es
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

Ir al canal en Telegram

📈 Análisis del canal de Telegram Assaye Derbie

El canal Assaye Derbie (@asayede) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 14 336 suscriptores, ocupando la posición 2 651 en la categoría Bloques y el puesto 2 347 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 14 336 suscriptores.

Según los últimos datos del 26 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -104, y en las últimas 24 horas de -8, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 35.99%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 12.61% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 5 158 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 808 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 30.

📝 Descripción y política de contenido

No se ha proporcionado la descripción del canal.

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 27 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Bloques.

14 336
Suscriptores
-824 horas
-327 días
-10430 días
Archivo de publicaciones
"ቀባሪ አታሳጣኝ" እያለች ስትለምን፥ ስትጸልይ ኑራ፥ ባልገባት ምክንያት ፥ ጧሪዎቿን ቀብራ አየኻት ኢትዮጵያን ፥ አየኻት እማማን መውደቂያ ታዛ አጥታ ፥ በእንባዋ ስትረግመን?! ለዚህች እናት ማረፊያ
"ቀባሪ አታሳጣኝ" እያለች ስትለምን፥ ስትጸልይ ኑራ፥ ባልገባት ምክንያት ፥ ጧሪዎቿን ቀብራ አየኻት ኢትዮጵያን ፥ አየኻት እማማን መውደቂያ ታዛ አጥታ ፥ በእንባዋ ስትረግመን?! ለዚህች እናት ማረፊያ የሚሆን አንድ ክፍል ቤት የላችሁም?? በእጃቸው የያዙት ወረቀት ላይ የተፃፈው የብሶት ማመልከቻ በግዕዝ ፊደላት ፈንታ በላቲን የተፃፈ ቢሆን ኖሮ ከአዲስ አበባ ያባረራቸው አካል ኮንዶሚንየም ይሰጣቸው ነበር።

አገር አልባው ባላገር ▬▬▬▬ ከጭፍጨፋ ተርፈው፣ ንብረታቸውን ተዘርፈውና ጎጇቸው ሲቃጠል አይተው ከወለጋ ምድር ከተፈናቀሉ በኋላ ለረዥም ጊዜያት ቢንከራተቱም ኢትዮጵያ የምትባለውን አገር ቀርቶ ኬንዳ
አገር አልባው ባላገር ▬▬▬▬ ከጭፍጨፋ ተርፈው፣ ንብረታቸውን ተዘርፈውና ጎጇቸው ሲቃጠል አይተው ከወለጋ ምድር ከተፈናቀሉ በኋላ ለረዥም ጊዜያት ቢንከራተቱም ኢትዮጵያ የምትባለውን አገር ቀርቶ ኬንዳ ዘርግተው የሚሰፍሩበት ምድር ማግኘት አልቻሉም፡፡ ወለጋ ድረስ ይመጣል ብለው ሲጠብቁት የነበረውን መንግሥት አዲስ አበባ ድረስ መጥተው ቢፈልጉትም ‹‹ከተማዬን ታቆሽሻላችሁ›› ብሎ አባረራቸው እንጂ መጠጊያ ታዛ አልሰጣቸውም፡፡ ብአዴንና አብንም በእኒህ አማራዎች ላይ የሚፈጸመውን ታይቶ የማይታወቅ የግፍ ግፍ ተመልክተው የመፍትሔ አካል ለመሆን አልደፈሩም፡፡ በሄዱበት እየተከተሉ ‹‹አይዟችሁ›› ከሚሏቸው የባልደራስ አመራሮች ውጭ ‹‹ኑ ወደ እኛ›› ብሎ የሚጠራቸው ወገን አላገኙም፡፡ በአረብ አገር የሚሰቃዩ ወገኖቻቸውን ያህል የሚሰቃዩበት የማጎሪያ ካምፕ የሚያመቻችላቸው መንግሥት ማግኘት አልቻሉም፡፡ አስከሬን እንኳን የሚቀበርበት ሁለት ክንድ መሬት አያጣም፡፡ ቆሻሻ እንኳን የሚጣልበት ኮሲ አይቸግረውም፡፡ በሕይወት ያሉት እኒህ አማራዎች ግን የሚያርፉበት የብስ ማግኘት አልቻሉም፡፡ ምን ብናደርግ ይሻል ይሆን? መፍትሔ አምጡ እስቲ...! Share

