ሞዐ ተዋሕዶ ልጆች ፔጅ
Ir al canal en Telegram
"ነፍሳችን በስጋ ስንኖር ብዙ መከራ አለባት። እንዲሁም ከስጋችን ከተለየች በኋላ እንደሰራነው ስራ ጥሩ ወይም መጥፎ እጣፈንታዎች ይገጥሟታል። ታዲያ በህይወት ስንኖር ነፍሳችንን የምታሻግር አንድ መንገድ አለች ይህችም ቀጥተኛዋ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ናት። " https://t.me/MoaeTewahedoB አስተያየት ና ጥያቄ ያለው ብቻ‼️ @sosi5555 ይህ ፔጅ ታህሳስ 30/4/2014
Mostrar más9 566
Suscriptores
-1124 horas
-527 días
-16730 días
Carga de datos en curso...
Canales Similares
Nube de Etiquetas
Sin datos
¿Algún problema? Por favor, actualice la página o contacte a nuestro gerente de soporte.
Menciones Entrantes y Salientes
---
---
---
---
---
---
Atraer Suscriptores
junio '26
junio '26
+35
en 0 canales
mayo '26
+50
en 1 canales
Get PRO
abril '26
+55
en 1 canales
Get PRO
marzo '26
+36
en 4 canales
Get PRO
febrero '26
+20
en 1 canales
Get PRO
enero '26
+26
en 2 canales
Get PRO
diciembre '25
+26
en 3 canales
Get PRO
noviembre '25
+50
en 4 canales
Get PRO
octubre '25
+59
en 1 canales
Get PRO
septiembre '25
+92
en 3 canales
Get PRO
agosto '25
+80
en 1 canales
Get PRO
julio '25
+68
en 2 canales
Get PRO
junio '25
+116
en 1 canales
Get PRO
mayo '25
+68
en 2 canales
Get PRO
abril '25
+101
en 6 canales
Get PRO
marzo '25
+104
en 4 canales
Get PRO
febrero '25
+105
en 5 canales
Get PRO
enero '25
+121
en 2 canales
Get PRO
diciembre '24
+122
en 1 canales
Get PRO
noviembre '24
+184
en 5 canales
Get PRO
octubre '24
+157
en 3 canales
Get PRO
septiembre '24
+344
en 5 canales
Get PRO
agosto '24
+151
en 5 canales
Get PRO
julio '24
+75
en 6 canales
Get PRO
junio '24
+250
en 4 canales
Get PRO
mayo '24
+203
en 4 canales
Get PRO
abril '24
+131
en 2 canales
Get PRO
marzo '24
+201
en 3 canales
Get PRO
febrero '24
+149
en 5 canales
Get PRO
enero '24
+152
en 3 canales
Get PRO
diciembre '23
+165
en 5 canales
Get PRO
noviembre '23
+355
en 6 canales
Get PRO
octubre '23
+267
en 4 canales
Get PRO
septiembre '23
+537
en 0 canales
Get PRO
agosto '23
+256
en 0 canales
Get PRO
julio '23
+343
en 0 canales
Get PRO
junio '23
+337
en 0 canales
Get PRO
mayo '23
+246
en 0 canales
Get PRO
abril '23
+348
en 0 canales
Get PRO
marzo '23
+793
en 0 canales
Get PRO
febrero '23
+828
en 0 canales
Get PRO
enero '23
+491
en 0 canales
Get PRO
diciembre '22
+440
en 0 canales
Get PRO
noviembre '22
+518
en 0 canales
Get PRO
octubre '22
+330
en 0 canales
Get PRO
septiembre '22
+357
en 0 canales
Get PRO
agosto '22
+385
en 0 canales
Get PRO
julio '22
+1 755
en 0 canales
Get PRO
junio '22
+628
en 0 canales
Get PRO
mayo '22
+954
en 0 canales
Get PRO
abril '22
+448
en 0 canales
Get PRO
marzo '22
+1 555
en 0 canales
Get PRO
febrero '22
+2 039
en 0 canales
| Fecha | Crecimiento de Suscriptores | Menciones | Canales | |
| 21 junio | 0 | |||
| 20 junio | 0 | |||
| 19 junio | +3 | |||
| 18 junio | 0 | |||
| 17 junio | 0 | |||
| 16 junio | +2 | |||
| 15 junio | 0 | |||
| 14 junio | 0 | |||
| 13 junio | +4 | |||
| 12 junio | +5 | |||
| 11 junio | +5 | |||
| 10 junio | +1 | |||
| 09 junio | +5 | |||
| 08 junio | +1 | |||
| 07 junio | +1 | |||
| 06 junio | 0 | |||
| 05 junio | +1 | |||
| 04 junio | +5 | |||
| 03 junio | 0 | |||
| 02 junio | 0 | |||
| 01 junio | +2 |
Publicaciones del Canal
+1
😭አሳዛኝ ልብ ሰባሪ ዜና
አሁን አሁን ኢትዮጵያ እየሆነ ያለው ለመናገር የሚከብድ ለሰሚውም ግራ የሚያጋባ ነገር እየተፈጠረ ነው በመጽሐፍ ታሪካቸውን ስናነብ የምንፈራቸው እነ ሄሮድስን እነ ፈርዖንን የሚያስንቅ ትውልድ ተፈጥሯል በዚህ ሁኔታ ሀገር አለን ወይ ያስብላል
