es
Feedback
ኖህቶኤል ከመጻሕፍት ገፅ📚

ኖህቶኤል ከመጻሕፍት ገፅ📚

Ir al canal en Telegram

ይህ የኖህቶኤል ሀሳቦች የሚንፀባረቁበት ቻናል ነው። በማንበብ ብቁ እና ጤናማ እውቀት ያላቸውን ትውልድ እናፍራ! @noahtoael for anything https://telega.io/c/Noahtoaels_Idea I blog about marketing and sales Buy ads: https://telega.io/c/Noahtoaels_Idea

Mostrar mĂĄs
3 205
Suscriptores
+324 horas
+197 dĂ­as
+4830 dĂ­as
Archivo de publicaciones
በታሪኩ መጨረሻ ላይ ምን የሚፈጠር ይመስልዎታል? 🤔🔥 አንዳንድ ታሪኮች ከመጀመሪያው ገጻቸው ጀምረው ሰንሰለት አይገመቴ ናቸዉ። "ቀጥሎ ምን ሊሆን ይችላል?" የሚለው ጥያቄ እንቅልፍ እስከሚነሳዎት ድረስ የሚገፋፉ፣ መጨረሻቸው ለማወቅ የሚከቡዱ ድንቅ ልብ-ወለዶች በአንድ ቦታ! 👉 ገምተው የማይጨርሱትን ዓለም ይቀላቀሉ፦ 🔗 https://t.me/Fiction_123

ጊዜ የሁሉ ነገር ፈዋሽም፣ የሁሉ ነገር አፍራሽም ነው። ዛሬ በጉልበቱ የሚመካውን ነገ ያደክመዋል፤ ዛሬ የሚያለቅሰውን ነገ ያፅናናዋል። የሰው ልጅ በህይወቱ ምንም ያህል ቢያቅድና ቢጥር፣ ከመጣበት አፈር ወደ አፈር መመለሱ የማይቀር የተፈጥሮ ህግ ነው። ስለዚህ በዚች አጭር የህይወት ዘመናችን ሰውን ከመጥላት፣ ከማሳነስና ቂም ከመያዝ ይልቅ፤ በምንችለው አቅም ፍቅርን መስጠትን እንለማመድ። ምክንያቱም በመጨረሻው ሰዓት ይዘነው የምንሄደው ያካበትነውን ሀብት ሳይሆን፣ በሰዎች ልብ ውስጥ የተውነውን በጎ ትዝታ ብቻ ነው። 📕ፍቅር እስከ መቃብር

💭 . . መናገር እየፈለግን ዝም የውስጣችንን ስቃይ እና መቃጠል ማሳየት እንፈልጋለን ግን ምንም ማድረግ አይቻልም. . . ብዙዎቻችን በዝምታ እየተሰቃየን ነው!!!

​ ከታሪኮቹ ጀርባ ያለውን የሰውን ልጅ ማንነት ይመርምሩ! 🧠💭 ​ስሜቶች፣ ውሳኔዎች፣ ፍርሃቶች እና ፍቅሮች በቃላት ሲቀመጡ... እያንዳንዱ ታሪክ የራሱ የሆነ የስነ-ልቦና ምስጢር አለው። ሰውን በሰፊው የሚተነትኑ፣ ከንባብ ባለፈ የሚያስተምሩ እና የሚያዝናኑ ድንቅ ታሪኮችን ለማንበብ ቻናላችንን ይከታተሉ። ​👉 ውስብስብ የሰዎች ግንኙነት እና ማራኪ ትረካዎች በአንድ ላይ! ​🔗 https://t.me/Fiction_123

ህይወት በድርድር አትሆንም... ታሪኮቹስ? 🎭 ​እያንዳንዱ ሰው በውስጡ የደበቀው፣ ለማንም ያልተነፈሰው እና ማታ ማታ ብቻ የሚያስበው አንድ ታሪክ አለው። በገፆች መካከል የሚቀበሩ፣ ማንነትን የሚፈትኑ እና እውነተኛ የህይወት ገፅታዎችን የሚያሳዩ ምርጥ ተከታታይ ታሪኮች እና ልብ ወለዶች! ​ልብ ሰቃይ እንደ ድራማ በ አይነ ህሊናዎ የሚመለከቷቸዉ ​እውነተኛ የህይወት ገፅታዎች ​የማይረሱ ገፀ-ባህሪያት ​አሁኑኑ ተቀላቀሉና የነፍስዎን ምግብ ያግኙ። 👇 ​🔗 https://t.me/Fiction_123

ከልቤ. . . ከነፍሴ. . . ከእኔነቴ ውስጥ እሷነቷን ለማክሰም ያልወጣሁት ተራራ ያልወረድኩት ዳገት የለም ጭራሹኑ እንደ ወይን እያደር እየጎላች ትመጣላች. . . ስሟ ሲነሳ እንደ አዲስ ማፍቀር  ያገረሽብኛል ልክ እንደ በፊት እንዳገኘዋት ቀን ልቤ መምታት አንደበቴ መተሳሰር ይጀምራል. . . ደውዬ ደህንነቷን መጠየቅ፣ ቁጥብ ሳቋን መኮምኮም የምረኛል. . . ግን አልችልም ዛሬ ትናት አደለም ሁለተኛ እድል አይሰጥም እሷን አይመልስልኝም. . . በነበር ባህር ውስጥ ከመ'ነከር ውጪ

