ኖህቶኤል ከመጻሕፍት ገፅ📚
Ir al canal en Telegram
ይህ የኖህቶኤል ሀሳቦች የሚንፀባረቁበት ቻናል ነው። በማንበብ ብቁ እና ጤናማ እውቀት ያላቸውን ትውልድ እናፍራ! @noahtoael for anything https://telega.io/c/Noahtoaels_Idea I blog about marketing and sales Buy ads: https://telega.io/c/Noahtoaels_Idea
Mostrar más3 383
Suscriptores
+324 horas
+137 días
+8330 días
Archivo de publicaciones
3 383
በመኖር በኩል
ደራሲ፦አድሃኖም ምትኩ
ክፍል አንድ
:
:
እውቀት
አባቴ የሚመላለስባት ሴተኛ አዳሪ እንዳለችው አወኩ። ፕሪፕ አራት ኪሎ ዳግማ ሚኒሊክ ነበር የተማርኩት ፍሬንዶቼ አራት ኪሎ ልጆች ነበሩ። ለትምህርትም ለጥናትም አራት ኪሎ ነበር የምንውለው። ብርሃን እና ሰላም መውጫና መውረ አንድ ቀጭን አስፋልት አለች መደዳውን ብዙ ሸሌዎች አሉ፤ ተሸንሽነው ከተደረደሩ ትናንሽ ቤቶች ውስጥ አመሻሽ ላይ በራቸውን ከፍተው የሚቆሙ መጋረጃ የሚጋረዱ በራሳቸው ላይ የሚያጨሱ ለሀላፊ አግዳሚ ጭናቸውን እያስጎበኙ ለማማለል የሚሞክሩ። እድሜያቸው የገፋ አፍላ ኮረዳዎች የግንባራቸውን ንቅሳት በስታይል የከለሉ ሜካፕ የተለቀለቁ የሚያምሩ ትንሽ የሚያምሩ ፉንጋ ሴቶች በየበሩ ይከለኮላሉ። አስታውሳለሁ ማክሰኞ ነበር 12 ሰዓት ላይ አባቴን አየሁት ከሽንሽን ቤቶቹ ወደ አንደኛው ሲገባ አላመንኩም ፈዘዝኩ አባቴ መሆኑ የገባኝ ካፊያ ጣለ አልጣለ ብሎ በሚለብሰው ቡኒ ጅልግ ያለ ጃኬት እና ትልቅዬ አስር ሰው ማስጠለል በሚችለው ዣንጥላው ነው ከጓደኞቼ ጋር በሚገቡት በሚወጡት ወንድ አዳሪዎች ላይ ሙድ ስለምንይዝ እሱ እንዳይሆን ፈራው። እራሱ ነው በተደጋጋሚ ሲገባ አየሁት እንደ ሌባ ወደ ኋላ ወደፊት ሳያይ ይገባል ትንሽ እንኳን ፈራ ተባ አይልም። ምናልባት ስለ ደጋገመው መሳቀቁን ረስቶት ይሆናል። ለእናቴ ተቆርቁሬ አቄምኩበት። እናቴ ስትምል እንኳን ይመር ይሙት ብላ ነው። በስሙ የምትምልበት ባሏ ይህንን አደረገ ቢሏት ምን ትል ይሆን? አባቴን የማይረባ ቦታ ስላየሁት አዘንኩ። አሻቅቤ አይቼው ታዘብኩት። አባት እንደዚህ አይነት አወዳደቅ ሲወድቅ ማየት መሰረት ይነዳል። አባት ሲመክር ሲጠቁም ነው ወጉ። አባቴ ደበረኝ። እናቴ ወገቤን፣ ቆሽቴን፣ ጀርባዬን፣ ጎኔን ስለምትል ነው ሌላ ሴት ጋር የሚሄደው? አመመኝ ስትል የሚሆነው ሁሉ እያስመሰለ ነበር ማለት ነው? ስለማይወዳት ነው? ስለማያከብራት ነው ሴተኛ አዳሪ ቅምጥ የሚይዘው? ቤታችን ውስጥ አባቴን ከምንም የማልቆጥረው ብቸኛ ሰው እኔ ሆንኩኝ። ሊቆጣኝ ከቃጣው ገላምጠዋለሁ መንገድ ስንገናኝ እንዳላየሁት እሆናለሁ እሱ ካለ አላወራም ወይም ሲያወራ አልሰማውም። የሆነ ቀን የአባቴን ቅመጥ ሴተኛ አዳሪ ስትሰዳደብ አየኋት አሙጥሙጣ ስትሰዳደብ ትክ ብዬ አየኋት። መርጦ ነው ቂጠ ግብዳዋን አሮጊቷን ፉንጋዋን ፈላጊ የሌላትን የወሸማት "ባታስከፍለው ነው በሱ ደሞዝ በቋሚነት የወሸማት አልኩኝ፡፡ አባቴን ወንድሞቼና እህቴ ያከብሩታል፡፡ ሲመርቃቸው አሜን ይላሉ፡፡ ደሞ ሴሰኛ ሰውዬ ለሚስቱ የማይታመን ለልጆቹ አርአያ የማይሆን መረቀኝ አልመረቀኝ ምን ሊጎልብኝ እላለው በልቤ፡፡ እኔ ውስጥ የተፈጠረውን የጥላቻ ስሜት አይቼ ለእህቴም ሆነ ለወንድሞቼ ለመናገር ድፍረት አጣሁ። በዚህም ብልግናውን ስለሸፈንኩለት እራሴን እንደባለ ውለታው ቆጠርኩ። ከአባቴ ጋር መነጋገር አቆምን። ሊያወራኝ ሲሞክር ልቤ ተቆለፈ። ልቤ ላይ የሌለ ክብር ከየት አመጣለሁ? የሆነ ስራ እንዳግዘው እንድሰራለት ካዘዘኝ በልበ ሙሉነት እንደማልችል ነግረዋለው። ድንገተኛ አቀያየሬን እንደ ጉርምስና ቁጥሮ ይሁን ወይ ጉዱን እንዳየሁበት ገብቶት አልተቆጣኝም። እንደውም የበለጠ ትሁት ለመምሰል ሞከረ። ይሄም የበለጠ ያናድዳል። ገመናቸውን ያወቅንባቸው ሰዎች ድራማ ለመስራት ሲሞክሩ ይቀፋል። በዝምታ እና ክብር በመንሳት ቀጣሁት። የሆነ ቀን ከመሰላል ላይ ወድቆ ሃኪም ቤት ተጣድፈን ወሰድነው። አይኑ እኔ ላይ ነበር። አባት አይደል? አሳድጎኝ የለ ከዛ ሁኔታ በፊት የሆነልኝን አውቃለሁ። አባቴ አባትም ነበር። እንደ ወንድሞቼ እንደ እህቴ አይሆን እንጂ እንደ እናቴ አይሆን እንጂ ትንሽ አዘንኩ። ከቀን ወደ ቀን አልተሻለውም። ጭንቅላቱ ላይ ደም ፈሰሰ አሉ። ሰርጀሪ ይሰራ ተባለ። ፈቀድን ተሰራ። ከአራት ቀን በኋላ ማዘርም፣ ሲስተርም፣ ወንድሞቼም ስላልነበሩ ብቻዬን እየጠበቅኩት ነርሶቹ አንድ መድሃኒት ያስፈልጋል ገዝተህ ና ብለውኝ ልገዛ ወጣሁ። ብዙ አልፋሁም። ሁለት ሶስት ቦታ እንደገባው መድሃኒቱን አገኘሁ። አቅራቢያው ካገኘሁት ካፌ ቡና ጠጥቼ ሳልጣደፍ ተመለስኩ። እናቴም ወንድሞቼም እህቴም መተው ነበር። ነገር ግን አባቴ በህይወት አልነበረም። በዚህ ቅጽበት ይሞታል ብዬ አስቤ አላውቅም። በልቤ የነበረው ቂም ባዶ ሆነብኝ። እጄን ጭንቅላቴ ላይ አድርጌ እንባዬ ዝም ብሎ እየፈሰሰ አባቴ አባቴ ብዬ አለቀስኩ። ስምህን ሲጣራ ነበር አሉ። ምን ሆኖ ነው የራቀኝ? ለምንድነው ያኮረፈኝ? ለምንድነው የተለወጠብኝ? እያለ ስምህን እየጠራ ቃዠ አሉኝ። ቤታችንን ሃዘን ዋጠው። ሁሉም ተሰበሩ። እናቴ የኔ አገልጋይ፣ ብርሃኔ፣ አጋዤ ልጅነቴ እያለች አለቀሰች። አባቴ አይደል አሳዝኖኛል ምን አለ ብልግናውን ባላየው ኖሮ ምናለ ባላቄምበት ብያለሁ። እውቀት አይደል ትካዜን የሚያበዛው እንደዛ እለት ማወቄን የጠላሁበት ጊዜን አላስታውስም። ደስታን የሚነጥቅ እውነት ምን ያደርጋል። አባቴ ባለፈ በሶስተኛው ቀን ነጠላ የለበሰች አንድ ግብዳ ሴት ለያዥ ለገናዥ እያስቸገረች ወንድሜ ወንድሜ እያለች እያበደች ቤታችን ገባች። የተሰቀለውን ፎቶ ስታይ ከተነጠፈው ምንጣፍ ላይ ተንከባለለች እንደ አዲስ አባቴ አባቴ ተባለ። አሁንም እንደገና አንባዬ እየፈሰሰ አባቴን አስነፈቀኝ። መቼስ አባቴ አይደለም የመጨረሻዋ ሰአት ስትመጣ ከእውነት ውለታ ይበልጥ የለ። በደንብ ሳየው አውቃታለሁ ሴተኛ ዳሬዋ ነች አባዬ የሚመላለስባት ቅምጡ። ጥይፍ አልኩ። ይህቺ ነች እንዳዲስ ሆድ ያስባሰችኝ። ብልግናችን ለምን አልተሰማም ለምን ገመና ሆነ ነው?
ይቀጥላል
3 383
"በማዕበል መሀል እንዳለች ታንኳ ልብህ በጭንቀት ስትናወጥ፣ ማዕበሉን ጸጥ ማድረግ ወደሚችለው ወደ ክርስቶስ ፊት ቅረብ። ጭንቀትህ የቱንም ያህል ከባድ ቢሆን፣ የእግዚአብሔር ቸርነት ግን ከዚያ ይበልጣል። እርሱ ስለ አንተ የሚያስብ አባት ነውና ነገ ምን እሆናለሁ ብለህ አትጨነቅ፤ የዛሬን ቀን የሰጠህ አምላክ የነገውንም ማዕበል በጥበቡ ያሳልፈዋል። ብዙ ጊዜ የምንጨነቀው ሁሉንም ነገር በራሳችን አቅም ለመወጣት ስንሞክር ነው፤ ነገር ግን ሸክምህን በጸሎት ወደ እርሱ ስትጥለው፣ እርሱ በልብህ ውስጥ ሰላምን ያሳድራል። ቅዱሳን ሐዋርያት በዓለም ሳሉ ብዙ መከራና ጭንቀት ገጥሟቸዋል፤ ነገር ግን ልባቸው አልፈራም፤ ምክንያቱም ከእነርሱ ጋር ያለው ጌታ ከዓለም ሁሉ እንደሚበልጥ ያውቁ ነበርና። አንተም ዛሬ ሸክምህን ለእርሱ ስጥ፤ እርሱ ደግሞ ዕረፍትን ይሰጥሃል።"
(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
3 383
Repost from ዘ ተ ሐ ር ያ ን 🧘🏻♂️
የባከነ ጊዜ!
“በአንድ በሚፈስ ወንዝ ውስጥ ከአንድ ጊዜ በላይ ማቋረጥ አትችልም” ይባላል፡፡ እውነት ነው!
ይህ አባባል ሲተነተን፣ አሁን በእግሮችህ ተራምደህ የገባህበት ወንዝ አልፏል፡፡ ስትገባበት የነበረው ውኃ ቀጥሎ ለሚፈስሰው ውኃ ስፍራውን ለቆ በመሄዱ ምክንያት ተመልሰህ ብታቋርጥ ሌላ ውኃ ነው የምታገኘው፡፡ ወንዙ አንድ ነው፣ ውኃው ግን የተለያ ነው፡፡ ፍሰቱ ተመሳሳይ ነው፣ ወንዙ ይዞት የሚመጣው ነገር ግን የተለያየ ነው፡፡ የአፈሳሰሱ ሂደት ያው ነው፣ የፈሰሰው የውኃው አካል ግን ሌላ ነው፡፡
የጊዜያችንም ጉዳይ እንደዚሁ ነው፡፡
⏱️ የሰዓታት፡- ነግቶ እስኪመሽ የሚመጡትና የሚሄዱት ሰዓታት በተመሳሳይ ስም ይጠራሉ፣ ይዘውት የሚመጡትና ይዘውት የሚሄዱት ምርጫ ግን የተለያየ ነው፡፡
⏱️ የቀናት፡- ከሰኞ እስከ እሁድ ያሉን ቀናት በስም ተመሳሳይ ናቸው፣ ይዘው መጥተው የሚያሳልፉት እድል ግን ልዩ ልዩ ነው፡፡
⏱️ የወራት፡- በየሰላሳ ቀናት የሚቀያየሩት ወራቶች መምጣትና መሄድ አንድ አይነት ነው፣ እነሱም ቢሆኑ ደግሞ የማይገኝ እድልን ይዘው መጥተው ጥርግ ብለው ይሄሉ፡፡
ጊዜ እንዲህ ነው! ሲመጣና ሲሄድ ያለው “አንድ አይነትነት” ያታልላል፡፡ የምንባንነው በወቅቱ ማድረግ የምንችለውን ነገር ማድረግ የማንችልበት ቀን ከመጣና ኋላ ከቀረን በኋላ ነው፡፡
ዶክተር እዮብ ማሞ
3 383
Repost from ዘ ተ ሐ ር ያ ን 🧘🏻♂️
ከሁሉም ነገር ተመችቷቹ አትደርሱም
ትንፋሽ አጥሯቹ ጉልበት ክዷቹ
ደክሟቹ ተዝለፍልፋቹ ነው የምትደርሱት
እንዲሁ የምንደርስበት ነገር የለም
ልማር ቢሉት ያው ነው ላስተምር ቢሉት ያው ነው
ልመንን ቢሉት ያው ነው ቢያገቡም ያው ነው
ቢነግዱም ያው ነው
ምንድነው ተራራ ያልሆነ ነገር???