አራት ወረዳ ተቆጣጠረ የሚባለው የኦነግ ታጣቂ ከአራት ኪሎው መንግሥት ቁጥጥር ውጭ ከመሰለህ ተሳስተኻል። ይህ ሁሉ ቲያትር በእነ ገተት የሚቀናበር ነው‼️😆 ሕዝባዊ ተቀባይነት እያጡ የመጡት ንጉሥም
አራት ወረዳ ተቆጣጠረ የሚባለው የኦነግ ታጣቂ ከአራት ኪሎው መንግሥት ቁጥጥር ውጭ ከመሰለህ ተሳስተኻል። ይህ ሁሉ ቲያትር በእነ ገተት የሚቀናበር ነው‼️😆 ሕዝባዊ ተቀባይነት እያጡ የመጡት ንጉሥም በ"ትህ-ኦነግ" ድጋፍ ዙፋናቸውን ለማስቀጠል ሳያስቡ አልቀሩም።

ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ "ለፓርላማው ያቀረብኳቸው ጥያቄዎች ተቆርጠው ቀሩብኝ" የሚል ይዘት ያለው ጽሑፍ ለጥፎ አየሁ። እኔ ደግሞ ዶክተር ደሳለኝን "መላሽ በሌለበት መድረክ ላይ ጥያቄህን አታባክን" ብዬ
ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ "ለፓርላማው ያቀረብኳቸው ጥያቄዎች ተቆርጠው ቀሩብኝ" የሚል ይዘት ያለው ጽሑፍ ለጥፎ አየሁ። እኔ ደግሞ ዶክተር ደሳለኝን "መላሽ በሌለበት መድረክ ላይ ጥያቄህን አታባክን" ብዬ መምከር እፈልጋለሁ። በበኩሌ ከምክር ቤት ይልቅ እስር ቤት መግባት የምመርጥ ቢሆን እግዜር እረግሞኝ ፓርላማ ብገባ ግን ለጠሚው የማቀርባቸው ጥያቄዎች እንዲህ የሚሉ መሆናቸው አይቀርም። 1. የምግብ ምርጫዎ ምንድን ነው? 2. የቤተ መንግሥቱ አዝመራ ከምን ደረሰ? 3. ቀበሮዎቹ ደህና ናቸው ወይ? 4.ያች ፈረንሳዊት ትደውላለች ወይ? 5. በሙቀት ስንቃጠል እያዩ ደመና መጭመቁን የተውት ምን ሆነው ነው? . . ከዚህ ውጭ ከእሳቸው መልስ እና መፍትሔ ይገኛል ብዬ አገራዊ ጥያቄ ለማቅረብ አልደፍርም።

ሳምንታዊ ቸክሊስት (አሳዬ ደርቤ) ▬▬▬▬ ➔ፋኖን የማሰልጠን ተግባር እንዲስፋፋ መቀስቀስ እና የሥልጠና መርሐ ግብሮችን መደገፍ፤ ➔በኦነግ ከወለጋ ተፈናቅለው፤ በኦሮሚያ ብልጽግና ደግሞ ከአዲስ አበባ ለተሳደዱ አማራዎች ጥብቅና መቆም፤ ➔በድርድር ሒደቱ ላይ ከአብን ይልቅ የአቻምየለህን ሐሳብ በመውሰድ የአማራ ሕዝብ ውክልና እንዲኖረው ጥረት ማድረግ፤ ➔በወልቃይትና በራያ በኩል ዳግም ጥቃት ለመክፈት ያሰፈሰፈውን ወረራ ሊመክት የሚችል ሃይል እንዲዘጋጅ መቀስቀስ፤ ➔አሸባሪው ሃይል በአፋር ሕዝብ ላይ እያደረሰ ያለውን በደል ለአለም አቀፉ ማሕበረሰብ ማሳወቅና ለተፈናቃዮች ድጋፍ ማድረግ፤ ጨምሩበት Share

የነበራቸውን ጸጋ ተገፍፈው፣ በመረጡት አካል ተክደው፣ በከባድ የሕልውና አደጋ ውስጥ የሚኖሩ ወገኖች "ጸጋ ተልከሰከሰች" የሚል ጽሑፍ የያዘ ቲሸርት አሳትመው ሙድ ሲይዙ ጤነኝነታቸው ያጠራጥረኛል። . በሱስ ብዛትና በተስፋ ማጣት ግንባራቸው አሸብሽቦ ፣ ቆዳቸው እንደ ሽቦ አልጋ እረግቦ ያለ እድሜያቸው ያረጁ ወጣቶች "ጂጂ ጠቆረች" እያሉ በኀዘን ሲቆራመዱ ፊታቸውን የሚመለከቱበት መስታወት ገዝቶ መስጠት ያምረኛል።