ማንበብ ይወዳሉ?💝

ጓደኛ ነበረችኝ. . . አሳሳቋ  የሚናፈቅ፣ ነገዬን በብሩህ ቀለም የሳለችልኝ. . . ጓደኛ ነበረችኝ. . . ነበረችኝ እንደማለት ደባሪ ቃል የለም. . . ለምን??? ነበረኝ ማለት አሁን አለመኖሩን ያሳያላ. . .፣ እንደማንደርስበት የሰማይ ክዋክብት መራቁን ያሳያላ  ይህ ደግሞ ጀምበር እክታዘቀዘቅ እየጠበቁ ከሚሊዮኖች ኮከብ ውስጥ መኖሯን እያሰቡ ሰላም ማለት ነው. . . ማን ያቃል ነገ??? ምናልባት ዛሬ ከኮከቦች ውስጥ አንዱ እሆን ይሆናል. . .

ስራ ፈት አደለሁም ፈልጌ ፈልጌ ስራ ያጣሁ ሲገኝ የስራ ልምድ በሚል ጥያቄ የተሰላቸው ወጣት ስራ አጥ ነኝ ጠዋት  እንደሰራተኛ ቁርስ በልቼ እወጣና ግማሹን ቀን በስራ ፍለጋ ግማሹን ሰው ሰፈር ሄዶ ድንጋይ በማሞቅ አሳልፌ ወደ ቤተሰቦቼ ቤት እመለሳለሁ "ይሄንን የመሰለ ውጤት ይዘህ ስራ ጠፋ አደል እንደዛ ከምቸክይ ከኛ ጋ ፈታ ብትይ ይሻልሽ ነበር" የሚሉኝ ጓደኞቼ እራቡንም ሆነ የሞራል ውድቀቱን አያዩም ነበር ቢሆንም በገንዘብ ይረዱኛል ፍቅረኛ አለችኝ "ብፀዳም ብቆሽሽ" ብሎ እዮብ የዘፈነላትን የምታስንቅ እንቁ!! አግኝቼ አላየኋትም በማጣቴ ግን አልተለየችኝም "እግዚአብሔር ቀን አለው ተስፋ እንዳትቆርጥ" እያለች ታፅናናኛለች ለኔ ግን አንዷም ቃል አታፅናናኝም ጎሎብኝ ያጎደልኩባቸው ስለሚመስለኝ እየናፈቁኝ አንኳን እነሱን ከማግኘት ለብቻዬ መንቀዋለልን እመርጣለሁ ታድያ ዛሬም የማሞቃት ድንጋይ ላይ ቁጭ ብዬ አንድ ኑሮ የደላቸው የሚመስሉ እናት ምስጥ ብለው አንድ ቦታ ሲያዩ አየኋቸው ዞሬ የሚያዩትን ስመለከት ሁለት በእኔ እድሜ ያሉ ወጣቶች እያወሩ ቆመዋል በመሀል እጁን ዘረጋላትና አቅፎ ሳማት ትንሽ ሄደችና ተመልሳ መጥታ ማውራት ጀመሩ  አውርተው ሰአቷን አየችና ተቃቅፈው አንገቷን ስሟት ወደ እሷ መንገድ ሄዱ ጥቂት ተራምደው ድጋሚ ስሟት ተመለሰ ወደ እሳቸው ስዞር አይናቸው እንባ አቅሯል "ባሏቸው ሞቶባቸው ይሆን" እያልኩ እሷቸው ጋ ሄጄ "አይ የወጣት ነገር ፍቅሮትን ቀሰቀሱቦት አደል" አልኳቸው "ብሶቴን ቀሰቀሱት እንጂ" አሉኝ እንደመተከዝ ብለው "ታሪክ መስማት እወዳለሁ ጊዜ አለኝ ንገሩኝ እስኪ" "እንደናንተ ወጣት እያለሁ ለሰው ለፍቅር ለማህበራዊ ሂወት ቦታ አልነበረኝም ትኩረቴ እስከ ጥግ እየሰሩ ገንዘብ ማግኘት ያሳደገኝን ድህነትን መበቀል ላይ ብቻ ነበር ለስራዬ ስል ብዙ የፍቅር ጥያቄ መልሻለሁ ፣ያለኝንም ፍቅር አጥቻለሁ፣ ብዙ ከመቆሜ የተነሳ ጤናዬም ተቃውሷል የኋላ ኋላ ልቡን በአርባ አመቴ ባገኘው ትዳሩ ከየት ይምጣ ከአንዱ እወልዳለሁ እንዳልል እድሜዬም ተላልፎኛል ብር ብቻውን ቢታቀፋት ምንዋጋ አለው ባለፀግነት በዙ ገንዘብ በኖረው አደለም ሰው ሲኖርህ አደብ ስገዛ ነው ባለፀጋ  የምትሆነው ለካ" ነግረውኝ ሲጨርሱ ዞር ብለው እንባቸውን ጠረግ አደረጉት በራሴ አፈርኩ እሳቸው ስራ እና ገንዘብ ብቻ ነው ያላቸው እኔ ጤነኛ ነኝ በዙሪያዬ የሚደርሱልኝ ሰዎች አሉኝ  እኛ ለራሳችን የጠላነውን ሂወት ሌላ ሰው ምን ያህል እንደሚመኘው ገባኝ አሳዘኑኝ  እማማን ከማደጎ ልጅ ማምጣት እንደሚችሉ እኔም  ልጃቸው እንደምሆን ነግሬያቸው ስልክ ተለዋውጠን ተለያየን ✍🦋

