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በስድስት የዓለም ዋንጫ ውድድሮች በመጫወት ክብረወሰን ያስመዘገበው ሊዮኔል
+1
በዓለም ዋንጫ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ክብረወሰንን የተጋራው ሊዮ ሜሲ.. አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በስድስት የዓለም ዋንጫ ውድድሮች በመጫወት ክብረወሰን ያስመዘገበው ሊዮኔል ሜሲ በ16 ግቦች የዓለም ዋንጫ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነትን ክብረ ወሰን ተጋርቷል፡፡ በፈረንጆቹ 2006 በጀርመን ዓለም ዋንጫ በ18 አመቱ ሀገሩን ወክሎ መጫወት የጀመረው የሮዛሪዮው ተወላጅ ሊዮኔል አንድሬስ ሜሲ የዘንድሮውን ጨምሮ በስድስት የዓለም ዋንጫዎች ተሳትፏል፡፡ ትናንት ምሽት አርጀንቲና አልጀሪያን 3 ለ 0 ባሸነፈችበት የምድብ የመጀመሪያ ጨዋታ ሦስቱንም ግቦች በማስቆጠር ሀትሪክ የሰራው ሜሲ የዓለም መነጋገሪያ ሆኗል፡፡ ለሀገሩ አርጀንቲና እስካሁን 200 ጨዋታዎችን ያደረገው የ38 አመቱ ኮከብ በጀርመናዊው ሚሮስላቭ ክሎስ ተይዞ የነበረውን የምንጊዜም የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ክብረወሰን ተጋርቷል፡፡ የ2022ቱ የኳታር ዓለም ዋንጫ አሸናፊው ሜሲ አሁንም የቡድኑ ቁልፍ ተጫዋች መሆኑን ከማስመስከር ባሻገር ሀገሩ በዘንድሮውም ዓለም ዋንጫ ለአሸናፊነት እንድትታጭ አስችሏል፡፡ የዘንድሮውን የዓለም ዋንጫ ጅማሮ በሀትሪክ ያሳመረው ሊዮ ሜሲ በቀጣይ ጨዋታዎች ክብረ ወሰኑን የግሉ የማድረግ ሰፊ እድል አለው፡፡ የ26 አመቱ ፈረንሳዊ ኪሊያን ምባፔ ትናንት ምሽት ሀገሩ ሴኔጋልን ባሸነፈችበት ጨዋታ ያስቆጠራቸውን ሁለት ግቦች ጨምሮ 14 ግቦችን ከመረብ ያሳረፈ ሲሆን፥ ክብረ ወሰኑን የግሉ ለማድረግ ከሜሲ ጋር ተፋጧል፡፡ ሊዮኔል ሜሲ በተጨማሪም በዓለም ዋንጫ ታሪክ በአንድ ጨዋታ ሦስት ግቦችን ያሰቆጠረ በእድሜ አንጋፋው ተጫዋች በመሆን ተጨማሪ ክብረ ወሰን የግሉ አድርጓል፡፡ በአቤል ነዋይ

ፖርቹጋል ከኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ.. አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫው የክሪስቲያኖ ሮናልዶ ሀገር ፖርቹጋል የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋን ዛሬ ምሽት ታደርጋለች፡፡ ፖ
+1
ፖርቹጋል ከኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ.. አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫው የክሪስቲያኖ ሮናልዶ ሀገር ፖርቹጋል የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋን ዛሬ ምሽት ታደርጋለች፡፡ ፖርቹጋል ምሽት 2 ሰዓት ላይ ከኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ጋር በሂውስተን ስታዲየም በምታደርገው ጨዋታ የማሸነፍ ቅድመ ግምት ተሰጥቷታል፡፡ የመጨረሻው የዓለም ዋንጫ ተሳትፎውን የሚያደርገው ፖርቹጋላዊ ኮከብ በጨዋታው ልዩነት ፈጣሪ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ በአውሮፓ የተለያዩ ክለቦች ቁልፍ… https://www.fanamc.com/archives/316942