የሰው ህይወቱ በዚህች ምድር ላይ
ብርቱ ሰልፍ ነው፣. . . ሰልፍ ውጊያ ነው፣
ከአጋንንት እና ከዚህ አለም አኗኗር ጋር ይዋጋል የሰው ልጅ፣
ስለዚህ ያንን አውቀን የምንኖረው ነው
አባ ገ/ኪዳን
3 383
ተፈታሁ!!
ሰዎች «ተለወጠ» አሉኝ፤ እኔ ግን ከእውነተኛው የራሴ እድፍ እንደነጻሁ አውቃለሁ። የትም ለማልደርሰው ስጣደፍ ነው የኖርኩት። እሮጣለሁ ሁሉንም ካልያዝኩ ያመለጠኝ ይመስለኛል። ያየሁትን ሁሉ ለማግኘት እቆፍራለሁ።ሌላ ሳይ የጀመርኩትን ትቼ ሌላውን አሳድዳለሁ። አእምሮዬ በተተበተቡ ድሪቶዎች ነው የተሞላው።የማይጠቅሙኝ መረጃዎች የማያስፈልጉኝ እቃዎች አደርጋቸዋለሁ እያልኩ ሳንሸራትታቸው በኖሩ እቅዶች ሁሉ ህይወቴ ውክብክብ ያለ ነበር ።ሁሉም የማደርገው ነገር አንገብጋቢ፣ አስፈላጊ ይመስለኝ ነበር ....
እቅድ በየቀኑ አወጣለሁ......
ጠረንቤዛዬ ላይ አነባቸዋለሁ እያልኩ የተዋስኳቸው መፅሀፎች፣የሆነ ቀን ይጠቅመኛል ብዬ ያኖርኳቸው...
እስክገዛው ድረስ 'አንገብጋቢ ነው' ያልኩት ከገዛሁት ሳምንት በኃላ ችላ ያልኩት እቃ....ግዜ ሲኖረኝ አደርገዋለሁ ያልኩት ነገር...
ቤቴ ብዙ ነገሩ ለመስራት ባዘጋጀኋቸው፣ ጀምሬ በተውኳቸው እና እንዳሉኝ በዘነጋውት ነገሮች ተሞልቷል....
ከምሰራው የምሞክረው ይበልጣል ፣ ከምተገብረው የማቅደው ይበዛል፣
ጥሩ ሰው ለመባል የምጥረው ጥሩ ከማደረገው ይበልጣል..... ከራሴ እርቄ የምጋጋጠው የታይታ ህይወቴ ቢዚ አድርጎኛል። አለው ማለት ብቻ ነበረ ኑሮዬ።
በዚ መሀል ደንገት ሰው ገጭቼ ዘብጥያ ወረድኩ ።
እስርቤትም የመጀመርያ ሰሞን አዲስነቱና አብሮነቱ ወከባ ነበር።በኋላ ግን በሆነ በተከለለ አጥር ውስጥ ከድብርት ጋር ተፋጠጥኩ...ከውጪው ዓለም ጋር ተለያየሁ።አሁን የምቸኩልለት የሚያጣድፈኝ እንደዛ የምንከወከውለት ጉዳይ ሁሉ ከአይምሮዬ ጠፋ
ከድብርቴ ስወጣ እርግት ስል ታወቀኝ።ስመገብ ስራመድ ስቀመጥ ሁሉ እኔና እኔ ብቻ ሆንን።የአምናውን ያን እኔን አየሁት።
እራስን እንደመቀየም አይነት ከባድ ስሜት ያለ አይመስለኝም !! ውስጥ በነበርኩበት ሰአት የድሮ ማንነቴን ሳስታውስ እራሴን ታዘብኩት።ነገሮች እንደዛው የሚቀጥሉ ...ሁሌ ደህንነት ሁሌ ገንዘብ ማግኘት ሁሌ ከጓደኞች ጋር መዝናናት ሁሌ ጤና ብቻ እንደሆነ የሚቀጥል ነበረ የሚመስለኝ።
ካልገመቱት እውነታ ጋር እንደመፋጠጥ አሳዛኝ ነገር የለም!
ጭንቅላት ውስጥ የፈጠሩትን ዓለም እንደማጣት አይነት ህመም የለም !
አክብደው የሚያዩትን ነገር ተራ ሆኖ እንደማግኘት ግራ የሚያጋባ ነገር የለም!
አውቀዋለሁ ያሉትን ነገር አለማወቅ አይነት አስፈሪ ነገር የለም !
እስርቤት ብቻዬን ስቆዝም በመታሰሬ አዝኜ መስሏቸው ነበር። እኔ ግን ያስደነገጠኝ የመጣሁትን መንገድ ስመለከት ነበረ።
የኖርኩትን ህይወት ሰከንድ ሳይቀር መዝግበዉ እንደሰጡኝ አይነት ነው ራሴን አገላብጬ ያየሁት ....
የማይረባ ማንነታችንን እርቃኑን ለመጀመርያ ግዜ ማየት እንዴት ያሳዝናል!!
የመጡበትን መንገድ ሲመለከቱ እርባና ቢስነቱ እንዴት ያስለቅሳል!!
ገነባሁ ያልኩት ነገር ሁሉ የገለባ ክምር ሆኖ አየሁት።የሄደው የማይመለሰው ጊዜ ቆጨኝ።
ከቆይታ በኋላ ተፈታሁ።ስፈታ ከዚ በፊት የኖርኩበት መንገድ ተቀይሯል።ጨለማው ውስጥ ያገኘሁት እኔ ያሳዝን ነበር….
ሰነፍ ነበር ጠንካራ አልነበረም….
