EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት)
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት)
تُعد قناة EOTC TV (በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት) (@eotctvchannel) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 29 489 مشتركاً، محتلاً المرتبة 2 418 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 1 159 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 29 489 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 30 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -6، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 7.71%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 5.50% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 2 273 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 620 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 4.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
وصف القناة غير متوفر.
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 31 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.
29 489
المشتركون
+124 ساعات
-37 أيام
-630 أيام
أرشيف المشاركات
ቁልቢ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በሰላም መጠናቀቁኔ በማስመልከት የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ወቅታዊ መግለጫ
የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ኃላፊ አቶ ብሩክ ወርቅነህ የዘንድሮው ሐምሌ 19 በቁልቢ የተከበረው የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በድሬዳዋ አስተዳደር ሙሉ በሙሉ በሰላም፣ በፍቅርና በታላቅ ስኬት መከበርና መጠናቀቁን አስመልክቶ መግለጫ ሰጥተዋል።
ለዚህም በዓል ከተለያዩ የዓለም ሀገራትና ከኢትዮጵያ ልዩ ልዩ አካባቢዎች የመጡ በብዙ ሺዎች የሚቆጠሩ እንግዶች በየብስ ትራንስፖርት፣ በባቡር፣ እንዲሁም በአየር መንገድ ወደ ድሬዳዋ ከተማ መግባታቸውን ገልጸዋል።
አስተዳደሩ ይህንን ግዙፍ ሕዝባዊ ፍሰት ለማስተናገድ ካለው ከፍተኛ ዝግጁነት የተነሳ፣ ከተማዋ ሁሉንም የሕብረተሰብ ክፍሎች በልዩ የእንግዳ ተቀባይነት እሴት አስተናግዳ የፍቅርና የአብሮነት ማዕከልነቷን ዳግም አስመስክራለች ብለዋል።
በዓሉ በዓመት ሁለት ጊዜ በታኅሣሥ እና በሐምሌ ወራት የሚከበር ታላቅ ሃይማኖታዊና ባህላዊ እሴት መሆኑን ያብራሩት አቶ ብሩክ፣ ይህ ታላቅ ሁነት በየዓመቱ የሕዝቦችን ትስስርና አንድነት ይበልጥ የሚያጠናክር መድረክ መሆኑን አብራርተዋል።
የቢሮ ኃላፊው አቶ ብሩክ ወርቅነህ በመግለጫቸው እንዳመለከቱት፣ ድሬዳዋ ዘንድሮም እንደ ወትሮው ሁሉ የመጡትን በርካታ እንግዶች የከተማዋን የቆየና ድንቅ የእንግዳ ተቀባይነት ስም በሚመጥን መልኩ በሰላም፣ በፍቅርና በአብሮነት ስሜት ተቀብላ አስተናግዳለች።
ከተማዋ በቀንም ሆነ በምሽት ሙሉ በሙሉ አስተማማኝ ሰላም የነበራት ከመሆኑም በላይ፣ ንቁና ደማቅ የኢኮኖሚና የማኅበራዊ እንቅስቃሴ የታየባት መሆኑን የጠቀሱት ኃላፊው፣ ይህም እንግዶች ያለምንም የጸጥታ ስጋትና በሙሉ ነፃነት እንዲንቀሳቀሱ አስችሏል ሲሉ ተናግረዋል።
