es
Feedback
የፍትህ መድረክ/justice forum

የፍትህ መድረክ/justice forum

Ir al canal en Telegram

በዚህ ቻናል ህግ ነክ ዜናዎች፣ ከህግ ጋር የተያያዙ የተመራረጡ ህግ ነክ ጽሁፎች ይቀርባሉ። "የተሻለች አለም እንድትኖረን ሁላችንም ለፍትህ እንቁም"!

Mostrar más
2 713
Suscriptores
+124 horas
+137 días
+6730 días

Carga de datos en curso...

Nube de Etiquetas
Sin datos
¿Algún problema? Por favor, actualice la página o contacte a nuestro gerente de soporte.
Menciones Entrantes y Salientes
---
---
---
---
---
---
Atraer Suscriptores
julio '26
julio '26
+104
en 11 canales
junio '26
+77
en 5 canales
Get PRO
mayo '26
+128
en 9 canales
Get PRO
abril '26
+66
en 8 canales
Get PRO
marzo '26
+302
en 3 canales
Get PRO
febrero '26
+471
en 9 canales
Get PRO
enero '26
+128
en 5 canales
Get PRO
diciembre '25
+112
en 7 canales
Get PRO
noviembre '25
+83
en 6 canales
Get PRO
octubre '25
+115
en 3 canales
Get PRO
septiembre '25
+124
en 5 canales
Get PRO
agosto '25
+76
en 3 canales
Get PRO
julio '25
+70
en 7 canales
Get PRO
junio '25
+87
en 2 canales
Get PRO
mayo '25
+62
en 2 canales
Get PRO
abril '25
+163
en 12 canales
Get PRO
marzo '25
+113
en 5 canales
Get PRO
febrero '25
+117
en 5 canales
Get PRO
enero '25
+97
en 0 canales
Get PRO
diciembre '24
+107
en 2 canales
Get PRO
noviembre '24
+121
en 0 canales
Get PRO
octubre '24
+110
en 0 canales
Get PRO
septiembre '24
+84
en 0 canales
Get PRO
agosto '24
+99
en 0 canales
Get PRO
julio '24
+18
en 0 canales
Get PRO
junio '24
+26
en 1 canales
Get PRO
mayo '24
+20
en 0 canales
Get PRO
abril '24
+33
en 0 canales
Get PRO
marzo '24
+66
en 0 canales
Get PRO
febrero '24
+26
en 0 canales
Get PRO
enero '24
+277
en 0 canales
Get PRO
diciembre '230
en 0 canales
Get PRO
noviembre '230
en 0 canales
Get PRO
octubre '230
en 0 canales
Get PRO
septiembre '230
en 0 canales
Get PRO
agosto '230
en 0 canales
Get PRO
julio '230
en 0 canales
Get PRO
junio '230
en 0 canales
Get PRO
mayo '230
en 0 canales
Get PRO
abril '230
en 0 canales
Get PRO
marzo '230
en 0 canales
Get PRO
febrero '230
en 0 canales
Get PRO
enero '230
en 0 canales
Get PRO
diciembre '220
en 0 canales
Get PRO
noviembre '220
en 0 canales
Get PRO
octubre '220
en 0 canales
Get PRO
septiembre '220
en 0 canales
Get PRO
agosto '220
en 0 canales
Get PRO
julio '220
en 0 canales
Get PRO
junio '220
en 0 canales
Get PRO
mayo '220
en 0 canales
Get PRO
abril '220
en 0 canales
Get PRO
marzo '220
en 0 canales
Get PRO
febrero '220
en 0 canales
Get PRO
enero '220
en 0 canales
Get PRO
diciembre '210
en 0 canales
Get PRO
noviembre '210
en 0 canales
Get PRO
octubre '210
en 0 canales
Get PRO
septiembre '210
en 0 canales
Get PRO
agosto '210
en 0 canales
Get PRO
julio '210
en 0 canales
Get PRO
junio '210
en 0 canales
Get PRO
mayo '21
+273
en 0 canales
Fecha
Crecimiento de Suscriptores
Menciones
Canales
27 julio+1
26 julio+3
25 julio+2
24 julio+6
23 julio+4
22 julio+4
21 julio+1
20 julio+4
19 julio+10
18 julio+3
17 julio+2
16 julio+6
15 julio+2
14 julio+1
13 julio+3
12 julio+2
11 julio+3
10 julio+4
09 julio+5
08 julio+9
07 julio+18
06 julio0
05 julio+1
04 julio+2
03 julio+2
02 julio+3
01 julio+3
Publicaciones del Canal
#ሪፖርት ፦ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ አርሲ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች በተፈጸሙ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ላይ ኢሰመጉ ያዘጋጀውን ሪፖርት ይፋ አድርጓል። @tikvahethiopia