የዋህ ነበር ስሜቱን ዋጥ ማድረግ …. የተሰማውን አለመናገር አይችልም ነበር። ከእስር ስወጣ የድሮ ማንነቴ ሞቶ ነበር።ስፈታ ስታሰር የነበርኩትን ያንን እኔን ጥዬው ወጣሁ።
ዛሬ ተፈታሁ!!❤️
3 383
ተፈታሁ!!
ሰዎች «ተለወጠ» አሉኝ፤ እኔ ግን ከእውነተኛው የራሴ እድፍ እንደነጻሁ አውቃለሁ። የትም ለማልደርሰው ስጣደፍ ነው የኖርኩት። እሮጣለሁ ሁሉንም ካልያዝኩ ያመለጠኝ ይመስለኛል። ያየሁትን ሁሉ ለማግኘት እቆፍራለሁ።ሌላ ሳይ የጀመርኩትን ትቼ ሌላውን አሳድዳለሁ። አእምሮዬ በተተበተቡ ድሪቶዎች ነው የተሞላው።የማይጠቅሙኝ መረጃዎች የማያስፈልጉኝ እቃዎች አደርጋቸዋለሁ እያልኩ ሳንሸራትታቸው በኖሩ እቅዶች ሁሉ ህይወቴ ውክብክብ ያለ ነበር ።ሁሉም የማደርገው ነገር አንገብጋቢ፣ አስፈላጊ ይመስለኝ ነበር ....
እቅድ በየቀኑ አወጣለሁ......
ጠረንቤዛዬ ላይ አነባቸዋለሁ እያልኩ የተዋስኳቸው መፅሀፎች፣የሆነ ቀን ይጠቅመኛል ብዬ ያኖርኳቸው...
እስክገዛው ድረስ 'አንገብጋቢ ነው' ያልኩት ከገዛሁት ሳምንት በኃላ ችላ ያልኩት እቃ....ግዜ ሲኖረኝ አደርገዋለሁ ያልኩት ነገር...
ቤቴ ብዙ ነገሩ ለመስራት ባዘጋጀኋቸው፣ ጀምሬ በተውኳቸው እና እንዳሉኝ በዘነጋውት ነገሮች ተሞልቷል....
ከምሰራው የምሞክረው ይበልጣል ፣ ከምተገብረው የማቅደው ይበዛል፣
ጥሩ ሰው ለመባል የምጥረው ጥሩ ከማደረገው ይበልጣል..... ከራሴ እርቄ የምጋጋጠው የታይታ ህይወቴ ቢዚ አድርጎኛል። አለው ማለት ብቻ ነበረ ኑሮዬ።
በዚ መሀል ደንገት ሰው ገጭቼ ዘብጥያ ወረድኩ ።
እስርቤትም የመጀመርያ ሰሞን አዲስነቱና አብሮነቱ ወከባ ነበር።በኋላ ግን በሆነ በተከለለ አጥር ውስጥ ከድብርት ጋር ተፋጠጥኩ...ከውጪው ዓለም ጋር ተለያየሁ።አሁን የምቸኩልለት የሚያጣድፈኝ እንደዛ የምንከወከውለት ጉዳይ ሁሉ ከአይምሮዬ ጠፋ
ከድብርቴ ስወጣ እርግት ስል ታወቀኝ።ስመገብ ስራመድ ስቀመጥ ሁሉ እኔና እኔ ብቻ ሆንን።የአምናውን ያን እኔን አየሁት።
እራስን እንደመቀየም አይነት ከባድ ስሜት ያለ አይመስለኝም !! ውስጥ በነበርኩበት ሰአት የድሮ ማንነቴን ሳስታውስ እራሴን ታዘብኩት።ነገሮች እንደዛው የሚቀጥሉ ...ሁሌ ደህንነት ሁሌ ገንዘብ ማግኘት ሁሌ ከጓደኞች ጋር መዝናናት ሁሌ ጤና ብቻ እንደሆነ የሚቀጥል ነበረ የሚመስለኝ።
ካልገመቱት እውነታ ጋር እንደመፋጠጥ አሳዛኝ ነገር የለም!
ጭንቅላት ውስጥ የፈጠሩትን ዓለም እንደማጣት አይነት ህመም የለም !
አክብደው የሚያዩትን ነገር ተራ ሆኖ እንደማግኘት ግራ የሚያጋባ ነገር የለም!
አውቀዋለሁ ያሉትን ነገር አለማወቅ አይነት አስፈሪ ነገር የለም !
እስርቤት ብቻዬን ስቆዝም በመታሰሬ አዝኜ መስሏቸው ነበር። እኔ ግን ያስደነገጠኝ የመጣሁትን መንገድ ስመለከት ነበረ።
የኖርኩትን ህይወት ሰከንድ ሳይቀር መዝግበዉ እንደሰጡኝ አይነት ነው ራሴን አገላብጬ ያየሁት ....
የማይረባ ማንነታችንን እርቃኑን ለመጀመርያ ግዜ ማየት እንዴት ያሳዝናል!!
የመጡበትን መንገድ ሲመለከቱ እርባና ቢስነቱ እንዴት ያስለቅሳል!!
ገነባሁ ያልኩት ነገር ሁሉ የገለባ ክምር ሆኖ አየሁት።የሄደው የማይመለሰው ጊዜ ቆጨኝ።
ከቆይታ በኋላ ተፈታሁ።ስፈታ ከዚ በፊት የኖርኩበት መንገድ ተቀይሯል።ጨለማው ውስጥ ያገኘሁት እኔ ያሳዝን ነበር….
ሰነፍ ነበር ጠንካራ አልነበረም….
የዋህ ነበር ስሜቱን ዋጥ ማድረግ …. የተሰማውን አለመናገር አይችልም ነበር። ከእስር ስወጣ የድሮ ማንነቴ ሞቶ ነበር።ስፈታ ስታሰር የነበርኩትን እኔን ጥዬው ነው የወጣሁት።
ዛሬ ተፈታሁ!!❤️
3 383
ተፈታሁ!!
ሰዎች «ተለወጠ» አሉኝ፤ እኔ ግን ከእውነተኛው የራሴ እድፍ እንደነጻሁ አውቃለሁ። የትም ለማልደርሰው ስጣደፍ ነው የኖርኩት። እሮጣለሁ ሁሉንም ካልያዝኩ ያመለጠኝ ይመስለኛል። ያየሁትን ሁሉ ለማግኘት እቆፍራለሁ።ሌላ ሳይ የጀመርኩትን ትቼ ሌላውን አሳድዳለሁ። አእምሮዬ በተተበተቡ ድሪቶዎች ነው የተሞላው።የማይጠቅሙኝ መረጃዎች የማያስፈልጉኝ እቃዎች አደርጋቸዋለሁ እያልኩ ሳንሸራትታቸው በኖሩ እቅዶች ሁሉ ህይወቴ ውክብክብ ያለ ነበር ።ሁሉም የማደርገው ነገር አንገብጋቢ፣ አስፈላጊ ይመስለኝ ነበር ....
