ar
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

الذهاب إلى القناة على Telegram

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Assaye Derbie

تُعد قناة Assaye Derbie (@asayede) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 335 مشتركاً، محتلاً المرتبة 2 651 في فئة المدوّنات والمرتبة 2 347 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 335 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 26 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -104، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -8، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 35.99‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 12.61‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 158 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 808 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 30.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

وصف القناة غير متوفر.

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 27 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة المدوّنات.

14 335
المشتركون
-824 ساعات
-327 أيام
-10430 أيام
أرشيف المشاركات
"ቀባሪ አታሳጣኝ" እያለች ስትለምን፥ ስትጸልይ ኑራ፥ ባልገባት ምክንያት ፥ ጧሪዎቿን ቀብራ አየኻት ኢትዮጵያን ፥ አየኻት እማማን መውደቂያ ታዛ አጥታ ፥ በእንባዋ ስትረግመን?! ለዚህች እናት ማረፊያ
"ቀባሪ አታሳጣኝ" እያለች ስትለምን፥ ስትጸልይ ኑራ፥ ባልገባት ምክንያት ፥ ጧሪዎቿን ቀብራ አየኻት ኢትዮጵያን ፥ አየኻት እማማን መውደቂያ ታዛ አጥታ ፥ በእንባዋ ስትረግመን?! ለዚህች እናት ማረፊያ የሚሆን አንድ ክፍል ቤት የላችሁም?? በእጃቸው የያዙት ወረቀት ላይ የተፃፈው የብሶት ማመልከቻ በግዕዝ ፊደላት ፈንታ በላቲን የተፃፈ ቢሆን ኖሮ ከአዲስ አበባ ያባረራቸው አካል ኮንዶሚንየም ይሰጣቸው ነበር።

አገር አልባው ባላገር ▬▬▬▬ ከጭፍጨፋ ተርፈው፣ ንብረታቸውን ተዘርፈውና ጎጇቸው ሲቃጠል አይተው ከወለጋ ምድር ከተፈናቀሉ በኋላ ለረዥም ጊዜያት ቢንከራተቱም ኢትዮጵያ የምትባለውን አገር ቀርቶ ኬንዳ
አገር አልባው ባላገር ▬▬▬▬ ከጭፍጨፋ ተርፈው፣ ንብረታቸውን ተዘርፈውና ጎጇቸው ሲቃጠል አይተው ከወለጋ ምድር ከተፈናቀሉ በኋላ ለረዥም ጊዜያት ቢንከራተቱም ኢትዮጵያ የምትባለውን አገር ቀርቶ ኬንዳ ዘርግተው የሚሰፍሩበት ምድር ማግኘት አልቻሉም፡፡ ወለጋ ድረስ ይመጣል ብለው ሲጠብቁት የነበረውን መንግሥት አዲስ አበባ ድረስ መጥተው ቢፈልጉትም ‹‹ከተማዬን ታቆሽሻላችሁ›› ብሎ አባረራቸው እንጂ መጠጊያ ታዛ አልሰጣቸውም፡፡ ብአዴንና አብንም በእኒህ አማራዎች ላይ የሚፈጸመውን ታይቶ የማይታወቅ የግፍ ግፍ ተመልክተው የመፍትሔ አካል ለመሆን አልደፈሩም፡፡ በሄዱበት እየተከተሉ ‹‹አይዟችሁ›› ከሚሏቸው የባልደራስ አመራሮች ውጭ ‹‹ኑ ወደ እኛ›› ብሎ የሚጠራቸው ወገን አላገኙም፡፡ በአረብ አገር የሚሰቃዩ ወገኖቻቸውን ያህል የሚሰቃዩበት የማጎሪያ ካምፕ የሚያመቻችላቸው መንግሥት ማግኘት አልቻሉም፡፡ አስከሬን እንኳን የሚቀበርበት ሁለት ክንድ መሬት አያጣም፡፡ ቆሻሻ እንኳን የሚጣልበት ኮሲ አይቸግረውም፡፡ በሕይወት ያሉት እኒህ አማራዎች ግን የሚያርፉበት የብስ ማግኘት አልቻሉም፡፡ ምን ብናደርግ ይሻል ይሆን? መፍትሔ አምጡ እስቲ...! Share