2
የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን የአፈፃፀም ችሎት መጀመሩን ያውቃሉ ? ******* ፌታይኮ የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን የተጣለበትን አገራዊ አደራ እና ህዝባዊ ኃላፊነት ይበልጥ ውጤታማ በሆነ መንገድ ለመወጣት ግልፅነትና ተጠያቂነት ያለው ቀልጣፋ የፍትህ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችሉ አዳዲስ አሰራሮችን በመዘርጋት ላይ ይገኛል። በዚሁ መሰረት ኮሚሽኑ የግብር ከፋዮችን እና የህዝብን እንግልት ለመቀነስ እንዲሁም ጉዳዮች በወቅቱና በቅልጥፍና ውሳኔ እንዲያገኙ ለማድረግ ሲባል ከዋናው ችሎት በተጨማሪ የአፈጻጸም ችሎት በመሰየም በማገልገል ላይ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ሰኞ፣ ረቡዕ እና አርብ ጠዋት እና ከሰዓት መደበኛ ችሎት የሚሰየም ሲሆን የአፈፃፀም ችሎት በየሁለት ሳምንቱ ማክሰኞ ጠዋት የሚቻል መሆኑን ለመግለፅ እንወዳለን፡፡ የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን ነፃና ገለልተኛነት ለፍትሐዊ የታክስ ሥርዓት ! የፌደራል ታክስ ይግባኝ ኮሚሽን የማህበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑ! ፌስ ቡክ፡- https://www.facebook.com/ftacofficial ቴሌግራም፡- https://t.me/ftac_official ትዊተር፡- https://twitter.com/federal_appeal ዩ ቱብ፡- https://www.youtube.com/channel/UCzpuuuXybdHh7BlgWXMVIGw
54
3
#ሪፖርት ፦ በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ አርሲ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች በተፈጸሙ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ላይ ኢሰመጉ ያዘጋጀውን ሪፖርት ይፋ አድርጓል። @tikvahethiopia
1
4
#ፍርድ ‎" የቀድሞ የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ዓለማየሁ ጢሞቴዎስ የ10 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶባቸዋል " - የሲዳማ ክልል ፍትሕ ቢሮ ‎ ‎የሲዳማ ክልል ፍትሕ ቢሮ እንዳስታወቀው
