MOR North West STO
Open in Telegram
ይህ ገፅ የሰሜን ምዕራብ አዲስ አበባ አ/ግ/ከ/ቅ/ፅ/ቤት የቴሌግራም ቻናል ነው። ይህን ሊንክ በመጫንና የማህበራዊ ሚዲያ ገፆቻችንን በመቀላቀል መረጃዎችን በፈጥነት ያግኙ:-https://linktr.ee/mornwsto ☎️ +251115574182/+251115577386
Show more8 270
Subscribers
+2424 hours
+597 days
+1 12030 days
Posts Archive
8 269
የማስረዳት ኃላፊነት እና አዲስ ማስረጃ ማቅረብ (በተሻሻለዉ ፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁ.1434/2018 መሠረት)
፩/ በዚህ ክፍል መሰረት ከታክስ ውሳኔ ጋር በተገናኘ በሚደረግ ማናቸውም የታክስ ክርክር ሂደት የታክስ ውሳኔ ትክክል ያለመሆኑን የማስረዳት ኃላፊነት የታክስ ከፋዩ ነው፡፡
፪/ በዚህ አዋጅ መሰረት ቅሬታ፣ ይግባኝ ወይም የውሳኔ ማስተካከያ ጥያቄን የሚያቀርብ ታክስ ከፋይ በታክስ ውሳኔ ወቅት ካቀረበው የተለየ አዲስ ማስረጃን ማቅረብ አይችልም፡፡
፫/ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (፪) የተደነገገው ቢኖርም አዲስ ማስረጃ በቅሬታ፣ ይግባኝ ወይም ስህተትን ለማረም በሚቀርብበት ወቅት ተቀባይነት ሊያገኝ የሚችለው፦
ሀ/ የማስረጃው አለመታየት በታክስ ከፍዩ የታክስ እዳ ላይ ከፍተኛ ጫናን የሚያስከትል ከሆነ፤
ለ/ ታክስ ከፋዩ ማስረጃውን ያገኘው የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያ ከደረሰው በኋላ ከሆነ፤ ወይም
ሐ/ ሰነዱ ያልቀረበው ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ከሆነ ፤ይሆናል::
8 269
Repost from Ministry of Revenues of Ethiopia/የገቢዎች ሚኒስቴር
የተሻሻለው የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ የማስረዳት ኃላፊነት እና አዲስ ማስረጃ ማቅረብን በተመለከተ ምን ይላል?
ነሐሴ 25/2018 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)
በተሻሻለው የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1434/2018 አንቀጽ 59 መሰረት ከታክስ ውሳኔ ጋር በተገናኘ በሚደረግ ማናቸውም የታክስ ክርክር ሂደት የታክስ ውሳኔ ትክክል ያለመሆኑን የማስረዳት ኃላፊነትን እና አዲስ ማስረጃ ማቅረብን በተመለከተ የሚከተለውን ይላል፡-
ከታክስ ውሳኔ ጋር በተገናኘ በሚደረግ ማናቸውም የታክስ ክርክር ሂደት የታክስ ውሳኔ ትክክል ያለመሆኑን የማስረዳት ኃላፊነት የታክስ ከፋዩ ነው፡፡
በዚህ አዋጅ መሰረት ቅሬታ፣ ይግባኝ ወይም የውሳኔ ማስተካከያ ጥያቄን የሚያቀርብ ታክስ ከፋይ በታክስ ውሳኔ ወቅት ካቀረበው የተለየ አዲስ ማስረጃን ማቅረብ አይችልም፡፡
ይሁን እንጂ ይህ ድንጋጌ ቢኖርም አዲስ ማስረጃ በቅሬታ፣ ይግባኝ ወይም ስህተትን ለማረም በሚቀርብበት ወቅት ተቀባይነት ሊያገኝ የሚችለው፦
👉 የማስረጃው አለመታየት በታክስ ከፋዩ የታክስ እዳ ላይ ከፍተኛ ጫናን የሚያስከትል ከሆነ፤
👉 ታክስ ከፋዩ ማስረጃውን ያገኘው የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያ ከደረሰው በኋላ ከሆነ፤ ወይም
👉 ሰነዱ ያልቀረበው ከአቅም በላይ በሆነ ምክንያት ከሆነ፤ ይሆናል፡፡