አራት ወረዳ ተቆጣጠረ የሚባለው የኦነግ ታጣቂ ከአራት ኪሎው መንግሥት ቁጥጥር ውጭ ከመሰለህ ተሳስተኻል። ይህ ሁሉ ቲያትር በእነ ገተት የሚቀናበር ነው‼️😆 ሕዝባዊ ተቀባይነት እያጡ የመጡት ንጉሥም
አራት ወረዳ ተቆጣጠረ የሚባለው የኦነግ ታጣቂ ከአራት ኪሎው መንግሥት ቁጥጥር ውጭ ከመሰለህ ተሳስተኻል። ይህ ሁሉ ቲያትር በእነ ገተት የሚቀናበር ነው‼️😆 ሕዝባዊ ተቀባይነት እያጡ የመጡት ንጉሥም በ"ትህ-ኦነግ" ድጋፍ ዙፋናቸውን ለማስቀጠል ሳያስቡ አልቀሩም።

ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ "ለፓርላማው ያቀረብኳቸው ጥያቄዎች ተቆርጠው ቀሩብኝ" የሚል ይዘት ያለው ጽሑፍ ለጥፎ አየሁ። እኔ ደግሞ ዶክተር ደሳለኝን "መላሽ በሌለበት መድረክ ላይ ጥያቄህን አታባክን" ብዬ
ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ "ለፓርላማው ያቀረብኳቸው ጥያቄዎች ተቆርጠው ቀሩብኝ" የሚል ይዘት ያለው ጽሑፍ ለጥፎ አየሁ። እኔ ደግሞ ዶክተር ደሳለኝን "መላሽ በሌለበት መድረክ ላይ ጥያቄህን አታባክን" ብዬ መምከር እፈልጋለሁ። በበኩሌ ከምክር ቤት ይልቅ እስር ቤት መግባት የምመርጥ ቢሆን እግዜር እረግሞኝ ፓርላማ ብገባ ግን ለጠሚው የማቀርባቸው ጥያቄዎች እንዲህ የሚሉ መሆናቸው አይቀርም። 1. የምግብ ምርጫዎ ምንድን ነው? 2. የቤተ መንግሥቱ አዝመራ ከምን ደረሰ? 3. ቀበሮዎቹ ደህና ናቸው ወይ? 4.ያች ፈረንሳዊት ትደውላለች ወይ? 5. በሙቀት ስንቃጠል እያዩ ደመና መጭመቁን የተውት ምን ሆነው ነው? . . ከዚህ ውጭ ከእሳቸው መልስ እና መፍትሔ ይገኛል ብዬ አገራዊ ጥያቄ ለማቅረብ አልደፍርም።

ሳምንታዊ ቸክሊስት (አሳዬ ደርቤ) ▬▬▬▬ ➔ፋኖን የማሰልጠን ተግባር እንዲስፋፋ መቀስቀስ እና የሥልጠና መርሐ ግብሮችን መደገፍ፤ ➔በኦነግ ከወለጋ ተፈናቅለው፤ በኦሮሚያ ብልጽግና ደግሞ ከአዲስ አበባ ለተሳደዱ አማራዎች ጥብቅና መቆም፤ ➔በድርድር ሒደቱ ላይ ከአብን ይልቅ የአቻምየለህን ሐሳብ በመውሰድ የአማራ ሕዝብ ውክልና እንዲኖረው ጥረት ማድረግ፤ ➔በወልቃይትና በራያ በኩል ዳግም ጥቃት ለመክፈት ያሰፈሰፈውን ወረራ ሊመክት የሚችል ሃይል እንዲዘጋጅ መቀስቀስ፤ ➔አሸባሪው ሃይል በአፋር ሕዝብ ላይ እያደረሰ ያለውን በደል ለአለም አቀፉ ማሕበረሰብ ማሳወቅና ለተፈናቃዮች ድጋፍ ማድረግ፤ ጨምሩበት Share

የነበራቸውን ጸጋ ተገፍፈው፣ በመረጡት አካል ተክደው፣ በከባድ የሕልውና አደጋ ውስጥ የሚኖሩ ወገኖች "ጸጋ ተልከሰከሰች" የሚል ጽሑፍ የያዘ ቲሸርት አሳትመው ሙድ ሲይዙ ጤነኝነታቸው ያጠራጥረኛል። . በሱስ ብዛትና በተስፋ ማጣት ግንባራቸው አሸብሽቦ ፣ ቆዳቸው እንደ ሽቦ አልጋ እረግቦ ያለ እድሜያቸው ያረጁ ወጣቶች "ጂጂ ጠቆረች" እያሉ በኀዘን ሲቆራመዱ ፊታቸውን የሚመለከቱበት መስታወት ገዝቶ መስጠት ያምረኛል።