ሩበን አሞሪም የኤሲሚላን አሰልጣኝ ሆኑ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የማንቼስተር ዩናይትድ የቀድሞ አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም የኤሲሚላን አሰልጣኝ ሆነው ተሾሙ፡፡ አሰልጣኙ በጣሊያኑ ክ
ሩበን አሞሪም የኤሲሚላን አሰልጣኝ ሆኑ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የማንቼስተር ዩናይትድ የቀድሞ አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም የኤሲሚላን አሰልጣኝ ሆነው ተሾሙ፡፡ አሰልጣኙ በጣሊያኑ ክለብ ኤሲሚላን እስከ ፈረንጆቹ 2028 የሚያቆያቸውን ውል ነው የተፈራረሙት፡፡ የ41 ዓመቱ አሰልጣኝ ማንቼስተር ዩናይትድን ለ14 ወራት ማሰልጠን ቢችሉም በውጤት ማጣት ምክንያት መሰናበታቸው አይዘነጋም፡፡ ኤሲሚላን በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት በሴሪ ኤው 5ኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ ይታወሳል፡፡

ወላይታ ድቻ ባሕር ዳር ከተማን አሸነፈ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ወላይታ ድቻ ባሕር ዳር ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል፡
+2
ወላይታ ድቻ ባሕር ዳር ከተማን አሸነፈ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ወላይታ ድቻ ባሕር ዳር ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡ ቀን 10 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የወላይታ ድቻን የማሸነፊያ ሁለት ግቦች ያሬድ ዳርዛ አስቆጥሯል፡፡ በተመሳሳይ ስታዲየም አስቀድሞ ቀን 7 ሰዓት ላይ የተገናኙት ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና መቐለ 70 እንደርታ ያለምንም ግብ አቻ መለያየታቸው ይታወቃል፡፡ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ የተገናኙት ሸገር ከተማ እና ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ያለምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል፡፡

ሪያል ማድሪድ የአንቶኒዮ ሩዲገርን ውል አራዘመ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሪያል ማድሪድ የተከላካዩን አንቶኒዮ ሩዲገር ውል ለተጨማሪ አንድ ዓመት ማራዘሙን ይፋ አድርጓል፡፡ ጀርመ
ሪያል ማድሪድ የአንቶኒዮ ሩዲገርን ውል አራዘመ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሪያል ማድሪድ የተከላካዩን አንቶኒዮ ሩዲገር ውል ለተጨማሪ አንድ ዓመት ማራዘሙን ይፋ አድርጓል፡፡ ጀርመናዊው ተጫዋች ሩዲገር በሎስብላንኮዎቹ ቤት እስከ ፈረንጆቹ 2027 ድረስ የሚቆይ ይሆናል፡፡ አንቶኒዮ ሩዲገር ከምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ በፈረንጆቹ 2022 ሪያል ማድሪድን መቀላቀሉ ይታወሳል፡፡

ፈረንሳይ ከሴኔጋል… አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለ
ፈረንሳይ ከሴኔጋል… አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ይደረጋሉ፡፡ በምድብ 9 ላይ የምትገኘው የሁለት ጊዜ የመድረኩ ሻምፒዮን ፈረንሳይ ከአፍሪካዊቷ ሀገር ሴኔጋል ጋር ምሽት 4 ሰዓት ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡ በዚሁ ምድብ የሚገኙት ኢራቅ እና ኖርዌይ ሌሊት 7 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡ በምድብ 10 የተደለደሉት አርጀንቲና እና አልጄሪያ ደግሞ ሌሊት 10 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን የሚያደርጉ ይሆናል፡፡

ቱኒዚያ በዓለም ዋንጫ ከአንድ ጨዋታ ሽንፈት በኋላ አዲስ አሰልጣኝ ሾመች አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ እየተሳተፈች የምትገኘው ቱኒዚያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታ ከተሸነ
ቱኒዚያ በዓለም ዋንጫ ከአንድ ጨዋታ ሽንፈት በኋላ አዲስ አሰልጣኝ ሾመች አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ እየተሳተፈች የምትገኘው ቱኒዚያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታ ከተሸነፈች በኋላ አዲስ አሰልጣኝ ሾመች፡፡ ሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር በስዊድን የደረሰባትን የ5 ለ 1 ሽንፈት ተከትሎ አሰልጣኝ ሳብሪ ላሞቺን ከኃላፊነት አሰናብታለች፡፡ በምትካቸውም የ57 ዓመቱን ፈረንሳዊ አሰልጣኝ ሄርቬ ሬናርድን የብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ አድርጋ ሾማለች፡፡ ሄርቬ ሬናርድ በአሰልጣኝነት ዘመናቸው ቱኒዚያ 5ኛ አፍሪካዊ ብሔራዊ ቡድናቸው ሲሆን፥ ከዚህ ቀደም ዛምቢያ፣ አንጎላ፣ ኮት ዲቯር እና ሞሮኮን ማሰልጠናቸው ይታወሳል፡፡ ምድብ 6 ላይ የምትገኘው ቱኒዚያ በቀጣይ ከጃፓን እና ኔዘርላንድስ ጋር ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ሦስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት ሦስት ጨዋታዎች ይደረ
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ሦስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት ሦስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡ በዕለቱ የመጀመሪያ ጨዋታ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከመቐለ 70 እንደርታ ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይገናኛሉ፡፡ በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ ባህር ዳር ከተማ ከወላይታ ድቻ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡ በሌላ የዛሬ መርሐ ግብር ሸገር ከተማ ከወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ቀን 10 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ፡፡

