MOR North West STO
Ir al canal en Telegram
ይህ ገፅ የሰሜን ምዕራብ አዲስ አበባ አ/ግ/ከ/ቅ/ፅ/ቤት የቴሌግራም ቻናል ነው። ይህን ሊንክ በመጫንና የማህበራዊ ሚዲያ ገፆቻችንን በመቀላቀል መረጃዎችን በፈጥነት ያግኙ:-https://linktr.ee/mornwsto ☎️ +251115578489/+251115578779
Mostrar más7 139
Suscriptores
+2924 horas
+5017 días
+1 41030 días
Archivo de publicaciones
7 142
ዉድ ግብር ከፋያችን
የ2018 ዓ.ም የሰኔ ወር የወርኃዊ የተጨማሪ እሴት ታክስ እና የኤክሳይዝ ማሳወቂያ ጊዜ እስከ ሐምሌ 30; 2018 ዓ.ም መሆኑ ይታወቃል ስለሆነም ከደንበኛዎ ለሀገር የሰበሰቡትን የመንግስት ግብር/ታክስ ያላሳወቃችሁ ግብር ከፋያችን የሚጠበቅባችሁን ታክስ እንድታሳወቁና እንድትከፍሉ እናሳስባለን፡፡
የሰሜን ምዕራብ አ.አ አነ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት
7 142
+4
ለአዲስ ግብር ከፋዮች የግማሽ ቀን ስልጠና ተሰጠ
ሐምሌ 24 ቀን 2018 ዓ.ም | አዲስ አበባ
በገቢዎች ሚኒስቴር ሰሜን ምዕራብ አዲስ አበባ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት አዲስ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ላወጡ ድርጅቶች የግማሽ ቀን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል፡፡
ስልጠናውን የሰጡት በቅ/ጽ/ቤቱ የታክስ ከፋዮች ትምህርት ባለሙያ አቶ አለማየሁ ሙሉ አዲስ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ያወጡ ድርጅቶች ሳያውቁ ወደ ቅጣት እንዳይገቡና ቀጣይ ማድረግ ስለሚገባቸው ተግባር ማስገንዘብ የስልጠናው ዓላማ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በስልጠናው ስለ ታክስ ምንነት፣ የደረሰኝ ህትመትና አጠቃቀም፣ ግብር ቀንሶ ስለማስቀረት (ዊዝሆልዲንግ) ታክስ፣ ስለተጨማሪ እሴት ታክስ፣ ለውጦችን ስለማሳወቅ፣ የታክስ ማስታወቂያ ጊዜዎችና ሌሎች አዲስ የታክስ ከፋይ መለያ ያወጡ ድርጅቶች ማወቅ ስለሚገባቸው ጉዳዮች ከታክስ ህጉ አንፃር ሰፊ ገለፃ ያደረጉ ሲሆን ከሰልጣኞች ለተነሱ ጥያቄዎች ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡
ይህን ሊንክ በመጫንና የማህበራዊ ሚዲያ ገፆቻችንን በመቀላቀል መረጃዎችን በፈጥነት ያግኙ:-https://linktr.ee/mornwsto
7 142
ምዝገባው የተሰረዘበት ሰው ግዴታዎች (በተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ቁ. 1341/2018 መሠረት
፩/ አንድ ሰው በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፲፮ ወይም ፲፯ መሠረት የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ የተሰረዘበት እንደሆነ፡-
ሀ) ታክስ የሚከፈልበትን የስራ እንቅስቃሴ ለማከናወን የሚጠቀምባቸውን ማናቸውንም ሰነዶች እና ማናቸውንም ዌብሳይት፤ ማህበራዊ ሚዲያ ወይም ሌላ የኤሌክትሮኒክ መድረክ ጨምሮ በማናቸውም መልኩ ይህ ሰው ለተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገበ መሆኑን የሚገልጹ ድርጊቶችን ወዲያውኑ ማቆም፣
ለ) ምዝገባው ከተሰረዘበት ቀን አንስቶ በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ ወይም የታክሱ ባለስልጣን በሚሰጠው የጽሑፍ ማስታወቂያ በሚገለጽ ቀደም ያለ ሌላ ጊዜ ውስጥ፣ የጸደቀውን ቅጽ በመጠቀም የመጨረሻውን የተጨማሪ እሴት ታክስ የገቢ ማስታወቂያ ማቅረብ እና የሚፈለግበትን የተጨማሪ እሴት ታክስ መክፈል፣ እና