በመኖር በኩል... ሕይወታችን ውስጥ ያሉትን ሰዎች እኛው ራሳችን የምንመርጥ ይመስለናል።  ግን እውነቱን እናውራ ከተበላ ለሕይወታችን በጣም የሚያስፈልጉን ሰዎች ብዙውን ጊዜ ሳይጠሩ ነው የሚመጡት። እንግዳ የነበረው ወዳጅ ይሆናል። ወዳጅ የተባለው ትዝታ ይሆናል። ትዝታ የሆነው ወደ ቁስል ይቀየራል። ቁስሉ ደግሞ ጥበበኛ ያደርገናል። ወደ ኋላ መለሾ ብለን ስንመለከት፣ ሕይወት ከታቀደላት መንገድ ይልቅ ማንነታችንን በዝምታ ወደቀረጹት ተከታታይ ገጠመኞች ታዘነብላለች። ዕጣ ፈንታ አለ የለም የሚለው ሌላ ጥያቄ ነው። ሊካድ የማይችለው ሀቅ ግን፣ አንዳንድ ሰዎች በነፍሳችን ላይ አሻራቸውን ጥለው ማለፋቸው ነው። አንዳንዶች ብርሃን ተሸክመው ሕይወታችን ውስጥ ይገባሉ። የራሳችንን ዋጋ በረሳን ጊዜ መልሰው ያስታውሱናል። ፈጽሞ አይጠገኑም ያልናቸውን የሕይወታችንን ክፍሎች እንድንፈውስ ይረዱናል። በሕይወታችን ውስጥ መኖራቸው፣ በበረሃ ውስጥ እየተንከራተቱ ውሃ የማግኘት ያህል ነው። ሌሎች ደግሞ እንደ ማዕበል ይመጣሉ። ይከዱናል፣ ያሳዝኑናል፣ ጥለውን ይሄዳሉ፣ ወይም ደግሞ ልንሸሻቸው የምንመኛቸውን እውነታዎች ፊት ለፊት እንድንጋፈጥ ያስገድዱናል። ስህተቶች ብለን እንጠራቸዋለን፤ ከዓመታት በኋላ ግን ታላቁ የሕይወት እድገታችን የጀመረው ከታላቁ የልብ ስብራታችን እንደሆነ እንረዳለን። የሰበሩን ሰዎች፣ ምን ያህል ፈተናዎችን ተቋቁመን ማለፍ እንደምንችል ጭምር አሳይተውናል። ምናልባት የሰው ልጅ ግንኙነት ዓላማ ይሄው ይሆናል። ሁሉም ሰው በሕይወታችን ውስጥ ለዘላለም እንዲቆይ አልተፈጠረም። አንዳንዶች በጓደኛ የተመሰሉ ትምህርቶች ናቸው። አንዳንዶች ማንነታችንን የሚያሳዩን መስተዋቶች ናቸው። አንዳንዶች ደግሞ ምዕራፎች እንጂ ሙሉ መጽሐፍት አይደሉም። ከዚያም በጣም ጥቂት የሆኑ ልዩ ሰዎች አሉ። በከፍታችንም ሆነ በውድቀታችን ጊዜ የሚያዩን። አድናቆት ሲጠፋና ችግሮች ሲመጡ አብረውን የሚቆዩ። ውድቀታችንን፣ ፍርሃታችንን፣ እና ተቃርኗችንን እያዩም ከእኛ ጋር ለመቆየት የሚመርጡ ሰዎች። ብዙ ግንኙነቶች ጊዜያዊ በሆኑበት ዓለም፣ ታማኝነት ቅዱስ ነገር ነው። ፍቅር በስሜት ጥልቀት፣ በመሻት ወይም በታላላቅ ቃልኪዳኖች አይለካም። ምናልባት ፍቅር የሚለካው አብሮ በመገኘት ነው፤ ሌሎችን በሚያስኮበልሉ ቀናቶች ውስጥ አብሮ በመቆየት። በሕይወታችን መጨረሻ ላይ፣ በሺዎች የሚቆጠሩ ፊቶችን ልንረሳ እንችላለን። ግን ራሳችንን ያለነሱ ማሰብ እስካንችል ድረስ ስሞቻቸው ከታሪካችን ጋር በጥልቅ የተገመዱ ጥቂት ሰዎች ሁልጊዜም ይኖራሉ። በዕጣ ፈንታ፣ በአጋጣሚ፣ ወይም በራሳችን ምርጫ የተጻፉ ይሁኑም አይሁኑም የኛ አንድ አካል ይሆናሉ። ✍ዮሓቶኤል

