ch
Feedback
FMC Sport ፋና ስፖርት

FMC Sport ፋና ስፖርት

前往频道在 Telegram

This is Fana Media Corporation’s (FMC) Sport official Telegram channel. For more updates please visit https://fanamc.com/amharic/

显示更多

📈 Telegram 频道 FMC Sport ፋና ስፖርት 的分析概览

频道 FMC Sport ፋና ስፖርት (@fmcsport) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 36 511 名订阅者,在 体育 类别中位列第 1 882,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 910

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 36 511 名订阅者。

根据 09 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -63,过去 24 小时变化为 2,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 已认证(Telegram 官方确认)
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 6.02%。内容发布后 24 小时内通常能获得 3.88% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 2 199 次浏览,首日通常累积 1 416 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 3

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
This is Fana Media Corporation’s (FMC) Sport official Telegram channel. For more updates please visit https://fanamc.com/amharic/

凭借高频更新(最新数据采集于 10 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 体育 类别中的关键影响点。

36 511
订阅者
+224 小时
+957
-6330
帖子存档
ፈረንሳይ ሞሮኮን በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍጻሜ አለፈች አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫው የሩብ ፍጻሜ የመጀመሪያ መርሐ ግብር ፈረንሳይ ሞሮኮን 2 ለ 0 በማሸነፍ ግማሽ ፍ
+3
ፈረንሳይ ሞሮኮን በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍጻሜ አለፈች አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫው የሩብ ፍጻሜ የመጀመሪያ መርሐ ግብር ፈረንሳይ ሞሮኮን 2 ለ 0 በማሸነፍ ግማሽ ፍጻሜውን ተቀላቅላለች። በቦስተን ጁሌት ስታዲየም በተደረገው የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ የፈረንሳይን ግቦች ኪሊያን ምባፔ እና ኦስማን ዴምቤሌ አስቆጥረዋል። በመጀመሪያው አጋማሽ ፍጹም ቅጣት ምት የሳተው ምባፔ በዚህ ዓለም ዋንጫ ከሊዮኔል ሜሲ እኩል 8 ግቦች በማስቆጠር ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነትን በጋራ እየመራ ይገኛል። ፈረንሳይ በሦስት ተከታታይ የዓለም ዋንጫ ውድድሮች ላይ የፍጻሜ ተፋላሚ ለመሆን በግማሽ ፍጻሜው ከስፔን እና ቤልጂየም አሸናፊ ጋር ትገናኛለች፡፡

ኒውካስል ዩናይትድ ሻን ስቱርን አስፈረመ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኒውካስል ዩናይትድ ሻን ስቱርን ከአያክስ አምስተርዳም ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡ ኒውካስል ዩናይትድ ለ18
ኒውካስል ዩናይትድ ሻን ስቱርን አስፈረመ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ኒውካስል ዩናይትድ ሻን ስቱርን ከአያክስ አምስተርዳም ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡ ኒውካስል ዩናይትድ ለ18 ዓመቱ ኔዘርላንዳዊ አማካይ 20 ሚሊየን ፓውንድ እና እየታየ የሚጨመር 3 ሚሊየን ፓውንድ ወጪ በማድረግ ተጫዋቹን የግሉ አድርጓል፡፡ ሻን ስቱርን በእንግሊዙ ክለብ ኒውካስል ዩናይትድ ቤት ለአምስት ዓመታት የሚያቆየውን ውል ተፈራርሟል፡፡ ተጫዋቹ በተጠናቀቀው የውድድር ዓመት ለአያክስ አምስተርዳም 24 ጨዋታዎችን አድርጎ አንድ ግብ ብቻ አስቆጥሯል፡፡ ኒውካስል ዩናይትድ ቀደም ሲል በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ባዙማን ቱሬን ከሆፈንሄይም ማስፈረሙ አይዘነጋም፡፡ በሌላ በኩል ኒውካስል ዩናይትድ በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት አንቶኒ ጎርደን ለባርሴሎና እንዲሁም ሳንድሮ ቶናሊን ለቶተንሃም ሆትስፐር አሳልፎ መስጠቱ ይታወቃል፡፡ በተጨማሪም ኒውካስል ዩናይትድ ብራዚላዊውን የቡድኑን አምበል ብሩኖ ጎማሬሽን የሚያጣበት ዕድል ሰፊ መሆኑ በስፋት እየተዘገበ ሲሆን ተጫዋቹ ክለቡን መልቀቅ እንደሚፈልግም አሳውቋል፡፡ በዚህም ክለቡ ቡድኑን ለማጠናከር በዝውውር መስኮቱ ንቁ ተሳትፎ እያደረገ ይገኛል፡፡ በመልካም ፈቃዱ

ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊ ሆነ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ሲዳማ ቡናን 2 ለ 0 በማሸነፍ የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊ ሆኗል
+2
ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊ ሆነ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ ሲዳማ ቡናን 2 ለ 0 በማሸነፍ የኢትዮጵያ ዋንጫ አሸናፊ ሆኗል፡፡ በአዲስ አበባ ስታዲየም በተካሄደው የኢትዮጵያ ዋንጫ የፍጻሜ ጨዋታ የወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን የማሸነፊያ ግቦች ኮንኮኒ ሀፊዝ እና በየነ ባንጃ አስቆጥረዋል፡፡ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ የኢትዮጵያ ዋንጫ ሻምፒዮን ሆኗል፡፡ የሊጉ ሻምፒዮን ሲዳማ ቡና በውድድር ዓመቱ ሁለተኛ ዋንጫ ማሳካት የሚችልበትን ዕድል ሳይጠቀምበት ቀርቷል፡፡

ፈረንሳይ ከሞሮኮ - የምሽቱ ተጠባቂ ጨዋታ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ጥምር አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው በ2026 የዓለም ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ
+2
ፈረንሳይ ከሞሮኮ - የምሽቱ ተጠባቂ ጨዋታ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 2፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ጥምር አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው በ2026 የዓለም ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ ጨዋታዎች ዛሬ ይጀምራሉ፡፡ ዛሬ ምሽት የሁለት ጊዜ የመድረኩ አሸናፊ ፈረንሳይ ከአፍሪካዊቷ ሀገር ሞሮኮ ጋር የምታደርገው ጨዋታ ይጠበቃል፡፡ ፈረንሳይ በ16ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ፓራጓይን እንዲሁም ሞሮኮ አዘጋጇን ሀገር ካናዳን በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን መቀላቀላቸው ይታወሳል፡፡ በዓለም ዋንጫ ታሪክ ለግማሽ ፍጻሜ በመድረስ ብቸኛዋ አፍሪካዊት ሀገር የሆነችው ሞሮኮ በድጋሚ ግማሽ ፍጻሜውን ለመቀላቀል ብርቱ ፉክክር እንደምታደርግ ይጠበቃል፡፡ ሞሮኮ በ2022 የኳታር የዓለም ዋንጫ ለመጀመሪያ ጊዜ ግማሽ ፍጻሜ መግባቷ የሚታወስ ሲሆን፥ በወቅቱ በፈረንሳይ 2 ለ 0 መሸነፏ አይዘነጋም፡፡ በዘንድሮው የዓለም ዋንጫ 7 ግቦችን በማስቆጠር ለወርቅ ጫማው እየተፋለመ የሚገኘው ፈረንሳዊው ኮከብ ኪሊያን ምባፔ በጨዋታው ልዩነት ፈጣሪ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ በተጨማሪም ማይክል ኦሊሴ፣ ኦስማን ዴምቤሌ በፈረንሳይ በኩል እንዲሁም ብራሂም ዲያዝ እና አዘዲን ኦናሂ በሞሮኮ በኩል የሚጠበቁ ተጫዋቾች ነው፡፡ ምሽት 5 ሰዓት ላይ በቦስተን ጁሌት ስታዲየም የሚደረገውን የሁለቱ ብሔራዊ ቡድኖች ጨዋታ አርጀንቲናዊው ዳኛ ፋኩንዶ ቴሎ ይመሩታል፡፡ የፈረንሳይ እና ሞሮኮ አሸናፊ በቀጣይ በግማሽ ፍጻሜው ከስፔን እና ቤልጂየም አሸናፊ ጋር የሚገናኝ ይሆናል፡፡

ማንቼስተር ዩናይትድ አንድሬይ ሳንቶስን ከቼልሲ ለማስፈረም ከስምምነት ደረሰ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ዩናይትድ ብራዚላዊውን የቼልሲ አማካይ አንድሬይ ሳንቶስ ለማስፈ
ማንቼስተር ዩናይትድ አንድሬይ ሳንቶስን ከቼልሲ ለማስፈረም ከስምምነት ደረሰ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ማንቼስተር ዩናይትድ ብራዚላዊውን የቼልሲ አማካይ አንድሬይ ሳንቶስ ለማስፈረም ከስምምነት ደርሷል፡፡ ማንቼስተር ዩናይትድ ለ22 ዓመቱ ተጫዋች ዝውውር 50 ሚሊየን ፓውንድ ለቼልሲ እንደሚከፍል ዘ አትሌቲክ ዘግቧል፡፡ ሳንቶስ በ2023 ከብራዚሉ ክለብ ቫስኮ ደ ጋማ ሰማያዊዎቹን መቀላቀሉ ታወሳል፡፡

