es
Feedback
EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት)

EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት)

Ir al canal en Telegram

📈 Análisis del canal de Telegram EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት)

El canal EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት) (@eotctvchannel) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 29 492 suscriptores, ocupando la posición 2 414 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 1 162 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 29 492 suscriptores.

Según los últimos datos del 31 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 5, y en las últimas 24 horas de 8, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 7.63%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 5.45% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 2 250 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 607 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 4.

📝 Descripción y política de contenido

No se ha proporcionado la descripción del canal.

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 01 agosto, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

29 492
Suscriptores
+824 horas
+137 días
+530 días
Archivo de publicaciones
ቁልቢ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በሰላም መጠናቀቁኔ በማስመልከት የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ወቅታዊ መግለጫ የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ብሩክ ወርቅነህ የዘንድሮው ሐምሌ 19 በቁልቢ የተከበረው የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በድሬዳዋ አስተዳደር ሙሉ በሙሉ በሰላም፣ በፍቅርና በታላቅ ስኬት መከበርና መጠናቀቁን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል። ለዚህም በዓል ከተለያዩ የዓለም ሀገራትና ከኢትዮጵያ ልዩ ልዩ አካባቢዎች የመጡ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ እንግዶች በየብስ ትራንስፖርት፣ በባቡር፣ እንዲሁም በአየር መንገድ ወደ ድሬዳዋ ከተማ መግባታቸውን ገልጸዋል። አስተዳደሩ ይህንን ግዙፍ ሕዝባዊ ፍሰት ለማስተናገድ ካለው ከፍተኛ ዝግጁነት የተነሳ፣ ከተማዋ ሁሉንም የሕብረተሰብ ክፍሎች በልዩ የእንግዳ ተቀባይነት እሴት አስተናግዳ የፍቅርና የአብሮነት ማዕከልነቷን ዳግም አስመስክራለች ብለዋል። በዓሉ በዓመት ሁለት ጊዜ በታኅሣሥ እና በሐምሌ ወራት የሚከበር ታላቅ ሃይማኖታዊና ባህላዊ እሴት መሆኑን ያብራሩት አቶ ብሩክ፣ ይህ ታላቅ ሁነት በየዓመቱ የሕዝቦችን ትስስርና አንድነት ይበልጥ የሚያጠናክር መድረክ መሆኑን አብራርተዋል። የቢሮ ኃላፊው አቶ ብሩክ ወርቅነህ በመግለጫቸው እንዳመለከቱት፣ ድሬዳዋ ዘንድሮም እንደ ወትሮው ሁሉ የመጡትን በርካታ እንግዶች የከተማዋን የቆየና ድንቅ የእንግዳ ተቀባይነት ስም በሚመጥን መልኩ በሰላም፣ በፍቅርና በአብሮነት ስሜት ተቀብላ አስተናግዳለች። ከተማዋ በቀንም ሆነ በምሽት ሙሉ በሙሉ አስተማማኝ ሰላም የነበራት ከመሆኑም በላይ፣ ንቁና ደማቅ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ እንቅስቃሴ የታየባት መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው፣ ይህም እንግዶች ያለምንም የጸጥታ ስጋትና በሙሉ ነፃነት እንዲንቀሳቀሱ አስችሏል ሲሉ ተናግረዋል። አስተዳደሩ የበዓሉን ታላቅነትና ስልታዊ ጠቀሜታ ከግምት ውስጥ በማስገባት ከድሬዳዋ መግቢያ፣ ከገነት መናፈሻ እንዲሁም ከድሬዳዋ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ጀምሮ እንግዶችን በከፍተኛ የአመራር አካላት አማካኝነት በክብርና በደመቀ ሁኔታ መቀበሉን አቶ ብሩክ ገልጸው፣ ምዕመናንና ጎብኚዎች በቆይታቸው በሄዱበት የልማትና የአገልግሎት ተቋማት ሁሉ የድሬዳዋን እውነተኛ የሕዝቦች መተሳሰብ መንፈስ በተግባር እንዲያዩና ደረጃውን የጠበቀ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ መደረጉንም አብራርተዋል። በተለየ መልኩ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የተመራውን የከፍተኛ የቤተክርስቲያኗ አባቶች ልዑካን ቡድን ከአውሮፕላን ማረፊያ ጀምሮ ደማቅና የመንግስትን ታላቅ አክብሮት የገለጸ የክብር አቀባበል ማድረጋቸውን አቶ ብሩክ በመግለጫቸው አስታውቀዋል። ይህንን የከፍተኛ አባቶች ቡድን በታላቅ ፍቅርና ድንቅ መስተንግዶ ያስተናገደው የድሬዳዋ አስተዳደር፣ በዓሉ ተጠናቆ እስኪመለሱ ድረስ ተገቢውን የክብር አሸኛኘት ማድረጉን ኃላፊው ገልጸዋል። በአጠቃላይ ድሬዳዋ ለዚህ ታላቅ በዓል መሳካት፣ ለሕዝብ ደህንነትና ጸጥታ ጥበቃ፣ ለአምልኮ ሥነ-ሥርዓቶች መቃናት እንዲሁም ለሕዝቦች ትስስርና አንድነት ያበረከተችው ዘርፈ ብዙ አስተዋፅዖ እጅግ ከፍተኛ መሆኑን አቶ ብሩክ ገልፀዋል። አስተዳደሩ ያሳየው የተቀናጀ፣ ሙያዊ እና ስኬታማ ሥራ ከተማዋን እጅግ የሚያስመሰግንና በቀጣይም መሰል ግዙፍ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ሁነቶችን የመቀበልና የማስተናገድ ከፍተኛ አቅምና ዝግጁነት እንዳላት በግልጽ ያሳየ መሆኑን አቶ ብሩክ ወርቅነህ በጽኑ አምነውበታል። በመጨረሻም አቶ ብሩክ የዘንድሮው በዓል በሰላም፣ በፍቅር እና በታላቅ አብሮነት በስኬት ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ቀንና ሌሊት ለደከሙ ለመላው የፀጥታ አካላት፣ ለትራንስፖርትና ሌሎችም አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እንዲሁም በአጠቃላይ ለድሬዳዋ ነዋሪዎች ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋፆ በታላቅ አክብሮት ምስጋናቸውን አቅረበዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ !

ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል (ሐምሌ ፳፪) ቀን በሰላም አደረሰን፤ አደረሳችሁ !!!
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል (ሐምሌ ፳፪) ቀን በሰላም አደረሰን፤ አደረሳችሁ !!!

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የሃያኛው ምዕት ዓመት ሰማዕት ሰማዕተ ጽድቅ ዘኢትዮጵያ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ሐምሌ ፳፪ ቀን ፲፱፻፳፰ ዓ.ም ለሀገራቸውና ለቤተክርስቲያናቸው ሲሉ ሰማዕት የሆኑበት ዕለት ነው፡፡ ዘ
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የሃያኛው ምዕት ዓመት ሰማዕት   ሰማዕተ ጽድቅ ዘኢትዮጵያ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ሐምሌ ፳፪ ቀን ፲፱፻፳፰ ዓ.ም ለሀገራቸውና ለቤተክርስቲያናቸው ሲሉ ሰማዕት የሆኑበት ዕለት ነው፡፡ ዘንድሮ በ፳፻፲፰ ዓ.ም የሰማዕቱን  ዘጠናኛ ዓመት እናዘክራለን፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለመጀመሪያ ጊዜ ከራሷ ልጆች አምስት ኢትዮጵያውያን መነኮሳት እስክንድርያ (ግብጽ) ድረስ ልካ በ፲፱፻፳፩ ዓ.ም. ከተሾሙት አምስት  ኢትዮጵያውያን ጳጳሳት አንዱ ሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ናቸው፡፡

ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ስምከ ሕያው ዘኢይመውት “ሰው የተመኘውን ከሠራ የሚጠብቀው ሞቱን ነው” የሚሉት ታላቁን የቤተክርስቲያን አባት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ሐምሌ ፳፪ ቀን ፲፱፻፹፪ ዓ.ም ዐረ
ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ ስምከ ሕያው ዘኢይመውት “ሰው የተመኘውን ከሠራ የሚጠብቀው ሞቱን ነው” የሚሉት ታላቁን የቤተክርስቲያን አባት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ሐምሌ ፳፪ ቀን ፲፱፻፹፪ ዓ.ም ዐረፉ፡፡ ዘንድሮ ፳፻፲፰ ዓ.ም ፴፮ኛ ዓመታቸውን እናዘክራለን፡፡ጥቂት ስለ ብፁዕነታቸው

የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤልና የቅዱስ ቂርቆስ ወኢየሉጣ ዓመታዊ በዓል ተከበረ

የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤልና የቅዱስ ቂርቆስ ወኢየሉጣ ዓመታዊ በዓል ተከበረ

ቅዱስ ፓትርያርኩ ገዳማት ከአደጋ ሊጠበቁ እንደሚገባ አሳሰቡ

ቅዱስ ፓትርያርኩ የእንግሊዝ አምባሳደርና በአፍሪካ ኅብረት የቋሚ መልእክተኛን አነጋገሩ