ጊዜ ለተስፋ መቁረጥ ያበድራል!! እንደ ደንቡ ለመኖር እንፍገመገማለን እንጂ፣ እንደ ደንቡ… እኛም ያለንን ተጣጥረን ከጊዜ ለመበደር መከራ እናያለን፣ ጊዜ ሀያል የሚሆንበት ተስፋ ሲይዝ ነው፣ ካልሆነ
ጊዜ ለተስፋ መቁረጥ ያበድራል!! እንደ ደንቡ ለመኖር እንፍገመገማለን እንጂ፣ እንደ ደንቡ… እኛም ያለንን ተጣጥረን ከጊዜ ለመበደር መከራ እናያለን፣ ጊዜ ሀያል የሚሆንበት ተስፋ ሲይዝ ነው፣ ካልሆነ ጊዜ ያን ያህል ሀይል የለውም፣ ተስፋ መሳሪያው ነው.. የጊዜ አምነዋለው፡ ተስፋዬን ጊዜዬን አልፈራውም ፡ ያለዚያ ግን ጊዜ ለተስፋ መቁረጥ ያበድራል

ልባችሁን፦ክብደት፣ሸክም፣ጫና፣መታፈን፣ጭንቀት፣ድካም ከሚያሰሟችሁ ሁኔታዎች ውስጥ በግዜ ውጡ።እየቆየ ሲሄድ እንደምስጥ ውስጣችሁን በልቶ ያፈርሳችል ማንነታችሁን ታጣላቹ ሰላም የማይሰጣቹ ቁስል ነገር እኔኮ እንዲ አልነበረኩም እስክትሉ ድረስ የምትወዱት እናንተን አጥፍቶ የተጨማደደ ማንነት ውስጥ ይከታችኋል።እንደዚ አይነት ስሜት የሚፈጥርባችሁን ነገሮች ከልባችሁ አርቁ።

ሙሉ ሕይወታችንን በመልክ ተከበን ነው የምናሳልፈው። አንዳንዶች መጽሐፍትን ማንበብ ይማራሉ። አንዳንዶች ደግሞ የሰዎችን ፊት ማንበብ ይማራሉ። በሁለቱ መካከል ያለውን ርቀት ማንበብ የሚማሩት ግን ጥቂቶች ናቸው። ሳቅ ደስታ አይደለም። በራስ መተማመን ጥንካሬ አይደለም። ደግነት ቅንነት አይደለም። ቃላትም ምንም ያህል ያማሩ ቢሆኑ፣ የማንነት ማረጋገጫ ሊሆኑ አይችሉም። የሰው ልጆች የጭምብል ፍጡራን ናቸው። ፍርሃታችንን ከትዕቢት፣ ብቸኝነታችንን ከኩራት፣ እና ራስ ወዳድነታችንን ከበጎነት ጀርባ እንደብቃለን። ሌሎችን እናታልላለን። ግን ከሌሎች በበለጠ የምናታልለው ራሳችንን ነው። ጥበብ የምትጀምረው ሰዎች የሚያወሩትን መጠየቅ ትተን፣ ተግባራቸው ምን ያሳያል ብለን መጠየቅ ስንጀምር ነው። ግን ብልህነት ብቻውን በቂ አይደለም። የሰላ አእምሮ ውሸቶችን መለየት እየቻለ እንኳን በውሸታሞች ወጥመድ ውስጥ ይወድቃል። ሁሉም ልብ የራሱ እውርነት አለው። በአታላዮች ወጥመድ የምንወድቀው አሳምነውን አይደለም፤ አጥብቀን መስማት የምንፈልገውን ስለሚነግሩን ነው። ተስፋ ስለምናደርግ እናምናለን። ሰው ስለሆንን ተስፋ እናደርጋለን። ክህደት በጣም የሚያቆስለውም ለዚህ ነው። ጠላት አካልህን ሊያቆስለው ይችላል። የማታውቀው ሰው አእምሮህን ሊረብሽ ይችላል። ግን ዘላለማዊ ጠባሳ ወደሚፈጠርባቸው የልብህ ክፍሎች ጠልቆ መድረስ የሚችለው ያመንከው ሰው ብቻ ነው።
በጣም ጥልቆቹ ቁስሎች የሚፈጠሩት በጥላቻ ሳይሆን በተሳሳተ ሰው ላይ በጣልከው እምነት ነው።
ቢሆንም ግን ጊዜ የራሱ ፍትህ አለው። ጊዜ ትወናዎችን ገፎ ይጥላል። የውሸት ወዳጆችን፣ ባዶ ቃልኪዳኖችን፣ እና የይስሙላ ፍቅርን ያጋልጣል። ጭምብሉ ለአንድ ቀን፣ ለአንድ ዓመት፣ ምናልባትም ለአስርት ዓመት ይቆይ ይሆናል። ግን እውነታ ታጋሽ ነው። ውሎ አድሮ፣ እያንዳንዱ ማስመሰል እየከበደ ይመጣል። እያንዳንዱ ትወና አድካሚ ይሆናል። እያንዳንዱ ቅዠት መሰንጠቅ ይጀምራል። ይህ ሲሆን፣ ሰዎች የሚገለጡት ነኝ ባሉት ማንነት ሳይሆን፣ አዘውትረው ለማድረግ በመረጡት ተግባር ነው። ከሕይወት ፈታኝ ትምህርቶች አንዱ ይህ ነው፡ እውነታ ቀስ ብሎ ነው የሚገለጠው። የሰዎች እውነተኛ ማንነት በቅጽበት አይታወቅም። በዓመታት ምልከታ፣ ብስጭት፣ ይቅርታ፣ መራራቅ እና የሕይወት ተሞክሮ ውስጥ ነው የሚገለጸው። ማንነት በትልልቅ ዲስኩሮች ውስጥ ሳይሆን፣ በትናንሽ ተደጋጋሚ ድርጊቶች ውስጥ ነው የሚገኘው። ስለዚህ በጥሞና ማዳመጥን ተማሩ፣ ግን ከዚያ በላይ በትዕግስት መታዘብን ልመዱ። ምክንያቱም አይኖች ሊታለሉ ይችላሉ። ቃላት አስቀድመው ሊጠኑ ይችላሉ። ፈገግታዎች ሊተወኑ ይችላሉ። ጊዜ ግን ከመነሻውም የተደበቀውን ነገር ገልጦ የሚያወጣበት የራሱ መንገድ አለው።😇 ✍ ዮሓቶኤል