ሮቤርቶ ማርቲኔዝ ከፖርቹጋል አሰልጣኝነታቸው ተነሱ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔናዊው አሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ ከፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን ጋር መለያየታቸውን የሀገሪቱ እግር ኳ
ሮቤርቶ ማርቲኔዝ ከፖርቹጋል አሰልጣኝነታቸው ተነሱ አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 1፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ስፔናዊው አሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ ከፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን ጋር መለያየታቸውን የሀገሪቱ እግር ኳስ ፌደሬሽን አስታውቋል፡፡ ፖርቹጋል በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ የ16ቱ ጥሎ ማለፍ ላይ በስፔን ተሸንፋ ከውድድሩ መሰናበቷ ለአሰልጣኙ ከቡድኑ ጋር መለያየት ምክንያት ሆኗል፡፡ ፖርቹጋል በዓለም ዋንጫው ከኮሎምቢያ እና ዴሞክራቲክ ኮንጎ ጋር አቻ ስትለያይ ኡዝቤኪስታን እና ክሮሽያን ማሸነፍ ችላለች፡፡ የ52 ዓመቱ አሰልጣኝ ሮቤርቶ ማርቲኔዝ በ2025 ከፖርቹጋል ጋር የአውሮፓ ኔሽንስ ሊግ ዋንጫን ማሸነፋቸው ይታወሳል። አሰልጣኙ በተደጋጋሚ የ41 ዓመቱን ተጫዋች ክሪስቲያኖ ሮናልዶን በቋሚ አሰላለፍ ውስጥ ማካተታቸው ለትችት የዳረጋቸው ሲሆን፤ በዚህ ምክንያት ለስንብት ሳይበቁ እንዳልቀረ ተነግሯል፡፡ የቤልጂየም ወርቃማ ትውልድን በማባከን የሚወቀሱት ማርቲኔዝ፤ ከፖርቹግል ብሔራዊ ቡድን ጋርም ተመሳሳይ ውድቀት በማስመዝገብ ተሰናብተዋል፡፡

ሜሲ ፍጹም ቅጣት ምት በሳተበት ጨዋታ ግብጽ አርጀንቲናን 1 ለ 0 እየመራች ነው አዲስ አበባ፣ ሰኔ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የ16ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ግብጽ አርጀንቲናን
+2
ሜሲ ፍጹም ቅጣት ምት በሳተበት ጨዋታ ግብጽ አርጀንቲናን 1 ለ 0 እየመራች ነው አዲስ አበባ፣ ሰኔ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የ16ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ግብጽ አርጀንቲናን 1 ለ 0 እየመራች የመጀመሪያውን አጋማሽ አጠናቅቃለች፡፡ የግብጽን የመሪነት ግብ ያሰር ኢብራሂም 15ኛው ደቂቃ ላይ ከመረብ አሳርፏል፡፡ በጨዋታው አርጀንቲና የፍጹም ቅጣት ምት አግኝታ የነበረ ቢሆንም ሊዮኔል ሜሲ ሳይጠቀምበት ቀርቷል፡፡ ሜሲ በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ ለሁለተኛ ጊዜ የፍጹም ቅጣት ምት የሳተ ሲሆን፥ በዓለም ዋንጫ ታሪክ በርካታ የፍጹም ቅጣት ምቶችን (4) በመሳት ብቸኛው ተጫዋች ሆኗል። ሜሲ በእግር ኳስ ሕይወቱ በአጠቃላይ 34 የፍጹም ቅጣት ምቶችን ስቷል፡፡

