MOR North West STO
Open in Telegram
ይህ ገፅ የሰሜን ምዕራብ አዲስ አበባ አ/ግ/ከ/ቅ/ፅ/ቤት የቴሌግራም ቻናል ነው። ዩቱዩብ https://shorturl.at/EyUPI ቴሌግራም @northwestMOR ፌስቡክ https://shorturl.at/UQjxc ተከታታይ እና የርቀት ስልጠና በነጻ ለመሰልጠን https://shorturl.at/l988k ☎️ +251115578489/+251115578779
Show more5 536
Subscribers
+524 hours
+307 days
+20930 days
Posts Archive
5 536
+4
የክፍል ሶስት ስልጠና ተጠናቀቀ
ሰኔ 9-2018 ዓ/ም አ.አ
በገቢዎች ሚኒስቴር ሰሜን ምዕራብ አዲስ አበባ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት የ2018 በጀት አመት ለአስረኛ ሁለተኛ ዙር የታክስ ትምህርት ሞጁላር ሰልጣኞች የታክስ አስተዳደር አዋጆችን በተመለከተ ሲሰጥ የነበረው ተከታታይ የሞጁለር ስልጠና ተጠናቀቀ፡፡
የክፍል ሳስት የመጨረሻ ክፍል የሆነው ስልጠና በታክስ ከፋዮች ትምህርት ባለሙያ አቶ ዘመዴ ለገሰ የተሰጠ ሲሆን የታክስ አስተዳደራዊ እና የወንጀል ቅጣቶች እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ሲሆን ሰልጣኞችም በክፍል ሶስት ስልጠና የታክስ አስተዳደር ላይ ያሉ የተለያዩ አዋጆች መመሪያዎችና ደንቦችን በተመለከተ ስልጠና ወስደው አጠናቀዋል፡፡
ይህን ሊንክ በመጫንና የማህበራዊ ሚዲያ ገፆቻችንን በመቀላቀል መረጃዎችን በፈጥነት ያግኙ:-https://linktr.ee/mornwsto
5 536
1072_2017_yaeekesaayeze_meleketocene_asetadaadare_sereaate_lamawasane.pdf4.42 KB
5 536
የሽያጭ መመዝገቢያ መሣሪያ ጥቅሞች ከግብር ከፋዩ አንፃር
▫️ ሻጭ ድርጅቶች እስቶካቸውን ለማወቅና ለመቆጣጠር ይረዳቸዋል፤
▫️ በሽያጭ ሠራተኞችና በድርጅቱ መካከል መተማመንን ያጠናክራል፤
▫️ ፍትሐዊ የግብር ውሳኔ እንዲከናወን ያግዛል፤
▫️ ጤናማ የገበያ ውድድር እንዲኖር ያደርጋል
▫️ ገዢዎች የሚከፍሉት ታክስ በትክክል ለመንግሥት ገቢ ለመደረጉ እርግጠኝነት ይሰማቸዋል፡፡
▫️ ዘመናዊ የሂሳብ መዝገብ አያያዝ እንዲኖር ያደርጋል
▫️ ደረሰኝ በእጅ ለማዘጋጀት የሚወስደውን ጊዜ ይቀንሳል
5 536
ይህን ሊንክ በመጫንና የማህበራዊ ሚዲያ ገፆቻችንን በመቀላቀል መረጃዎችን በፈጥነት ያግኙ:-https://linktr.ee/mornwsto
5 536
በተሻሻለው የገቢ ግብር አዋጅ 1395/2017 ንዑስ አንቀጽ 29 መሠረት ከዲጅታል ይዘት ፈጠራ ከሚገኝ ገቢ ግብር እንዲከፈልበት ያደርጋል፡፡