ጎንደሬ፣ ጎጃሜ፣ ሸዋ ወሎዬ የሚባል Cultural Identity እንጂ ፣ ጎንደሬ ወይም ጎጃሜ፣ ሸዋ ወይም ወሎዬ የሚባል Political Identity የለም። የነገ እጣ ፈንታህ አንድ ነው። ሸኔም
ጎንደሬ፣ ጎጃሜ፣ ሸዋ ወሎዬ የሚባል Cultural Identity እንጂ ፣ ጎንደሬ ወይም ጎጃሜ፣ ሸዋ ወይም ወሎዬ የሚባል Political Identity የለም። የነገ እጣ ፈንታህ አንድ ነው። ሸኔም በለው ወ*ያኔ አሜሪካም በለው ብልጽግና "አማራ" ብሎ ነው የሚውያቅህ! ትንግርቱ ገ/ጻድቅ (ረ/ፕሮፌሰር)

ለመጽሐፋችን የሕትመት ድጋፍ በጠየቅነው መሠረት የመጽሐፉን አስፈላጊነቱን የተረዱ ሁለት ደግ ሰዎች 20+30=50% ወጪውን ሲሸፍኑ ሌሎች ደግሞ 20 % ድጋፍ አድርገው 70% ደርሰናል። እናምከመጽሐፉ የሚገኘው ገቢ ለተሰው የፋኖ ቤተሰቦች የሚውል መሆኑን በመረዳት በዚህ ታሪካዊ መጽሐፍ ሕትመት ላይ አሻራችሁን ማሳረፍ የምትሹ ወገኖች በኢንቦክስ መጥታችሁ "አለን" ትሉኝ ዘንድ እጋብዛለሁ።

ለእነዚህ አርሶ አደሮች ጥርና የካቲት ማለት አዝመራቸውን ሰብስበው፣ አዲስ ቦላሌና ቀሚስ አሰፍተው ልጆቻቸውን የሚድሩበት ነበረ። አሁን ግን ለረዥም ዘመን ጥረው የገነቡት ሰቀላ ቤት፣ ያፈሩት ጥሪት፣
+2
ለእነዚህ አርሶ አደሮች ጥርና የካቲት ማለት አዝመራቸውን ሰብስበው፣ አዲስ ቦላሌና ቀሚስ አሰፍተው ልጆቻቸውን የሚድሩበት ነበረ። አሁን ግን ለረዥም ዘመን ጥረው የገነቡት ሰቀላ ቤት፣ ያፈሩት ጥሪት፣ ወደ ጎተራ ያስገቡት ምርት በዘረኞች ጥቃት ተቃጥሎ ልጆቻቸውን ጎጆ በሚያወጡበት ወቅት ወደ ጎዳና ወጥተዋል። ለሚጋቡ ልጆቻቸው ዳስ ጥለው በሚደሰቱበት የጫጉላ ወራት፣ ማንነትን መሠረት ባደረገ ጥቃት ለሚገደሉ ልጆቻቸው የእዝን ድንኳን ተክለው ማንባት ቢሰለቻቸው.... ሕግ በሌለበት ምድር ላይ "በሕግ አምላክ" እያሉ መሞት፣ ከአገር አልባ ሰማይ ስር "የአገር ያለህ" እያሉ ኡኡ ማለት ቢቸካቸው....ይሄው ከጎዳና ላይ ወድቀው የአምላክን ፍርድ በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ።

ሰፊው ሕዝብ በታክሲ መሄድ ከብዶት ኤርገንዶውን ገርግዶ በእግሩ መጓዝ ጀምሯል። ጠባቡ አመራር ደግሞ በV-8 መኪና መንቀሳቀስ አሰልች ሆኖበት በኪራይ አውሮፕላን መንፈላሰስ ይዟል። በአጭር ጊዜ ውስጥ
ሰፊው ሕዝብ በታክሲ መሄድ ከብዶት ኤርገንዶውን ገርግዶ በእግሩ መጓዝ ጀምሯል። ጠባቡ አመራር ደግሞ በV-8 መኪና መንቀሳቀስ አሰልች ሆኖበት በኪራይ አውሮፕላን መንፈላሰስ ይዟል። በአጭር ጊዜ ውስጥ የሕዝቡን ኑሮ አራቁቶ በቅንጦት የሚሰቃዩ አመራሮችን የቀፈቀፈ ፓርቲ ይሄን ዐየሁ!!😆

