es
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

Ir al canal en Telegram

📈 Análisis del canal de Telegram Assaye Derbie

El canal Assaye Derbie (@asayede) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 14 336 suscriptores, ocupando la posición 2 651 en la categoría Bloques y el puesto 2 347 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 14 336 suscriptores.

Según los últimos datos del 26 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -104, y en las últimas 24 horas de -8, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 35.99%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 12.61% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 5 158 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 808 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 30.

📝 Descripción y política de contenido

No se ha proporcionado la descripción del canal.

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 27 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Bloques.

14 336
Suscriptores
-824 horas
-327 días
-10430 días
Archivo de publicaciones
photo content
+3

‹‹እልልታ የዋጠው እሪታ›› አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ባለፉት አራት ዓመታት ብዙ ዓይነት ትዕይንቶችን አስተናግደናል፡፡ በአዘቦት ቀርቶ በሰንበት እና በአውዳመት ሥራ በማይፈቱ አረመኔ ቡድኖች በርካታ ንጹሐን ተሰውተውብናል፡፡ ‹‹ይሄን ያህል ንጹሐን አለቁ›› የሚል ዜና በወጣ ቅጽበትም መርዶውን የሚያድበሰብሱ ሰበር መረጃዎች እየተለቀቁ… እሪታውን እልልታ ሲውጠው ታዝበናል፡፡ በጥንት ትርክት ጥቃት ይፈጸምበት ዘንድ የተፈረደበት አካልም ‹‹ሾርት ሚሞሪ›› እስኪባል ድረስ ዛሬ የሚደረግበትን እየጣለ በተቀደደለት ቦይ ሲፈስስ፣ አጥፊዎቹ ደግሞ ተከሳሽ በሚሆኑባቸው ጉዳዮች ላይ ወቃሽ እና አልቃሽ ሆነው ሲከሰቱ አይተናል፡፡ የሰሜን እዝ ተወግቶ ወደ ሕግ ማስከበር ዘመቻ በገባንበት ጊዜ ደግሞ የአማራና የአፋር ልዩ ሃይሎች እንዲሁም ሚሊሻዎች ከመከላከያ ሠራዊቱ ጎን ተሰልፈው ከባድ ዋጋ ቢከፍሉም በሕይወት የተረፉት ያለ ሜዳሊያ፣ የተሰውት ያለ መታሰቢያ ሲቀሩ አስተውለናል፡፡ በአፋርና በአማራ ክልሎች ላይ ወረራ ከተፈጸመበት ጊዜ አንስቶ ደግሞ በትሪሊየን የሚቆጠር ቁሳዊ ውድመትና በዋጋ የማይተመን ሰብዓዊ ጉዳት አስተናግደናል፡፡ ይሄንንም ወረራ ለመቀልበስ ከመከላከያ ሠራዊቱ ጎን የተሰለፉ የሁለቱ ክልል ልዩ ሃይሎች፣ ሚሊሻዎች፣ ፋኖዎች እና አናብስቶች ሕይወታቸውንና አካላቸውን ሰውተዋል፡፡ አሁንም ጭምር…፡፡ እኔ ደግሞ አንድ ፎልደር ከፍቼ፣ የሥልጣን ሽግግር ከተካሄደበት ጊዜ አንስቶ… ተከስተው የረሳናቸውን፣ ተሰውተው ያላስታወስናቸውን፣ ተወግተን የተከሰስንባቸውን፣ ታምነን የተካድንባቸውን… አበይት ክስተቶች ስክሪን ሾት እያደረግኩ በስንኝ እና በስድ ጽሑፍ ሳጠናቅራቸው ነበር፡፡ እስከ ጣርማ በር ደርሶ በነበረው ወራሪ ሃይልም ሲፈጸሙ የነበሩ ውድመቶችና ሲከፈሉ የነበሩ መስዋዕትነቶች፣ የዩቲዩብ ሰበር ዜና ሆነው እንዳይቀሩ በየ እለቱ እየመዘገብኩ ተመሳሳዩን ሳደርግ ነበር፡፡ ከሶሻል ሚዲያ ካሰባሰብኩት መረጃ ላይም ወረራ በተፈጸመባቸው ቦታዎች ተንቀሳቅሼ ከሰዎች አንደበት የሰማኋቸውን እና በዐይኔ ያየኋቸውን ስጨምርበት ልክ እንደ ጀመርነው ጦርነት በምዕራፍ የሚቀጥሉ እንጂ በአንድ መጽሐፍ የሚጠቃለሉ አልሆኑም፡፡ እናም ተያያዥነት ያላቸውን ምዕራፎች መራርጬ አንድ ፋይል ላይ ስደረድራቸው ‹‹እልልታ የዋጠው እሪታ›› የሚል ርዕስ ያለው አራተኛ መጽሐፌ ለመሆን በቁ፡፡ ይሄንንም መጽሐፍ ልክ እንደ ሌሎች መጽሐፎቼ ላሳትም በፍላሽ ይዤ ወደ ማተሚያ ቤት ሳመራ የወረቀትና የቀለም ዋጋ በጣም በመወደዱ የተነሳ ያለን አቅም መጽሐፍ ለማሳተም የሚበቃ ሆኖ አልተገኘም፡፡ እናም ‹‹የመጽሐፉን አስፈላጊነት በተረዱ ወገኖች እገዛና ድጋፍ ታትሞ ከሽያጩ የሚገኘው ገቢ ደግሞ በጦርነቱ ለተሰው የፋኖ ቤተሰቦች እንዲውል›› ወስኜ ወደ እናንተ አመጣሁት፡፡ ስለዚህ ‹‹በእኛ የጋራ ድጋፍ ላለፉት ዓመታት የተፈጸመው ጥቃትና ውድመት እንዲሁም የተከፈለው መስዋዕትነት በመጽሐፍ መልክ ታትሞ አሁን ባለውም ሆነ በሚመጣው ትውልድ መታወስ ይገባዋል›› ብላችሁ የምታምኑ ወገኖች ከስር በተመጠው አካውንት የአቅማችሁን ብታበረክቱ ፣ መጽሐፉ ታትሞ ሲወጣ…ከምስጋና ገጽ ላይ፣ ከዚህ በፊት የተለያዩ እገዛዎችን ካደረጉ ወገኖች ጋር ሥማችሁን አስፍሬ ኮፒውን በአድራሻችሁ የምልክ ይሆናል፡፡ Commercial bank 1000187948871 Assaye derbie