በዚሁም መሠረት ከዲጂታል ይዘት ፈጠራ የሚገኝ ገቢ ማለት አንድ ግለሰብ፣ ድርጅት የቪዲዮ ማጋሪያ አገልግሎቶችን፣ የማህበራዊ ሚዲያ መድረኮችን፣ የድምጽ ማስተላለፊያ (ፖድካስት) አገልግሎቶችን እና የቀጥታ ስርጭት መድረኮችን ጨምሮ በኦንላይን መድረኮች ላይ ዲጂታል ይዘትን በመፍጠር እና በማሰራጨት የሚያገኘው ማንኛውም የገንዘብ ወይም በአይነት የሚገኝ ገቢ ነው።
ይህም የሚከተሉትን ገቢዎች ያካትታል፦
ሀ) ማስታወቂያዎች እና ስፖንሰርሺፖች፣
ለ) የምርት ስም ስምምነቶች እና ድጋፎች፣
ሐ) የአጋርነት ግብይት እና የምርት ምደባዎች
መ) የደጋፊዎች አስተዋጽኦ፣ የገንዘብ ስጦታዎች ወይም የብዙሃን የገንዘብ ማሰባሰብ
(ክራውድ ፈንዲንግ)፣
ሠ) የአባልነት ክፍያዎች፤
ረ) የዲጂታል ወይም የአካላዊ ሸቀጦች ሽያጭ፣
ሰ) ለማስተዋወቂያ እንቅስቃሴ ምትክ የተገኙ ዕቃዎች ወይም አገልግሎቶች እና
ሸ/ ከዚህ በላይ ከተጠቀሱት ጋር ተመሳሳይነት ያላቸው ሌሎች ክፍያዎች፡፡
5 536
Repost from Ministry of Revenues of Ethiopia/የገቢዎች ሚኒስቴር
+4
አዲሱ የግብር ከፋዮች ምደባ (tax payers’ segmentation) ከሚቀጥለው በጀት ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል
ሰኔ 03 / 2018 ዓ.ም (ገቢዎች ሚኒስቴር)
የ2019 በጀት ዓመት የታክስ ከፋዮች የደረጃ ምደባ ኮሚቴ ያከናወናቸውን ተግባራት አስመልክቶ ለበላይ አመራሮች ሪፖርት አቅርቧል፡፡
በዚህ ወቅት የገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ የምደባው ዓላማ ግብር ከፋዮች ተገቢውን አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ፣ የሚኒስቴር መ/ቤቱን ተደራሽነት ለማስፋት እንዲሁም የግብር ከፋዮችን አደረጃጀት ለማስፋት ታስቦ ነው ብለዋል፡፡ ይህም የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የጎላ ሚና እንደሚኖረው የገለጹት ሚኒስትሯ ለተግባራዊነቱም የሚመለከታቸው አካላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል፡፡
የታክስ ከፋዮች የደረጃ ምደባ ኮሚቴውን ሪፖርት ያቀረቡት አቶ ደረጄ ፋና ምደባው የተካሄደው ዓለምአቀፋዊ ተሞክሮዎችን መሠረት አድርጎ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ለግብር ከፋዮች ተገቢውን አገልግሎት በመስጠት የሚሰበሰበውን ገቢም ለማሳደግ ጉልህ ሚና እንዳለውም አብራርተዋል፡፡
በውይይት መድረኩ ላይ የገቢዎች ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታዎች እና የቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጆች ተሳትፈውበታል፡፡
በሽመልስ ሲሳይ
ፎቶ፡- ክፍሌ ኣዳፍሬ
5 536
Repost from Ministry of Revenues of Ethiopia/የገቢዎች ሚኒስቴር