አራት መቶ ፍቅር... "ጥግት በለኝ?" "ተጠጋሁሽኮ ፍቅር!ከዚህ በላይ የት ድረስ ልጠጋሽ?" "ውስጤ ድረስ፤ነፍሴ ድረስ፤ልቤ ድረስ ተጠጋኝ" "ልብሽን ያምሻላ!" "ስትርቀኝ ከሚያመኝ ህመም አይብስም" ድምጿ ለስላሳ ነው።ነፍሷ ለስላሳ ናት።መልኳም ውበቷም አካሏም ለስላሳ ነው ስሟ ሲተረጎም የእንጀራ መገኛ ማለት ነው።አብረን ተቀምጠን ንፋስ ፀጉሯን አምጥቶ ፊቴ ላይ ነስንሶት ያውቃል።(ፀጉሯ ከሻሽ ወጥቶ ስለማያውቅ ይሄ ፈጠራ ነው።)ባለመነጣጠል ነው የኖርነው።ቀን ማታ ሌሊታችን አንድ ላይ ነበር።ግትርም ናት።ከአቋሟ ፈቀቅ የማትል ግትር።ንዴቷ ልቧ ላይ ቁጭ የሚልባት።ስትናደድ ደስ ትለኛለች ኩርፊያዋ ይጣፍጠኛል።በገና ደርዳሪ ናት።የልቤን አውታር በፍቅር ጣቶቿ የፍቅርን መዝሙር የፈጠርችባት እሷ ናት። የድሮዋን ጨረቃ ይመስላል ፊቷ።ያሁኗን ጨረቃ ስለማላቃት ወይም ካየኋት ስለቆየሁ ይመስለኛል የማመሳስላት በልጅ አይኖቼ አያት ከነበረችው ጨረቃ ጋር ነው።ሙቀቷ በልጅነታችን እንሞቃት እንደነበረችዋ ጀንበር ነው።እንደ ሰሞኗ  ፀሀይ ስለማታቃጥል ስሞቃት ነው የኖርኩት። "የማያልቅ ፍቅር የፈጣሪ ፍቅር ብቻ ነው።እየተቀየርሽ ነው?" "በምኔ ልተነፍስ?እንዴት ብየ ልቆም ነው ባንተ ላይ የምቀየረው?" "አይኖችሽ ውስጥ አይቻለሁ።የተፈጠረ ነገር አለ?" "የኔና ያንተ ታሪክ የተፃፈውኮ በአንድ ኪታብ ነው።ስሜ ሲነሳ ያንተም ስም አብሮ አለበት።የግሌ የሆነ የራሴ ህይወት የለኝም።ነገር አለሜ ውስጥ ሁላ አለህበት።ንገረኝ አይኖቼ ውስጥ መሰልቸት ካየህ ልቤ ውስጥስ ምን ታየህ? " እኔንጃ!እሱንማ አንቺ ንገሪኝ" "በቃ እንደዛ ከሆነ ያይኖቼን ነገር ችላ ብለህ እለፈው።የልቤ እውነት ይበቃሃል" "ንገሪኝ ልብሽ ምን ይላል?" "አንተ ለኔ ፅላት እንደሚቀመጥበት ማደርያ ታቦት ነህ ፅላት ያለ ታቦት ማደርያ እንደሌለው የኔም ልብ ያላንተ ነፍስያ ማደርያ የላትም ከሌለህ ቆብ እና ቢጫ ፎጣን ትመርጣለችና።" "አለምንሽም።" "ጊዜ ያሳምንሀል።"                                    ቀዳማዊ ዮሓቶኤል!