ጎንደሬ፣ ጎጃሜ፣ ሸዋ ወሎዬ የሚባል Cultural Identity እንጂ ፣ ጎንደሬ ወይም ጎጃሜ፣ ሸዋ ወይም ወሎዬ የሚባል Political Identity የለም። የነገ እጣ ፈንታህ አንድ ነው። ሸኔም
ጎንደሬ፣ ጎጃሜ፣ ሸዋ ወሎዬ የሚባል Cultural Identity እንጂ ፣ ጎንደሬ ወይም ጎጃሜ፣ ሸዋ ወይም ወሎዬ የሚባል Political Identity የለም። የነገ እጣ ፈንታህ አንድ ነው። ሸኔም በለው ወ*ያኔ አሜሪካም በለው ብልጽግና "አማራ" ብሎ ነው የሚውያቅህ! ትንግርቱ ገ/ጻድቅ (ረ/ፕሮፌሰር)

ለመጽሐፋችን የሕትመት ድጋፍ በጠየቅነው መሠረት የመጽሐፉን አስፈላጊነቱን የተረዱ ሁለት ደግ ሰዎች 20+30=50% ወጪውን ሲሸፍኑ ሌሎች ደግሞ 20 % ድጋፍ አድርገው 70% ደርሰናል። እናምከመጽሐፉ የሚገኘው ገቢ ለተሰው የፋኖ ቤተሰቦች የሚውል መሆኑን በመረዳት በዚህ ታሪካዊ መጽሐፍ ሕትመት ላይ አሻራችሁን ማሳረፍ የምትሹ ወገኖች በኢንቦክስ መጥታችሁ "አለን" ትሉኝ ዘንድ እጋብዛለሁ።

ለእነዚህ አርሶ አደሮች ጥርና የካቲት ማለት አዝመራቸውን ሰብስበው፣ አዲስ ቦላሌና ቀሚስ አሰፍተው ልጆቻቸውን የሚድሩበት ነበረ። አሁን ግን ለረዥም ዘመን ጥረው የገነቡት ሰቀላ ቤት፣ ያፈሩት ጥሪት፣
+2
ለእነዚህ አርሶ አደሮች ጥርና የካቲት ማለት አዝመራቸውን ሰብስበው፣ አዲስ ቦላሌና ቀሚስ አሰፍተው ልጆቻቸውን የሚድሩበት ነበረ። አሁን ግን ለረዥም ዘመን ጥረው የገነቡት ሰቀላ ቤት፣ ያፈሩት ጥሪት፣ ወደ ጎተራ ያስገቡት ምርት በዘረኞች ጥቃት ተቃጥሎ ልጆቻቸውን ጎጆ በሚያወጡበት ወቅት ወደ ጎዳና ወጥተዋል። ለሚጋቡ ልጆቻቸው ዳስ ጥለው በሚደሰቱበት የጫጉላ ወራት፣ ማንነትን መሠረት ባደረገ ጥቃት ለሚገደሉ ልጆቻቸው የእዝን ድንኳን ተክለው ማንባት ቢሰለቻቸው.... ሕግ በሌለበት ምድር ላይ "በሕግ አምላክ" እያሉ መሞት፣ ከአገር አልባ ሰማይ ስር "የአገር ያለህ" እያሉ ኡኡ ማለት ቢቸካቸው....ይሄው ከጎዳና ላይ ወድቀው የአምላክን ፍርድ በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ።

ሰፊው ሕዝብ በታክሲ መሄድ ከብዶት ኤርገንዶውን ገርግዶ በእግሩ መጓዝ ጀምሯል። ጠባቡ አመራር ደግሞ በV-8 መኪና መንቀሳቀስ አሰልች ሆኖበት በኪራይ አውሮፕላን መንፈላሰስ ይዟል። በአጭር ጊዜ ውስጥ
ሰፊው ሕዝብ በታክሲ መሄድ ከብዶት ኤርገንዶውን ገርግዶ በእግሩ መጓዝ ጀምሯል። ጠባቡ አመራር ደግሞ በV-8 መኪና መንቀሳቀስ አሰልች ሆኖበት በኪራይ አውሮፕላን መንፈላሰስ ይዟል። በአጭር ጊዜ ውስጥ የሕዝቡን ኑሮ አራቁቶ በቅንጦት የሚሰቃዩ አመራሮችን የቀፈቀፈ ፓርቲ ይሄን ዐየሁ!!😆