ከዋና ከተማው ውጭ የሆኑ በየገጠሩ ያሉ ወገኖቻችን ዕለት ዕለት እንደበግ እየተጎተቱ ሲታረዱ ሲሸጡ ሲለወጡ ማየት ከጀመርን ቆይተናል የዛሬውን ለይት የሚያደርገው መሐል አዲስ አበባ ላይ መፈጸሙ ነው
😭ይህ በፎቶ የምናየው ሩጦ ያልጠገበ ለፍቶ አዳሪ ወጣት አዲስ አበባ ሳሪስ አካባቢ የካዲስኮ ጤና ጣቢያ ሥራ አድሮ ጧት 12 ሰዓት ቤተክርስቲያን ሲሄድ እጅግ በሚዘገንን ግፍ ገድለውታል ያሳዝናል
እንደሰማሁት የልጁ የትውልድ ሀገር ጎንደር ታጭ አርማጭሆ ኩርቢ አቡነ ቤተክርስቲያን ነው
በዚያ አካባቢ ላሉ ወዳጅ ዘመድ ቤተሰብ አድርሱልን ስላሉን ነው
ቢያንስ ወጥተው እንዲቀበሏቸው ሁላችሁም በማኅበራዊ መገናኛው ተባበሯቸው
መድኃኔዓለም ነፍሱን በቅዱሳን እቅፍ ያሳርፍልን 😭
| 2 | 🕰🔔
9:00
ተንስኡ ለጸሎት
በዚህ ሰዓት ይህንን የምታይ ሰው የምታደርገውን ለ2 ደቂቃም ብትሆን ተውና ልዑል እግዚአብሔር እያሰብን ቢያንስ አንድ አባታችን ሆይ እንጸልይ
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አገር ውስጥ ያላቹሁ በስደትም በስራም እንኳን ቢሆን አንድ አባታችን ሆይ እንበል🥰
@MoaeTewahedoB | 685 |
| 3 | 🕰🔔
6:00
ተንስኡ ለጸሎት
በዚህ ሰዓት ይህንን የምታይ ሰው የምታደርገውን ለ2 ደቂቃም ብትሆን ተውና ልዑል እግዚአብሔር እያሰብን ቢያንስ አንድ አባታችን ሆይ እንጸልይ
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አገር ውስጥ ያላቹሁ በስደትም በስራም እንኳን ቢሆን አንድ አባታችን ሆይ እንበል🥰
@MoaeTewahedoB | 734 |
| 4 | ሰኔ 14-የከበሩ ቅዱሳን አክራ፣ ዮሐንስ፣ አብጥልማ እና ፊሊጶስ በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡ እነዚህም አራት የከበሩ ቅዱሳን በጌታችን ስም ሰማዕት ይሆኑ ዘንድ በምክር ተስማሙ፡፡ አክራና ፊሊጶስ ወንድማማቾች ሲሆኑ እነርሱም የከበሩ ባለጸጎች ናቸው፡፡ ዮሐንስና አብጥልማ ግን የከበሩ ቀሳውስት ናቸው፡፡ አራቱም ሰማዕት ይሆኑ ዘንድ ከተስማሙ በኋላ ቀርጥስ ወደሚባል አገር ሄደው በከሃዲው መኮንንነ ፊት ቆመው የጌታችንን አምላክነት መሰከሩ፡፡ መኮንኑም በቀስት እንዲነድፏቸው አዘዘ፡፡ ነገር ግን ቀስቶቹ ሳይነኳቸው ቀሩ፡፡
ዳግመኛም በእቶን እሳት ውስጥ ጨመሯቸው፣ ጌታችንም መልአኩን ልኮ አዳናቸው፡፡ ከዚህም በኋላ በፈረሶች ጅራት ላይ አሥረው ከቀርጥስ እስከ ይምንሑር አገር ድረስ ጎተቷቸው፡፡ አሁንም ጌታችን ፈውሳቸውና ምንም ጉዳት እንዳላገኛቸው ሆኑ፡፡ ከዚህም በኋላ መኮንኑ ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ ራስ ራሶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጧቸው አዘዘ፡፡ እንደትእዛዙም ከይምንሑር ከተማ አውጥተው በሰይፍ አንገታቸውን ቆረጧቸውና የሰማዕትነታቸው ፍጻሜ ሆነ፡፡ እነርሱም የክብርን አክሊል ተቀዳጁ፡፡
ፃ ከምትባል አገር ሰዎቸ መጥተው የቅዱስ አክራን ሥጋ ወሰዱ፡፡ ከይምንሑር ከተማ የመጡ ሰዎች ደግሞ የቅዱስ ፊሊጶስን፣ የቅዱስ ዮሐንስንና የቅዱስ አብጥልማ ሥጋቸውን ወስደው ለሁሉም የተዋቡ አብያተ ክርስቲያናትን ሠርተውላቸው የሰማዕታትን ሥጋቸውን በውስጣቸው አኖሩ፡፡ ከቅዱሳኑም ሥጋ አስገራሚ ተአምራት ተፈጽመው ታዩ፡፡ ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን፡፡
በወርሃዊ በዓላቸው ታስበው የሚውሉትንና በመርዛማ እባብ የተነደፈው ሰው እምነታቸውን ከተቀባ ጠበላቸውን ከጠጣ ፈጥኖ የሚድንባቸውን አቡነ አካለ ክርስቶስን ይወቋቸው! እርሳቸውም ጎናቸውን ሳያሳርፉ አንድ የወይራ ዛፍ ተደግፈው 40 ዓመት ቆመው የጸለዩ ታላቅ አባት ናቸው።
የቤጌምድሩ አቡነ አካለ ክርስቶስ ከአባታቸው ከገላውዲዮስ ከእናታቸው ወለተ አዳም ጌታችን በተወለደበት ዕለት ታኅሣሥ 29 ቀን ተወለዱ፡፡ በተወለዱም ጊዜ ሙት አስነሥተዋል፡፡ የአቡነ እስትንፋሰ
ክርስቶስ ደቀ መዝሙር ሲሆኑ በ21 ዓመታቸው ነው በሐይቅ ገዳም የመነኮሱት፡፡ ‹‹ዘገብርኤል›› የተባለ በስሙ አሳሳች የሆነ ጣዖት አምላኪ ለጣዖት አልሰገድክም ብሎ ወስዶ በእጅጉ አሠቃቷቸዋል፡፡ በ5 ችንካሮች ቸንክሮ ሲያሠቃያቸው ጌታችን ተገልጦላቸው እንደ ጊዮርጊስ ጽና ብሎ ተስፋውን ሰጥቷቸዋል፡፡
ጻድቁ ሀገራቸው ጋይንት ሲሆን በዚሁ አካባቢ ምዕራፈ ቅዱሳን በተባለው ቦታ አንድ የወይራ ዛፍ ተደግፈው 40 ዓመት ቆመው የጸለዩባት ወይራ ዛፍ ዛሬም በገዳሙ ተከብራ ትኖራለች፡፡
(ከአቡነ ተክለ ሃይማኖት ቀጥለው በደብረ ሊባኖስ ገዳም በእጨጌነት የተሾሙ የመጀመሪያ ዕጨጌ አቡነ ኤልሳዕም ከተጋድሎአቸው ብዛት የተነሣ በሕይወት ዘመናቸው ሁሉ ጎናቸውን አሳርፈው ተኝተው አያውቁም ነበር፡፡ ነገር ግን ማረፍ ሲኖርባቸው በወንበር ላይ ተደግፈው ትንሽ ብቻ ያርፉ ነበር፡፡ አቡነ ኤልሳዕ በሞት ያረፉትም እንደልማዳቸው ጎናቸውን ሳያሳርፉ በወንበር ላይ እንደተደገፉ ነበር፡፡ አባታችን ስለዚህም ጉዳይ ሲናገሩ እንዲህ ይሉ ነበር፡- ‹‹ነፍስ ትጋትን ትወዳለች፣ ሥጋ ግን ይደክማል፡፡ ለመነኮሳትና ለእግዚአብሔር አገልጋዮች ሁሉ መኝታ ማብዛት አይገባቸውም፡፡ መኝታ ማብዛት ነፍስን ይጎዳል፣ ሰውነትንም ያደክማል፡፡›› የአቡነ ኤልሳዕ በረከታቸው ይደርብ።)
ወደ አቡነ አካለ ክርስቶስ ገድል እንመለስና የጻድቁ ቤተ መቅደሳቸው ሳይታጠን የቀረ እንደሆነ ወይም ዲያቆኑ መብራት ሳያጠፋ የሄደ እንደሆነ የጻድቁ መቋሚያቸው እንደ ሰው አፍ አውጥታ ታቃጭላለች፡፡ ያበደ ሰው በመቋሚያዋ 7 ጊዜ ቢተሻሽባት ይድናል፡፡ በአካባቢው ብዙ መርዛማ እባቦች ቢኖሩም የአቡነ አካለ ክርስቶስን ስም ከተጠራባቸው ምንም ጉዳት አያደርሱም፡፡ በሌላም ቦታ ሆኖ እባብ የነደፈው ሰው እምነታቸውን ከተቀባ ጸበላቸውን ከጠጣ ፈጥኖ ይድናል፡፡ ይህም ለጻዲቁ የተሰጣቸው ልዩ ቃልኪዳን ነው፡፡
የአቡነ አካለ ክርስቶስ በረከታቸው ይደርብ በጸሎታቸው ይማረን!