#ፍርድ ‎" የቀድሞ የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ዓለማየሁ ጢሞቴዎስ የ10 ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶባቸዋል " - የሲዳማ ክልል ፍትሕ ቢሮ  ‎ ‎የሲዳማ ክልል ፍትሕ ቢሮ እንዳስታወቀው የቀድሞ የሲዳማ ክልል ሰላም እና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊዎች  ዓለማየሁ ጢሞቴዎስ እና የቀድሞ ፖሊስ ኮሚሽነር የነበሩት ሽመልስ ቶማስ በሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ የእስራት ውሳኔ ተላልፎባቸዋል። ‎ ‎የሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት በቀድሞው የሲዳማ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ እና የፖሊስ ኮሚሽነር ላይ በክልሉ ፍትህ ቢሮ ከሳሽነት በቀረቡ ክሶች ላይ የጽኑ እስራት ውሳኔ አስተላልፏል። ፍርድ ቤቱ የሰውና የሰነድ ማስረጃ በማመሳከር  ተከሳሾቹን ጥፋተኛ ያላቸው፤ ኃላፊዎቹ ስልጣንን አላግባብ በመገልገል የሲዳማ ነፃነት ሠራዊት (ሲነሠ) የተባለ ታጣቂ ቡድን በማደራጀትና ተደራራቢ የሰብዓዊ መብት ጥሰት መፈጸማቸውን በማረጋገጥ ውሳኔ ማስተላለፉን ቢሮው አስታውቋል። ‎ ‎በዚህም መሰረት ፍርድ ቤቱ ዛሬ ሐምሌ 20/11/2018 ዓ.ም. በዋለው ችሎት አንደኛ ተከሳሽ አቶ ዓለማየሁ ጢሞቴስ በ10 ዓመት ከ5 ወር ጹኑ እስራት እና 4000 ሺ ብር እንዲቀጡ እንዲሁም ሁለተኛ ተከሳሽ አቶ ሽመልስ ቶማስ በ1 ዓመት ከ6 ወር ጽኑ እስራት እና 1 ሺህ ብር እንዲቀጡ ውሳኔ ማስተላለፉን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከቢሮው ያገኘው መረጃ ያመላክታል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሀዋሳ ሃምሌ 20 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia
43
5
ኤፕስቲን በዚህ ሁሉ ወቅት ሌሎች ሴቶችን እየመለመለ መቀጠሉ "በጣም ያሳፍራል" የምትለው እምባ እየተናነቃት ነው። አንድ አጋዥ ሠራተኛ ቢያንስ ሌላ አጋዥ ሠራተኛ ማምጣት ይጠበቅባታል። እንደነሱ ያሉ ወጣት ሴቶችን እንዲመለምሉ ይነገራቸው ነበር። "አንድም ሆነ አሥር ሰው ተባባሪ ነን" ትላለች። አሁን ላይ ታሪኳን መናገር የፈለገችው እንዴት ኤፕስቲን ሴቶችን እንደሚያጠምድ እና በወጥመዱ ልጆች ብቻ ሳይሆን አዋቂዎችም ተጠልፈው እንደሚወድቁ ለማሳወቅ እንደሆነ ትናገራለች። > "የብዝበዛ መረብ ዘርግቶ ነበር። ይህም ጠቅሞታል። እንደ ቢል ክሊንተን ያሉ ሰዎች ለእራት ቤቱ እየሄዱ ሲጨብጡት ስናይ 'እኔ ማነኝ ጥያቄ የማነሳው? ማን ስለሆንኩ ነው የምናገረው?' ብለን እናስባለን። ለጥቃቱ እውቅና የሚሰጥ ነው።" > አናያ እና ሳራ ለኤፕስቲን ተጎጂዎች ከተዘጋጀው ካሳ ተጠቃሚ ሆነዋል። ካሳው ተጎጂዎችን በገንዘብ ለመደገፍ የዋለ ሲሆን ማስረጃዎችም ተሰባስበዋል። > "በሕይወት ሳለ ይሄንን ለአንድም ሰው አልተነፈስኩም። አሁን ድምጼ አንዲትም ሴት ብትሆን ከበዝባዥ ግንኙነት እንድትወጣ ይረዳል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ። የተለየሁ ሰው አይደለሁም። ግን ከዚህ ጥቃት ለመትረፍ አቅሙን ማግኘት ችያለሁ። እኔ ማድረግ ከቻልኩ አንቺም ትችያለሽ።" >
