FMC Sport ፋና ስፖርት
前往频道在 Telegram
This is Fana Media Corporation’s (FMC) Sport official Telegram channel. For more updates please visit https://fanamc.com/amharic/
显示更多📈 Telegram 频道 FMC Sport ፋና ስፖርት 的分析概览
频道 FMC Sport ፋና ስፖርት (@fmcsport) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 36 527 名订阅者,在 体育 类别中位列第 1 868,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 905 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 36 527 名订阅者。
根据 17 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -537,过去 24 小时变化为 -5,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 6.97%。内容发布后 24 小时内通常能获得 3.44% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 2 548 次浏览,首日通常累积 1 256 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 4。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“This is Fana Media Corporation’s (FMC) Sport official Telegram channel.
For more updates please visit
https://fanamc.com/amharic/”
凭借高频更新(最新数据采集于 18 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 体育 类别中的关键影响点。
36 527
订阅者
-524 小时
-247 天
-53730 天
帖子存档
36 527
በዓለም ዋንጫ የጋሪ ሊንከርን ክብረ ወሰን የተጋራው ሃሪ ኬን…
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) እንግሊዛዊው የፊት መስመር ተጫዋች ሃሪ ኬን በዓለም ዋንጫ ውድድር በርካታ ግቦችን በማስቆጠር የሀገሩን ልጅ ጋሪ ሊንከር ክብረ ወሰን ተጋርቷል፡፡ በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታ ትናንት ምሽት እንግሊዝ ክሮሺን 4 ለ 2 ማሸነፏ ይታወቃል፡፡ እንግሊዛዊው የ32 ዓመቱ…
https://www.fanamc.com/archives/316987
36 527
+1
በዓለም ዋንጫ የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ክብረወሰንን የተጋራው ሊዮ ሜሲ..
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በስድስት የዓለም ዋንጫ ውድድሮች በመጫወት ክብረወሰን ያስመዘገበው ሊዮኔል ሜሲ በ16 ግቦች የዓለም ዋንጫ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነትን ክብረ ወሰን ተጋርቷል፡፡
በፈረንጆቹ 2006 በጀርመን ዓለም ዋንጫ በ18 አመቱ ሀገሩን ወክሎ መጫወት የጀመረው የሮዛሪዮው ተወላጅ ሊዮኔል አንድሬስ ሜሲ የዘንድሮውን ጨምሮ በስድስት የዓለም ዋንጫዎች ተሳትፏል፡፡
ትናንት ምሽት አርጀንቲና አልጀሪያን 3 ለ 0 ባሸነፈችበት የምድብ የመጀመሪያ ጨዋታ ሦስቱንም ግቦች በማስቆጠር ሀትሪክ የሰራው ሜሲ የዓለም መነጋገሪያ ሆኗል፡፡
ለሀገሩ አርጀንቲና እስካሁን 200 ጨዋታዎችን ያደረገው የ38 አመቱ ኮከብ በጀርመናዊው ሚሮስላቭ ክሎስ ተይዞ የነበረውን የምንጊዜም የውድድሩ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ክብረወሰን ተጋርቷል፡፡
የ2022ቱ የኳታር ዓለም ዋንጫ አሸናፊው ሜሲ አሁንም የቡድኑ ቁልፍ ተጫዋች መሆኑን ከማስመስከር ባሻገር ሀገሩ በዘንድሮውም ዓለም ዋንጫ ለአሸናፊነት እንድትታጭ አስችሏል፡፡
የዘንድሮውን የዓለም ዋንጫ ጅማሮ በሀትሪክ ያሳመረው ሊዮ ሜሲ በቀጣይ ጨዋታዎች ክብረ ወሰኑን የግሉ የማድረግ ሰፊ እድል አለው፡፡
የ26 አመቱ ፈረንሳዊ ኪሊያን ምባፔ ትናንት ምሽት ሀገሩ ሴኔጋልን ባሸነፈችበት ጨዋታ ያስቆጠራቸውን ሁለት ግቦች ጨምሮ 14 ግቦችን ከመረብ ያሳረፈ ሲሆን፥ ክብረ ወሰኑን የግሉ ለማድረግ ከሜሲ ጋር ተፋጧል፡፡
ሊዮኔል ሜሲ በተጨማሪም በዓለም ዋንጫ ታሪክ በአንድ ጨዋታ ሦስት ግቦችን ያሰቆጠረ በእድሜ አንጋፋው ተጫዋች በመሆን ተጨማሪ ክብረ ወሰን የግሉ አድርጓል፡፡
በአቤል ነዋይ
36 527
+1
ፖርቹጋል ከኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ..