በዚህ አዋጅ መሰረት “አዲስ ማስረጃ” ማለት የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያ ከደረሰው በኋላ በታክስ ከፋዩ የሚቀርብ አዲስ ሰነድ፤ መረጃ፤ ማስረጃ፤ ፍሬ-ነገር ሲሆን፤
👉 በመጀመሪያው የታክስ አወሳሰን ሂደት ለታክስ ባለስልጣኑ ያልቀረበ፤
👉 ለታክስ ውሳኔ ማስታወቂያው ትክክለኛነት አግባብነት ያለው እና መሰረታዊ የሆነ፤ እና
👉 በተወሰነው የታክስ መጠን ወይም በታክስ ከፋዩ ግዴታ ላይ መሰረታዊ ለውጥ የሚያስከትል ነው፡፡
8 269
የተሻሻሉ የታክስ ስሌቶች እና የይርጋ ጊዜ ገደብ (በተሻሻለዉ ፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁ.1434/2018 መሠረት)
አግባብነት ባለው የታክስ ሕግ በሌላ አኳኋን ካልተደነገገ በስተቀር፣ ባለሥልጣኑ በዚህ አንቀጽ ንዑስ አንቀጽ (፩) መሠረት ማንኛውንም የታክስ ስሌት፡-
ሀ) የታክስባለስልጣኑየታክስ ማጭበርበር ድርጊት የተፈፀመ መሆኑን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ያገኘ እንደሆነ የራስ ታክስ ስሌት ማስታወቂያውን ካቀረበበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር ፲ (አስር) ዓመት ውስጥ፤ ወይም
ለ) በሌላ በማናቸውም ሁኔታ በሚከተለው የይርጋ ጊዜ ውስጥ፡ -
(፩) ታክስ ከፋዩ በራሱ የሚያሰላው የታክስ ስሌት ሲሆን ታክስ ከፋዩ የራስ ታክስ ስሌት ማስታወቂያውን ካቀረበበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር ፭ (አምስት) ዓመት ውስጥ፤
(፪) ለሌላ ማንኛውም የታክስ ስሌት ባለሥልጣኑ ለታክስ ከፋዩ የታክስ ስሌት ማስታወቂያ ከሰጠበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር ፭ (አምስት) ዓመት ውስጥ ሊያሻሽል ይችላል፡፡
በዚህ አንቀጽ የተደነገገው ቢኖርም የታክስ ማጭበርበር ድርጊት መፈጸሙ በማስረጃ የተረጋገጠ በሚሆንበት ጊዜ የታክሱ ባለስልጣን የ ፲ (አስር) ዓመቱን የይርጋ ጊዜ ገደብ ሳያልፍ በማናቸውም ጊዜ የታክስ ውሳኔ ማሻሻያን ሊያደርግ ይችላል፡፡
የታክሱ ባለሥልጣን ለፋይናንስ ተቋሙ የዕግድ ትዕዛዝ በደረሰው በ፲ የሥራ ቀናት ጊዜ ውስጥ ትዕዛዙ እንዲቀጥል ለማድረግ የሚያስችል የፍርድ ቤት ፈቃድ ማግኘት አለበት፡፡
8 269
ለውጦችን ስለማሳወቅ
🔘 የንግድ ስራ አሰራር ጋር በተያያዘ የሚደረጉ ለውጦችን ስለማሳወቅ መመሪያ ቁ.143/2011
ታክስ ከፋዩ የሚያሳውቃቸው ለውጦች
ማንኛውም ታክስ ከፋይ ከሚከተሉት ውስጥ ማንኛውንም ጉዳይ በተመለከተ ለውጥ ሲከሰት ለውጡ በተከሰተ በ፴ (በሠላሳ) ቀናት ውስጥ ለውጡን ለባለሥልጣኑ በጽሁፍ ማሳወቅ አለበት፣
▫️ በንግድ ድርጅቱ ስያሜና በአክሲዮን ባለድርሻ አባላት ላይ የተደረገ ለውጥ፤
▫️ በድርጅቱ ስም የተመዘገበ አድራሻ ለውጥ ፤
▫️ በዋነኛ የሥራ እንቅስቃሴው/ በቅርንጫፍ/ በንግድ ሥራው ዘርፍ/መስክ ለውጥ፤
▫️ በድርጅቱ መተዳደሪያ ደንብ/የመመስረቻ ጽሑፍ / የሽርክና ስምምነት ላይ የተደረገ ለውጥ፤
▫️ በድርጅቱ ወይም በታክስ እንደራሴው የባንክ ሂሳብ ወይም የባንክ ቅርንጫፍ አድራሻ ላይ የተደረገ ለውጥ፣
ሙሉውን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ፡- https://acesse.one/a9btkj2
8 269
Repost from Ministry of Revenues of Ethiopia/የገቢዎች ሚኒስቴር
የተሻሻለው አዋጅ ስለታክስ ማጭበርበር ምን ይላል?