የተወሰኑ ኮፒዎችን የሕትመት ወጪ በመሸፈን በዚህ ታሪካዊ መጽሐፍ የምስጋና ገጽ ላይ ሥምዎን ተጠቃሽ ያድርጉ!! https://www.facebook.com/100999818947578/posts/16452888
የተወሰኑ ኮፒዎችን የሕትመት ወጪ በመሸፈን በዚህ ታሪካዊ መጽሐፍ የምስጋና ገጽ ላይ ሥምዎን ተጠቃሽ ያድርጉ!! https://www.facebook.com/100999818947578/posts/164528885928004/

የተወሰኑ ኮፒዎችን በማሳተም ሥምዎን በዚህ ታሪካዊ መጽሐፍ የምስጋና ገጽ ላይ ተጠቃሽ ያድርጉ!

ከስድስት ወር በፊት የአማራ ሳይንት ፈርጥ ስለሆነው ስለ ኮሎኔል ጌታቸው ተፈራ ጀግንነት ስተርክ "ሙገሳህ የትውልድ መንደርን መሠረት ያደረገ ነው" ብለው የተከራከሩኝ ነበሩ። ከሰሞኑን ግን ያ አድናቆ
+1
ከስድስት ወር በፊት የአማራ ሳይንት ፈርጥ ስለሆነው ስለ ኮሎኔል ጌታቸው ተፈራ ጀግንነት ስተርክ "ሙገሳህ የትውልድ መንደርን መሠረት ያደረገ ነው" ብለው የተከራከሩኝ ነበሩ። ከሰሞኑን ግን ያ አድናቆቴ እውነት መሆኑን በሚገልጽ መልኩ፣ የበላይ ዘለቀን ብርጌድ የሚመራው ይህ ኮሎኔል "በሁሉም አውደ ውጊያዎች ላይ ያሳየኸው ጀግንነት እና ብቃት ገራሚ ነበር" ተብሎ ከአማራ ልዩ ሃይል በአንደኝነት ተመርጧል። እንኳን ደስ አለህ አንተ የአማራ ኩራት!‼️

በአፋርም ሆነ በአማራ፣በሶማሌም ሆነ በትግራይ እየሆነ ያለው ነገር ሁሉ በጠቅላይ ሚኒስትሩ እና በክልላዊ ፓርቲያቸው እቅድ የሚመራ ነው። ግቡ ደግሞ ልክ እንደ ሸገር የተሰለቀጠች አገር እውን ማድረግ ነው።

ሕግ ቢኖር ኑሮ ፥ ዳኛ ቢኖር ኑሮ፤ አሳሪው ነበረ ከታሜ ክፍል ውስጥ ፥ የሚገኝ ታጉሮ። ፍቱት...‼️ ንጹሕ አትወንጅሉ ፥ በእራሳችሁ ጥፋት።
ሕግ ቢኖር ኑሮ ፥ ዳኛ ቢኖር ኑሮ፤ አሳሪው ነበረ ከታሜ ክፍል ውስጥ ፥ የሚገኝ ታጉሮ። ፍቱት...‼️ ንጹሕ አትወንጅሉ ፥ በእራሳችሁ ጥፋት።

የአማራ ብልጽግና አመራሮች በብድር ሥም የዘረፉት 60 ሚሊዮን ብር በአስቸኳይ ወደ ካዝናው መመለስ ይኖርበታል! የክልሉን አለመረጋጋት እንደ መልካም አጋጣሚ ተጠቅመው ዝርፊያ የፈጸሙ አመራሮችም በሕግ ሊጠየቁ ይገባል።

አንዳንድ መንግሥታት የሕዝብን የዳቦ ጥያቄ መመለስ ባለመቻላቸው ሲገረሰሱ አይተናል። ድግስ ወዳዱ ብልጽግና፣ ከሕዝብ ርሐብ ባለፈ የአመራሩን ጥጋብ ማስታገስ ተስኖት በውስኪ ስካር እየተንገዳገደ ነው።😆

የእለት ጉርሱን ተነጥቆ ፆም ያድር ዘንድ የተፈረደበትን ሕዝብ "ከርሳም" እና "ፈርሳም" ብሎ የሚዘልፍ ጥጋበኛ አመራር ለአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ቀርቶ ለአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት አይመጥንም።