በሚሊዮን የሚቆጠር ብድር ወስደው፣ ትርፋማ የሆኑ የብአዴን አመራሮች፣ የምርጫ ጊዜ "ደፋሩ የልማትና የጸረ ሙስና አርበኛ" ብለው ያወደሱትን ሰው፣ ዛሬ ምን ብለው ቢሰድቡት ጥሩ ነው? "የከሰረ ብአዴን
በሚሊዮን የሚቆጠር ብድር ወስደው፣ ትርፋማ የሆኑ የብአዴን አመራሮች፣ የምርጫ ጊዜ "ደፋሩ የልማትና የጸረ ሙስና አርበኛ" ብለው ያወደሱትን ሰው፣ ዛሬ ምን ብለው ቢሰድቡት ጥሩ ነው? "የከሰረ ብአዴን‼️" 😂

በአማራ ሕዝብ ላይ የሚሰነዘር የትኛውም ጥቃት የማያስቆጣቸው፣ የበላይ አካል ስድብ እንደ ዘቢብ የሚጣፍጣቸው፣ ሆድ እንጂ ልብ የሌላቸው... የብአዴን እንኩቶዎች "ንጉሰ ነገሥቱ ተነካ" ብለው አቶ ጸጋ
በአማራ ሕዝብ ላይ የሚሰነዘር የትኛውም ጥቃት የማያስቆጣቸው፣ የበላይ አካል ስድብ እንደ ዘቢብ የሚጣፍጣቸው፣ ሆድ እንጂ ልብ የሌላቸው... የብአዴን እንኩቶዎች "ንጉሰ ነገሥቱ ተነካ" ብለው አቶ ጸጋ ላይ አካኪ ዘራፍ እያሉ ነው። የሚገርመው ነገር ታዲያ "በሚሊን የሚቆጠር ብር ዘርፋችሁ ተከፋፍላችኋል" ተብሎ የቀረበባቸውን ክስ "የተከፋፈልነው ዘርፈነው ሳይሆን ተበድረነው ነው" 😂 ብለው በከፊል ከመካዳቸው ውጭ የሰውየውን ክሶች ማስተባበል አልቻሉም! 😁