አርጀንቲና ከግብጽ - ኮሎምቢያ ከስዊዘርላንድ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫው ሩብ ፍጻሜውን የሚቀላቀሉ ሁለት ተጨማሪ ብሔራዊ ቡድኖች የሚታወቁባቸው የጥሎ ማለፍ የመጨ
+2
አርጀንቲና ከግብጽ - ኮሎምቢያ ከስዊዘርላንድ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 30፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫው ሩብ ፍጻሜውን የሚቀላቀሉ ሁለት ተጨማሪ ብሔራዊ ቡድኖች የሚታወቁባቸው የጥሎ ማለፍ የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬ ይደረጋሉ፡፡ ምሽት 1 ሰዓት ላይ የሦስት ጊዜ የመድረኩ አሸናፊ አርጀንቲና ከአፍሪካዊቷ ሀገር ግብጽ ጋር ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡ አርጀንቲና በ32ቱ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ለመጀመሪያ ጊዜ በዓለም ዋንጫ የተሳተፈችውን ኬፕ ቨርዴን በማሸነፍ 16ቱን መቀላቀሏ ይታወሳል፡፡ ተጋጣሚዋ ግብጽ በበኩሏ አውስትራሊያን በመለያ ምት በማሸነፍ ነበር 16ቱን የተቀላቀለችው፡፡ 7 ግቦችን በማስቆጠር ከኪሊያን ምባፔ እና ኧርሊንግ ብራውት ሀላንድ ጋር የከፍተኛ ግብ አስቆጣሪነት ደረጃውን እየመራ የሚገኘው ሊዮኔል ሜሲ በዛሬው ጨዋታ ልዩነት ፈጣሪ እንደሚሆን ይጠበቃል፡፡ በሌላ መርሐ ግብር ስዊዘርላንድ ከኮሎምቢያ ምሽት 5 ሰዓት ላይ ይገናኛሉ፡፡ ስዊዘርላንድ በ32ቱ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ አልጄሪያን እንዲሁም ኮሎምቢያ ሌላኛዋን አፍሪካዊት ሀገር ጋናን በመርታት 16ቱን መቀላቀላቸው አይዘነጋም፡፡ ዛሬ ምሽት የሚደረጉ የ16ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታዎች አሸናፊ ሀገራት በሩብ ፍጻሜው እርስ በእርስ የሚገናኙ ይሆናል፡፡ ፈረንሳይ፣ ሞሮኮ፣ እንግሊዝ፣ ኖርዌይ፣ ስፔን እና ቤልጂየም እስካሁን ድረስ ሩብ ፍጻሜውን የተቀላቀሉ ብሔራዊ ቡድኖች ናቸው፡፡

ስፔን ፖርቹጋልን በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቀለች አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የ16ቱ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ስፔን ፖርቹጋልን 1 ለ 0 በማሸነፍ ሩብ ፋጻሜ
+3
ስፔን ፖርቹጋልን በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቀለች አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የ16ቱ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ስፔን ፖርቹጋልን 1 ለ 0 በማሸነፍ ሩብ ፋጻሜውን ተቀላቅላለች። የስፔንን ብቸኛ የማሸነፊያ ግብ ሜሪኖ ከመረብ አሳርፏል።

ጆርዳን ሄንደርሰን ከዓለም ዋንጫ ውጪ ሆነ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) እንግሊዛዊው ተጫዋች ጆርዳን ሄንደርሰን ከ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ውድድር ውጪ ሆኗል፡፡ የብሬንትፎርዱ አማካ
ጆርዳን ሄንደርሰን ከዓለም ዋንጫ ውጪ ሆነ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) እንግሊዛዊው ተጫዋች ጆርዳን ሄንደርሰን ከ2026ቱ የዓለም ዋንጫ ውድድር ውጪ ሆኗል፡፡ የብሬንትፎርዱ አማካኝ ትላንት ምሽት እንግሊዝ ሜክሲኮን 3 ለ 2 ባሸነፈችበት ጨዋታ የማስታወቂያ ቦርድ ለመዝለል ሲሞክር ወድቆ መጎዳቱ ተመላክቷል፡፡ በዚህም ተጫዋቹ ቀዶ ጥገና እንደሚያስፈልገው እና እንግሊዝ በቀጣይ ከምታደርጋቸው ከዓለም ዋንጫ ጨዋታዎች ውጪ መሆኑ ተረጋግጧል፡፡ ከጉዳቱ በኋላ ሄንደርሰን ወደ ሆስፒታል የተወሰደ ሲሆን÷ ወደ ብሔራዊ ቡድኑ ማረፊያ አለመመለሱም ነው የተገለጸው፡፡ የ36 ዓመቱ ተጫዋች በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ 6 ደቂቃ ብቻ ለእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ግልጋሎት ሰጥቷል፡፡