(ምንጭ፦ ሐመር 8ኛ ዓመት ቁ.2 1992 ዓ.ም፣ ገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖት፣ የቅዱሳን ታሪክ ገጽ 144 እና 159)
@MoaeTewahedoB | 597 |
| 5 | 🕰🔔
11:00
ተንስኡ ለጸሎት
በዚህ ሰዓት ይህንን የምታይ ሰው የምታደርገውን ለ2 ደቂቃም ብትሆን ተውና ልዑል እግዚአብሔር እያሰብን ቢያንስ አንድ አባታችን ሆይ እንጸልይ
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አገር ውስጥ ያላቹሁ በስደትም በስራም እንኳን ቢሆን አንድ አባታችን ሆይ እንበል🥰
@MoaeTewahedoB | 551 |
| 6 | 🕰🔔
9:00
ተንስኡ ለጸሎት
በዚህ ሰዓት ይህንን የምታይ ሰው የምታደርገውን ለ2 ደቂቃም ብትሆን ተውና ልዑል እግዚአብሔር እያሰብን ቢያንስ አንድ አባታችን ሆይ እንጸልይ
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አገር ውስጥ ያላቹሁ በስደትም በስራም እንኳን ቢሆን አንድ አባታችን ሆይ እንበል🥰
@MoaeTewahedoB | 774 |
| 7 | 🕰🔔
6:00
ተንስኡ ለጸሎት
በዚህ ሰዓት ይህንን የምታይ ሰው የምታደርገውን ለ2 ደቂቃም ብትሆን ተውና ልዑል እግዚአብሔር እያሰብን ቢያንስ አንድ አባታችን ሆይ እንጸልይ
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አገር ውስጥ ያላቹሁ በስደትም በስራም እንኳን ቢሆን አንድ አባታችን ሆይ እንበል🥰
@MoaeTewahedoB | 775 |
| 8 | https://t.me/Moae_TewahedoB
#የትሩፋት_ሥራ_ጀምር
ጨክነህ ቆርጠህ የትሩፋትን ሥራ ጀምር፡፡ በትሩፋት አጠገብ እየተጠራጠርህ አትኑር፡፡ ክብር ይግባውና እግዚአብሔር ከማመን ተስፋ ወጥተህ በልብህ እንኳ አትጠራጠር፡፡ ትሩፋትህ ረብህ ጥቅም የሌለው እንዳይሆን የትሩፋት ሥራ ክቡድ አይምሰልህ፡፡ መሐሪ እግዚአብሔር ለለመኑት ሰዎች ጸጋውን ፈጽሞ እንዲሰጣቸው እመን እንጂ ስጦታው እንደየሥራችን አይደለም፡፡ በትጋታችን፣ በማመናችንና በመሻታችን መጠን ነው እንጂ እንደ ሃይማኖትህ ይደረግልህ ብሏልና፡፡
የትሩፋት ሥራም ይህች ናት፣ አንዱ መተምተሚያ አዘጋጅቶ መሐል ራሱን ይተመትመዋል፡፡ በየጊዜው በሚጸልየው ጸሎት እንዳያፍር ትቀርበኛለች ብሎ ያዝናል፡፡ አንዱ አብዝቶ ይሰግዳል፣ ልጸልይ ያለውን ይጸልያል፣ ስለ ጸሎቱ ፈንታ ብዙ ያለቅሳል፣ በልቅሶው ረብህ ጥቅም ያገኝበታል፡፡ አንዱ የልቡና ሥራ የምትሆን ትሩፋትን በመዘከር ይጋደላል፣ ወደ ተወሰነለት ጸጋ ይደርሳል፣ አንዱ ምግብ ነስቶ ሰውነቱን በረኃብ ያስጨንቃታል ጸሎቱን መፈጸም የማይቻለው እስኪሆን ድረስ፣ አንዱ ተናዶ እየመላለሰ ዳዊት ይጸልያል። በመድገም ዘወትር ጸሎትን ገንዘብ ያደርጋታል፣ አንዱ መጽሐፍ ለመመልከት፣ ለመድገም ጽሙድ ሆኖ ይኖራል፣ አንዱ ከአምላክ በተገኙ መጻሕፍት ያለውን ትርጓሜ ምሥጢር ያስበዋል፣ ያስተውለዋል፣ ይመረምረዋል። ወደ ሥራው ይሳባል፤ አንዱ የዐቢይ ምዕራፉን መለያ አይቶ ምሥጢሩን ያደንቃል፣ ዝምታ ይሰለጥንበታል፡፡ በልማድ መጽሐፍ ከመመልከት በልማድ ከመድገም ይከለከላል፡፡
አንዱ ደግሞ ሁሉንም አንድ አድርጎ ይሠራቸዋል፡፡ በዚህም ይሰለቻል፡፡ ዓለማዊ ሥራ ይሠራል፣ ለሐኬት ጽሙድ ሆኖ ይኖራል። አንዱ መጽሐፍ ከመመልከት ጥቂት ምሥጢር ያገኛል፡፡ በዚህም ትዕቢት ያድርበታል፡፡ በሰው መዘበት ያድርበታል፤ ይበድላል፡፡ አንዱ የልማድ ምክንያት ይሰለጥንበታል፣ አንዱም ይህን ሁሉ ድል ይነሣል፤ ከዚህ ሁሉ ይጠበቃል፡፡ ዕንቁ ክርስቶስን ገንዘብ እስኪያደርገው ወደኋላ አይመለስም፡፡ ደስ ብሎህ እግዚአብሔር ያዘዘውን የትሩፋት ሥራ ጀምር፡
ምክር ወተግሣጽ ዘማር ይስሐቅ | 604 |
| 9 | 🕰🔔
3:00
ተንስኡ ለጸሎት
በዚህ ሰዓት ይህንን የምታይ ሰው የምታደርገውን ለ2 ደቂቃም ብትሆን ተውና ልዑል እግዚአብሔር እያሰብን ቢያንስ አንድ አባታችን ሆይ እንጸልይ
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አገር ውስጥ ያላቹሁ በስደትም በስራም እንኳን ቢሆን አንድ አባታችን ሆይ እንበል🥰
@MoaeTewahedoB | 728 |
| 10 | #የቅዱስ_ሚካኤል_ሰይፍ
🍂በቤተ ክርስቲያናችን ስለቅዱስ ሚካኤል ከሚሳሉት ሥዕሎች አንዱና ነባሩ ደግሞ ቅዱስ ሚካኤል ሰይፍ ይዞ የሚሳለው ሥዕል ነው። ቅዱስ ሚካኤል ሰይፍ ይዞ ከሚሳልባቸው ሥዕሎች ሁለት ደግሞ ነባር እና የታወቁ እንደሆኑ ይሰማኛል። አንደኛው ዲያብሎስን በግራ እግሩ ረግጦ፣ በግራ እጁ ሚዛን ይዞ፣ በቀኝ እጁ ደግሞ የተመዘዘ ሰይፍ ከፍ አድርጎ ይዞ ክንፉን አሰይፎ የሚሳለው ሥዕል ነው። ሁለተኛ ደግሞ በቤተ መቅደሳችን በተለይም በመቅደሱ ዋናዉ በር አንደኛው ተከፋች ላይ ልክ እንደ ሥልጡን እና ንቁ የንጉሥ የቅር ዘብ ቀጥ ብሎ ቆሞ በግራ እጁ አፎቱን በቀኝ እጁ ደግሞ የተመዘዘውን ሰይፍ ይዞ የሚሳለው ሥዕል ነው።
https://t.me/MoaeTewahedoB