የተወሰኑ ኮፒዎችን የሕትመት ወጪ በመሸፈን በዚህ ታሪካዊ መጽሐፍ የምስጋና ገጽ ላይ ሥምዎን ተጠቃሽ ያድርጉ!! https://www.facebook.com/100999818947578/posts/16452888
የተወሰኑ ኮፒዎችን የሕትመት ወጪ በመሸፈን በዚህ ታሪካዊ መጽሐፍ የምስጋና ገጽ ላይ ሥምዎን ተጠቃሽ ያድርጉ!! https://www.facebook.com/100999818947578/posts/164528885928004/

የተወሰኑ ኮፒዎችን በማሳተም ሥምዎን በዚህ ታሪካዊ መጽሐፍ የምስጋና ገጽ ላይ ተጠቃሽ ያድርጉ!

ከስድስት ወር በፊት የአማራ ሳይንት ፈርጥ ስለሆነው ስለ ኮሎኔል ጌታቸው ተፈራ ጀግንነት ስተርክ "ሙገሳህ የትውልድ መንደርን መሠረት ያደረገ ነው" ብለው የተከራከሩኝ ነበሩ። ከሰሞኑን ግን ያ አድናቆ
+1
ከስድስት ወር በፊት የአማራ ሳይንት ፈርጥ ስለሆነው ስለ ኮሎኔል ጌታቸው ተፈራ ጀግንነት ስተርክ "ሙገሳህ የትውልድ መንደርን መሠረት ያደረገ ነው" ብለው የተከራከሩኝ ነበሩ። ከሰሞኑን ግን ያ አድናቆቴ እውነት መሆኑን በሚገልጽ መልኩ፣ የበላይ ዘለቀን ብርጌድ የሚመራው ይህ ኮሎኔል "በሁሉም አውደ ውጊያዎች ላይ ያሳየኸው ጀግንነት እና ብቃት ገራሚ ነበር" ተብሎ ከአማራ ልዩ ሃይል በአንደኝነት ተመርጧል። እንኳን ደስ አለህ አንተ የአማራ ኩራት!‼️

በአፋርም ሆነ በአማራ፣በሶማሌም ሆነ በትግራይ እየሆነ ያለው ነገር ሁሉ በጠቅላይ ሚኒስትሩ እና በክልላዊ ፓርቲያቸው እቅድ የሚመራ ነው። ግቡ ደግሞ ልክ እንደ ሸገር የተሰለቀጠች አገር እውን ማድረግ ነው።

ሕግ ቢኖር ኑሮ ፥ ዳኛ ቢኖር ኑሮ፤ አሳሪው ነበረ ከታሜ ክፍል ውስጥ ፥ የሚገኝ ታጉሮ። ፍቱት...‼️ ንጹሕ አትወንጅሉ ፥ በእራሳችሁ ጥፋት።
ሕግ ቢኖር ኑሮ ፥ ዳኛ ቢኖር ኑሮ፤ አሳሪው ነበረ ከታሜ ክፍል ውስጥ ፥ የሚገኝ ታጉሮ። ፍቱት...‼️ ንጹሕ አትወንጅሉ ፥ በእራሳችሁ ጥፋት።

የአማራ ብልጽግና አመራሮች በብድር ሥም የዘረፉት 60 ሚሊዮን ብር በአስቸኳይ ወደ ካዝናው መመለስ ይኖርበታል! የክልሉን አለመረጋጋት እንደ መልካም አጋጣሚ ተጠቅመው ዝርፊያ የፈጸሙ አመራሮችም በሕግ ሊጠየቁ ይገባል።

አንዳንድ መንግሥታት የሕዝብን የዳቦ ጥያቄ መመለስ ባለመቻላቸው ሲገረሰሱ አይተናል። ድግስ ወዳዱ ብልጽግና፣ ከሕዝብ ርሐብ ባለፈ የአመራሩን ጥጋብ ማስታገስ ተስኖት በውስኪ ስካር እየተንገዳገደ ነው።😆

የእለት ጉርሱን ተነጥቆ ፆም ያድር ዘንድ የተፈረደበትን ሕዝብ "ከርሳም" እና "ፈርሳም" ብሎ የሚዘልፍ ጥጋበኛ አመራር ለአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ቀርቶ ለአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት አይመጥንም።