ትችት እያስተናገደ የሚገኘው አወዛጋቢው የባሎጉን ቀይ ካርድ መሻር… አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፊፋ የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች ፎላሪን ባሎጉን የቀይ ካርድ ቅጣት እንዲነሳ
+2
ትችት እያስተናገደ የሚገኘው አወዛጋቢው የባሎጉን ቀይ ካርድ መሻር… አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) ፊፋ የአሜሪካ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች ፎላሪን ባሎጉን የቀይ ካርድ ቅጣት እንዲነሳ መወሰኑን ተከትሎ ከፍተኛ ትችት እያስተናገደ ይገኛል፡፡ አዘጋጇ ሀገር አሜሪካ ቦሲኒያን 2 ለ 0 በማሸነፍ ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፏን ባረጋገጠችበት የ32ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ባሎጉን 64ኛው ደቂቃ ላይ በቀጥታ ቀይ ካርድ ከሜዳ መሰናበቱ ይታወሳል፡፡ ፊፋ ባሎጉን የተመለከተውን ቀጥታ ቀይ ካርድ በማንሳት በትናንትናው ዕለት ያሳለፈው አወዛጋቢ ውሳኔ ከተለያዩ አካላት ከፍተኛ ተቃውሞ ገጥሞታል፡፡ የአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ውሳኔውን ተከትሎ ባወጣው መግለጫ የሚመለከታቸው ኃላፊዎች ደንቡን ተግባራዊ ማድረግ አለባቸው ሲል አሳስቧል፡፡ እግርኳስ የሚመራው በደንብ መሆኑን የገለጸው ማህበሩ ቀይ ካርድ ግዴታ እንጂ ፍላጎት አይደለም ያለው ማህበሩ የውድድር ህጎች ተግባራዊ ካልሆኑ ውድድሩ ታማኝነቱን እንደሚያጣ አመልክቷል፡፡ እንዲህ ዓይነት ውሳኔ ምሳሌ ሊፈጥር እንደሚችል በመግለፅ በተመሳሳይ ሁኔታዎች እኩል አያያዝ ካልተተገበረ ውድድሩን ይጎዳል ሲል በመግለጫው አመልክቷል። የሊቨርፑል የቀድሞ አሰልጣኝ የርገን ክሎፕ ቀይ ካርዱ መነሳቱን ተከትሎ በሰጡት አስተያየት፥ የፊፋው ፕሬዚዳንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ እና የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ስለ እግርኳስ ሀሳብ የላቸውም ሲሉ ተችተዋል፡፡ የቤልጂየም ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ሩዲ ጋርሽያ በተመሳሳይ ፍሎሪን ባሎጉን የተመለከተው ቀይ ካርድ በመነሳቱ ተቃውሟቸውን ገልጸዋል፡፡ አዘጋጇ ሀገር አሜሪካ ወደ ሩብ ፍጻሜው ለመግባት ዛሬ ሌሊት 9 ሰዓት ላይ ከቤልጂየም ጋር ትጫወታለች፡፡

ቶተንሃም ሆትስፐር ሳንድሮ ቶናሊን አስፈረመ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሰሜን ለንደኑ ክለብ ቶተንሃም ሆትስፐር ጣሊያናዊውን ተጫዋች ሳንድሮ ቶናሊን ከኒውካስል ዩናይትድ ማስፈረ
ቶተንሃም ሆትስፐር ሳንድሮ ቶናሊን አስፈረመ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የሰሜን ለንደኑ ክለብ ቶተንሃም ሆትስፐር ጣሊያናዊውን ተጫዋች ሳንድሮ ቶናሊን ከኒውካስል ዩናይትድ ማስፈረሙን ይፋ አድርጓል፡፡ ቶተንሃም ሆትስፐር የክለቡን የዝውውር ክብረ ወሰን በመስበር በ100 ሚሊየን ፓውንድ የዝውውር ሒሳብ ተጫዋቹን የግሉ አድርጓል፡፡ የ26 ዓመቱ ተጫዋች በሰሜን ለንደኑ ክለብ እስከ ፈረንጆቹ 2032 ድረስ የሚያቆየውን ውል ነው የተፈራረመው፡፡ ሳንድሮ ቶናሊ በፈረንጆቹ 2023 ኒውካስል ዩናይትድን የተቀላቀለ ሲሆን÷ 110 ጨዋታዎችን አድርጎ 10 ግቦችን አስቆጥሯል፡፡ ተጫዋቹ በኒውካስል ዩናይትድ ቆይታው የካራባኦ ካፕ ዋንጫን ማሳካቱ ይታወሳል፡፡