🍂ሁለቱም ሥዕሎቹ ነባር እና አብዛኛው ኦርቶዶክሳዊያን ሊያውቋቸው የሚችሉ እንደሆነ እገምታለሁ። የመጀመሪያው ሥዕል ከላይ እንደተገለጸው ከመጀመሪያው ዲያብሎስን ተዋግቶ ያሸነፈው እና እስካሁንም እያሳደደ የሚዋጋው እርሱ መሆኑን ለማሳየት የሚሣል ሥዕል ነው። ሁለተኛውም ቅዱስ ሚካኤል ዲያብሎስን የተዋጋው የቀድሞው ሣጥናኤል ከራሱ ትዕቢትንና ክፋትን አመንጭቶ ራሱን ከቅድስና ለይቶ በእውነት እና በእምነት ወይም በእግዚአብሔር መንግሥት ላይ ጦርነት ሲከፈት እምነትን እና እውነትን (ቤተ ክርስቲያንን) ለመጠበቅ የእምነት ስይፉን አንሥቶ የተቃወመው አንዱ እርሱ መሆኑን ለማሳየት ነው። በመቅደሱ በር ላይ እንዲህ ሆኖ የሚሳለውም የእምነት እና የእውነት መገለጫ የሆነችውን ቤተ ክርስቲያንን የሚጠበቅ እና ዲያብሎስን ከሰማያዊ ክብሩ እንደጣለው አሁንም ያ ክብሩ ወደ ሚገለጽባት እውነተኛ አምልኮ ወደሚፈጸምባት ቤተ ክርስቲያን እንዳይገባ ከሚጠብቁት ዋነኞች ተቀዳሚው እርሱ ስለሆነ ነው።
🍂በአጭር ቃል የቅዱስ ሚካኤል ሰይፍ ዲያብሎስን የተዋጋው፣ የጣለው፣ ከሰማይ ያስለቀቀው እና አሁንም የሚያሳድደው እና ቤተ ክርስቲያንንም የሚጠብቅ ቅዱስ ሚካኤል መሆኑን ለመግለጽ ነው። በዓሉን በደስታ እና በታላቅ ሥርዓት የምናከብረውም አሁንም ቅዱስ ሚካኤል በዚያው አገልግሎት ላይ ስለሆነ እና እኛንም ክከፉው ከዲያብሎስ ወጥመድ እንደ ባሕራን እንደ አፎምያ እየጠበቀ፣ በቤተ ክርስቲያን በእውነተኛ አምልኮ ከእግዚአብሔር ጋር እንድንገናኝ የሚጠብቀን፣ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ኃጢአታችንን ይቅር ብሎ ይቀበለን ዘንድ የሚያማልደንም ስለሆነ ነው።
🍂በዚህ ቅር የሚላቸው እና የሚያዝኑ ካሉ ዲያብሎስ አሸንፏቸው አሁንም ሚካኤል ከእነርሱ ልቡና እንዳያባርረው እና እንዳያሳድደው በሚፈራው በዲያብሎስ የተታለሉ ሞኞች እና አላዋቂዎች ብቻ ናቸው። እነርሱን እኛ አንጠላቸውም፣ ለምን በዚህ ሀሳብ እንደወደቁ ወይም ማን እንዳታለላቸው እናውቃለንና። ይልቁንም በሕዝቅያስ ላይ ከእጄ ማን ያስልሃል እያለ ሲፎክር የነበረ የሰናክሬምን ጦር በአንድ ምሽት እንደመታ በተታለሉት ላይ አድሮ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚፈጽሙትን ቅዱሳን መላእክትንና በእነርሱ ጥበቃ እና አማልጅነት ወደ እግዚአብሔር ለመቅረብ የምንጣጣረውን ክርስቲያኖችን የሚሳደበውን ክፉ መንፈስ ከእነርሱ ላይ አባርሮ እና ወደ ልቡናቸው መልሶ አብረን ለማምለክ እንዲያበቃን እንለምነዋለን።
🍂ስለዚህ የቅዱስ ሚካኤል ሰይፍ ዲያብሎስን የምታርድ ቤተ ክርስቲያን ወይም እውነት እና እምነት የሚጠበቁባት እግዚአብሔር በመልአኩ ላይ ያስያዛት ረቂቅ ኃይል ናት እና ስናያት እንደሰታለን፣ እንጽናናለንም። እርሷን የሚጠሉ፣ የሚፈሩ እና የሚሸሹም ሠራዊተ ዲያብሎስ እና እርሱ ያታለላቸው ወይም ይህን የማያውቁ ሰዎች ብቻ ናቸው።
🍂ባለሰይፉ ቅዱስ ሚካኤል ዛሬም ዲያብሎስ በአንዳንድ ስሑት ልጆቿ ውሉደ ጥምቀት ላይ ሳይቀር አድሮ የሚገዳደራትን ቤተ ክርስቲያን እና መመስገኛውን ቤተ መቅደሱን በረቂቅ የመዋኢነት ሰይፉ ይጠብቅልን፣ እኛንም ዲያብሎሳዊት ከሆነች ትዕቢት፣ ክፋት እና ዐመጻ በቸርነቱ ይጠብቀን፣ አሜን። ለዐቢይ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል በዓል እንኳን አደረሳችሁ።
#ቴሌግራም_ፔጅ_አስተማሪ_ትምህርቶች_ለማግኘት
https://t.me/Moae_TewahedoB | 650 |
| 11 | 🕰🔔
3:00
ተንስኡ ለጸሎት
በዚህ ሰዓት ይህንን የምታይ ሰው የምታደርገውን ለ2 ደቂቃም ብትሆን ተውና ልዑል እግዚአብሔር እያሰብን ቢያንስ አንድ አባታችን ሆይ እንጸልይ
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አገር ውስጥ ያላቹሁ በስደትም በስራም እንኳን ቢሆን አንድ አባታችን ሆይ እንበል🥰
@MoaeTewahedoB | 825 |
| 12 | 🕰🔔
9:00
ተንስኡ ለጸሎት
በዚህ ሰዓት ይህንን የምታይ ሰው የምታደርገውን ለ2 ደቂቃም ብትሆን ተውና ልዑል እግዚአብሔር እያሰብን ቢያንስ አንድ አባታችን ሆይ እንጸልይ
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አገር ውስጥ ያላቹሁ በስደትም በስራም እንኳን ቢሆን አንድ አባታችን ሆይ እንበል🥰
@MoaeTewahedoB | 862 |
| 13 | 🕰🔔
6:00
ተንስኡ ለጸሎት
በዚህ ሰዓት ይህንን የምታይ ሰው የምታደርገውን ለ2 ደቂቃም ብትሆን ተውና ልዑል እግዚአብሔር እያሰብን ቢያንስ አንድ አባታችን ሆይ እንጸልይ
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አገር ውስጥ ያላቹሁ በስደትም በስራም እንኳን ቢሆን አንድ አባታችን ሆይ እንበል🥰
@MoaeTewahedoB | 814 |
| 14 | #14ቱ_የቅዱስ_ሚካኤል_ዐመታዊ_ክብረ_በዓላቶቹ ◈
1ኛ. #ኅዳር_12 የተሾመበት ዲያብሎስን ድል የነሳበት ሕዝበ እስራኤል የመራበት ዕለት ነው።
2ኛ0 #ኅዳር_13 በዓለመ መላእክት ያሉ አእላፍ መላእክት በዓለ ሲመቱን ተሰብስበው ያከበሩበት ቀን ነው። ዕለቱ ምነአእላፍ መላእክት ይባላል።