የጉምሩክ ማሻሻያ አዋጅ ፀደቀ
ሰኔ 02 / 2018 ዓ.ም (ገቢዎች ሚኒስቴር)
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በ24ኛ መደበኛ ስብሰባው የጉምሩክ አዋጅን ለማሻሻል የቀረበውን ረቂቅ አዋጅ መርምሮ አፅድቋል።
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ደሳለኝ ወዳጀ ሪፖርት እና የውሳኔ ሀሳብ ለምክር ቤቱ አቅርበዋል።
ረቂቅ አዋጁ የኮንትሮባንድ ንግድን ለመከላከል የሚደረገውን ጥረት በማጠናከር ረገድ ጉልህ ሚና እንዳለው ሰብሳቢው ገልጸዋል።
ረቂቅ አዋጁ በዘርፉ ሀገራችን ከፈረመቻቸው ዓለም አቀፍ ስምምነቶች ጋር የተጣጣመ እንዲሆን የሚያስችል ሲሆን፣ በጉምሩክ አሠራር ውስጥም ፍትሃዊነት እንዲረጋገጥ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥር መሆኑ ተገልጿል።
በተጨማሪም፣ ረቂቅ አዋጁ በሀገራችን እያደገ የመጣውን የማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ ልማት የሚደግፍ እንዲሁም ኢንቨስትመንትን የሚያበረታታ መሆኑን የኮሚቴው ሰብሳቢ አመላክተዋል።
ረቂቅ አዋጁ በነባሩ አዋጅ ውስጥ የተደነገጉ ገደቦችን በተግባር ላይ ሲውሉ ይስተዋሉ የነበሩ የአተገባበር ችግሮችን ለመቅረፍ ያስችሉ ዘንድ አስፈላጊ ድንጋጌዎችን ያካተተ መሆኑንም አንስተዋል።
አስመጪዎች በቀረጥ እና ታክስ አወሳሰን ላይ ያላቸውን አቤቱታ በማቅረብ ሂደት ያጋጥሟቸው የነበሩ የአሠራር መሰናክሎችን ለማስወገድ የሚያስችሉ ድንጋጌዎችን ያካተተ ረቂቅ አዋጅ መሆኑን ጠቁመዋል።
የምክር ቤት አባላት በበኩላቸው፣ በረቂቅ አዋጁ ዝግጅት ወቅት የተከናወነው ሥራ አስፈላጊውን የሕግ ምርመራ እና ግምገማ ሂደት የተከተለ መሆኑን እና አዋጁም በተገቢው ሁኔታ ታይቶ እና ተገምግሞ የቀረበ መሆኑን ገልጸዋል።
በኮንትሮባንድ ጭነት ምክንያት ተሽከርካሪ እንዲወረስ የሚያስችል ድንጋጌ ቢኖርም፣ ባለቤቱ በድርጊቱ ተሳታፊ ባልሆነበት ሁኔታ ንብረቱ ሊወረስ እንደማይገባም አንሥተዋል።
ባለቤቱ ተሽከርካሪውን አሽከርካሪ እንዲጠቀምበት በውል ሲያስረክብ፣ ታማኝና ለሕግ ተገዥ የሆነ ሹፌር መቅጠር እንዲሁም ለሚደርስ ጉዳት ወይም ሕገ-ወጥ ድርጊት ተገቢ ዋስትና መውሰድ እንዳለበት ተጠቁሟል።
ምክር ቤቱ በረቂቅ አዋጁ ላይ ሰፊ ውይይት ካደረገ በኋላ፣ የጉምሩክ አዋጅን እንደገና ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅን፣ አዋጅ ቁጥር 1425/2018 አድርጎ በሁለት ተቃውሞ በአብላጫ ድምፅ ማፅደቁን ከምክር ቤቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።
ዘገባው የኢቢሲ ነው፡፡
5 536
እንደ ዓይነት ጥቅሞች የማይቆጠሩ
▫️በሠንጠረዥ “ሠ” ከገቢ ግብር ነጻ የሆኑ ገቢዎች መሠረት ከግብር ነጻ የተደረገ ጥቅም፤