መናገር አልችልበትም ማውራት ከተሳናቸው የምለየው  እየቻልኩ ባለመቻሌ ነው መጡ ሄዱ እረገጡኝ አከበሩኝ ተናገሩኝ አልተናገሩኝ መልሴ ዝምም ነበር ትዝ ይለኛል highschool እያለን እረፍት ሰአት ላይ አልወጣም ነበር ባዶ ክፍል ውስጥ በሩን እዘጋና መስኮቱ መስታወት ላይ ስለማልደርስ ወንበር ላይ ወጥቼ አላፊ አግዳሚውን አይ ነበር ታድያ አንድ ቀን ያለ ልምዴ መፅሐፍ እረስቼ ስለነበር ልዋስ ወጣሁ ተመልሼ ደብተሬን ሳየው ደብተሬ ላይ "ዝም ለበግም አልበጃት እሷ አስር ሆና አንድ ነብር ፈጃት" ተብሎ ተፅፎ አገኘሁ ለዛውም በማውቀው የእጅ ፅሁፍ አይገርምም ለዚህም መልስ አልጠሁም እያብሰለሰልኩት ወደ ቤት ተመለስኩ " ዝምታ መልስ ነው ዝምታ ወርቅ ነው..." እያልኩ ድክመቴን በጥቅስ መሸፈኔ አሳፈረኝ ይሄንን ሁሉ አባባል ለድክመቴ ስጠቀም እንዴት "ካለመናገር ደጅ አዝማችነት ይቀራል"ን እረሳሁት ልክ ናቸው በቦታው እንጂ ያለቦታው የሚያምር የለም መናገር ባለብህ ሰአት ካልተናገርክ ማድረግ ያለብህ ሰአት ካላደረክ ትላንትህን መኖርህ ነው እንደ በጓ ትፈጃለህ (ትበላለህ)! ያቺ መልእክት ለኔ መንቂያ ነበረች "ዝም ለበግም አልበጃት እሷ አስር ሆና አንድ ነብር ፈጃት!! " ✍🦋