3ኛ. #ታኅሣሥ_12 ዱራታወስና ሚስቱ ቲወብስታን የረዳበት ዕለት ነው።
4ኛ. #ጥር_12 የደሃዋን ልጅ ተላፊኖስን የረዳበት ያዕቆብን ከወንድሙ ከኤሳው እጅ የጠበቀበት ዕለት ነው።
5ኛ. #የካቲት_12 የሚበላው የሚጠጣው የሚለብሰው ላጣ አንድ ሰው በሰው አምሳል ተገልጦ ከሀብታም ሲበደር ዋስ የሆነበት ሶምሶንን ረድቶ አሕዛብን ያጠፋበት ዕለት ነው።
6ኛ . #መጋቢት_12 ማቴዎስ የተባለውን ሰው እና ሚስቱን ልጆቹን የረዳበት የበለአምን አህያ ያናገረበት ዕለት ነው
7ኛ. #ሚያዝያ_12 አዳምን ወደ ገነት ያስገባበት ኤርምያስን ከእስር ቤት ያወጣበት ዕለት ነው።
8ኛ. #ግንቦት_12 ዳንኤል በአንበሳ ጉድጓድ ውስጥ ሳለ እንባቆምን ምግብ አስይዞ በአንዲት የእራስ ጠጉሩ አንጠልጥሎ ከኢየሩሳሌም ዳንኤል ወዳለበት ወደ ባቢሎን ወስዶ ዳንኤልን በጉድጓዱ ውስጥ የመገበበት ዕለት ነው።
9ኛ. #ሰኔ_12 ባሕራንን ከባሕር ያወጣበት አፎምያን ከሰይጣን ያዳነበት ዕለት ነው
10ኛ. #ሐምሌ_12 የደኀይቱን ልጅ ተለሀሶንን ከባሕር አውጥቶ የጠበቀበት ንጉሥ ሰናክሬምን ከነሠራዊቱ ደምስሶ ጻድቁ ሕዝቅያስን ያዳነበት ዕለት ነው።
11ኛ. #ነሐሴ_12 ሶስናን ከእደ ረበናት ያዳነበት ንጉሥ ቆስጠንጢኖስን ረድቶ መክስምያኖስን ድል ያደረገበት ዕለት ነው።
12ኛ. #ጳጉሜን_3 ቅዱስ ሩፋኤል ላሣረገው የዐመቱን ጸሎት ዕጣን ወደ እግዚአብሔር የሚያቀርብበት ዕለት ነው።
13ኛ. #መስከረም_12 ሰማዕቱ ፋሲለደስን የረዳበት ነቢዩ ኢሳይያስ ወደ ነቢዩ ሕዝቅያስ ሔዶ እንዲመክረው ያደረገበት ዕለት ነው።
14ኛ. #ጥቅምት_12 ነቢዩ ሳሙኤል ዳዊትን ቀብቶ እንዲያነግሰው የላከበትና ዳዊትን የረዳበት ዕለት ነው።
በዚኽ በዓላት ወደ ፈጣሪው 14 ልመናዎችን ያቀርባል።
ቅዱስ ያሬድን የቅዱስ ሚካኤል ልመናዎች 14 እንደሆኑ ገልጿል።
ወአሰርቱ ወአርባዕቱ ትንብልናከ በማለት ዘምሯል
14ቱ ልመናዎቹ በ 14ቱ በዓላቶቹ በጉልበቱ እየሰገደ ፈጣሪውን ለሰው ምሕረት ይቅርታ እንዲደረግላቸው የሚለምናቸው ልመናዎች ናቸው።
እንግዲኽ በየወሩ የሚከበሩ የቅዱስ ሚካኤል ወርኃዊ በዓላቶች የዐመቱ ናቸው ማለት ነው ።
የሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ረድኤቱ ፣ ጸሎትና ምልጃው አይለየን ፥ ይጠብቀንም ፤ ለዘለዐለሙ አሜን ።
ወስበሐት ለእግዚአብሔር ይቆየን
@MoaeTewahedoB | 624 |
| 15 | 🕰🔔
3:00
ተንስኡ ለጸሎት
በዚህ ሰዓት ይህንን የምታይ ሰው የምታደርገውን ለ2 ደቂቃም ብትሆን ተውና ልዑል እግዚአብሔር እያሰብን ቢያንስ አንድ አባታችን ሆይ እንጸልይ
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አገር ውስጥ ያላቹሁ በስደትም በስራም እንኳን ቢሆን አንድ አባታችን ሆይ እንበል🥰
@MoaeTewahedoB | 738 |
| 16 | 🥰 | 511 |
| 17 | 💖ቅዱስ ሚካኤል የአምላክ የክብሩ ሕያው ታቦት💖
በመጽሐፍ ቅዱስ ምስክርነት መሠረት፥ ቅዱሳን መላእክት የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለመፈጸም፣ ስሙን ለመቀደስና ለሰው ልጆች የምሕረትና የፍርድ መልእክትን ለማድረስ የተሾሙ ብርሃናዊያን ጠባቂዋች ናቸው። ከእነዚህም መካከል “የአምላክ ሕያወ ታቦት”፣ የአምላክ ስምና የባሕርዩ መገለጫዎች ተሸካሚ ተብሎ የሚወደሰው ታላቁ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ነው።
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል እነዚህን መለኮታዊ ሀብታት እንዴት ተሸክሞ እንደሚገለጥ በቅዱሳት መጻሕፍት እውነት እንቃኛለን፦
1. የአምላክ ስም እና የክብሩ ተሸካሚ ሕያው ታቦት
ቅዱስ ሚካኤል ስሙ ራሱ ምስክር ነው፤ “ሚካኤል” ማለት “እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው?” ማለት ነው። የአምላክን ስምና ክብር ተሸክሞ ስለሚጓዝ፣ እግዚአብሔር ለእስራኤል ልጆች መሪ አድርጎ ሲሰጣቸው እንዲህ ብሎ ነበር፦
“በመንገድ ይጠብቅህ ዘንድ... እነሆ እኔ መልአክን በፊትህ እሰዳለሁ። ... ስሜ በእርሱ ስለ ሆነ አትከራከረው፤ ኃጢአታችሁንም ይቅር አይልም።” (ዘጸአት 23፥20-21)
ይህ ጥቅስ ቅዱስ ሚካኤል የአምላክን ስምና ሥልጣን ተሸክሞ የሚጓዝ መለኮታዊ ወኪል መሆኑን ያረጋግጣል።
2. የአምላክ ፍቅር፣ ምሕረት እና የብስራት ተሸካሚ ሕያው ታቦት
ቅዱስ ሚካኤል የሰው ልጅ ወዳጅና ስለ ሰው ልጆች ምሕረትን የሚለምን የምሕረት መልአክ ነው። በመጽሐፈ ዳንኤል ላይ ስለ ሕዝቡ የሚቆም ታላቅ አለቃ ተብሏል፦
“ስለ ሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል፤” (ዳንኤል 12፥1)
ለቅዱሳን የሚደረገውን ምሕረትና ጸሎት ወደ እግዚአብሔር የሚያሳርግ፣ የአምላክን የፍቅርና የደኅንነት ብስራት ለዓለም የሚያበስር ታማኝ አገልጋይ ነው። (ራእይ 8፥3-4)
3. የአምላክ ፍርድ እና የቁጣ ተሸካሚ ሕያው ታቦት