▫️ቀጣሪ ተመሳሳይ ጥቅም የሚያቀርብበትን ድግግሞሽ ከግምት ውስጥ በማስገባት ዋጋው አነስተኛ ከመሆኑ የተነሳ ማስላቱ ምክንያታዊ ያልሆነ እና ለአስተዳደር የማያመች ጥቅም፤
▫️በቀጣሪው ወይም በቀጣሪው ስም በሚተዳደር የሠራተኞች ምግብ ቤት፣ ካፊቴሪያ ወይም የመመገቢያ ክፍል ያለምንም ልዩነት ለመደበኛ ሠራተኞች ጥቅም ብቻ ተብሎ የሚቀርብ የምግብና የመጠጥ አገልግሎት ድጎማ፤
▫️የሥራ አመራር አካል ላልሆነ ተቀጣሪ በሩቅ ሥፍራ የሚቀርብ የማረፊያ ወይም የመኖሪያ ቤት አገልግሎት፤
▫️ተቀጣሪው እንዲጠቀምበት በቀጣሪው የሚቀርብ ተንቀሳቃሽ ስልክ፤
▫️በቀጣሪው በቀረበ የተንቀሳቃሽ ስልክ የተደረገን ጥሪ ጨምሮ ቀጣሪ ለተቀጣሪ የሚሸፍነው የተንቀሳቃሽ ስልክ ጥሪዎች ወጪ፤
▫️በዩኒቨርሲቲ፣ በኮሌጅ ወይም በጎልማሶች ትምህርት በሚሰጥ ሌላ ተቋም የሚሰጥ ትምህርት መከታተል እንድችል ቀጣሪ ለተቀጣሪ የሚፈጽመው የትምህርት ወይም ሥልጠና ክፍያ፤
▫️ለተቀጣሪ ጥቅም የሚቀርብ የደህንነት ጥበቃ አገልግሎት፤
▫️ሆቴሎች፣ ሬስቶራንቶች እና የምግብ አገልግሎት የሚያቀርቡ ሌሎች ተቋሞች ለተቀጣሪዎቻቸው የሚያቀርቡት የምግብና መጠጥ አገልግሎት፤
▫️ለተቀጣሪዎች የሚቀርብ የደንብ ልብስ እና የሥራ መገልገያ ፡፡
▫️በማንኛውም ሁኔታ በዓይነት ጥቅሞች ላይ የሚከፈለው ጠቅላላ ግብር ተቀጣሪው በወሩ ከሚያገኘው የደመወዝ ገቢ አስር በመቶ (10%) መብለጥ የለበትም፡፡
5 536
ከተጨማሪ እሴት ታክስ ነፃ የሆነ የመድህን አገልግሎት
▫️ ከረዥም ጊዜ የመድህን ስራ በስተቀር ሌላ ማናቸውም የመድህን አገልግሎት የተጨማሪ እሴት ታክስ ይከፈልበታል።
▫️“የረዥም ጊዜ የመድህን ስራ” የሚለው ሐረግ በመድህን ስራዎች አዋጅ ቁጥር 746/2004 (እንደተሻሻለ) የተሰጠው የሚከተለዉ ትርጉም ይኖረዋል፡፡
▫️ የረዥም ጊዜ የመድህን ስራ የሚባሉት፡
• የህይወት መድህን፤
• የተወሰነ ገንዘብ በተወሰነ ጊዜ የሚክፈል ግዴታ (annuity);
• የጡረታ ዋስትና (pension);
• ዘላቂ የጤና መድህን፤
▫️በተጨማሪም በሰው አካል እና ህይወት ላይ ለደረሰ ጉዳት የሚከፈል ካሳ ከታክሱ ነፃ ነው
5 536
ዉድ ግብር ከፋዮቻችን
የ2018 ዓ.ም የሚያዝያ ወር የወራዊ የተጨማሪ እሴት ታክስ እና የኤክሳይዝ ማሳወቂያ እንዲሁም የሒሳብ ሪፖርታችሁን በጥቅምት ወር ለምታጠናቅቁ ግብር ከፋዮች የ2ኛ ሩብ ዓመት የቅድሚያ ግብር ክፍያ (Advance payment) ጊዜ እስከ ግንቦት 30, 2018 ዓ.ም መሆኑ ይታወቃል ስለሆነም ከደንበኛዎ ለሀገር የሰበሰቡትን የመንግስት ግብር(ታክስ) ያላሳወቃችሁ ግብር ከፋያችን የሚጠበቅባችሁን ታክስ እንድታሳወቁና እንድትከፍሉ እናሳስባለን፡፡
የሰሜን ምዕራብ አ.አ አነ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት
ግብር ለሀገር ክብር !!