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 10፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫው የክሪስቲያኖ ሮናልዶ ሀገር ፖርቹጋል የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋን ዛሬ ምሽት ታደርጋለች፡፡ ፖርቹጋል ምሽት 2 ሰዓት ላይ ከኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ጋር በሂውስተን ስታዲየም በምታደርገው ጨዋታ የማሸነፍ ቅድመ ግምት ተሰጥቷታል፡፡ የመጨረሻው የዓለም ዋንጫ ተሳትፎውን የሚያደርገው ፖርቹጋላዊ ኮከብ በጨዋታው ልዩነት ፈጣሪ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ በአውሮፓ የተለያዩ ክለቦች ቁልፍ…
https://www.fanamc.com/archives/316942
36 527
ሩበን አሞሪም የኤሲሚላን አሰልጣኝ ሆኑ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የማንቼስተር ዩናይትድ የቀድሞ አሰልጣኝ ሩበን አሞሪም የኤሲሚላን አሰልጣኝ ሆነው ተሾሙ፡፡
አሰልጣኙ በጣሊያኑ ክለብ ኤሲሚላን እስከ ፈረንጆቹ 2028 የሚያቆያቸውን ውል ነው የተፈራረሙት፡፡
የ41 ዓመቱ አሰልጣኝ ማንቼስተር ዩናይትድን ለ14 ወራት ማሰልጠን ቢችሉም በውጤት ማጣት ምክንያት መሰናበታቸው አይዘነጋም፡፡
ኤሲሚላን በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት በሴሪ ኤው 5ኛ ደረጃን ይዞ ማጠናቀቁ ይታወሳል፡፡
36 527
+2
ወላይታ ድቻ ባሕር ዳር ከተማን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ወላይታ ድቻ ባሕር ዳር ከተማን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡
ቀን 10 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ የወላይታ ድቻን የማሸነፊያ ሁለት ግቦች ያሬድ ዳርዛ አስቆጥሯል፡፡
በተመሳሳይ ስታዲየም አስቀድሞ ቀን 7 ሰዓት ላይ የተገናኙት ኢትዮ ኤሌክትሪክ እና መቐለ 70 እንደርታ ያለምንም ግብ አቻ መለያየታቸው ይታወቃል፡፡
በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ የተገናኙት ሸገር ከተማ እና ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ያለምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል፡፡
36 527
ሪያል ማድሪድ የአንቶኒዮ ሩዲገርን ውል አራዘመ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ሪያል ማድሪድ የተከላካዩን አንቶኒዮ ሩዲገር ውል ለተጨማሪ አንድ ዓመት ማራዘሙን ይፋ አድርጓል፡፡
ጀርመናዊው ተጫዋች ሩዲገር በሎስብላንኮዎቹ ቤት እስከ ፈረንጆቹ 2027 ድረስ የሚቆይ ይሆናል፡፡
አንቶኒዮ ሩዲገር ከምዕራብ ለንደኑ ክለብ ቼልሲ በፈረንጆቹ 2022 ሪያል ማድሪድን መቀላቀሉ ይታወሳል፡፡
36 527
ፈረንሳይ ከሴኔጋል…
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ይደረጋሉ፡፡
በምድብ 9 ላይ የምትገኘው የሁለት ጊዜ የመድረኩ ሻምፒዮን ፈረንሳይ ከአፍሪካዊቷ ሀገር ሴኔጋል ጋር ምሽት 4 ሰዓት ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡
በዚሁ ምድብ የሚገኙት ኢራቅ እና ኖርዌይ ሌሊት 7 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
በምድብ 10 የተደለደሉት አርጀንቲና እና አልጄሪያ ደግሞ ሌሊት 10 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን የሚያደርጉ ይሆናል፡፡
36 527
ቱኒዚያ በዓለም ዋንጫ ከአንድ ጨዋታ ሽንፈት በኋላ አዲስ አሰልጣኝ ሾመች
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ እየተሳተፈች የምትገኘው ቱኒዚያ በመጀመሪያ የምድብ ጨዋታ ከተሸነፈች በኋላ አዲስ አሰልጣኝ ሾመች፡፡
ሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር በስዊድን የደረሰባትን የ5 ለ 1 ሽንፈት ተከትሎ አሰልጣኝ ሳብሪ ላሞቺን ከኃላፊነት አሰናብታለች፡፡