ነሐሴ 20/2018 ዓ.ም (የገቢዎች ሚኒስቴር)
በተሻሻለው የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 1434/2018 መሰረት “የታክስ ማጭበርበር” ማለት ታክስን ለመሰወር ወይም ህጋዊ ያልሆነ የታክስ ጥቅም ለማግኘት ሲባል የሚከተሉትን ድርጊቶች መፈጸም ነው፤
👉 ሐሰተኛ የሂሳብ መዝገቦችን፣ ሰነዶችን፣ ደረሰኞችን ወይም ሌሎች ሰነዶችን ማቅረብ፣
👉 ገቢን፣ ግብይትን ወይም ታክስ የሚከፈልበትን እንቅስቃሴ መደበቅ፣
👉 ሐሰተኛ ደረሰኞችን ማዘጋጀት ወይም መጠቀም፣
👉 ሐሰተኛ የታክስ ማስታወቂያ ማቅረብ
👉 ሰነዶችን ማጥፋት፣ መቀየር፣ መደበቅ፣
👉 ከአንድ በላይ ወይም ትይዩ የሂሳብ መዛግብትን ወይም ሰነዶችን ማዘጋጀትና መያዝ፣ እንዲሁም ለታክስ ባለስልጣኑና ለሌሎች አካላት ማቅረብ፤
👉ሐሰተኛ የተቀናሽ ወጪዎችን፣ የግብር ወይም የታክስ ነፃ መብት፣ የተመላሽን ወይም የማካካሻ ጥያቄን ማቅረብ፤
👉 ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ የታክስ ግዴታን ለመቀነስ ማናቸውንም ሌሎች ድርጊቶች መፈጸም ወይም ሕግ እንዲፈፅሙ የሚያስገድዳቸውን አለመፈጸም፡፡
በአዋጁ የተሻሻሉ የታክስ ስሌቶች እና የይርጋ ጊዜ ገደብን በተመለከተ ሲገልጽ የታክስ ባለስልጣኑ የማጭበርበር ድርጊት የተፈጸመ መሆኑን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ያገኘ እንደሆነ የራስ ታክስ ስሌት ማስታወቂያውን ካቀረበበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር 10 (አስር) ዓመት ውስጥ ሊያሻሽል ይችላል ይላል፡፡
ይሁን እንጂ በአዋጁ ንዑስ አንቀጽ 5 ላይ የታክስ ማጭበርበር ድርጊት መፈጸሙ በማስረጃ የተረጋገጠ በሚሆንበት ጊዜ የታክሱ ባለስልጣን የ10 (አስር) ዓመቱን የይርጋ ጊዜ ገደብ ሳያልፍ በማናቸውም ጊዜ የታክስ ውሳኔ ማሻሻያን ሊያደርግ እንደሚችል ይገልጻል፡፡
8 269
እንኳን ለ1 ሺህ 501ኛው የነብዩ መሀመድ ልደት (መውሊድ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
የሰሜን ምዕራብ አዲስ አበባ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
8 269
+4
የክፍል ሁለት ማጠቃለያ ፈተና ተሰጠ።
ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም | አዲስ አበባ
የሰሜን ምዕራብ አዲስ አበባ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ለ2019 በጀት አመት ለአንደኛ ዙር ታክስ ትምህርት ሞጁላር ሰልጣኞች በዛሬው እለት የክፍል ሁለት ማጠቃለያ ፈተና ሰጠ፡፡
ይህን ሊንክ በመጫንና የማህበራዊ ሚዲያ ገፆቻችንን በመቀላቀል መረጃዎችን በፈጥነት ያግኙ:-https://linktr.ee/mornwsto
8 269
+9
የ2019 በጀት ዓመት የሐምሌ ወር የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ተካሄደ።
ነሐሴ 15 ቀን 2018 ዓ.ም. | አዲስ አበባ
የገቢዎች ሚኒስቴር ሰሜን ምዕራብ አዲስ አበባ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት፣ ለ2019 በጀት ዓመት የሐምሌ ወር የዕቅድ አፈጻጸም የሚገመግም ስብሰባ፣ የስራ ሂደት አስተባባሪዎችና የቡድን መሪዎች በተገኙበት አካሂዷል።