ሐ) የተሰጠውን የተጨማሪ እሴት ታክስ ዋና የምዝገባ የምስክር ወረቀት እና የዚህን የምስክር ወረቀት ይፋዊ ቅጂዎች ወዲያውኑ ለታክሱ ባለስልጣን የመመለስ፣ ግዴታ አለበት፡፡
፪/ የተመዘገበ ሰው የተጨማሪ እሴት ታክስ ገቢውን በማስታወቅ እና የተጨማሪ እሴት ታክስን በመክፈል ረገድ ያለበትን ግዴታ ጨምሮ ምዝገባው ጸንቶ በነበረበት ጊዜ ውስጥ ካከናወናቸው ተግባራት ወይም ካልፈጸማቸው ግዴታዎች ጋር በተያያዘ የሚኖርበት ግዴታ እና ተጠያቂነት ምዝገባው በመሰረዙ ምክንያት ቀሪ አይሆንም፡፡
፫/ ምዝገባው በሚሰረዝበት ቀን ያልተቀናነሰው የግብአት ታክስ በዚህ አዋጅ አንቀጽ ፵፱ በተመለከተው መሠረት እንዲፈጸም ይደረጋል፡፡
7 142
ተቀናሽ የማይደረጉ ወጪዎች እና ኪሳራዎች
▫️ የካፒታልነት ባህርይ ያላቸው ወጪዎች፤
▫️ የኩባንያ አክሲዮን ወይም የሽርክና ማህበር መሠረት የሆነውን ካፒታል ለማሳደግ የሚወጣ ወጪ፤
▫️ ከተቀጣሪው የወር ደመወዝ 15% (አሥራ አምስት መቶኛ) በላይ በፈቃደኝነት የሚደረግ የጡረታ ወይም የፕሮቪደንት ፈንድ መዋጮ፤
▫️ የአክሲዮን ድርሻ እና የትርፍ ድርሻ ክፍፍል፤
▫️ በመድን፣ በካሳ ወይም በዋስትና ውል መሠረት የተመለሰ ወይም ሊመለስ የሚችል ወጪ ወይም ኪሳራ፤
▫️ ማንኛውንም ሕግ ወይም ውል በመጣስ የሚጣል የገንዘብ ቅጣት ወይም የሚከፈል ካሳ፤
▫️ ግብር ከፋዩ በሂሳብ መዝገቡ የሚይዘው በወቅቱ ወጪ ያልተደረገ ነገር ግን ለወደፊት በግብር ዓመቱ ለሚከሰቱ ወጪዎች ወይም ኪሳራዎች መጠባበቂያ ይሆን ዘንድ የሚያዝ ገንዘብ ወይም የመጠባበቂያ ሂሣብ፤
▫️ ግብር ከፋዩ ለራሱ የሚያወጣው የግል ውጪ፤
▫️ በገቢ ግብር አዋጅ ወይም በውጭ ሀገር የታክስ ሕግ መሠረት የተከፈለ የገቢ ግብር ወይም ተመላሽ የሚደረግ የተጨማሪ እሴት ታክስ፤
▫️ መሥሪያ ቤቱን ወክሎ በተለያዩ ቦታዎች ለሚገኝ ተቀጣሪ ከተቀጣሪው ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ 10% (አሥር በመቶ) በላይ የሚከፈል የኃላፊነት አበል፤
▫️ ከሚከተሉት በስተቀር ለመዝናኛ የሚወጣ ወጪ፤
ሀ. የግብር ከፋዩ የንግድ ሥራ የመዝናኛ አገልግሎት መስጠት ሲሆን፤ወይም
ለ. ተቀናሽ እንዲደረግ በሚፈቅደው ልክ በማዕድን ማውጣት፣ በማኑፋክቸሪንግ ወይም በግብርና ሥራ የተሠማራ ቀጣሪ ሠራተኞቹን ለማዝናናት የሚያወጣው ወጪ፤
▫️ ለበጎ አድራጎት ከሚሰጥ ስጦታ ውጭ የሚደረግ ስጦታ ወይም እርዳታ፤
▫️ ግብር ከፋዩ አንድን የንግድ ሥራ ሀብት ግንኙነት ላለው ሰው ሲያስተላልፍ የሚደርስ ኪሳራ፤
▫️ ማናቸውም ግብር ከፋይ ወደ ባንክ ሂሳብ ገቢ ከሚደረግ ቼክ፤ ወደ ባንክ ሂሳብ ገቢ ከሚደረግ የባንክ ድራፍት፤ ከአንድ የባንክ ሂሳብ ወደሌላ የባንክ ሂሳብ እና ወይም በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ፈቃድ በተሰጣቸው የክፍያ መፈፀሚያ መንገዶች ገንዘብ ከማስተላለፍ ውጪ በአንድ ቀን ውስጥ ለአንድ ሰው ከብር 50,000 (ሃምሳ ሺህ ብር) በላይ በሆነ ጥሬ ገንዘብ የፈጸመው ወይም የፈጸማቸው ክፍያዎች፤
7 142
Repost from Ministry of Revenues of Ethiopia/የገቢዎች ሚኒስቴር
“ካቀድነው በላይ ለመፈጸም ሌት ተቀን መስራት ይጠበቅብናል”
- ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ (የገቢዎች ሚኒስትር)
ሐምሌ 21/2018 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)