በምትካቸውም የ57 ዓመቱን ፈረንሳዊ አሰልጣኝ ሄርቬ ሬናርድን የብሔራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ አድርጋ ሾማለች፡፡
ሄርቬ ሬናርድ በአሰልጣኝነት ዘመናቸው ቱኒዚያ 5ኛ አፍሪካዊ ብሔራዊ ቡድናቸው ሲሆን፥ ከዚህ ቀደም ዛምቢያ፣ አንጎላ፣ ኮት ዲቯር እና ሞሮኮን ማሰልጠናቸው ይታወሳል፡፡
ምድብ 6 ላይ የምትገኘው ቱኒዚያ በቀጣይ ከጃፓን እና ኔዘርላንድስ ጋር ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡
36 527
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ ሦስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት ሦስት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡
በዕለቱ የመጀመሪያ ጨዋታ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ከመቐለ 70 እንደርታ ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ይገናኛሉ፡፡
በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ ባህር ዳር ከተማ ከወላይታ ድቻ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
በሌላ የዛሬ መርሐ ግብር ሸገር ከተማ ከወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ቀን 10 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይጫወታሉ፡፡
36 527
ሜሲ እና ምባፔ የምንጊዜም የዓለም ዋንጫ ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ለመሆን…
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በፈረንጆቹ 1930 መደረግ በጀመረው የዓለም ዋንጫ ውድድር ጀርመናዊው ሚሮስላቭ ክሎስ የመድረኩን ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ደረጃን እየመራው ይገኛል፡፡ የጀርመን ብሔራዊ ቡድን የቀድሞ ኮከብ ሚሮስላቭ ክሎስ በዓለም ዋንጫ ውድድር 24 ጨዋታዎችን አድርጎ 16 ግቦችን በማስቆጠር የዓለም ዋንጫ የምን ጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪዎች ደረጃን እየመራ ይገኛል፡፡ ሚሮስላቭ ክሎስ…
https://www.fanamc.com/archives/316875
36 527
+5
ግብጽ እና ቤልጂዬም አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ የመጀመሪያ ምድብ ጨዋታ ግብጽ እና ቤልጂዬም 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።
36 527
+3
ስፔን እና ኬፕ ቨርዴ አቻ ተለያዩ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የምድብ ስምንት የመጀመሪያ ጨዋታ ስፔን እና ኬፕ ቨርዴ 0 ለ 0 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።
ለዓለም ዋንጫ አሸናፊነት ትልቅ ግምት ከተሰጣቸው ብሔራዊ ቡድኖች መካከል የሆነችው ስፔን ከኬፕ ቨርዴ ጋር ባደረገችው የውድድሩ የመጀመሪያ ጨዋታ አቻ ተለያይታለች።
በጨዋታው የስፔን ተጫዋቾች ግብ ለማስቆጠር በተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርጉም የኬፕ ቨርዴን መረብ መድፈር ሳይችሉ ቀርተዋል።
36 527
+2
አርባምንጭ ከተማ ምድረ ገነት ሽረን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር አርባምንጭ ከተማ ምድረ ገነት ሽረን 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡
በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ቀን 9 ሰዓት ላይ በተደረገው ጨዋታ የአርባምንጭ ከተማን የማሸነፊያ ግቦች አቡዱልራህማን መሐመድና ቴዎድሮስ አጨ አስቆጥረዋል፡፡
በዚሁ ስታዲየም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ሀድያ ሆሳዕና ከፋሲል ከነማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