5 536
ዉድ ግብር ከፋዮቻችን
የ2018 ዓ.ም የሚያዝያ ወር የወራዊ የተጨማሪ እሴት ታክስ እና የኤክሳይዝ ማሳወቂያ እንዲሁም የሒሳብ ሪፖርታችሁን በጥቅምት ወር ለምታጠናቅቁ ግብር ከፋዮች የ2ኛ ሩብ ዓመት የቅድሚያ ግብር ክፍያ (Advance payment) ጊዜ እስከ ግንቦት 30, 2018 ዓ.ም መሆኑ ይታወቃል ስለሆነም ከደንበኛዎ ለሀገር የሰበሰቡትን የመንግስት ግብር(ታክስ) ያላሳወቃችሁ ግብር ከፋያችን የሚጠበቅባችሁን ታክስ እንድታሳወቁና እንድትከፍሉ እናሳስባለን፡፡
የሰሜን ምዕራብ አ.አ አነ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት
ግብር ለሀገር ክብር !!
5 536
ዉድ ግብር ከፋዮቻችን
የ2018 ዓ.ም የሚያዝያ ወር የወራዊ የተጨማሪ እሴት ታክስ እና የኤክሳይዝ ማሳወቂያ እንዲሁም የሒሳብ ሪፖርታችሁን በጥቅምት ወር ለምታጠናቅቁ ግብር ከፋዮች የ2ኛ ሩብ ዓመት የቅድሚያ ግብር ክፍያ (Advance payment) ጊዜ እስከ ግንቦት 30, 2018 ዓ.ም መሆኑ ይታወቃል ስለሆነም ከደንበኛዎ ለሀገር የሰበሰቡትን የመንግስት ግብር(ታክስ) ያላሳወቃችሁ ግብር ከፋያችን የሚጠበቅባችሁን ታክስ እንድታሳወቁና እንድትከፍሉ እናሳስባለን፡፡
የሰሜን ምዕራብ አ.አ አነ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት
ግብር ለሀገር ክብር !!
5 536
ዉድ ግብር ከፋዮቻችን
የ2018 ዓ.ም የሚያዝያ ወር የወራዊ የተጨማሪ እሴት ታክስ እና የኤክሳይዝ ማሳወቂያ እንዲሁም የሒሳብ ሪፖርታችሁን በጥቅምት ወር ለምታጠናቅቁ ግብር ከፋዮች የ2ኛ ሩብ ዓመት የቅድሚያ ግብር ክፍያ (Advance payment) ጊዜ እስከ ግንቦት 30, 2018 ዓ.ም መሆኑ ይታወቃል ስለሆነም ከደንበኛዎ ለሀገር የሰበሰቡትን የመንግስት ግብር(ታክስ) ያላሳወቃችሁ ግብር ከፋያችን የሚጠበቅባችሁን ታክስ እንድታሳወቁና እንድትከፍሉ እናሳስባለን፡፡
የሰሜን ምዕራብ አ.አ አነ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት
ግብር ለሀገር ክብር !!
5 536
Repost from Ministry of Revenues of Ethiopia/የገቢዎች ሚኒስቴር
በኢ-ክሊራንስ መተግበሪያ የሚሰጡ አገልግሎቶች
ግንቦት 22/2018 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)
"ኢ-ታክስ" ታክስን ለማሳወቅ፣ ክፍያን ለማከናወን፣ ከዕዳ ነጻ ማረጋገጫ (Tax Clearance) ፣ የተለያዩ ታክስ ነክ ማብራሪያዎች እና ግብር ከፋዮች የራሳቸውን የታክስ መረጃ ለማየት እንዲሁም ሌሎች ተጨማሪ አገልግሎቶችን በኤሌክትሮኒክስ ዘዴ ለማግኘት የሚያስችል ሥርዓት ነው፡፡
በዚህ ሥርዓት ከሚሰጡ አገልግሎቶች ውስጥ ግብር ከፋዩ በየትኛውም ቦታና በማንኛውም ጊዜ (ሰዓት) የኢ-ክሊራንስ አገልግሎትን ማግኘት ይችላል፡፡
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