እቅድ በየቀኑ አወጣለሁ......
ጠረንቤዛዬ ላይ አነባቸዋለሁ እያልኩ የተዋስኳቸው መፅሀፎች፣የሆነ ቀን ይጠቅመኛል ብዬ ያኖርኳቸው...
እስክገዛው ድረስ 'አንገብጋቢ ነው' ያልኩት ከገዛሁት ሳምንት በኃላ ችላ ያልኩት እቃ....ግዜ ሲኖረኝ አደርገዋለሁ ያልኩት ነገር...
ቤቴ ብዙ ነገሩ ለመስራት ባዘጋጀኋቸው፣ ጀምሬ በተውኳቸው እና እንዳሉኝ በዘነጋውት ነገሮች ተሞልቷል....
ከምሰራው የምሞክረው ይበልጣል ፣ ከምተገብረው የማቅደው ይበዛል፣
ጥሩ ሰው ለመባል የምጥረው ጥሩ ከማደረገው ይበልጣል..... ከራሴ እርቄ የምጋጋጠው የታይታ ህይወቴ ቢዚ አድርጎኛል። አለው ማለት ብቻ ነበረ ኑሮዬ።
በዚ መሀል ደንገት ሰው ገጭቼ ዘብጥያ ወረድኩ ።
እስርቤትም የመጀመርያ ሰሞን አዲስነቱና አብሮነቱ ወከባ ነበር።በኋላ ግን በሆነ በተከለለ አጥር ውስጥ ከድብርት ጋር ተፋጠጥኩ...ከውጪው ዓለም ጋር ተለያየሁ።አሁን የምቸኩልለት የሚያጣድፈኝ እንደዛ የምንከወከውለት ጉዳይ ሁሉ ከአይምሮዬ ጠፋ
ከድብርቴ ስወጣ እርግት ስል ታወቀኝ።ስመገብ ስራመድ ስቀመጥ ሁሉ እኔና እኔ ብቻ ሆንን።የአምናውን ያን እኔን አየሁት።
እራስን እንደመቀየም አይነት ከባድ ስሜት ያለ አይመስለኝም !! ውስጥ በነበርኩበት ሰአት የድሮ ማንነቴን ሳስታውስ እራሴን ታዘብኩት።ነገሮች እንደዛው የሚቀጥሉ ...ሁሌ ደህንነት ሁሌ ገንዘብ ማግኘት ሁሌ ከጓደኞች ጋር መዝናናት ሁሌ ጤና ብቻ እንደሆነ የሚቀጥል ነበረ የሚመስለኝ።
ካልገመቱት እውነታ ጋር እንደመፋጠጥ አሳዛኝ ነገር የለም!
ጭንቅላት ውስጥ የፈጠሩትን ዓለም እንደማጣት አይነት ህመም የለም !
አክብደው የሚያዩትን ነገር ተራ ሆኖ እንደማግኘት ግራ የሚያጋባ ነገር የለም!
አውቀዋለሁ ያሉትን ነገር አለማወቅ አይነት አስፈሪ ነገር የለም !
እስርቤት ብቻዬን ስቆዝም በመታሰሬ አዝኜ መስሏቸው ነበር። እኔ ግን ያስደነገጠኝ የመጣሁትን መንገድ ስመለከት ነበረ።
የኖርኩትን ህይወት ሰከንድ ሳይቀር መዝግበዉ እንደሰጡኝ አይነት ነው ራሴን አገላብጬ ያየሁት ....
የማይረባ ማንነታችንን እርቃኑን ለመጀመርያ ግዜ ማየት እንዴት ያሳዝናል!!
የመጡበትን መንገድ ሲመለከቱ እርባና ቢስነቱ እንዴት ያስለቅሳል!!
ገነባሁ ያልኩት ነገር ሁሉ የገለባ ክምር ሆኖ አየሁት።የሄደው የማይመለሰው ጊዜ ቆጨኝ።
ከቆይታ በኋላ ተፈታሁ።ስፈታ ከዚ በፊት የኖርኩበት መንገድ ተቀይሯል።ጨለማው ውስጥ ያገኘሁት እኔ ያሳዝን ነበር….
ሰነፍ ነበር ጠንካራ አልነበረም….
የዋህ ነበር ስሜቱን ዋጥ ማድረግ …. የተሰማውን አለመናገር አይችልም ነበር። ከእስር ስወጣ የድሮ ማንነቴ ሞቶ ነበር።ስፈታ ስታሰር የነበርኩትን እኔን ጥዬው ነው የወጣሁት።
ዛሬ ተፈታሁ!!❤️
3 383
Repost from ዘ ተ ሐ ር ያ ን 🧘🏻♂️
private ነገር ይኑርህ. . .
እንደምታስበው ሁሉም ሰው ባንተ ነገር ደስተኛ የሆነ አይምሰልህ. . . ላንተ ተኝቶ የማያድር ብዙ ሰው አለ. . . እና ለምን ብለህ ነው ሁሉንም ነገርህን ምታሳየው man. . . በR/ship'ም እንደዛ ነው እስቲ ዝም ብለህ tiktok or ሌላ social media ላይ ድሮ ሲያስቀኑን የነበሩ couples አሁን የት እንዳሉ ተመልከት. . . ለምን ይመስልካል??
የሰው አይን ከምታስበው በላይ አደገኛ ነው . . . ድጋሚ ማንንም ሰው እንዳታምን አድርጎክ ነው ሚጎዳክ. . . ምንም ነገር ስትጀምሩ ፈጣሪን አስቀድሙ እርሱ አሳምሮ ይሰጣቹሀል።
ዝም ብለህ ስራ. . . ማንም የማይገምተው ሰው ሁን. . .
ያኔ ካንተ በላይ አሸናፊ አይኖርም
3 383
Repost from ዘ ተ ሐ ር ያ ን 🧘🏻♂️
አንዳንድ ጊዜ ሰው ብቻውን የሚቀርበት ቀን አለ ብቻውን የሚቀርበት ቀን ማለት ነው ምንም. . . አንተን እኔ ሞቼም አልተውህም ያለህ ሰው ሁሉ ምንም. . . የሰው ልጅ የልፋቱን ዋጋ እግዚአብሔርን ካደረገ ሰው ምንም ይንሳው በሰላም ይኖራል በዚህ አለም ከባዱ ነገር ልብን ሰላም ማድረግ ነው ከሰው ጋር በሰላም ለመኖር መቼም ዋሽቶም ቀጥፎም አስመስሎም ይ'ኖራል፣ ልብን ሰላም ለማድረግ ግን ዋሽቶም ቀጥፎም አስመስሎም ማረግ አይቻልም. . .