በቢሾፍቱ ከተማ ሲካሄድ የቆየው የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ኮሚሽን የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ውይይት መድረክ በዛሬው እለት ተጠናቋል።
የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሴ መድረኩን ባጠቃለሉበት ወቅት የ2018 በጀት ዓመት የሁለቱም ተቋማት እቅድ አፈጻጸም እጅግ ውጤታማ ሆኖ መጠናቀቁን በድጋሚ አስታውሰዋል፡፡
በውይይት መድረኩ ብዙ ጠቃሚ እና ለወደፊቱ እንደግብዓት የሚወሰዱ ሀሳቦች መነሳታቸውን የጠቆሙት ሚኒስትሯ በውይይቱ ልክ ለመተግበር ሌት ተቀን መትጋት ይጠበቅብናል ሲሉ አሳስበዋል፡፡ የ2019 በጀት ዓመት አፈጻጸምም ከአቀድነው በላይ የሚሳካበት እና አስደሳች ውጤት የሚመዘገብበት እንደሚሆንም ያላቸውን እምነት ገልጸዋል፡፡
የጉምሩክ ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ (ዶ/ር) በበኩላቸው አሁን ያለውን እና ቀጣይ ተልዕኮዎችን መሸከም የሚችል መዋቅር እና ብቃትን መሰረት ያደረገ የሰው ኃይል ስምሪት በተያዘው የበጀት ዓመት ተግባራዊ ከሚደረጉ ቁልፍ ጉዳዮች መካከል አንዱ መሆኑን አብራርተዋል።
በዘንድሮው የበጀት ዓመት በገቢ አሰባሰብ አዲስ ታሪክ የሚጻፍበት እንደሆነ የተናገሩት ኮሚሽነሩ ለገቢ አሰባሰቡ ስኬት ተግዳሮት የሚሆኑ ጉዳዮች ከወዲሁ ተለይተው የመፍትሔ አቅጣጫዎች መቀመጣቸውን ገልጸዋል።
በመድረኩ የገቢዎች ሚኒስቴር የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸምን እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ በሚኒስቴሩ የስትቴጂክ ፕላን እና ፕሮጀክት አስተዳደር ዳይሬክተር በአቶ ተመስገን ተሰማ እንዲሁም የጉምሩክ ኮሚሽን የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸምን እና የ2019 በጀት ዓመት እቅድ ደግሞ በአቶ አብዲሳ ዱፌራ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተካሂዶበታል፡፡
በእለቱ በሁለቱም ተቋማት ጥሩ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ቅንጫፍ ጽ/ቤቶች የምስጋና እና የማበረታቻ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡
በመድረኩ ገቢዎች ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታዎች፣ የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነሮች፣ እንዲሁም የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች ተሳትፈዋል።
7 142
የታክስ ዴቢት ወይም ክሬዲት ደረሰኝ (በመመሪያ ቁጥር 1063-2017 መሠረት)
1. ታክስ ከፋይ የሽያጭ መመዝገቢያ ሥርዓቱን አገልግሎት በመጠቀም እና በታክስ ዴቢት ወይም በታክስ ክሬዲት ደረሰኝ አማካኝነት የሽያጭ ዋጋ ማስተካከያ ማድረግ ይችላል፤
2. ባለስልጣኑ ልዩ ልዩ መስፈርቶችን በመጠቀም በሽያጭ መመዝገቢያ ሥርዓት የሚከናወነውን የታክስ ዴቢት እና ታክስ ክሬዲት ደረሰኝ መጠን እና ጊዜ ላይ ገደብ ሊጥል ይችላል፣
7 142
“የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራው የኢትዮጵያ የታክስ ገቢ ከጠቅላላ ሃገራዊ ምርት አንጻር ያለውን ጥምርታ ከነበረበት የቁልቁለት ጎዞ ወጥቶ እድገት ማሳየት እንዲጀምር በማድረግ አበረታች ውጤት አምጥቷል”
- ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ (የገቢዎች ሚኒስትር)
ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)
የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ኮሚሽን የ2018 በጀት ዓመት እቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ በቢሾፍቱ ከተማ መካሄድ ጀምሯል።
መድረኩን የከፈቱት የገቢዎች ሚኒስትር ዓይናለም ንጉሴ ሃገራችን ኢትዮጵያ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርም ትግበራ ውስጥ እንደምትገኝ ገልጸው ከኢኖሚ ሪፎርም አጀንዳዎች ውስጥ አንዱ ቁልፍ ጉዳይ ሃገራዊ የገቢ አሰባሰብ አቅምን ማሳደግ መሆኑን ተናግረዋል።
ይህንን የሪፎርም አጀንዳ ተግባራዊ ለማድረግ በ2017 በጀት አመት የተጀመረው የመካከለኛ ዘመን የገቢ ስትራቴጂ ትግበራ የኢትዮጵያ የታክስ ገቢ ከጠቅላላ ሃገራዊ ምርት አንጻር ያለውን ጥምርታ ከነበረበት የቁልቁለት ጎዞ ወጥቶ እድገት ማሳየት እንዲጀምር በማድረግ አበረታች ውጤት አምጥቷልም ብለዋል።
በ2018 በጀት ዓመት መጀመሪያ ከሀገር ውስጥ ታክስ እና ከወጭ ንግድ ቀረጥና ታክስ 1.28 ትሪሊዮን ለመሰብሰብ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም በበጀት ዓመቱ አጋማሽ በነበረን መልካም አፈጻጸም እቅዳችን ከልሰን 1.50 ትሪሊዮን ለመሰብሰብ መታቀዱን አስታውሰዋል::
በዚሁ መሰረት ከሃገር ውስጥ ታክስ ብር 774.7 ቢሊዪን እና ከውጭ ንግድ ቀረጥ ታክስ ብር 725.3 ቢሊየን ለመሰብሰብ ታቅዶ ከሀገር ውስጥ ታክስ ብር 780.4 ቢሊዮን እና ከውጭ ንግድ ቀረጥና ታክስ 738.2 ቢሊየን ብር በድምሩ 1ትሪሊየን 518 ቢሊዮን ብር በመሰብሰብ የእቅዱን 101.24% ማሳካት መቻሉን አሳውቀዋል።
አፈጻጸሙ ከ2017 በጀት ዓመት አፈፃፀም ጋር ሲነፃፀር የብር 618.39 ቢሊዮን ወይም የ68.69% ዕድገት እንዳለውም ጨምረው ገልጸዋል።
በዚህ በጀት ዓመት የተያዘውን 2ትሪሊዮን 83 ቢሊዮን ብር እቅድ ለማሳካት በሁለቱም ተቋማት ደንበኛ ተኮር የአገልግሎት አሰጣጥ ተቋማዊ አቅም ግንባታ እና የመልካም አስተዳደር ማሻሻያ፣ የሰው ሀብት ብቃትን በማሳደግ፣ የሕግ ተገዥነትን እና የህግ ማስከበር አቅምን ማሳደግ ፤ የደረሰኝ ሎተሪ ስርዓትን መተግበር ፣ ህብረተሰቡ ደረሰኝ የመጠየቅ ባህል እንዲጎለብት መስራት ኢ መደበኛ የኢኮኖሚ እቅስቃሴት በመግታት ፤ የታክስ መሰረትን ማስፋት፤ ውጤታማ የኮንትሮባንድ ቁጥጥር ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ መስራት ይኖርብናል ብለዋል።
በመጨረሻም 2018 በጀት አመት በስኬት እንድጠናቀቅ ግደታቸውን የተወጡ ግብርና ታክስ ከፋዮች፤ የገቢዎች ሚኒስቴር እና የጉምሩክ ኮሚሽን አመራሮች፣ ሠራተኞች፣ የደህንነትና የጸጥታ አካላት ምስጋና አቅርበዋል።
የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር ደበሌ ቃበታ (ዶ/ር) በበኩላቸው መድረኩ በ2018 በጀት ዓመት የነበሩ ጠንካራ አፈጻጸሞችን እና ልምዶችን የምንለዋወጥበት እንዲሁም ድክመቶቻችንን ለመቅረፍ የምንመክርበት ይሆናል ብለዋል።
በመድረኩ የገቢዎች ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዎች፣ የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነሮች እንዲሁም የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም አባገዳዎች እና ሀደሲንቄዎች ተሳትፈዋል።
7 142
+5
ውድ ግብር ከፋዮቻችን!!