ሜሲ እና ምባፔ የምንጊዜም የዓለም ዋንጫ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ለመሆን… አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በፈረንጆቹ 1930 መደረግ በጀመረው የዓለም ዋንጫ ውድድር ጀርመናዊው ሚሮስላቭ
ሜሲ እና ምባፔ የምንጊዜም የዓለም ዋንጫ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ለመሆን… አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በፈረንጆቹ 1930 መደረግ በጀመረው የዓለም ዋንጫ ውድድር ጀርመናዊው ሚሮስላቭ ክሎስ የመድረኩን ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ደረጃን እየመራው ይገኛል፡፡ የጀርመን ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ ኮከብ ሚሮስላቭ ክሎስ በዓለም ዋንጫ ውድድር 24 ጨዋታዎችን አድርጎ 16 ግቦችን በማስቆጠር የዓለም ዋንጫ የምን ጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪዎች ደረጃን እየመራ ይገኛል፡፡ ሚሮስላቭ ክሎስ… https://www.fanamc.com/archives/316875

ግብጽ እና ቤልጂዬም አቻ ተለያዩ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ ምድብ ጨዋታ ግብጽ እና ቤልጂዬም 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።
+5
ግብጽ እና ቤልጂዬም አቻ ተለያዩ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ ምድብ ጨዋታ ግብጽ እና ቤልጂዬም 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።

ስፔን እና ኬፕ ቨርዴ አቻ ተለያዩ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የምድብ ስምንት የመጀመሪያ ጨዋታ ስፔን እና ኬፕ ቨርዴ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋ
+3
ስፔን እና ኬፕ ቨርዴ አቻ ተለያዩ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የምድብ ስምንት የመጀመሪያ ጨዋታ ስፔን እና ኬፕ ቨርዴ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል። ለዓለም ዋንጫ አሸናፊነት ትልቅ ግምት ከተሰጣቸው ብሔራዊ ቡድኖች መካከል የሆነችው ስፔን ከኬፕ ቨርዴ ጋር ባደረገችው የውድድሩ የመጀመሪያ ጨዋታ አቻ ተለያይታለች። በጨዋታው የስፔን ተጫዋቾች ግብ ለማስቆጠር በተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርጉም የኬፕ ቨርዴን መረብ መድፈር ሳይችሉ ቀርተዋል።

አርባምንጭ ከተማ ምድረ ገነት ሽረን አሸነፈ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አርባምንጭ ከተማ ምድረ ገነት ሽረን 2 ለ 0
+2
አርባምንጭ ከተማ ምድረ ገነት ሽረን አሸነፈ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አርባምንጭ ከተማ ምድረ ገነት ሽረን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የአርባምንጭ ከተማን የማሸነፊያ ግቦች አቡዱልራህማን መሐመድና ቴዎድሮስ አጨ አስቆጥረዋል፡፡ በዚሁ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ሀድያ ሆሳዕና ከፋሲል ከነማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡ አስቀድሞ ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገ በሌላ የሊጉ ጨዋታ ነገሌ አርሲ ሀዋሳ ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡ የነገሌ አርሲን የማሸነፊያ ግቦች አለኝታ ማርቆስ እና ሮሆቦት ስላሎ አስቆጥረዋል፡፡ ሀዋሳ ከተማን ከሽንፈት ያልታደገውን ግብ ደግሞ ጌታነህ ከበደ ከመረብ አሳርፏል። በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ መደረግ በጀመረው ጨዋታ አዳማ ከተማ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 0 እየመራ ይገኛል፡፡