ልብን ሰላም ለማድረግ እግዚአብሔርን ዋጋ ማድረግ ነው
አባ ገ/ኪዳን
3 383
Repost from ዘ ተ ሐ ር ያ ን 🧘🏻♂️
🌿✨ መልካም አዲስ ዓመት! ✨🌿
አዲሱ ዓመት የሰላም፣ የጤና፣ የደስታ፣ የፍቅርና የበረከት ዓመት ይሁንልን።
ያለፈው ዓመት ያስተማረንን ትምህርት ይዘን፣ አዲሱን ዓመት በተስፋ፣ በእምነትና በአዲስ
●ጉልበት እንቀበል።
●ምኞታችሁ ይሳካ፣
●ስኬታችሁ ይበዛ፣
●ፍቅራችሁ ይጠና፣
●ቤታችሁ በሰላም ይሞላ፣
እያንዳንዱ ቀንም ከቀድሞው የተሻለ ይሁን።
እንኳን ለ2019 ዓ.ም. አዲስ ዓመት በሰላምና በጤና አደረሳችሁ! 🎉
3 383
Repost from ዘ ተ ሐ ር ያ ን 🧘🏻♂️
"እወድሀለው" ብላኝ በረጅሙ ተነፈሰች. . . አተነፋፈሷ ዜማ ነበረው ዘወትር ሊሰሙት እንደሚናፍቁት አይነት አንዳንዴ ምን የሙዚቃ መሳርያ ትወዳለህ ሲሉኝ የእሷ ትንፋሽ ማለት ይቃጣኛል. . . እነዛ እንቧይ የሚያክሉ እይኖቿን አይኔ ላይ ተክላ "ዝም አልክ እኮ እ. . ." ስትለኝ "እኔም" ብዬ አንገቴን ደፋው ከዛች እለት ጀምሮ "እኔም" ተተርጉማ ሌላ መልክ ያዘች የመውደዴ ጥግ ተለካበት. . . ተመዘነበት ወደቅሁ. . . አንዳንዴ በዚህች ቃል ተረግሜ ነው የፍቅር አድባር የሸሸኝ እላለሁ. . .
3 383
Repost from ጥንቅሻ✍🏼🦋
ቢልልኝ ብዬ እንጂ
ነገ የኔ ቢሆን
.
.
እስከሚሰፍርልኝ
.
እዛ የዘነበው ፣ለኔ ቢያካፋልኝ
ይሀው እፈጋለሁ
ሲበላ ሲጠጣ
ከዳር ሁኜ እያየሁ....
3 383
"በ18ኛው ክፍለ ዘመን በፈረንሳይ ውስጥ ድንገት አንድ የሚያስፈራ ነገር ተከሰተ። የከተማዋ ቆንጆ ወጣት ሴቶች አስከሬን ለምን እና እንዴት እንደሞቱ እንኳን ሳይታወቅ ጸጉራቸው በሙሉ ተላጭቶና እርቃናቸውን ተደርገው በየመንገዱ ወድቀው መገኘት ጀመሩ። ዘመኑ ሽቶ በጣም ተወዳጅ እና ተፈላጊ የሆነበት ጊዜ ነው። በዚ ወቅት ነበር አንድ ከተፈጥሮ በላይ የሆነ የማሽተት እና የማንኛውንም ነገር ጠረን የመለየት ብቃት ያለው ልጅ የተወለደው። ነገር ግን እናቱ በከፋ ድህነት የምትኖር እና ከዚ በፊትም የወለደቻቸው ልጆች ተወልደው በህይወት ባለመቆየታቸው ይሄኛውም የማይቆይ መስሏት እንብርቱን ቆርጣ ከምትሰራበት ጠረንቤዛ ስር ትደብቀዋለች። ይሄኛው ልጅ ግን ፍጹም የተለየ ነበር። ገና እንደተወለደ ያከባቢውን ሽታ መለየት ጀመረ። ለመጀመሪያ ጊዜ ሲያለቅስ በገበያው ውስጥ ያለ ሰው ሁሉ ሰምቶ ሲሰበሰብ እናትዬው ታመልጣለች። በዚህም ልጇን ለመግደል ሞክራለች ተብላ የሞት ፍርድ ይፈረድባትና ህጻኑ ወላጅ አልባ ልጆችን ለምታሳድገው ማዳም ጋላርድ ለተባለች ሴት ተሰጠ። ጋላርድ ከሌሎች ልጆች ጋር ትቀላቅለዋለች። አንድ ልጅ ህጻኑ በተኛበት በጣቱ ሊነካው ሲል በድንገት ጣቱን አጥብቆ በመያዝ ያሸተዋል። ልጆቹ እሱን መንከባከብ የነሱ ሃላፊነት እንደሆነ ሲያውቁም በትራስ አፍነው ሊግድሉት ሲሉ ማዳም ጋላርድ መጥታ አዳነችው። ዓመታት አልፈው ዕድሜው አምስት ዓመት ቢሆንም ዣን መናገር አልቻለም። ሌሎቹ ልጆች በተፈጥሮው እና በሚያደርጋቸው ነገሮች እንደ ጤነኛ ስለማይቆጥሩትይሸሹት ነበር። ስለዚህ ዣን ጊዜውን በልዩ የማሽተት ችሎታው ሲዝናና እና አዳዲስ መአዛዎችን በመፍጠር ያሳልፋል። እረጅም እርቀት ላይ ያለን ወይም ሊሸት የማይችል ነገር ቢሆን እንኳ የትኛውንም ሽታ የመለየት እና የማሽተት ችሎታ ነበረው። ዕድሜው 13 ሲሆን እና መናገር ሲጀምር ማዳም ጋላርድ በማሳደጊያ ውስጥ ቦታ ስላልነበራት ዣንን ግሪማል ለሚባል የቆዳ ፋብሪካ ባለቤት ሸጠችው። ዣን በቆዳ ፋብሪካው ውስጥ በየቀኑ ከባድ ስራ ሲሰራና ሲላላክ ይውላል።ነገር ግን አንድ ቀን ወደ ከተማ ሄዶ አዳዲስ ሽታዎችን ለማሽተት ይመኝ ነበር።
ይቀጥል ካላቹ react ❤️
3 383
ድሮ በአንድ ትልቅ ተራራ ግርጌ ላይ የሚኖሩ፣ ጎን ለጎን የተቀመጡ ሁለት በጣም ግዙፍና ውብ የዓለት ድንጋዮች ነበሩ።
ሁለቱም ድንጋዮች ጠንካራና የብዙ ዘመናት ታሪክ ያላቸው ነበሩ። አንድ ቀን በዓለም ታዋቂ የሆነ አንድ የቅርጻ ቅርጽ ባለሙያ ወደዚያ ተራራ መጣ።