ከብራዚል ብሔራዊ ቡድን በይፋ መሰናበቱን ያሳወቀው ኔይማር ጁኒየር… አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ የ16ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ብራዚል ትናንት ምሽት በኖርዌይ
+2
ከብራዚል ብሔራዊ ቡድን በይፋ መሰናበቱን ያሳወቀው ኔይማር ጁኒየር… አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2026ቱ የዓለም ዋንጫ የ16ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ብራዚል ትናንት ምሽት በኖርዌይ ያልተጠበቀ ሽንፈት አስተናግዳ ከውድድሩ ተሰናብታለች፡፡ በጨዋታው 67ኛ ደቂቃ ላይ ጋብሬል ማርቲኔሊን ተክቶ ወደ ሜዳ የገባው ኔይማር ዳ ሲልቫ ሳንቶስ ጁኒየር ብራዚልን ከሽንፈት ያልታደገች ግብ በፍጹም ቅጣት ምት አስቆጥሯል፡፡ ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ በከፍተኛ ሀዘን የተስተዋለው ኔይማር ጁኒየር ራሱን ከብሔራዊ ቡድኑ ማግለሉን በእንባ ታጅቦ ይፋ አደርጓል፡፡ የ34 አመቱ ተጫዋች "ከብራዚል ጋር ዋንጫ ለማሳካት ብዙ ሞክሬያለው፤ ከቡድኑ ጋር በዚሁ ሜትላይፍ ስታዲየም የጀመርኩትን ሙከራ በዚሁ ስታዲየም ቋጭቼያለሁ" ሲል ተደምጧል፡፡ ኔይማር 80 ግቦችን ለብሔራዊ ቡድኑ በማስቆጠር የሀገሩ የምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ ሲሆን፥ የዘንድሮውን ጨምሮ በ2014፣ 2018 እና 2022ቱ የዓለም ዋንጫ ውድድሮች ላይ ብራዚልን በመወከል አራት ጊዜ መጫወት ችሏል፡፡ በድንቅ ተሰጥኦው፣ ቄንጠኛ አጨዋወቱና ግብ አስቆጣሪነቱ የሚታወቀው ኔይማር በታሪክ የሚታወሱ ድንቅ የተጫዋችነት ጊዜያትን ማሳለፍ ችሏል፡፡ በአቤል ነዋይ

እንግሊዝ ሜክሲኮን በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቀለች አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የ16ቱ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ እንግሊዝ ሜክሲኮን 3 ለ 2 በማሸነፍ ሩብ ፋ
+4
እንግሊዝ ሜክሲኮን በማሸነፍ ሩብ ፍጻሜውን ተቀላቀለች አዲስ አበባ፣ ሰኔ 29፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የ16ቱ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ እንግሊዝ ሜክሲኮን 3 ለ 2 በማሸነፍ ሩብ ፋጻሜውን ተቀላቅላለች። ለእንግሊዝ ጁድ ቢሊንግሀም ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ፥ ቀሪዋን ግብ ደግሞ ሃሪ ኬን በፍጹም ቅጣት ምት ከመረብ አሳርፏል። በጨዋታው ኳንሳህ በሰራው ጥፋት በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል። የሜክሲኮን ግቦች ጁሊያን ኩዊኖንስ እና ራውል ሄሚኔዝ (በፍጹም ቅጣት ምት) አስቆጥረዋል። እንግሊዝ በቀጣዩ ዙር የሩብ ፍጻሜ ጨዋታ ከኖርዌይ ጋር የምትገናኝ ይሆናል።

የኢትዮጵያ የፕሪሚየር ሊግ ተጠናቀቀ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2018 ዓ.ም የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በዛሬው ዕለት ፍጻሜውን አግኝቷል። የሊጉ ሻምፒዮን ሲዳማ ቡናን ከ
+5
የኢትዮጵያ የፕሪሚየር ሊግ ተጠናቀቀ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2018 ዓ.ም የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ በዛሬው ዕለት ፍጻሜውን አግኝቷል። የሊጉ ሻምፒዮን ሲዳማ ቡናን ከኢትዮ ኤሌክትሪክ ያገናኘው የሊጉ የመጨረሻ መርሐ ግብር ጨዋታ ቀን 10 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ተካሂዷል። በዚህም ጨዋት ኢትዮ ኤሌክትሪክ አቤል ሃብታሙ ባስቆጠራት የፍጹም ቅጣት ምት ግብ ሻምፒዮኑ ሲዳማ ቡናን ማሸነፍ ችሏል። የውድድሩ ሻምፒዮን መሆኑን አስቀድሞ ያረጋገጠው ሲዳማ ቡና በዛሬው ዕለት የ2018 ዓ.ም የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ይረከባል።