photo content
+4

የብልጽግና ኢትዮጵያ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ መሪዋን የምትመስለው የብልጽግና ኢትዮጵያ የሚሞቱላትን እየቀበረች፣ የሚወጓትን ከፍ ከፍ የምታደርግ ናት፡፡ በግብረ ገብነት ፈንታ አረመኔነት የሚያስገብራት፣ ከአርበኛ ይልቅ ቁማርተኛ ቀልቧን የሚገዛት፣ እራሷን እንደ አገር ተቀብላ ክልሎቿን ሳታዋድድ፣ አሕጉር ሆና አገራትን ማዋኻድ የሚያሰኛት ቀጣፊ አገር ናት፡፡ ‹‹አትፈርሺም›› የሚላትን የምትንቅ፣ ‹‹እናትሺን›› የሚሏትን የምታሞላቅቅ፣ ለሰላቢዋ መድሃኒት እየቀመመች፣ ለወጌሻዋ መርዝ የምትጠምቅ ከሃዲ አገር ናት፡፡ (ካላመንክ ትናንት ‹‹ድረስልኝ›› ብላ የጠራችውን የአፋር ሕዝብ ዛሬ ‹‹ወግድልኝ›› ብላ ከማን እጅ እንደጣለችው ተመልከት፡፡) . ይህቺ ከንቱ አገር የቤቷን ሰላም ሳታሰፍን የአገራትን ችግር ካልፈታሁ ብላ ስታለቀልቅ በጎረቤቶቿ ዘንድ የተናቀች አገር እንደሆነች ሁሉ፣ አማራውን ለእራሱ ሳይሆን እና እራሱን ሳያድን እርሷን ለማትረፍ በየስፍራው የሚጨፈጨፍ ሕዝብ በመሆኑ በጣም ትንቀዋለች፡፡ ምክንያቱም… ➔እርሷ የምትወደው የውጫዊ ሃይል ተላላኪ ሆኖ በሉዓላዊነቷና በሕልውናዋ ላይ የሚደራደርን ነው፡፡ ➔እርሷ የምታከብረው ‹‹ዓባይ ግድብ የኔ ነው›› እያለ ቦንድ ሲገዛ ሰንብቶ ከመተከል ምድር እየተጨፈጨፈ የሚፈናቀለውን ሳይሆን ‹‹ግድቡን ለማስቆም- ጠባቂውን ማውደም›› የሚል ውል ከእነ ግብጽ ጋር ተዋውሎ የሚጨፈጭፈውን ነው፡፡ ➔እርሷ የምትንከባከበው ከወንድሞቹ ጋር ተባብሮ ድንበሯን የሚጠብቀውን ሳይሆን ከሱዳኖች ጎን ወግኖ ጎኗን የሚያደቅቀውን ነው፡፡ ➔ጡቷን የምታጠባው ማንነቱን ጥሎ ዜግነቱን አንጠልጥሎ ለሚንቀዋለል ሕዝብ ሳይሆን በዘሩ ተደራጅቶ ከጠላቷ ጋር እየመከረ ሕልውናዋን አደጋ ላይ ለሚጥል ኢ-መደበኛ ሃይል ነው፡፡ ፍትሕ የምትቸረውም ወንጀለኛ፣ ጉልበተኛና አመጸኛ ሆነው ለሚገኙ ብቻ ነው፡፡ እናም… ባንዳ ልጇ ከሱዳን ጋር ተጠቃቅሶ በለኮሰው ጦርነት ባንድ አቅጣጫ እንዳስወረራት ስትረዳ ኮሪደሩን ብቻ ሳይሆን ጎንደርንም ጭምር ለመናጢ ልጇ ገብራ ‹‹የዛሬን ማረኝ›› ማለት ያሰኛታል፡፡ ‹‹እገነጠላለሁ›› የሚል ሐሳቡን ለማስቀየርም ራያን ብቻ ሳይሆን ወሎንም ጭምር ሰጥታ ‹‹አትሂድብኝ›› ማለት ይቃጣታል፡፡ የሕገ መንግሥት ጥያቄ ሲነሳም፣ መልስ የምትሰጠው ‹‹ሕገ መንግሥቱ የአገርን ሕልውና የካደ ነው›› እያለ ሕልውናው ለሚከስመው ሕዝብ ሳይሆን እናትነቷን ክዶ ልጆቿን በሞት ለሚቀጣው ነው፡፡ ምክንያቱም የዚህች አገር ሕግ የሚሻሻለው ያለጥፋታቸው ሞት በተፈረደባቸው ንጹሐን ሰሚ አልባ ጩኸት ሳይሆን፣ ፍርዱን በሚያስተላልፉ ዳኞች እና ንጹሐንን በሚቀጥፉ ወንጀለኞች ውሳኔ ነው፡፡ ምክንያቱም… ሁሌ ሰለባ ለሚሆን ለአንድ ሕዝብ ብላ ሕገ-መንግሥት አታሻሽልም!

በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ እራሱ ላይ ያመጸ መንግሥት ተከስቶ ባያውቅም የእኛው ለዛ ቢስ መንግሥት ግን ዓባይ በረሃ ላይ መንገድ ዘግቶ "ከእንደገና አውርዳችሁ አንግሡኝ" እያለ ነው 😁 አንፍረው ገደሉን
በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ እራሱ ላይ ያመጸ መንግሥት ተከስቶ ባያውቅም የእኛው ለዛ ቢስ መንግሥት ግን ዓባይ በረሃ ላይ መንገድ ዘግቶ "ከእንደገና አውርዳችሁ አንግሡኝ" እያለ ነው 😁 አንፍረው ገደሉን እኮ...‼️

ሽመልስ አብዲሳ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ➔የአማራዎች ደም የመስኖ ውሃ የሚመስለው... ➔ከጭፍጨፋ በኋላ የሚከሰተው የፌስቡክ እሪታ ለሌላ ጭፍጨፋ የሚያነሳሳው... ➔"ይሄንን ያህል አማራ ማስገደል" የሚል
ሽመልስ አብዲሳ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ➔የአማራዎች ደም የመስኖ ውሃ የሚመስለው... ➔ከጭፍጨፋ በኋላ የሚከሰተው የፌስቡክ እሪታ ለሌላ ጭፍጨፋ የሚያነሳሳው... ➔"ይሄንን ያህል አማራ ማስገደል" የሚል ሳምንታዊና ወርሐዊ እቅድ ያለው... ➔በሚያደርጋቸው ንግግሮች እንደ ዙቄል መቆጠሩ ደስ የሚያሰኘው... ➔የአማራ ውድመት የኦሮሞ ልማት ነው" የሚል መፎክር ያለው... ➔በንግግርም ሆነ በተግባር ከአማራ አመራሮች ጋር እንደ ልጅ መበሻሸቅ ደስ የሚያሰኘው.... ➔በአራት ኪሎው መንግሥት "ምርጥ አመራር" የሚል አድናቆት የተቸረውና የጥፋት ቸክሊስት የሚሰጠው... ➔የአማራዎች እልቂት ሽልማት እንጂ ቅጣት የሚያመጣ የማይመስለው... ➔የደንብ ልብሱን ቀይሮ የዘር ማጽዳት የሚፈጽም የጸጥታ ሃይል ያለው... . . ፍትሕ ትዘገያለች እንጂ ተዳፍና አትቀርም!!!

ኢዜአ በስህተት የዘገበው እለት የአማራን መጨፍጨፍ፤ ግፍህ ይረሳ ዘንድ ዋልታ ቲቪን ጥለፍ፤ አሳዬ ደርቤ

የሆነ አጀንዳ ለመስጠትም ሆነ ለመጥለፍ ሲታሰብ "አማራን መጨፍጨፍ" ባሕል የሆነው፤ ሕዝባቸውን ሰውተው ሥልጣናቸውን እና ጥቅማቸውን ማስከበር የሚሹ ሆዳሞች ከልባሞች ቦታ ላይ ስለተቀመጡ ነው። እልቂቱን ማስቆም የሚቻለው ደግሞ፤ ለበላይ አካል በማገልገል ፈንታ ለሕዝብ የሚታገል ክልላዊ መንግሥት እና ባመነበት አጀንዳ ላይ የትኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል የተዘጋጀ ብርቱ የፖለቲካ ድርጅት መፍጠር ሲቻል ነው። ከዚህ ውጭ ግን፣ የግርድና ወንበር ላይ ተቀምጠው፤ "ግብር" የሚከፍላቸውን ሕዝብ ለጠላት የሚገብሩ አመራሮች ተሸክሞ፣ ከአክቲቪስቶች እጅ መፍትሔ መጠበቅ ዋጋ የለውም።

በአራት ኪሎው ኢ-መደበኛ ሃይል በቄለም ወለጋ ዞን ከተገደሉ 168 ንጹሓን መሃከል የ87ቱ አስከሬን አንድ ቦታ ላይ ተከምሮ ተገኝቷል። ዐቢይ ሆይ አንተ የተሾምክባት ቀን የተረገመች ትሁን!