ድንጋዮቹን ሲያይ በጣም ተደሰተና ከእነዚህ ድንጋዮች በአንዱ ላይ በዓለም ላይ እጅግ አስደናቂ የሆነ የንጉሥ ሃውልት እሰራበታለሁ ብሎ ወሰነ።
ባለሙያው መዶሻውንና መቅረጫውን አውጥቶ ወደ መጀመሪያው ድንጋይ ተጠጋ።
ባለሙያው በመዶሻው መቅረጫውን እየመታ ድንጋዩን መውቀር ጀመረ። በመዶሻው በሃይል በመታው ቁጥር ድንጋዩ ከፍተኛ ህመም ይሰማው ነበር።
ጥቂት ቀናት እንደዚህ ከተወቀረ በኋላ፣ መጀመሪያው ድንጋይ ህመሙን መታገስ አቃተው።
በቁጣና በጩኸት ለባለሙያው እንዲህ አለው እባክህ ተወኝ! ቁስሉና ህመሙ በጣም በረታብኝ።
ከዚህ በላይ መዶሻህን መታገስ አልችልም። እባክህ እንዳለው ተወኝና በሰላም ልኑርበት ባለሙያውም አዘነለት።
መልካም፣ ካልታገስከኝ እተውሃለሁ ብሎ መዶሻውን አነሳ። መጀመሪያው ድንጋይ ምንም ቅርጽ ሳይኖረው፣ ዝም ብሎ እንደነበረው ተራ ዓለት ሆኖ ቀረ
ባለሙያው ወደ ሁለተኛው ድንጋይ ዞረ። መዶሻውንና መቅረጫውን አንስቶ መውቀር ጀመረ።
ይህኛው ድንጋይም ልክ እንደ መጀመሪያው ከፍተኛ ህመም ይሰማው ነበር። ነገር ግን በውስጡ እንዲህ ብሎ አሰበ፦
ይህ ህመም ለጥቂት ጊዜ ነው፤ ከዚህ በስተጀርባ ግን ታላቅ ቅርጽና ክብር አለ። ስለዚህ መታገስ አለብኝ
ቀናት ወደ ሳምንታት፣ ሳምንታት ወደ ወራት ተቀየሩ። ባለሙያው ድንጋዩን ደጋግሞ ወቀረው፣ ሰነጠቀው፣ አስተካከለው።
ድንጋዩ በታላቅ ትዕግስት ህመሙን ሁሉ ዋጥ አድርጎ ጸጥ አለ። ከብዙ ወራት ትዕግስትና ስራ በኋላ፣ ያ ተራ ዓለት የነበረው ድንጋይ ተለውጦ፣
በዓለም ላይ እጅግ በጣም ያማረ፣ ግርማ ሞገስ ያለው ታላቅ የንጉሥ ሃውልት ሆነ። ሃውልቱ ተሰርቶ ሲያልቅ
ከአካባቢው የመጡ ሰዎች በሙሉ በሃውልቱ ውበት ተደመሙ። በትልቅ ስነ-ስርዓትም በከተማው መሃል ባለው ትልቅ አደባባይ ላይ ሊያቆሙት ወሰኑ።
ሰዎች ሃውልቱን በክብር ተሸክመው ሲወስዱት፣ ያ ህመሙን መታገስ አቅቶት የነበረው መጀመሪያው ድንጋይ ግን መሬት ላይ ተጥሎ ቀርቶ ነበር።
ከተማው መሃል ሃውልቱ በክብር ቆመ። ይሁንና ወደ አደባባዩ የሚመጡት በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ጫማቸው በጭቃ እንዳይበላሽ
መሬት ላይ የሚነጠፍ ጠንካራ ድንጋይ አስፈለጋቸው። ስለዚህ ሰዎቹ ወደ ተራራው ተመልሰው ያንን
ህመም ያልታገሰውን መጀመሪያውን ድንጋይ ፈልጠው አምጥተው ሃውልቱ ስር መሬት ላይ አነጠፉት። አሁን ሁኔታው እንዲህ ሆነ
ሁለተኛው ድንጋይ በትዕግስቱ ምክንያት የክብር ሃውልት ሆኖ ወደ ሰማይ ቀና ብሎ ቆመ፤ ሰዎች ሁሉ በአድናቆት ይመለከቱታል፣ ያከብሩታል።
መጀመሪያው ድንጋይ በትዕግስት ማጣቱ ምክንያት መሬት ላይ ተነጥፎ፣ በየቀኑ በሰው እግርና ጫማ እየተረገጠ ይኖራል።
ፈተናን ፈርቶ መሸሽ በወቅቱ ሰላም ሊሰጠን ይችላል፤ ነገር ግን የወደፊት ክብራችንን ያሳጣናል።
3 383
ምልሰት -ሄራን- 8
"አዲስ አበባ ደርሼ እክስቴ ቤት አረፍኩ።አክስቴ የወንድሟን ምትክ ያገኘች ያህል ስለተሰማት በደስታ ተቀበለችኝ።ከወላጆቼ አግኝቼው የማላውቀው አይነት ፍቅርና ክብር ተቸረኝ።ጊዜ ሳታጠፋ ያቋረጥኩትን የዩንቨርስቲ ትምህርት ለመቀጠል ከአንዱ የግል ኮሌጅ አስመዘገበችኝ።አዲሱ አኗኗር ተመቸኝ።
ሸገር ገብቼ ሶስት ወር ገደማ እንደቆየሁ ሌላ ህይወትን እንድወዳት የሚያደርግ የእድል በር ተከፈተልኝ።አንዱ ቆንጅየ የጅማ ልጅ መምህሬ አይኑን እኔ ላይ ጣለ።የምንገናኝበት ሰፊ ሁኔታ ስለነበረ ለመቀራረብ ቻልን።ጠበስኩት!!በሁሉ ነገሩ የተሟላ አይነት ሰው ነበረ።ገንዘብ አለው፤ያምራል፤ከነዚህ ሁሉ በላይ ደግሞ አብዝቶ ይጠነቀቅልኛል"
"ከዚያስ?"
"ሰውየው ሳይመሽብህ አትሄድም?በኋላ ሚስትክ ደውላ እንደ ባለፈው እንዳትቆልፍህ"
"የትኛዋ ሚስቴ?"
"ውይ ወንዶች!!ከሃዲዎች እኮ ናችሁ።እንዴት እንደምጠላችሁ!!"
"ለወንድ ልጅ ያለሽ ጥላቻ በጣም የተጋነነ ነው።ግምትሽ ደግሞ የተሳሳተ"
"ኧረባክህ?እንደውም በበቂ ሁኔታ ጠልቻችኋለሁ ብዬ አላምንም።ይሄው ላንተስ አጠገብህ ተቀምጬ ታሪኬን እየተናዘዝኩልህ አይደል?"