በዩጂን ዳይመንድ ሊግና በፒችትሪ የጎዳና ሩጫ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸነፉ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2026 የፕሪፎንቴይን ክላሲክ - ዩጂን ዳይመንድ ሊግ እና በአሜሪካ የ
+2
በዩጂን ዳይመንድ ሊግና በፒችትሪ የጎዳና ሩጫ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸነፉ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ2026 የፕሪፎንቴይን ክላሲክ - ዩጂን ዳይመንድ ሊግ እና በአሜሪካ የፒችትሪ የጎዳና ሩጫ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸንፈዋል። በአሜሪካዋ ዩጂን በተካሄደው የዳይመንድ ሊግ የሁለት ማይል ርቀት ውድድር አትሌት አለሺኝ ባወቀ በቀዳሚነት አጠናቅቃለች፡፡ አትሌቷ ውድድሩን በበላይነት ያጠናቀቀችው የወቅቱ ፈጣን የሆነ ሰዓት 9 ደቂቃ ከ20 ሴኮንድ ከ02 ማይክሮ ሴኮንድ በማስመዝገብ ነው፡፡ ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት ሒሩት መሸሻ ሁለተኛ ደረጃን ይዛ ውድድሯን ጨርሳለች፡፡ በዚሁ ርቀት የተሳተፉት አትሌት ማርታ አለማየሁ 4ኛ፣ አትሌት የኔዋ ንብረት 7ኛ እንዲሁም አትሌት አሳየች አይቼው 8ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድራቸውን አጠናቅቀዋል። በሌላ በኩል የአሜሪካ የነጻነት ቀን ክብረ በዓል አካል ሆኖ በተካሄደው በ57ኛው የፒችትሪ የጎዳና ላይ ሩጫ ውድድር አትሌት ፅጌ ገብረሰላማ በ31:02 በሆነ ሰዓት በመግባት ውድድሯን በበላይነት አጠናቅቃለች። ሌላኛዋ ኢትዮጵያዊት አትሌት መልክናት ውዱ 2ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሯን ጨርሳለች፡፡

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዓመቱ የመዝጊያ ጨዋታ ሲዳማ ቡና ከኢትዮ ኤሌክትሪክ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2018 ዓ.ም የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመጨረሻ ጨዋታ በዛሬው
+1
የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የዓመቱ የመዝጊያ ጨዋታ ሲዳማ ቡና ከኢትዮ ኤሌክትሪክ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) የ2018 ዓ.ም የሲቢኢ ኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የመጨረሻ ጨዋታ በዛሬው ዕለት ይደረጋል፡፡ በዚህም የሊጉ ሻምፒዮን ሲዳማ ቡና ከኢትዮ ኤሌክትሪክ በሚያደርጉት ጨዋታ የውድድር ዓመቱ ፍጻሜውን ያገኛል፡፡ የሁለቱ ቡድኖች ጨዋታ ቀን 10 ሰዓት ላይ በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ይደረጋል። ሻምፒዮኑ ሲዳማ ቡና የዛሬውን ጨዋታ የሚያሸንፍ ከሆነ ነጥቡን ወደ 71 ከፍ ማድረግ ይችላል፡፡ ኢትዮ ኤሌክትሪክ ድል የሚያደርግ ከሆነ ደግሞ ነጥቡን 54 በማድረስ 5ኛ ደረጃን ይዞ ውድድር ዓመቱን የሚያጠናቅቅ ይሆናል፡፡ ምድረ ገነት ሽረ፣ ድሬዳዋ ከተማ፣ መቐለ 70 እንደርታ እና አርባ ምንጭ ከተማ ወደ ከፍተኛ ሊጉ የወረዱ ቡድኖች ናቸው፡፡