የልምዣት.... የተወለደችበትን ከተማ ለቃ ስትወጣ የልጅነት ጓደኞቿ ሲሰናበቷት የነበረውን ሁነት አትረሳውም።ራሷን ጨምሮ ታናሽ እህቷንና ብቸኛ እናቷን ድህነት ገፈታትሮ ሲያባርራቸው ማረፊያ ፍለጋ ወደ ትልቅ ከተማ ተሰደዱ።ያሳደዳቸው ድህነት እዛም አለቀቃቸውም።ከነሱ ቀድሞ መድረሻቸው ጋር ጠበቃቸው። ይባስ ብሎ  በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ እናታቸው በጠና ታማ አልጋ ላይ ዋለችና በ10 አመቷ የቤተሰቡ ሀላፊነት እጇ ላይ ወደቀ።እናቷ የታመመች ሰሞን የመንደራቸው ሰዎች የሚቀመስ ነገር እያመጡ ያግዟቸው ነበር።በኋላ ላይ ግን መስጠት ሰለቻቸውና ቤታቸው ዝር የማል ሰው ሲጠፋ በህፃን አእምሮዋ መፍትሄ ያለችውን ነገር ማድረግ ጀመረች። ጠዋት ትወጣና ሰው የሚበዛባቸው ዳቦ ቤቶች ገብታ ሶስት ዳቦ ለመስረቅ ትሞክራለች።ተሳክቶላትም ሳይሳካላትም ቀርቶ ያውቃል።አንዳንድ ዳቦ ቤቶች አይተው እንዳላዩ ያልፏታል።በዚህ ግብግብ ውስጥ ሳለች አንድ ባለሀብት እዛው መንደራቸው ውስጥ ትልቅየ ዳቦ ቤት ከፈተና የተለመደ ተግባሯን በቅርበት መከወኗን ቀጠለች።አንድ ቀን ሳይቀናት ቀርቶ የዳቦ ቤቱ ባለቤት ፊት ዳቦ ስትሰርቅ እጅ ከፍንጅ ተይዛ ቀረበች።ጠየቃት... "መስረቅ ሀጥያት እንደሆነ አታውቂም?እንደሚያሳስርስ አታውቂም?" "እናቴን አሞብኝ ልትሞትብኝ ነው።ታናሼና ህመምተኛ እናቴ የሚቀምሱት ስለሌላቸው ነው የሰረቅኩት።እባክህ ይቅርታ አድርግልኝ?" "አባትሽስ አብሯችሁ የለም?" "አባቴን አላቀውም።ታናሽ እህቴ በተወለደችበት ወቅት ነው ጥሎን የጠፋው።ያለችን እናታችን ነበረች።እሷም ወደቀች" የብላቴናዋ እንባ ያረገዘ አይን የልጅነቱን መልክ አስታወሰው።ሆዱ ራርቷል።አማራጭ ማጣት የት ጋር እንደሚያደርስ ገብቶታል። "አንቺ ልጅ ቤታችሁን ታሳይኛለሽ?" "ለእናቴ ልትነግራት ከሆነ ትሞትብኛለች እባክህ እንደዚህ አታድርግ?" ምንም እንደማይነግርባት አሳምኗት ከመቀመጫው ተነሳ።"ልጆች በርከት ያለ ዳቦ አዘጋጁልኝ።የዚችን ቆንጅየ እናት ልጠይቃት እፈልጋለሁ"ብሎ ፊት ፊት እየመራች ደሳሳ ቤታቸው አደረሰችው።በሩ ተከፈተ።ወደ ውስጥ መግባት ሲጀምር አይኑ ግድግዳ ላይ የተሰቀለ ፎቶ ላይ አረፈ።ፎቶው የሰርግ ፎቶ ሆኖ በሙሽሪትና በሙሽራው መካከል ያለው ቦታ ተቆርጦ ተለያይቶ በአንድ ፍሬም ውስጥ ተሰቅሏል።ህፃኗ ሾለ ፎቶው ገለፃ ጀመረች። "ይቺ እናቴ ናት።ይሄ ደግሞ አባቴ!" ደርቆ ቀረ።ተንቀጠቀጠ።ማመን አቃተው።በፍሬሙ ውስጥ የራሱን ወጣት ፎቶ ማየቱ ሊጥለው ደረሰ።ጥሏቸው የሄደው ሀላፊነት ከብዶት ነበር።ድህነት ቤተሰብ የማስተዳደር አቅሙን ሲፈታተነው ኮበለለ።በእርግጥ ልጆቹንና ሚስቱን በዛ መልክ አጋፍጦ መሄዱ ልክ አይደለም።ሄደ።ታገለ።አሸነፈ።ብር ያዘ። አልጋ ላይ የተኮራመተች የቀድሞ ሚስቱን በሙሉ አይኑ ማየት አቅቶት አቀረቀረ።እየታገለ ተነፈሰ። "በጣም በድያችኋለሁ።ሁሉም ነገር የኔ ጥፋት ነበረ።ድህነት ነበር ያሳደደኝ።በዛ በኩል ሳመልጠው በዚህ በኩል ልጄን ዳቦ እስከመስረቅ በሚደርስ በቀል ተበቀለኝ።ልካሳችሁ ወደ ህይወታችሁ መልሱኝ የማለት ድፍረቱ የለኝም።ከዚህ በኋላ ልጆቼ ዳቦ ለመብላት ዳቦ እንዲሰርቁ ግን አልፈቅድም።ከዛሬ ጀምሮ ያ ዳቦ ቤት የናንተ ነው።በተጨማሪም እንደ አባት በፈለጋችሁኝ ጊዜ ሁሉ አጠገባችሁ ለመገኘት ቃል እገባለሁ" ከአልጋው ውስጥ የሚያቃስት የሚርገበገብ ድምፅ ወጣ። "መጨረሻየን አላቀውም።ምናልባት በዚሁ ተኝቼ ልቀር እችላለሁ።ሞትን ፈርቼው አላውቅም።እስከዛሬ ከህመሜ በላይ ያሳስበኝ የነበረው የልጆቼ ጉዳይ ነበር።ከተመለስክላቸው የልጆቼን ነገር አደራ!" ቀዳማዊ ዮሓቶኤል!