እግዚአብሔር በኃጢአትና በትዕቢት ላይ የሚፈርደውን ፍርድና ቁጣ የሚፈጽመው በቅዱስ ሚካኤል አማካኝነት ነው። ሰይጣን በትዕቢት በደበረ ጊዜ፣ የአምላክን የፍርድ ቁጣ ተሸክሞ ከሰማይ የጣለው እሱ ነው።
“በሰማይም ሰልፍ ሆነ፤ ሚካኤልና መላእክቱ ዘንዶውን ተዋጉት።” (ራእይ 12፥7)
እግዚአብሔር በፈርዖንና በክፉዎች ላይ የፍርድ ቁጣውን ሲያወርድ፣ ቅዱስ ሚካኤል የዚያ መለኮታዊ ፍርድ አስፈጻሚ ነበረ።
4. የአምላክ ትሕትና ተሸካሚ ሕያው ታቦት
ቅዱስ ሚካኤል ታላቅና ኃያል መልአክ ቢሆንም፣ የፍጹም ትሕትና ምሳሌ ነው። ከዲያብሎስ ጋር በሙሴ ሥጋ እንኳ በተከራከረ ጊዜ ፍርድን ለአምላክ ሰጠ እንጂ በስድብ አልተናገረም።
“የመላእክት አለቃ ሚካኤል ግን ከዲያብሎስ ጋር በተከራከረ ጊዜ ስለ ሙሴ ሥጋ ሲነጋገር፦ ‘ጌታ ይገሥጽህ’ አለው እንጂ የሥድብን ፍርድ ሊናገረው አልደፈረም።” (ይሁዳ 1፥9)
ይህ የሚያሳየው የአምላክን የትሕትና ባሕርይ የተሸከመና ለፍጡራን ሁሉ የሚያሳይ መሆኑን ነው።
5. የመንግሥቱና የአገዛዙ ተሸካሚ ሕያው ታቦት
በመጨረሻው ዘመን፣ የእግዚአብሔር መንግሥትና አገዛዝ በምድር ላይ ሲገለጥ፣ ቅዱስ ሚካኤል የንጉሡን የክርስቶስን ዳግም ምጽአት አዋጅ ተሸክሞ በታላቅ ድምፅ ይመጣል።
“ጌታ ራሱ በትእዛዝ በመላእክትም አለቃ ድምፅ በእግዚአብሔርም መለከት ከሰማይ ይወርዳልና…” (1ኛ ተሰሎንቄ 4፥16)
ስለሆነም፣ ቅዱስ ሚካኤል እንደ “ሕያው ታቦት” ነው። ታቦት የእግዚአብሔር ቃል፣ ክብሩና ሕጉ ማደሪያ እንደሆነ ሁሉ፤ ቅዱስ ሚካኤልም የአምላክን ፍቅር፣ ምሕረት፣ ቁጣ፣ ፍርድና መንግሥት ተሸክሞ ለፍጥረት ሁሉ የሚያደርስ የብርሃን ታቦት ነው። ስሙ በእርሱ ላይ አለ፤ ክብሩም በእርሱ ላይ ያበራል።
የመልአኩ የቅዱስ ሚካኤል ተራዳኢነትና ጥበቃ አይለየን። አሜን።
@MoeTewahedoB | 468 |
| 18 | +++ እንኳን አደረሳችሁ! ሰኔ ፲፪/12 +++
[በዓለ ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት፥ ወአፎምያ ቅድስት፥ ወባሕራን ቀሲስ፥ ወቅዱስ ላልይበላ ንጉሥ ወጻድቅ]
√ የዕለቱ ግጻዌ (መልክታት፣ ምስባክ፣ ወንጌል)
✝ ምስባክ ዘነግህ
ይትዐየን መልአከ እግዚአብሔር ዐውዶሙ።
ለእለ ይፈርህዎ ወያድኅኖሙ።
ጠዐሙ ወታእምሩ ከመ ኄር እግዚአብሔር።
ትርጉም፦
የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል። ያድናቸውማል። እግዚአብሔር ቸር እንደሆነ ቅመሱ ዕወቁም።
(መዝ ፴፫÷፯ /33÷7)
✝ ወንጌል ዘነግህ
የማቴዎስ ወንጌል ፳፬ : ፴ - ፴፮ /24 : 30-36
+ መልእክታት
➊. ኤፌሶን ፩ : ፲፫ - ፍጻሜ /1:13-ፍጻሜ
፲፫
እናንተም ደግሞ የእውነትን ቃል፥ ይኸውም የመዳናችሁን ወንጌል፥ ሰምታችሁ ደግሞም በክርስቶስ አምናችሁ፥ በተስፋው መንፈስ በመንፈስ ቅዱስ ታተማችሁ፤
፲፬
እርሱም የርስታችን መያዣ ነው፥ ለእግዚአብሔር ያለውን ሁሉ እስኪዋጅ ድረስ፥ ይህም ለክብሩ ምስጋና ይሆናል።
፲፭
ስለዚህ እኔ ደግሞ በእናንተ ዘንድ ስለሚሆን በጌታ በኢየሱስ ስለ ማመንና ለቅዱሳን ሁሉ ስለሚሆን መውደድ ሰምቼ፥
፲፮
ስለ እናንተ እያመሰገንሁ ስጸልይ ስለ እናንተ ማሳሰብን አልተውም፤
፲፯
የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ።
፲፰-፲፱
ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንዲሆን በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምን ከሁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንዲሆን ታውቁ ዘንድ ነው፤
፳-፳፩
ክርስቶስንም ከሙታን ሲያስነሣው ከአለቅነትና ከሥልጣንም ከኃይልም ከጌትነትም ሁሉ በላይና በዚህ ዓለም ብቻ ሳይሆን ነገር ግን ሊመጣ ባለው ዓለም ደግሞ ከሚጠራው ስም ሁሉ በላይ በሰማያዊ ስፍራ በቀኙ ሲያስቀምጠው በክርስቶስ ባደረገው ሥራ የብርታቱ ጉልበት ይታያል፤
፳፪
ሁሉንም ከእግሩ በታች አስገዛለት ከሁሉ በላይም ራስ እንዲሆን ለቤተ ክርስቲያን ሰጠው።
፳፫
እርስዋም አካሉና ሁሉን በሁሉ የሚሞላ የእርሱ ሙላቱ ናት።
➋. ይሁዳ ፩ : ፱ - ፲፬ /1:9-14
፱
የመላእክት አለቃ ሚካኤል ግን ከዲያብሎስ ጋር በተከራከረ ጊዜ ስለ ሙሴ ሥጋ ሲነጋገር። ጌታ ይገሥጽህ አለው እንጂ የስድብን ፍርድ ሊናገረው አልደፈረም።
፲
እነዚህ ግን የማያውቁትን ሁሉ ይሳደባሉ፥ አእምሮም እንደሌላቸው እንስሶች በፍጥረታቸው በሚያውቁት ሁሉ በእርሱ ይጠፋሉ።
፲፩
ወዮላቸው፥ በቃየል መንገድ ሄደዋልና ስለ ደመወዝም ለበለዓም ስሕተት ራሳቸውን አሳልፈው ሰጥተዋል በቆሬም መቃወም ጠፍተዋል።
፲፪
እነዚህ ከእናንተ ጋር ሲጋበዙ በፍቅር ግብዣችሁ እንደ እድፍ ናቸው፤ እንደ እረኞች ያለ ፍርሃት ራሳቸውን ይጠብቃሉ፤ በነፋስ የተወሰዱ ውኃ የሌለባቸው ደመናዎች፥ ፍሬ የማያፈሩ ሁለት ጊዜ የሞቱ ከነሥራቸው የተነቀሉ በበጋ የደረቁ ዛፎች፥
፲፫
የገዛ ነውራቸውን አረፋ እየደፈቁ ጨካኝ የባሕር ማዕበል፥ ድቅድቅ ጨለማ ለዘላለም የተጠበቀላቸው የሚንከራተቱ ከዋክብት ናቸው።
.