በስብሰባው በቀረበው ሪፖርት መሠረት፣ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በሐምሌ ወር ብር 404,546,606.90 ገቢ ለመሰብሰብ አቅዶ የነበረ ሲሆን፣ በተግባር ብር 438,679,627.03 መሰብሰብ ተችሏል። በዚህም መሠረት ከተያዘው ዕቅድ 108.44 በመቶ አፈጻጸም መመዝገቡ ተገልጿል።
የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ስራ አስኪያጅ አቶ ኪሮስ ደበሱ፣ በሐምሌ ወር ለተመዘገበው ውጤታማ የገቢ አሰባሰብ አፈጻጸም አመራሩንና ሰራተኛውን እንዲሁም ግብራቸውን በታመኝነት የሚከፍሉ ግብር ከፋዮችን ያመሰገኑ ሲሆን፣ የተያዘውን ዓመታዊ ዕቅድ በተሟላ ሁኔታ ለማሳካት ትኩረት የተሰጠው ጥረት ማድረግ አስፈላጊ መሆኑን አስገንዝበዋል።ስብሰባው በቀረበው የአፈጻጸም ሪፖርት ላይ ጥልቅ ውይይት ከተደረገ በኋላ፣ በቀጣይ ወራት ትኩረት ሊደረግባቸው በሚገቡ ተግባራት ላይ አቅጣጫ በማስቀመጥ ተጠናቋል።
ይህን ሊንክ በመጫንና የማህበራዊ ሚዲያ ገፆቻችንን በመቀላቀል መረጃዎችን በፈጥነት ያግኙ:-https://linktr.ee/mornwsto
8 269
+5
የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ቁጥር 1341/2016 ላይ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ።
ነሐሴ 15 ቀን 2018 ዓ.ም | አዲስ አበባ
የሰሜን ምዕራብ አዲስ አበባ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ጽ/ቤት ከተሻሻለው የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) አዋጅ ቁጥር 1341/2016 አፈጻጸም እና ድንጋጌዎች ጋር ተያይዞ ለግብር ከፋዮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ።
በስልጠና መድረኩ ላይ በአዲሱ የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ የተካተቱ አሰራሮች፣ የህግ ማሻሻያዎች ላይ ሰፊ ማብራሪያ ተሰጥቷል።
ስልጠናውን የሰጡት የታክስ ከፋዮች ትምህርት መሪ ባለሙያ በሆኑት በወ/ሮ አልማዝ ሰለሞን እንደገለፁት ስልጠናው በአዋጁ ላይ የተካተቱትን አዳዲስ ነጥቦች፣ ለውጦች እና አፈጻጸም በተመለከተ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ያለመ መሆኑን የገለፁ ሲሆን ግብር ከፋዮች ህጉን ተረድተው በግንዛቤ ላይ የተመሰረተ የታክስ ተገዥነት ባህል እንዲያሳድጉ አሳስበዋል ።
ይህን ሊንክ በመጫንና የማህበራዊ ሚዲያ ገፆቻችንን በመቀላቀል መረጃዎችን በፈጥነት ያግኙ:-https://linktr.ee/mornwsto
8 269
+4
የክፍል አንድ ማጠቃለያ ፈተና ተሰጠ፡፡
ነሐሴ 14 ቀን 2018 ዓ.ም | አዲስ አበባ
የሰሜን ምዕራብ ዲስ አበባ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በ2019 በጀት ዓመት ለሁለተኛ ዙር የታክስ ትምህርት ሞጁላር ሰልጣኞችን በዛሬው እለት የክፍል አንድ ማጠቃለያ ፈተና ሰጠ፡፡
ይህን ሊንክ በመጫንና የማህበራዊ ሚዲያ ገፆቻችንን በመቀላቀል መረጃዎችን በፈጥነት ያግኙ:-https://linktr.ee/mornwsto