አማርኛ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ➔የዲጂታል ወያኔዎች የሥራ እና የሤራ ቋንቋ ሆኖ አማራ መስለው ኦሮሞውን፣ ኦሮሞ መስለው አማራውን፣ ኦርቶዶክስ መስለው ሙስሊሙን፣ ሙስሊም መስለው ኦርቶዶክሱን እየዘለፉ አገር የሚያፈራርሱበትና የእርስ በርስ ግጭት የሚቀሰቅሱበት ሆኖ ሳለ... ➔አሸባሪዎች እና አጭበርባሪዎች በፌደራሊስት ሥም ተሰባስበው አማራን ስለማጥፋት የሚመክሩበት የመግባቢያ ቋንቋ ሆኖ ሳለ... ➔አማራዎች በቋንቋቸው ተመርጠው የሚገደሉበትና የሚፈናቀሉበት ሆኖ ሳለ... ➔ለአማርኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች ያላቸውን ጥላቻ በአማርኛ የሚያሠራጩ ብሔርተኞች ትልቅ ቢዝነስ የሚሸቅሉበት ሆኖ ሳለ... ➔አማርኛ መናገር የቻለ ኢትዮጵያዊ ሁሉ አማራ ክልል ገብቶ የሚቀጠርበትና የስለላ ሥራ የሚሠራበት ሆኖ ሳለ .... "የአማርኛ ቋንቋ መስፋፋት የጠቀመው አማራውን ብቻ ነው" ብለው የሚያስቡ ሃይሎች ግርም ይሉኛል። እንደ እውነቱ ከሆነ ግን... ➔አማራ የሚጠቀመው ልክ እንደሌሎች ብሔሮች ሁሉ ሚስጥሩን የሚመክርበትና ማንነቱን የሚገልጽበት ክልላዊ ቋንቋ ቢኖረው ነበር። አማራ የሚጠቀመው እንደ አፋን ኦሮሞ ያሉ ቋንቋዎችን የሚናገሩ እልፍ አእላፍ አማራዎች ቢኖሩት ነበር። (ሌላውን ተወውና አማርኛ ተናጋሪዎቹ የአዲስ አበባ ልጆች የወቅቱን ቋንቋ ቢችሉ ኖሮ ከቅጥሩም ሆነ ከወንበሩ በዚህ ልክ መች ይገፉ ነበር??) Share

በባለፈው ሳምንት "300 መቶ ንጹሐን ወለጋ ውስጥ ተገደሉ" ሲባል አልልታውን ሲያቀልጥ የከረመ ጀዝባ፤ "አንድ የሞሮኮ ሕፃን ጉድጓድ ውስጥ ገብቶ ሞተ" በሚል ዜና እሪታውን እያቀለጠ ነው። አስመሳይ!