አስቀድሞ ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተደረገ በሌላ የሊጉ ጨዋታ ነገሌ አርሲ ሀዋሳ ከተማን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡
የነገሌ አርሲን የማሸነፊያ ግቦች አለኝታ ማርቆስ እና ሮሆቦት ስላሎ አስቆጥረዋል፡፡
ሀዋሳ ከተማን ከሽንፈት ያልታደገውን ግብ ደግሞ ጌታነህ ከበደ ከመረብ አሳርፏል።
በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ መደረግ በጀመረው ጨዋታ አዳማ ከተማ ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን 2 ለ 0 እየመራ ይገኛል፡፡
36 527
ሪያል ማድሪድ ኩኩሬላን ማስፈረሙን ይፋ አደረገ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የስፔኑ ክለብ ሪያል ማድሪድ ማርክ ኩኩሬላን ከቼልሲ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡
ስፔናዊው የግራ መስመር ተጫዋች በሪያል ማድሪድ ቤት እስከ ፈረንጆቹ 2032 ድረስ የሚያቆየውን ውል ነው የተፈራረመው፡፡
ሪያል ማድሪድ ለ27 ዓመቱ ተጫዋች 55 ሚሊየን ዩሮ እና እየታየ የሚጨመር 5 ሚሊየን ዩሮ የዝውውር ሒሳብ የሚከፍል ይሆናል፡፡
ኩኩሬላ የምዕራብ ለንደኑን ክለብ ቼልሲ በ2022 ከብራይተን መቀላቀሉ ይታወሳል፡፡
ተጫዋቹ በቼልሲ በነበረው ቆይታ የኮንፈረንሰ ሊግ እና የዓለም ክለቦች ዋንጫዎችን ማሸነፉ አይዘነጋም፡፡
36 527
በዓለም ዋንጫ ለመጀመሪያ ጊዜ የምትሳተፈው ኬፕ ቨርዴ ከስፔን…
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ሜክሲኮ እና ካናዳ አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026 የዓለም ዋንጫ የምድብ የመጀመሪያ ዙር ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ይደረጋሉ፡፡
በምድብ 8 የመጀመሪያ ጊዜ የዓለም ዋንጫ ተሳትፎዋን የምታደርገው አፍሪካዊቷ ኬፕ ቨርዴ ምሽት 1 ሰዓት ላይ ከስፔን ጋር ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡
የአንድ ጊዜ የመድረኩ ሻምፒዮን ስፔን በኦፕታ ቅድመ ትንተና መሰረት የ2026ቱን የዓለም ዋንጫ እንደምታነሳ ቅድመ ግምት አግኝታለች፡፡
በዚሁ ምድብ የሚገኙት ሳዑዲ አረቢያ እና ዩራጋይ ሌሊት 7 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
በምድብ 7 የተደለደሉት ቤልጂየም ከግብፅ ምሽት 4 ሰዓት እንዲሁም ኢራን ከኒውዚላንድ ሌሊት 10 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን የሚያደርጉ ይሆናል፡፡
36 527
በኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 8፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት አራት ጨዋታዎች ይደረጋሉ፡፡
በዕለቱ የመጀመሪያ ጨዋታ ቀን 7 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም ነገሌ አርሲ ከሀዋሳ ከተማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
ነገሌ አርሲ በዛሬው ጨዋታ ነጥብ የሚጥል ከሆነ ሲዳማ ቡና ቀሪ 3 ጨዋታዎች እያሉት የሊጉ ሻምፒዮን መሆኑን ያረጋግጣል፡፡
በተመሳሳይ ስታዲየም ቀን 10 ሰዓት ላይ አዳማ ከተማ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይገናኛሉ፡፡
በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ደግሞ ቀን 9 ሰዓት ላይ አርባምንጭ ከተማ ከምድረ ገነት ሽረ እንዲሁም ምሽት 12 ሰዓት ላይ ሀድያ ሆሳዕና ከፋሲል ከነማ ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
36 527
+2
ኢትዮጵያ መድን ድሬዳዋ ከተማን አሸነፈ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ኢትዮጵያ መድን ድሬዳዋ ከተማን 1 ለ 0 አሸንፏል፡፡
ምሽት 12 ሰዓት ላይ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ወገኔ ገዛኸኝ የኢትዮጵያ መድንን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ አስቆጥሯል፡፡