እንደሚታወቀው በገቢዎች ሚኒስቴር ከሀምሌ 1 /2018 ዓ.ም ጀምሮ ተግበራዊ የሆነ፡ የግብር ከፋዮች የቅ/ጽ/ቤት አዲስ ምደባ መከናወኑ ይታወቃል፤ ስለሆነም፡ በአዲሱ ምደባ መሠረት ወደ ቅ/ፅ/ቤታችን የተመደባችሁ ውድ ግብር ከፋዮቻችን እንኳን በደህና መጣችሁ! እያልን ከሀምሌ 1 ጀምሮ ከንግድ እንቅስቃሴያችሁ ካገኛችሁት ዓመታዊ የንግድ ትርፍ እንዲሁም በውክልና ከሕዝብ የሰበሰባችሁትን ግብርና ታክስ በወቅቱ፣ በታማኝነትና በፍቃደኝነት አሳውቃችሁ እንድትከፍሉ ጥሪያችንን ስናስተላልፍ በታላቅ አክብሮት ነው።
በእኛም በኩል እንደተለመደው ሁሉ ቀልጣፋ፣ ጥራት ያለውና የላቀ አገልግሎት ለመስጠት ዝግጁ መሆናችንን እናረጋግጣለን።
“የእኛና የእናንተ የጠበቀ አጋርነት ለሀገራችን እድገት መሰረት ነው፤ መልካምና የስኬት አመት እንዲሆንልን እንመኛለን!”
አናመሰግናለን!!
7 142
+5
ለአዲስ ግብር ከፋዮች የኢ-ታክስ ስልጠና ሰጠ።
ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም | አዲስ አበባ
የሰሜን ምዕራብ አዲስ አበባ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት አዲስ ወደ ንግድ ዓለም ለተቀላቀሉ ግብር ከፋዮች ሲሰጥ የቆየውን የኢ-ታክስ (E-Tax) ስልጠና በዛሬው ዕለትም ሰጥቷል።
የኤሌክትሮኒክስ ታክስ ማሳወቅ ድጋፍ እና ክትትል ቡድን አስተባባሪ አቶ ቀናቴ ዱጉማ እንደገለጹት፤ ስልጠናው በዚህ ወቅት መሰጠቱ ግብር ከፋዮች ግብራቸውን በወቅቱ እና በዘመናዊ የኢ-ታክስ ስርዓት እንድያሳውቁ ትልቅ እገዛ ያደርጋል። አቶ ቀናቴ አያይዘውም፣ ሰልጣኞች ስልጠናውን ካጠናቀቁ በኋላ ግብራቸውን በኢ-ታክስ እንዲያሳውቁና በኢ-ፔይመንት (E-Payment) ክፍያቸውን እንዲፈጽሙ በስልክና በአካል አስፈላጊው ማብራሪያና ድጋፍ ሲደረግላቸው መቆየቱን ገልጸው፤ ይህ የመረጃና ድጋፍ አሰጣጥ ሂደት በቀጣይም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
ይህን ሊንክ በመጫንና የማህበራዊ ሚዲያ ገፆቻችንን በመቀላቀል መረጃዎችን በፈጥነት ያግኙ:-https://linktr.ee/mornwsto
7 142
+4
የ 2019 በጀት አመት የአንደኛ ዙር የሞጁላር ትምህርት ስልጠና መሰጠት ተጀመረ
ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም | አዲስ አበባ
በገቢዎች ሚኒስቴር ሰሜን ምዕራብ አዲስ አበባ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት የ2019 በጀት አመት የአንደኛ ዙር የታክስ ትምህርት ሞጁላር ሰልጣኞችን ማሰልጠን ጀመረ።