አስተዳደሩ የበዓሉን ታላቅነትና ስልታዊ ጠቀሜታ ከግምት ውስጥ በማስገባት ከድሬዳዋ መግቢያ፣ ከገነት መናፈሻ እንዲሁም ከድሬዳዋ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ጀምሮ እንግዶችን በከፍተኛ የአመራር አካላት አማካኝነት በክብርና በደመቀ ሁኔታ መቀበሉን አቶ ብሩክ ገልጸው፣ ምዕመናንና ጎብኚዎች በቆይታቸው በሄዱበት የልማትና የአገልግሎት ተቋማት ሁሉ የድሬዳዋን እውነተኛ የሕዝቦች መተሳሰብ መንፈስ በተግባር እንዲያዩና ደረጃውን የጠበቀ ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ መደረጉንም አብራርተዋል።
በተለየ መልኩ የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ እና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የተመራውን የከፍተኛ የቤተክርስቲያኗ አባቶች ልዑካን ቡድን ከአውሮፕላን ማረፊያ ጀምሮ ደማቅና የመንግስትን ታላቅ አክብሮት የገለጸ የክብር አቀባበል ማድረጋቸውን አቶ ብሩክ በመግለጫቸው አስታውቀዋል።
ይህንን የከፍተኛ አባቶች ቡድን በታላቅ ፍቅርና ድንቅ መስተንግዶ ያስተናገደው የድሬዳዋ አስተዳደር፣ በዓሉ ተጠናቆ እስኪመለሱ ድረስ ተገቢውን የክብር አሸኛኘት ማድረጉን ኃላፊው ገልጸዋል።
በአጠቃላይ ድሬዳዋ ለዚህ ታላቅ በዓል መሳካት፣ ለሕዝብ ደህንነትና ጸጥታ ጥበቃ፣ ለአምልኮ ሥነ-ሥርዓቶች መቃናት እንዲሁም ለሕዝቦች ትስስርና አንድነት ያበረከተችው ዘርፈ ብዙ አስተዋፅዖ እጅግ ከፍተኛ መሆኑን አቶ ብሩክ ገልፀዋል።
አስተዳደሩ ያሳየው የተቀናጀ፣ ሙያዊ እና ስኬታማ ሥራ ከተማዋን እጅግ የሚያስመሰግንና በቀጣይም መሰል ግዙፍ አህጉራዊና ዓለም አቀፋዊ ሁነቶችን የመቀበልና የማስተናገድ ከፍተኛ አቅምና ዝግጁነት እንዳላት በግልጽ ያሳየ መሆኑን አቶ ብሩክ ወርቅነህ በጽኑ አምነውበታል።
በመጨረሻም አቶ ብሩክ የዘንድሮው በዓል በሰላም፣ በፍቅር እና በታላቅ አብሮነት በስኬት ተከብሮ እንዲጠናቀቅ ቀንና ሌሊት ለደከሙ ለመላው የፀጥታ አካላት፣ ለትራንስፖርትና ሌሎችም አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እንዲሁም በአጠቃላይ ለድሬዳዋ ነዋሪዎች ላበረከቱት ከፍተኛ አስተዋፆ በታላቅ አክብሮት ምስጋናቸውን አቅረበዋል።
የድሬዳዋ አስተዳደር የመንግስት ኮምኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ !
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል
እንኳን ለሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል ዓመታዊ ክብረ በዓል (ሐምሌ ፳፪) ቀን
በሰላም አደረሰን፤ አደረሳችሁ !!!
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ
የሃያኛው ምዕት ዓመት ሰማዕት
ሰማዕተ ጽድቅ ዘኢትዮጵያ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ሐምሌ ፳፪ ቀን ፲፱፻፳፰ ዓ.ም ለሀገራቸውና ለቤተክርስቲያናቸው ሲሉ ሰማዕት የሆኑበት ዕለት ነው፡፡ ዘንድሮ በ፳፻፲፰ ዓ.ም የሰማዕቱን ዘጠናኛ ዓመት እናዘክራለን፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ለመጀመሪያ ጊዜ ከራሷ ልጆች አምስት ኢትዮጵያውያን መነኮሳት እስክንድርያ (ግብጽ) ድረስ ልካ በ፲፱፻፳፩ ዓ.ም. ከተሾሙት አምስት ኢትዮጵያውያን ጳጳሳት አንዱ ሰማዕቱ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ናቸው፡፡
ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ካልዕ
ስምከ ሕያው ዘኢይመውት
“ሰው የተመኘውን ከሠራ የሚጠብቀው ሞቱን ነው” የሚሉት ታላቁን የቤተክርስቲያን አባት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ ሐምሌ ፳፪ ቀን ፲፱፻፹፪ ዓ.ም ዐረፉ፡፡ ዘንድሮ ፳፻፲፰ ዓ.ም ፴፮ኛ ዓመታቸውን እናዘክራለን፡፡ጥቂት ስለ ብፁዕነታቸው
የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤልና የቅዱስ ቂርቆስ ወኢየሉጣ ዓመታዊ በዓል ተከበረ
የመልአኩ የቅዱስ ገብርኤልና የቅዱስ ቂርቆስ ወኢየሉጣ ዓመታዊ በዓል ተከበረ
ቅዱስ ፓትርያርኩ ገዳማት ከአደጋ ሊጠበቁ እንደሚገባ አሳሰቡ
ቅዱስ ፓትርያርኩ የእንግሊዝ አምባሳደርና በአፍሪካ ኅብረት የቋሚ መልእክተኛን አነጋገሩ