ሪያል ማድሪድ ኩኩሬላን ማስፈረሙን ይፋ አደረገ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የስፔኑ ክለብ ሪያል ማድሪድ ማርክ ኩኩሬላን ከቼልሲ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡ ስፔናዊው የግራ መስመር
ሪያል ማድሪድ ኩኩሬላን ማስፈረሙን ይፋ አደረገ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የስፔኑ ክለብ ሪያል ማድሪድ ማርክ ኩኩሬላን ከቼልሲ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡ ስፔናዊው የግራ መስመር ተጫዋች በሪያል ማድሪድ ቤት እስከ ፈረንጆቹ 2032 ድረስ የሚያቆየውን ውል ነው የተፈራረመው፡፡ ሪያል ማድሪድ ለ27 ዓመቱ ተጫዋች 55 ሚሊየን ዩሮ እና እየታየ የሚጨመር 5 ሚሊየን ዩሮ የዝውውር ሒሳብ የሚከፍል ይሆናል፡፡ ኩኩሬላ የምዕራብ ለንደኑን ክለብ ቼልሲ በ2022 ከብራይተን መቀላቀሉ ይታወሳል፡፡ ተጫዋቹ በቼልሲ በነበረው ቆይታ የኮንፈረንሰ ሊግ እና የዓለም ክለቦች ዋንጫዎችን ማሸነፉ አይዘነጋም፡፡

በዓለም ዋንጫ ለመጀመሪያ ጊዜ የምትሳተፈው ኬፕ ቨርዴ ከስፔን… አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የ
በዓለም ዋንጫ ለመጀመሪያ ጊዜ የምትሳተፈው ኬፕ ቨርዴ ከስፔን… አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ይደረጋሉ፡፡ በምድብ 8 የመጀመሪያ ጊዜ የዓለም ዋንጫ ተሳትፎዋን የምታደርገው አፍሪካዊቷ ኬፕ ቨርዴ ምሽት 1 ሰዓት ላይ ከስፔን ጋር ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡ የአንድ ጊዜ የመድረኩ ሻምፒዮን ስፔን በኦፕታ ቅድመ ትንተና መሰረት የ2026ቱን የዓለም ዋንጫ እንደምታነሳ ቅድመ ግምት አግኝታለች፡፡ በዚሁ ምድብ የሚገኙት ሳዑዲ አረቢያ እና ዩራጋይ ሌሊት 7 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡ በምድብ 7 የተደለደሉት ቤልጂየም ከግብፅ ምሽት 4 ሰዓት እንዲሁም ኢራን ከኒውዚላንድ ሌሊት 10 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን የሚያደርጉ ይሆናል፡፡

በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት አራት ጨዋታዎች ይደረ
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡ በዕለቱ የመጀመሪያ ጨዋታ ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ነገሌ አርሲ ከሀዋሳ ከተማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡ ነገሌ አርሲ በዛሬው ጨዋታ ነጥብ የሚጥል ከሆነ ሲዳማ ቡና ቀሪ 3 ጨዋታዎች እያሉት የሊጉ ሻምፒዮን መሆኑን ያረጋግጣል፡፡ በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ አዳማ ከተማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይገናኛሉ፡፡ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ደግሞ ቀን 9 ሰዓት ላይ አርባምንጭ ከተማ ከምድረ ገነት ሽረ እንዲሁም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ሀድያ ሆሳዕና ከፋሲል ከነማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

ኢትዮጵያ መድን ድሬዳዋ ከተማን አሸነፈ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ መድን ድሬዳዋ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል፡
+2
ኢትዮጵያ መድን ድሬዳዋ ከተማን አሸነፈ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ መድን ድሬዳዋ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡ ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ወገኔ ገዛኸኝ የኢትዮጵያ መድንን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ አስቆጥሯል፡፡ ቀደም ሲል በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ቡናን 2 ለ 1 እንዲሁም ቅዱስ ጊዮርጊስ መቻልን 3 ለ 0 አሸንፈዋል።

ሲዳማ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሲዳማ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ተጋ
+4
ሲዳማ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሲዳማ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል፡፡ ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ቡናን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡ ለሲዳማ ቡና የማሸነፊያ ግቦቹን ያሬድ ባየህ እና ብርሃኑ በቀለ ሲያስቆጥሩ÷ ኢትዮጵያ ቡናን ከሽንፈት ያልታደገች ግብ ዘላለም አባተ ከመረብ አሳርፏል፡፡ በተመሳሳይ ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ሌላኛው የዕለቱ ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ መቻልን 3 ለ 0 ሲያሸንፍ ፍፁም ጥላሁን፣ ሀብታሙ ጉልላት እና የአብስራ ጎሳዬ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል፡፡ የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል ምሽት 12 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ መድን ከድሬ ዳዋ ከተማ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡

አትሌት ማሞ ሐጫሉ እና ማኅሌት ካሳሁን የቦቆጂ ታላቁ ሩጫን አሸነፉ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ለ5ኛ ጊዜ በቦቆጂ በተደረገው 12 ኪ.ሜ የሩጫ ውድድር በወንዶች አትሌት ማሞ ሐጫሉ
+2
አትሌት ማሞ ሐጫሉ እና ማኅሌት ካሳሁን የቦቆጂ ታላቁ ሩጫን አሸነፉ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ለ5ኛ ጊዜ በቦቆጂ በተደረገው 12 ኪ.ሜ የሩጫ ውድድር በወንዶች አትሌት ማሞ ሐጫሉ ከኦሮሚያ ኮንስትራክሽን አሸንፏል። በውድድሩ አትሌት አማን ቃዲ እና አትሌት አልዬ ቃሲም ተከታትለው በመግባት ሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቅቀዋል። በሴቶች የአሰላ አትሌቲክስ ክለብ አትሌቷ ማኅሌት ካሳሁን ስታሸንፍ÷ አትሌት ኪያ ፍስሃ ከአሰላ አትሌቲክስ ማሠልጠኛ ሁለተኛ፣ አትሌት ድርቤ ኢርኮ ሶስተኛ ወጥተዋል። መነሻና መድረሻውን በቦቆጂ ስታዲየም ባደረገው ከ15 ዓመት በታች የአዳጊዎች ሻምፕዮና በሴቶች ዓባይ ከተማ በወንዶች ደግሞ ካሊድ ሱልጣን ማሸነፍ ችለዋል። በውድድሩ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዲኤታ አቶ መኪዩ ሙሐመድ፣ የቱሪዝም ሚኒስትር ዲኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር)፣ የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሮዛ ቢያ ጨምሮ የተለያዩ የመንግሥት ስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። በዳዊት መሐሪ

በዓለም ዋንጫ የአፍሪካ ተወካዮቹ ኮትዲቯር እና ቱኒዚያ ከተጋጣሚዎቻቸው ጋር የሚያደርጉት ጨዋታ… አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ አዘጋጅነት እየተካሄደ በ
+2
በዓለም ዋንጫ የአፍሪካ ተወካዮቹ ኮትዲቯር እና ቱኒዚያ ከተጋጣሚዎቻቸው ጋር የሚያደርጉት ጨዋታ… አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026ቱ ዓለም ዋንጫ አፍሪካን የሚወክሉት ኮትዲቯር እና ቱኒዚያ ዛሬ ምሽት ከተጋጣሚዎቻቸው ጋር ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡ በዚህም መሰረት ኮትዲቯር ከደቡብ አሜሪካዊቷ ሀገር ኢኳዶር ከሌሊቱ 8 ሰዓት ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡ በርካታ የአውሮፓ ሊጎች ልምድ ያላቸውን ተጫዋቾች የያዘቸው ኮትዲቯር ለኢኳዶር ፈተና እንደምትሆን ይጠበቃል፡፡ ሌላኛዋ የአፍሪካ ተወካይ ሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር ቱኒዚያ ከሲዊዲን ጋር ከሌሊቱ 11 ሰዓት ላይ የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡ ቀደም ብሎ ምሽት 2 ሰዓት ላይ ጀርመን ከካራካኦ የምታደርገው ጨዋታ ይጠበቃል፡፡ ኔዘርላንድ ከጃፓን የሚያደርጉት ጨዋታም ሌላኛው ዛሬ ምሽት የሚከናወን መርሐ ግብር ነው፡፡ ትናንት ምሽት በተደረጉ የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎች አውስትራሊያ ቱርኪዬን 2 ለ 0 እንዲሁም ስኮትላድ ሃይቲን 1 ለ 0 አሸንፈዋል፡፡ ሞሮኮ ከብራዚል እንዲሁም ኳታር ከስዊዘርላንድ በተመሳሳይ አንድ አቻ በሆነ ውጤት ጨዋታቸውን አጠናቅቀዋል፡፡