➌. ግብረ ሐዋርያት ፩ : ፲ - ፲፪ /1:10-12
፲
እርሱም ሲሄድ ወደ ሰማይ ትኵር ብለው ሲመለከቱ ሳሉ፥ እነሆ፥ ነጫጭ ልብስ የለበሱ ሁለት ሰዎች በአጠገባቸው ቆሙ፤
፲፩
ደግሞም። የገሊላ ሰዎች ሆይ፥ ወደስማይ እየተመለከታችሁ ስለ ምን ቆማችኋል? ይህ ከእናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት፥ እንዲሁ ይመጣል አሉአቸው።
፲፪
በዚያን ጊዜ ደብረ ዘይት ከሚባለው ተራራ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሱ፥ እርሱም ከኢየሩሳሌም የሰንበት መንገድ ያህል የራቀ ነው።
✝ ምስባክ ዘቅዳሴ
ሶበ ትሬእዮሙ ለጠቢባን ይመውቱ።
ወከማሁ ይትኃጐሉ አብዳን እለ አልቦሙ ልብ።
ወየኀድጉ ለባዕድ ብዕሎሙ።
ትርጉም፦
ብልሐተኞች እንዲሞቱ፥ ሰነፎችችና ደንቆሮች በአንድነት እንዲጠፉ፥
ገንዘባቸውንም ለሌሎች እንዲተዉ አይቶአል።
{ መዝ ፵፱ : ፲ }
✝ ወንጌል ዘቅዳሴ
የማቴዎስ ወንጌል ፳፭ : ፲፬ - ፴፩ /25:14-31
፲፬
ወደ ሌላ አገር የሚሄድ ሰው ባሮቹን ጠርቶ ያለውን ገንዘብ እንደ ሰጣቸው እንዲሁ ይሆናልና፤
፲፭
ለእያንዳንዱ እንደ ዓቅሙ፥ ለአንዱ አምስት መክሊት ለአንዱ ሁለት ለአንዱም አንድ ሰጠና ወደ ሌላ አገር ወዲያው ሄደ።
፲፮
አምስት መክሊትም የተቀበለው ሄዶ ነገደበት ሌላም አምስት አተረፈ፤
፲፯
እንዲሁም ሁለት የተቀበለው ሌላ ሁለት አተረፈ።
፲፰
አንድ የተቀበለው ግን ሄዶ ምድርን ቈፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረ።
፲፱
ከብዙ ዘመንም በኋላ የእነዚያ ባሮች ጌታ መጣና ተቆጣጠራቸው።
፳
አምስት መክሊት የተቀበለውም ቀረበና ሌላ አምስት መክሊት አስረክቦ። ጌታ ሆይ፥ አምስት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ፥ ሌላ አምስት መክሊት አተረፍሁበት አለ።
፳፩
ጌታውም። መልካም፥ አንተ በጎ ታማኝም ባሪያ፤ በጥቂቱ ታምነሃል፥ በብዙ እሾምሃለሁ፤ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው።
፳፪
ሁለት መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ። ጌታ ሆይ፥ ሁለት መክሊት ሰጥተኸኝ ነበር፤ እነሆ፥ ሌላ ሁለት መክሊት አተረፍሁበት አለ።
፳፫
ጌታውም። መልካም፥ አንተ በጎ፥ ታማኝም ባሪያ፤ በጥቂቱ ታምነሃል፥ በብዙ እሾምሃለሁ፥ ወደ ጌታህ ደስታ ግባ አለው።
፳፬
አንድ መክሊትም የተቀበለው ደግሞ ቀርቦ። ጌታ ሆይ፥ ካልዘራህባት የምታጭድ ካልበተንህባትም የምትሰበስብ ጨካኝ ሰው መሆንህን አውቃለሁ፤
፳፭
ፈራሁም ሄጄም መክሊትህን በምድር ቀበርሁት፤ እነሆ፥ መክሊትህ አለህ አለ።
፳፮
ጌታውም መልሶ እንዲህ አለው። አንተ ክፉና ሃኬተኛ ባሪያ፥ ካልዘራሁባት እንዳጭድ ካልበተንሁባትም እንድሰበስብ ታውቃለህን?
፳፯
ስለዚህ ገንዘቤን ለለዋጮች አደራ ልትሰጠው በተገባህ ነበር፥ እኔም መጥቼ ያለኝን ከትርፉ ጋር እወስደው ነበር።
፳፰
ስለዚህ መክሊቱን ውሰዱበት አሥር መክሊትም ላለው ስጡት፤
፳፱
ላለው ሁሉ ይሰጠዋልና ይበዛለትማል፤ ከሌለው ግን ያው ያለው እንኳ ይወሰድበታል።
፴
የማይጠቅመውንም ባሪያ በውጭ ወዳለው ጨለማ አውጡት፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል።
፴፩
የሰው ልጅ በክብሩ በሚመጣበት ጊዜ ከእርሱም ጋር ቅዱሳን መላእክቱ ሁሉ፥ በዚያን ጊዜ በክብሩ ዙፋን ይቀመጣል፤
✝ ቅዳሴ ~ ያዕቆብ ዘሥሩግ (ተንሥኡ) - በዕዝል ዜ | 600 |
| 19 | 🕰🔔
3:00
ተንስኡ ለጸሎት
በዚህ ሰዓት ይህንን የምታይ ሰው የምታደርገውን ለ2 ደቂቃም ብትሆን ተውና ልዑል እግዚአብሔር እያሰብን ቢያንስ አንድ አባታችን ሆይ እንጸልይ
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
እግዚኦ ተሰኃለነ❖
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አቤቱ ማረን ይቅርም በለን✥
አገር ውስጥ ያላቹሁ በስደትም በስራም እንኳን ቢሆን አንድ አባታችን ሆይ እንበል🥰
@MoaeTewahedoB | 612 |
| 20 | ባለቤቷ አስተራኒቆስ ከዚህ ዓለም የሚያርፍበት ጊዜ እንደደረሰ ባወቀ ጊዜ ይሰጡት የነበረውን ምጽዋት እና የሦስቱን በዓላት መታሰቢያ ማድረግ እንዳታስታጉል ከአደራ ጋር አዘዛት፡፡ እርሷም የመልአኩን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል ያሥልላት ዘንድ ባለቤቷን ጠይቃ አሠርቶ ሰጣት፡፡ በከበረ ቦታም አኖረችው፡፡ ባሏ ካረፈ በኋላ ያዘዛትን መንፈሳዊ ሥራ ከወትሮው አስበልጣ መሥራት ቀጠለች፡፡ ባሏም ታሞ ሞቶ ከሀብቷ ከንብረቷ እየሰጠች እየመጸወተች በጾም በጸሎት ተወስና ትኖር ነበር፡፡ ሰይጣን ለምቀኝነት አያርፍምና ደግ መነኩሴ መስሎ አጋንንትን መነኮሳይያት አስመስሎ መጥቶ ከደጅ ሆኖ አስጠራት፡፡ እርሷም "ከቤት ገብታችሁ በቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ፊት ጸልዩልኝ" አለቻቸው፡፡