"ጥላቻሽ ከየት ጀመረ?"
"ከአባቴ ነዋ!ከዛ ሴትነቴን ፍለጋ ዙሪያየን ከበውኝ ቀማሴን ከገለብኩላቸው በኋላ ጨረቃ ላይ ጥለውኝ የውሃ ሽታ የሆኑ ወንዶች ጥላቻየን በእጥፍ አሳደጉት"
"ምናልባት አንቺ ጋር ችግር ቢኖርስ?ራስሽን ፈትሸሽ ታውቂያለሽ?"
"ሚሊዮን ጊዜ!!መልሱ ያለው ግን ራሳቸው ወንዶቹ ጋር ነው።እስከ ሚያገኙኝ ድረስ በእጅ በእግሬ ይገቡና ልቤንም ጭኖቼንም ስከፍትላቸው ከኔ አርባ ክንድ ይርቃሉ።በነገራችን ላይ በማስመሰል ከሴቶች ይልቅ ወንዶች ይብሳሉ።ውይ ምላሳቸው!"
"ወደ ታሪክሽ እንመለስ?"
"አንተ መራታ እዚህ ታሳድረኛለች ብለህ አስበህ ባልሆነ!"
"ሰአቱ ገና ነው ሁለት ሰአት ሲሆን እወጣለሁ"
"ከደስታየ ጋር ተገናኝቼ ከንፈሮቼ ፈገግታን መለማመድ ሲጀምሩ ሌላ ቀፋፊ ክስተት ከፊቴ ተጋረጠ።የአክስቴ ባል ሊተናኮለኝ ከጀለ።ቀን ቀን ቤት ውስጥ ሰው ከሌለ ስቀመጥ ስነሳ ሲጎመዥብኝ አስተዋልኩ።በጣም መጠንቀቅ እንዳለብኝ ገባኝ።በኔ ሰበብ አክስቴን መጥፎ ሁኔታ ላይ እንዳላስቀምጣት ሰጋሁ"
"ይገርማል ከዛስ?"
"የሆነ ቀን ስዘናጋ ጠብቆ ተጠመጠመብኝ። ቀፈፈኝ። ጨምድጄ ይዤ ሶፋ ላይ ወርውሬው እንደተለመደው ልብሴን ሸክፌ ከአክስቴ ቤት ወጣሁ።የምሄድበት ስላልነበረኝ ብቸኛው ተስፋየ ያ የጅማው ልጅ ነበር።ስረጋጋ ደወልኩለት።ስልኩ ግን ዝግ ሆነ።አማራጭ አልነበረኝም።ሲመሽ ስልኬን ባልሆነ ዋጋ ሽጬ አንዱ ሆቴል አልጋ ይዤ አደርኩ።በሁለተኛው ቀን በሌላ ሰው ስልክ ስደውል እንደተዘጋ ነው።በሶስተኛው ቀን ግን አገኘሁት።ሁኔታውን ሲሰማ እየበረረ ደረሰልኝ።ሁኔታውን እንደ መልካም አጋጣሚ ቆጥሮት ጊዜ ሳይወስድ ቤት ተከራይቶ እንደ ባልና ሚስት አብረን መኖር ጀመርን"
"እሺ ከዛ በኋላስ?"
"አቦ በቃ ውጣልኝ ሁለት ሰአት አልፏል ቀሪውን ሌላ ጊዜ እንግርሃለሁ"
"ጥሩ!ሲም ካርድሽ አንቺ ጋ ነው?"
"አዎ ምነው?"
"የታለ?"
"ምን ፈልገህ ነው?"
"ነገ ስልክ ይዤልሽ እመጣለሁ።ከዛ እንደተለመደው ምሳችንን እየበላን የቀረውን ታሪክ ትነግሪኛለሽ"
"ግን ይሄ ሁሉ ለምን?"
"ስለወደድኩሽ!ቢያንስ በዚች እንኳን ልደግፍሽ ስለፈለግኩ"
"ከጀርባው ግን ሌላ ፍላጎት የለበትም አይደል?"
"የዋህነቷ አሳዘነችኝ። አላውቅም!አሁን በእርግጠኝነት የማውቀው ነገር ባሳለፍሽው ውጣ ውረድ ከልብ መነካቴን ነው።ጫማየን መልሰሽ አታደርጊልኝም?"
"የገጠር ሰው አይደለህ?ጫማህ እዚሁ ይደርልህናበባዶ እግርህ አቅጥነው"
•••ለመማረር የሚያበቃት በቂ ሸክም ተሸክማለች።ያለ እድሜዋ በርካታ ሰቆቃዎችን ማስተናገዷ እንዳደከማት ግልፅ ሆኖልኛል።ጫማዬን ተጫምቼ በሯን ከፍታ ስትሸኘኝ•••
"ደህና እደሪ።ነገ ጠዋት ስለምመጣ ከቤት እንዳላጣሽ" አልኳት።በሯን ዘግታ ስትመለስ ወደ ጨለማው ጠለቅኩ።
ይቀጥላል•••
ዮሓቶኤል
3 383
«መጽሐፍ ቅዱስን ስታነቡ ስሞቹን ዝም ብላችሁ አልፋችኋቸው ታውቃላችሁ? 🤔📖 እያንዳንዱ ስም በስተጀርባው የራሱ የሆነ ድንቅ ምሥጢር እንዳለውስ ያውቁ ኖሯል? 🔍✨
ከፍጥረት ጀምሮ እስከ ሐዋርያት ዘመን ድረስ ያሉ ከ2,000 በላይ ስሞችን፣ ጥልቅ የዕብራይስጥና የግሪክ ሥርወ-ቃል ትርጉማቸውን እንዲሁም የተሟላ የዘር ሐረግ ታሪካቸውን በአንድ ጥራዝ ሰብስበን ይዘንላችሁ መጥተናል! 📜👑
መጽሐፍ ቅዱስን በጥልቀት ለማጥናት፣ ለማስተማር ወይም ለልጅዎ ትርጉም ያለው መንፈሳዊ ስም ለመምረጥ ከዚህ የተሻለ ሁሉን አቀፍ ዲጂታል ማጣቀሻ የለም! 👶🙌📚
አሁኑኑ በስልክዎ ወይም በኮምፒውተርዎ በPDF ያውርዱት፤ በYeBuna.com በቴሌብር፣ በሲቢኢ ብር ወይም በባንክ በደቂቃዎች ውስጥ ከፍለው ወዲያውኑ በእጅዎ ያስገቡ! ⚡📲💳👇»
👇ለመግዛት👇
https://ye-buna.com/Babilan?ref=product_detail&product=6a9af18f0d584_Babilan