ብራዚል ከኖርዌይ፤ እንግሊዝ ከሜክሲኮ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ጥምር አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው በ2026 የዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜውን ለ
+2
ብራዚል ከኖርዌይ፤ እንግሊዝ ከሜክሲኮ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በአሜሪካ፣ ካናዳ እና ሜክሲኮ ጥምር አስተናጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው በ2026 የዓለም ዋንጫ ሩብ ፍጻሜውን ለመቀላቀል የሚደረጉ ጨዋታዎች ዛሬም ቀጥለው ይደረጋሉ፡፡ የአምስት ጊዜ የመድረኩ አሸናፊ ብራዚል ምሽት 5 ሰዓት ላይ ከኖርዌይ ጋር ጨዋታዋን ታደርጋለች፡፡ በ32ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ ብራዚል ጃፓንን እንዲሁም ተጋጣሚዋ ኖርዌይ ደግሞ ኮትዲቫርን በማሸነፍ 16ቱን መቀላቀላቸው ይታወሳል፡፡ በዘንድሮ የዓለም ዋንጫ ውድድር 4 ግቦችን ያስቆጠረው ቪኒሸስ ጁኒየር በብራዚል ብሔራዊ ቡድን በኩል ተጠባቂው ተጫዋች ነው፡፡ በሌላ በኩል አምስት ግቦችን ማስቆጠር የቻለው የኖርዌይ ብሔራዊ ቡድን የፊት መስመር ተጫዋች ኤርሊንግ ብራውት ሃላንድ ሌላኛው በዛሬው ጨዋታ የሚጠበቅ ተጫዋች ነው፡፡ በሌላ መርሐ ግብር አዘጋጇ ሀገር ሜክሲኮ ሌሊት 9 ሰዓት ላይ ከእንግሊዝ ጋር ትገናኛለች፡፡ አንድም ግብ ሳይቆጠርባት ሁሉንም ጨዋታዎች በማሸነፍ እዚህ የደረሰችው ሜክሲኮ በዛሬው ጨዋታ ለእንግሊዝ ትልቅ ፈተና ትሆናለች ተብሎ ይጠበቃል፡፡ በ32ቱ ጥሎ ማለፍ ጨዋታ እንግሊዝ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን እንዲሁም ሜክሲኮ ኢኳዶርን በማሸነፍ 16ቱን መቀላቀላቸው ይታወሳል፡፡ እንግሊዝ ከፈረንጆቹ 1966 በኋላ የዓለም ዋንጫን ለማሳካት የምታደርገውን ጉዞ ለማጠናከር ወደ ሜዳ የምትገባ ይሆናል፡፡ አምስት ግቦችን በማስቆጠር ለወርቅ ጫማው እየተፋለመ የሚገኘው እንግሊዛዊው የፊት መስመር ተጫዋች ሃሪ ኬን በጨዋታው ይጠበቃል፡፡

ሞሮኮ ካናዳን በማሸነፍ ሩብ ፋጻሜውን ተቀላቀለች አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የ16ቱ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ሞሮኮ አዘጋጇን ካናዳ 3 ለ 0 በማሸነፍ ሩብ ፋጻ
+3
ሞሮኮ ካናዳን በማሸነፍ ሩብ ፋጻሜውን ተቀላቀለች አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የ16ቱ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ ሞሮኮ አዘጋጇን ካናዳ 3 ለ 0 በማሸነፍ ሩብ ፋጻሜውን ተቀላቅላለች፡፡ የሞሮኮን የማሸነፊያ ግቦች ኡናሂ (ሁለት) እና ራሂሚ ከመረብ አሳርፈዋል።

አርጀንቲና ኬፕ ቨርዴን በማሸነፍ 16ቱን ተቀላቀለች አዲስ አበባ፣ ሰኔ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ የ32ቱ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ አርጀንቲና ኬፕ ቨርዴን 3 ለ 2 በማሸነፍ 16ቱን ተቀላ
+2
አርጀንቲና ኬፕ ቨርዴን በማሸነፍ 16ቱን ተቀላቀለች አዲስ አበባ፣ ሰኔ 26፣ 2018 (ኤፍ ኤም ሲ) በዓለም ዋንጫ የ32ቱ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ አርጀንቲና ኬፕ ቨርዴን 3 ለ 2 በማሸነፍ 16ቱን ተቀላቅላለች። ቡድኖቹ የመደበኛውን ጊዜ በአቻ ውጤት አጠናቅቀው ወደ ተጨማሪ ጊዜ አምርተው ነበር። በጨዋታው የአርጀንቲናን ግቦች ሜሲ፣ ማርቲኔዝ እና ቦርጀስ (በራስ ላይ) አስቆጥረዋል። የኬፕ ቨርዴን ግቦች ዱአርቴ እና ካርባል ከመረብ አሳርፈዋል። ሊዮኔል ሜሲ በዚህ የዓለም ዋንጫ ውድድር ያስቆጠረውን ግብ ሰባት አድርሷል።