➔ትናንት ከወንድሞቹ ጋር ተባብሮ ኢትዮጵያን የታደገው የአፋር ሕዝብ፤ ዛሬ የኢትዮጵያን ጠላት ለብቻው ተሸክሞ አንድ ዞን ሲወረርበት... ➔ትናንት ሕይወቱን ገብሮ ለአገሩ ያለውን ታማኝነት የገለጸው የ
➔ትናንት ከወንድሞቹ ጋር ተባብሮ ኢትዮጵያን የታደገው የአፋር ሕዝብ፤ ዛሬ የኢትዮጵያን ጠላት ለብቻው ተሸክሞ አንድ ዞን ሲወረርበት... ➔ትናንት ሕይወቱን ገብሮ ለአገሩ ያለውን ታማኝነት የገለጸው የአፋር አርበኛ፤ ዛሬ ክሕደት ታቅፎ በከባድ መሣሪያ ሲደበደብ... ➔ትናንት "በባንዳነት ከሚገኝ ሲሳይ ለኢትዮጵያዊነት የሚከፈል ስቃይ እመርጣለሁ" በሚል አቋም ዋጋ የከፈለው ሕዝብ፤ ዛሬ "ከእኛ ጋር እንዲትደራደር አፋርን ውረር" የሚል ይሁንታ በተሰጠው አሸባሪ ሲዘረፍና ሲጨፈጨፍ... ➔ትናንት ያለምንም ጫጫታ ጠላትን ተጋፍጠው የአገራቸውን ቀጣይነት ያረጋገጡት አናብስቶች፣ ዛሬ እልቂት ተፈርዶባቸው ያለማንም እርዳታ በዲሽቃ ሲደበደቡ.. ማገዝ ቢያቅተን እንኳን ጥቃታቸውን ማውገዝ እንዴት ተሳነን? ደማቸውን ለሰጡን ድምፃችንን መስጠት እንዴት አቃተን? የአፋርን ኢትዮጵያዊ ስሜት ማጥፋት የሚሻ አገር አፍራሽ ቁማርተኛ ሃይል፣ ከባንዳ ታንክ ስር ጥሎ ሲያስመታቸው "ምን እየሠራህ ነው?" ብሎ መጠየቅ እንዴት ተሳነን? Share https://www.facebook.com/100999818947578/posts/161877912859768/

አሸባሪው ሃይል አፋርን ወርሮ፣ ትናንት በእኛ ላይ ያደረገውን ያለምንም ጫጫታ ሲደግመው፤ የተወሰነ ልዩ ሃይል ልኮ ማገዝ ባይቻል እንኳን የአማራ ብልጽግናም ሆነ አብን ወረራውን ማውገዝ እንዴት ተሳናቸው?

ኢሰመኮ ካወጣው ሪፖርት ላይ የከረዩ አባገዳዎችን የገደሏቸው የመንግሥት የጸጥታ ሃይሎች መሆናቸውን ካነበብኩ በኋላ ለቅዱስ ሲኖዶሱ ጥሪ መልስ የሚሰጥ የጸጥታ ሃይል ባለመላካቸው አመሠገንኳቸው። የሚገርሙ ጉዶች!

ለአፋር አናብስቶች አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬▬ ➔ሕይወት የሠጣችሁት፤ እልቂት ቢልክላችሁም ➔ድል ያስረከባችሁት፤ ትግል ለኩሶ ቢያቀብላችሁም... ➔"አናብስቶች" እያሉ ሲያወደሷችሁ የነበሩ ሚዲያዎች፤ ለብቻች
+2
ለአፋር አናብስቶች አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬▬ ➔ሕይወት የሠጣችሁት፤ እልቂት ቢልክላችሁም ➔ድል ያስረከባችሁት፤ ትግል ለኩሶ ቢያቀብላችሁም... ➔"አናብስቶች" እያሉ ሲያወደሷችሁ የነበሩ ሚዲያዎች፤ ለብቻችሁ ከተሸከማችሁት ጦርነት ጋር ቢረሷችሁም... ➔ደብረ ጽዮንን ሲያቅፍ፤ ሃጂ አወል አርባን ለመጥለፍ የሚከጅል እጅ ቢያጋጥማችሁም... ➔ሲጠራችሁ የደረሳችሁለት፣ ስትጠሩት ቢያኮርፋችሁም... ➔ያፈነገጠበትን ክልል ሲያባብል፤ እናንተን ገፍትሮ የሚጥል ከሃዲ ቢያጋጥማችሁም.... ቁማርተኛውን እንጂ አገራችሁን እንዳትቀየሟት። ይህ ሁሉ ቁማርና ክሕደት በልባችሁ ያለውን አገራዊ ስሜት ለማጥፋት ታስቦ የሚደረግ ነውና ዓላማውን እንዳትወርሱለት። በተረፈ የተጣለባችሁን ትግል በድል እንደምትወጡት አልጠራጠርም!

የገዢው ፓርቲ ቀጣይ እቅድ ከአሸባሪው ጋር የጀመረውን ጦርነት በውይይት ቋጭቶ አገር ማረጋጋት ሳይሆን ከአዲስ ጠላት ጋር የሚካሄድ ደማቅ ጦርነት ማሰናዳት ነው።