ስልጠናው የታክስ ህግ፣ደንብና መመሪያ ለግብር ከፋዮች ግንዛቤ ለመስጠት ያለመ ሲሆን ግብር ከፋዮች መብታቸው አውቀው ግዴታቸውን እንዲወጡ የሚያደርግ ተከታይ የሞጁላር ስልጠና ነው።የመጀመሪያ ሴምስትር የታክስ ትምህርት ሞጁላር ትምህርቱም ሲጀምር ትኩረቱን ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ ግብር ላይ ያደረገውን የመጀመሪያ ሞጁል ስልጠና የተሰጠ ሲሆን የዕለቱንም ስልጠና ያሰለጠኑት የታክስ ከፋዮች ትምህርት መሪ ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ አልማዝ ሰሎሞን ናቸው፡፡
ይህን ሊንክ በመጫንና የማህበራዊ ሚዲያ ገፆቻችንን በመቀላቀል መረጃዎችን በፈጥነት ያግኙ:-https://linktr.ee/mornwsto
7 142
+4
የክፍል ሁለት ማጠቃለያ ፈተና ተሰጠ።
ሐምሌ 14 ቀን 2018 ዓ.ም | አዲስ አበባ
የሰሜን ምዕራብ አዲስ አበባ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለ2018 በጀት አመት ለአስራ አራተኛ ዙር ታክስ ትምህርት ሞጁላር ሰልጣኞች በዛሬው እለት የክፍል ሁለት ማጠቃለያ ፈተና ሰጠ፡፡
ይህን ሊንክ በመጫንና የማህበራዊ ሚዲያ ገፆቻችንን በመቀላቀል መረጃዎችን በፈጥነት ያግኙ:-https://linktr.ee/mornwsto
7 142
የዴስክ ኦዲት(በመመሪያ ቁጥር 1063-2017 መሠረት)
1. የዴስክ ኦዲት ኦዲተሩ በቢሯቸዉ ሆነዉ ከዚህ በታች በተዘረዘሩት ምክንያቶች የሚያከናዉኑት ነዉ ፡፡
ሀ) በአንድ የጠለየ የገቢ ርዕስ ታክስ ከፋዩ ያስታወቀዉ የሽያጭ ገቢ አጥጋቢ ምክንያት ባልቀረበበት ሁኔታ ዝቅተኛ ሆኖ ሲገኝ፣
ለ) የታክስ ማስታወቂያዉ ከተከፈለዉ ታክስ ጋር የማይጣጣም ሆኖ ሲገኝ፣
ሐ) አንድ ወይም ከአንድ በላይ የታክስ ደረሰኞች ማስታወቂያ ያልቀረበባቸዉ ሲሆን፣
መ) የግብር ከፋዩ ወጪዎች ወይም ተቀናሾች የማይፈቀዱ ከሆነ፣
ሠ) የታክሱ ባለሥልጣን የታክሱን ስሌት ለማከናወን የሚያስችል በቂ ሰነድ ባገኘበት በማናቸዉም ሌላ ሁኔታ፣
2. የዴስክ ኦዲት በሚደረግበት ጊዜ ኦዲት እየተደረገ ስለመሆኑ ታክስ ከፋዩ የጽሑፍ ማስታወቂያ እንዲደርሰዉ ማድረግ አስፈላጊ አይደለም ፡፡ ሆኖም ባለሥልጣኑ የመጨረሻዎን የታክስ ስሌት ማስታወቂያ ለታክስ ከፋዩ በጽሑፍ ወይም በአካል ተገኝቶ ማብራሪያ እንዲሰጥ ፣ጥያቄዎችን እንዲመልስ ወይም ሰነዶችን እንዲያቀርብ መጋበዝ አለበት ፡፡
7 142
የኤክሣይዝ ታክስ የሚጣልባቸው ዕቃዎች
👉የቅንጦት ዕቃዎች፡- መሠረታዊ ያልሆኑ የኢኮኖሚ ደረጃን ለማሳየት
ጥቅም ላይ የሚውሉ፣ያለነዚህ ዕቃዎች መኖር ስለሚቻል፣ ቁጠባን
አያበረታቱም ምሳሌ፡- ኮስሞቲክስ፣ ሽቶ
👉ጉዳት የሚያስከትሉ ዕቃዎች፡- በተጠቃሚው ጤና ማህበራዊ ኑሮ እና
ኢኮኖሚ ላይ ችግር የሚያስከትሉ ዕቃዎች፡- ሲጃራ፣ አልኮል መጠጥ
👉ፍጆታቸው የማይቀንስ ዕቃዎች:- ዋጋቸው በመጨመሩ ምክንያት
እምብዛም የፍላጐት/የፍጆታ መቀነስ የማይታይባቸው ዕቃዎች
ምሳሌ፡- ጨው