🥀 ሰይጣናቱም "እኛማ በነግህ ጸልየናል?" አሏት፡፡ ቀጥሎም ሰይጣን "...እንደው አንቺ ግን ይህ ሁሉ ጾም ጸሎት ምን ያደርገልሻል? ሀብትሽን ሰጥተሸ መጨረስሽስ ስለምንድን ነው? በዚያ ላይ አንቺ ስትደክሚ የሚደግፍሽ ስታረጂ
የሚጦርሽ ልጅ የለሽም ሁለተኛ ማግባት ኃጢአት መስሎሻልን? እነ አብርሃም እነ ዳዊ ከብዙ ሴቶች ብዙ ልጆች ወልደው የለምን? አሁንም ቤት ሰሪ ጎመን ዘሪ ልጅ ያስፈልግሻልና ባል አግቢ፣ እሺ በይኝ" አላት፡፡
ቅድስት አፎምያም "አባ ቆብህ መልካም ነበር ንግግርህ ግን ክፉ ነው፣ አትጹሚ አትጸልዩ ያልከኝ ጌታ ምጽዋት አበድር እመስዋዕት ብሎ የለምን? ሁለተኛ ባል አግቢ ማለትንስ ከምን አገኘኸው? እርግቦች እንኳ ባሎቻቸው ከሞቱባቸው ከሌላ ወንድ አይቀርቡም ታዲያ ጥንቱን በንጽሕና ሊኖር የተፈጠረ ሰው ሁለተኛ አላገባም ቢል ዕዳ ፍዳ ሊሆንበት ነውን?" ብላ ሞገተችው፡፡
🥀የሰው ልጆች ጠላት የሆነው ሰይጣንም በመልካም አገልግሎት ስትበረታ አይቷታልና ዝም ብሎ ሊተዋት አልወደደም፡፡ ከላይ እንዳየነው በመጀመሪያ ባል ሳታገባ ማገልገሏን ትታ ሌላ ባል አግብታ ልጅ ወልዳ እንድትኖር በብዙ ማባበል ጠየቃት፡፡ ባሏ መንግሥተ ሰማያትን ስለወረሰ ምንም ምጽዋት እንደማይሻ አስመስሎ ነገራት፡፡ ቅድስት አፎምያ ግን ዳግመኛ ትዳር ላለመመሥረት ቃል ኪዳን እንደገባች ርግብንና ዖፈ መንጢጥን አብነት አድርጋ እነርሱ እንኳ በሕይወት ዘመናቸው ከአንድ ባል ውጪ ሌላ ባል እንደማያውቁ በመጥቀስ አሳቡን እንደማትቀበለው ገለጸችለት፡፡ ሰይጣንም አስመሳይ መሆኑ አላዋጣ ሲለው ማንነቱን ቀይሮ ሊያንቃት ቢሞክር የእግዚአብሔርንና የቅዱስ ሚካኤልን ስም ጠርታ አባረረችው፡፡ እርሱም ተመልሶ መጥቶ እንደሚያጠፋት ዝቶባት እንደአቧራ በኖ እንደ ጢስም ተኖ ጠፋ፡፡ https://t.me/MoaeTewahedoB
🥀በሰኔ 12 ቀን የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያዘጋጀች ሳለች ሰይጣን ብርሃናዊ መልአክ መስሎ መጣ፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል እንደሆነ ገልጾ የመጀመሪያውን የመሰለ ከንቱ ምክሩን አሰማምሮ አቀረበላት፡፡ አሳቡንም የእግዚአብሔር ፈቃድና አሳብ እንደሆነ አድርጎ ለማሳመን ሞከረ፡፡ ሰይጣን አስቀድሞ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በገዳመ ቆሮንቶስ መጻሕፍትን እየጠቀሰ እንደተፈታተነው ሁሉ ቅድስት አፎምያንም ለማሳመንም አብርሃምን፣ ይስሐቅን፣ ያዕቆብን፣ ዳዊትን የመሳሰሉ ደጋግ አባቶችን ታሪክ እየጠቀሰ ወደ ትዳር እንድትገባ ደጋግሞ ወተወታት፡፡ ቅድስት አፎምያም በእግዚአብሔር ኃይል ጸንታ በቅዱስ ሚካኤልም ተራዳኢነት ታምና "የእግዚአብሔር መልአክ ከሆንክ መንፈሳዊ ማረጋገጫህ የሆነው የመስቀል ምልክት የታለ?" በማለት በምድራዊ ንጉሥና በጭፍራው መካከል የሚኖርን የጋራ መግባቢያ መንገድ ዋቢ አድርጋ ጠየቀችው፡፡ ለጊዜው "በእኛ በመላእክት ዘንድ እንዲህ አይደለም" ብሎ ሊሸነግላትና አቋሟን ሊያስቀይራት ሞከረ፡፡ ከቤቷ ያለ የቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ላይ ያለውን ምልክት አብራርታ የእርሱ ግን ከዛ ጋር አንድነት እንደሌለው አረጋገጠችበት፡፡ በመቀጠልም ከቤቷ ላለው ለቅዱስ ሚካኤል ሥዕል እጅ እንዲነሣ ጠየቀችው፡፡
🥀በዚህ ጊዜ መልኩ ወደ ትክክለኛ ሰይጣናዊ ማንነቱ ተለወጠና ጨለማ ለብሶ እየዛተ አነቃት፡፡ ቅድስት አፎምያም የከበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤልን "ድረስልኝ" እያለች በጠራችው ጊዜ መልአኩም ፈጥኖ በመድረስ ከሰይጣን እጅ አዳናት፡፡
የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ለሰይጣኑ ተገቢውን ቅጣት ሰጥቶ ቅድስት አፎምያን ባረካት፡፡ የዕረፍት ቀኗ በዚህ ቀን መሆኑን ነግሮ ቤቷን እንድታዘጋጅ አዘዛት፡፡ የበዓሉን ዝግጅት አከናውና ሥጋ ወደሙን ተቀብላ ኤጲስ ቆጶሱንና ካህናቱን እንደየመዓርጋቸው ጠርታ በቤቷ አክብራ ተቀበለቻቸው፡፡ ለነዳያንና ለጾም አዳሪዎች በኤጲስ ቆጶሱና በካህናቱ እጅ ገንዘቧን መጽውታ መንገዷን አሳመረች፡፡ ስለ ኃጢአቷ እንዲጸልዩላት ተማፅና በፊታቸው ተንበርክካ ጸለየች፡፡ ባሏ ያሠራላትን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል አቅፋ ስማ ከተማጸነች በኋላ ሰኔ 12 ቀን በሰላም ዐረፈች፡፡ ረድኤት በረከቷ ይደርብን፣ በጸሎቷ ይማረን!
ቴሌግራም ቻናል ተቀላቀሉ
https://t.me/MoaeTewahedoB
https://t.me/MoaeTewahedoB
https://t.me/MoaeTewahedoB | 698 |
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