ከእለታት ግማሽ ቀን... "ልጄ" "የኔ ልጅ" •••በእድሜ የጠኑ አዳፋ ቀሚስ የለበሱ ሴትዮ ናቸው።ከተጨማተረ ፊታቸው ሾር ጭል ጭል በምትል አይናቸው እያዩኝ፣ሽቦ የምታክል ሰላላ ኦጃቸውን ዘርግተው ምፅዋት ይለምኑኛል" "ልጄ እራቴን ጣልልኝ?" •••ምን አይነት ውስጥ ድረስ የሚሰማ  ድምፅ ነው!እናቴን ይመስላሉ።ማማ'ዬን ይመስላሉ።የሷ እጆችም እንደሳቸው ክንዶች የሰለሉ ነበሩ።በህይወት ውጣውረድ ደክማ ነው የኖረችው።ህይወት ቂ ጧ አልሸፈን ብሏት በዚህ ስትጎትት፣በዛ ስትገለጥባት እንዲሁ ከሰውነት በታች ሆና ነው የኖረችው።ልዩነቱ እማዬ ደፍራ ጎዳና ወጥታ ምፅዋት አለመነችም••• " የኔ ልጅ እራቴን ጣልልኝ" "እግዚያብሄር ይስጥልኝ እማየ" "እግዜሩ ምን አገባው?አሁን እኔ በሱ ስም ምፅዋት ስጠይቅ ሰምተሃል?እኔ የለመንኩት አንተን ነው።እግዜርም አላህም ሰይጣንም አያገባቸውም" "ይስሙኝ እናቴ" "አንተ ስማኝ!!እንደው ምን ብትጨክን ነው አንተን ለምኜህ ከእግዜሩ ምታገናኘኝ?እግዜሩንማ ቀለሜ እስከሚለቅ ድረስ ለመንኩት።ሰርክ በየደብሩ እየተመላለስኩ ሰው አርገኝ አልኩት።የሱ ጆሮ የሚሰማው መርጦ ነው።አሁን ደግሞ አንተ እግዚሃር ይስጦት ትላለህ!እሱማ ከለከለኝ!እሱማ ለእናንተ ሰጠ!እኔ እናንተን ነው ልመናዬ።እናንተ ስጡኝ" "ይፀልዩ እማየ" "ሂሂሂሂሂሂሂሂ"ባልተሟላ ጥርስ አሽሙር የሚመስል ሳቅ ሳቁና ቀጠሉ። "አይ ፀሎት!ሂሂሂሂ!ያልፀለይኩበት ደብር ያልረገጥኩት ጠንቋይ ቤት የለም።እኔ ምናቸው ነኝ እና ይሰሙኛል?አየህ በወጣትነቴ ነው ከመከራ ጋር ግብ ግብ መግጠም የጀመርኩት።ገና ትዳር ስመሰርት ባሌን ሳገባ ነው ፈተናዬ የጀመረው።መጀመሪያ ማህፀኔን አድርቆ ልጅ ነሳኝ።ባሎቼ ይቺ በቅሎ ብለው እየጣሉኝ በነኑ።ከስጋየም ከነፍሴም ሳልሆን ይሄው በ86 አመቴ እናንተን አስቸግራለሁ።አሁን አታስለፍልፈኝ እራቴን ስጠኝ" "እማይ እግዛቤር ይስጦት አልኮት'ኮ" "እሱማ ከለከለኝ አልኩህ አበይ!" •••ያሳዝናሉ።ልብ ይነካሉ።ደክመዋል።አይኖቻቸው ሰርጉደዋል።ከአጠገባቸው መራቅ ፈለግኩ።ቶሎ ከእይታቸው ማምለጥ ፈለግኩ።በትዝብት ባይናቸው ተከተሉኝ።አላወቁም እኔም ድፍረት አጥቼ እንጂ  እንደ እሳቸው ብለምንና ርሃቤን ባስታግስ ደስ ባለኝ።በደንብ ርቀታችን መስፋቱን ሳረጋግጥ ዞሬ አየኋቸው••• "የኔ ልጅ ስማ ናማ እቃ ጣልኩ አቀብለኝ" •••ተመለስኩ።አጠገባቸው ደረስኩ።በሰለለ እጃቸው ጀርባየን ተመተሙ።"ርቦሃል አይደል?ከለመንኩት ብሰጥህ አይዋጥልህም።እንካ ይቺን መቶ ብር አንዱ ሻይ ቤት ገብተህ ብላ!አየ ልጄ!እኔን አፈር ልብላልህ" •••በሀዘን ተሰናብቻቸው ስሄድ ለራሳቸው ሳይሆን ለቀጣዩ የኔ ቢጤ ሌላ እራት ሲለምኑ ተሰማኝ••• "ልጆቼ እራቴን ጣሉልኝ" እራት ለምነው እራት የሚሰጡ እናት!! ቀዳማዊ ዮሓቶኤል!

የፍቅር ጥያቄውን በጨዋ ደንብ አቀረበላት። እዝን አለች። አለች፦ “ታውቃለህ እንዴት እንደማከብርህ። ያንተን ያህል የምቀርበው ሰውም የለኝም። ከአንተ በላይ ምቾቴን የሚሰጠኝ ሰው የለም። የነፍሴ ሰው ነህ። የልቤ ሰው ነህ። ግን ይህንንም ታውቃለህ። የእናቴ ልጅ ማለት ነህ። በሁለታችን መሃል ሌላ ነገር ግን፣ የኃጢያት ያህል ነው።” “እሺ” አላት “ትረዳኛለህ አደል?” “ደግነቱ. . . እኔም አንቺም ሁላችንም እንሞታለን። ሁለመናችን አፈር ይለብሳል። አፈር።” ተፍለቀለቀ።

ኖህቶኤል ከመጻሕፍት ገፅ📚 - Estadísticas y analítica del canal de Telegram @noahtoaels_idea