ቀደም ሲል በተደረጉ የሊጉ ጨዋታዎች ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ቡናን 2 ለ 1 እንዲሁም ቅዱስ ጊዮርጊስ መቻልን 3 ለ 0 አሸንፈዋል።
36 527
+4
ሲዳማ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ35ኛ ሳምንት ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሲዳማ ቡና እና ቅዱስ ጊዮርጊስ ተጋጣሚዎቻቸውን አሸንፈዋል፡፡
ቀን 9 ሰዓት ላይ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ የሊጉ መሪ ሲዳማ ቡና ኢትዮጵያ ቡናን 2 ለ 1 አሸንፏል፡፡
ለሲዳማ ቡና የማሸነፊያ ግቦቹን ያሬድ ባየህ እና ብርሃኑ በቀለ ሲያስቆጥሩ÷ ኢትዮጵያ ቡናን ከሽንፈት ያልታደገች ግብ ዘላለም አባተ ከመረብ አሳርፏል፡፡
በተመሳሳይ ሰዓት በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም በተደረገው ሌላኛው የዕለቱ ጨዋታ ቅዱስ ጊዮርጊስ መቻልን 3 ለ 0 ሲያሸንፍ ፍፁም ጥላሁን፣ ሀብታሙ ጉልላት እና የአብስራ ጎሳዬ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል፡፡
የሊጉ መርሐ ግብር ሲቀጥል ምሽት 12 ሰዓት ላይ ኢትዮጵያ መድን ከድሬ ዳዋ ከተማ በአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
36 527
+2
አትሌት ማሞ ሐጫሉ እና ማኅሌት ካሳሁን የቦቆጂ ታላቁ ሩጫን አሸነፉ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ለ5ኛ ጊዜ በቦቆጂ በተደረገው 12 ኪ.ሜ የሩጫ ውድድር በወንዶች አትሌት ማሞ ሐጫሉ ከኦሮሚያ ኮንስትራክሽን አሸንፏል።
በውድድሩ አትሌት አማን ቃዲ እና አትሌት አልዬ ቃሲም ተከታትለው በመግባት ሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃን ይዘው አጠናቅቀዋል።
በሴቶች የአሰላ አትሌቲክስ ክለብ አትሌቷ ማኅሌት ካሳሁን ስታሸንፍ÷ አትሌት ኪያ ፍስሃ ከአሰላ አትሌቲክስ ማሠልጠኛ ሁለተኛ፣ አትሌት ድርቤ ኢርኮ ሶስተኛ ወጥተዋል።
መነሻና መድረሻውን በቦቆጂ ስታዲየም ባደረገው ከ15 ዓመት በታች የአዳጊዎች ሻምፕዮና በሴቶች ዓባይ ከተማ በወንዶች ደግሞ ካሊድ ሱልጣን ማሸነፍ ችለዋል።
በውድድሩ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዲኤታ አቶ መኪዩ ሙሐመድ፣ የቱሪዝም ሚኒስትር ዲኤታ እንደገና አበበ (ዶ/ር)፣ የኦሮሚያ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሮዛ ቢያ ጨምሮ የተለያዩ የመንግሥት ስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
በዳዊት መሐሪ
36 527
+2
በዓለም ዋንጫ የአፍሪካ ተወካዮቹ ኮትዲቯር እና ቱኒዚያ ከተጋጣሚዎቻቸው ጋር የሚያደርጉት ጨዋታ…
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 7፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የ2026ቱ ዓለም ዋንጫ አፍሪካን የሚወክሉት ኮትዲቯር እና ቱኒዚያ ዛሬ ምሽት ከተጋጣሚዎቻቸው ጋር ጨዋታቸውን ያደርጋሉ፡፡
በዚህም መሰረት ኮትዲቯር ከደቡብ አሜሪካዊቷ ሀገር ኢኳዶር ከሌሊቱ 8 ሰዓት ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡
በርካታ የአውሮፓ ሊጎች ልምድ ያላቸውን ተጫዋቾች የያዘቸው ኮትዲቯር ለኢኳዶር ፈተና እንደምትሆን ይጠበቃል፡፡
ሌላኛዋ የአፍሪካ ተወካይ ሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር ቱኒዚያ ከሲዊዲን ጋር ከሌሊቱ 11 ሰዓት ላይ የመጀመሪያ የምድብ ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡
ቀደም ብሎ ምሽት 2 ሰዓት ላይ ጀርመን ከካራካኦ የምታደርገው ጨዋታ ይጠበቃል፡፡
ኔዘርላንድ ከጃፓን የሚያደርጉት ጨዋታም ሌላኛው ዛሬ ምሽት የሚከናወን መርሐ ግብር ነው፡፡
ትናንት ምሽት በተደረጉ የዓለም ዋንጫ ጨዋታዎች አውስትራሊያ ቱርኪዬን 2 ለ 0 እንዲሁም ስኮትላድ ሃይቲን 1 ለ 0 አሸንፈዋል፡፡
ሞሮኮ ከብራዚል እንዲሁም ኳታር ከስዊዘርላንድ በተመሳሳይ አንድ አቻ በሆነ ውጤት ጨዋታቸውን አጠናቅቀዋል፡፡
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