93
6
አናያ በዚህ ክፉኛ አዘነች። ኤፕስቲንም ፍሎሪዳ፣ ፓልም ቢች ሄዳ እንድታገኘው ነገራት። በወቅቱ ተከስሶ ተይዞ የነበረ ቢሆንም፤ የዚያን ቀን ግን በፈቃድ ተለቅቆ ነበር (የተከሰሰው አንዲት ልጅ በሐሰተኛ መታወቂያ አሳስታው እንደሆነ በወቅቱ ሲናገር ተደምጧል)። አናያ በፖሊስ መዝገብ ላይ ስሟን ጽፋ ከኤፕስቲን ጋር ተገናኘች። በዚያም ከጀርባ በሚገኝ ክፍል ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ወሲባዊ ጥቃት ፈጸመባት። (በፖሊስ ይዞታ ላይ ሳለ ቢያንስ ሁለት ሴቶች ወሲባዊ ጥቃት እንዳደረሰባቸው ተናግረዋል።) አናያ ላይ ወሲባዊ ጥቃት አድርሶ በጀርባ በር ካስወጣት በኋላ ውጪ ላሉ አጋሮቹ "ዐይን አፋር ናት" እያለ መቀለድ ጀመረ። ሁሉም ስለሳቁባት ራሷን መውቀሷን ትናገራለች። > "ምናልባት የተፈጠረው ነገር ችግር የለውም ብዬ አሰብኩ። ችግሩ እኔ ለነገሩ ምላሽ የሰጠሁበት መንገድ እንደሆነ ተሰማኝ። ሩሲያዊ ቤተሰቦቼ ነገሮችን ስለሚያጠብቁ እና በአስተዳደጌ ምክንያት መሰለኝ። ችግር ያለብኝ ግን እኔ ሳልሆን አሱ ነበር።" > የኤፕስቲን ፋይሎች ይፋ ሲሆኑ በትክክል የተከሰተውን ነገር እንዳወቀች አናያ ትናገራለች። ሞዴሎችን የሚመለምለው ተቋም ኃላፊን ብታገኝም አብረዋት እንደማይሠሩ የገለጹላት ኤፕስቲን ባለው ወቅት ሳይሆን ከዓመት በኋላ ነው። ከኤፕስቲን ጋር አብራ ወራት ስታሳልፍ ለውድቀት እያዘጋጃት እንደነበር ታምናለች። "እየመለመለኝ ነበር" የምትለው አናያ፤ ኤፕስቲን ደካማ በሆነችበት እና ብቻዋን በሆነበችበት ጊዜ ጥቃቱን መፈጸሙን ትገልጻለች። ቀስ በቀስ የሚደረግ ምልመላ ዒላማ የተደረጉ ሰዎች እንዳይነቁ እና አደጋ ውስጥ መውደቃቸውን እንዳይገነዘቡ ያደርጋል ስትል አናያ ትናገራለች። የሥነ-ልቦና ባለሙያዋ ዶ/ር ታራ *"ከዕይታ ውጪ የሆነ ቦምብ ማለት ነው"* ሲሉ ይገልጹታል። 'ኔክስት ኤጀንሲ' ኃላፊ ፌዝ ኬትስ ጠበቃ በሰጡት መግለጫ፤ ኃላፊቷ በኤፕስቲን የሰዎች ሕገ-ወጥ ዝውውር ውስጥ እጃቸው አለ ማለት ወይም ስለ ጉዳዩ ያውቃሉ ማለት "ሐሰተኛ እና ስም ማጥፋት" መሆኑን ገልጸዋል። የኤጀንሲውን ውሳኔ ለአናያ የሚያሳውቀው ኤፕስቲን ነው መባሉ "ያልተለመደ፣ ሐሰተኛ እና ማስረጃ የሌለው" መሆኑን ጠቅሰው፣ ኤጀንሲው ሞዴሎቹን የሚመርጠው በራሱ መንገድ እንደሆነ እና የኤፕስቲን ፈቃድ እንደማያስፈልገው አክለዋል። ከአንድ ጊዜም በላይ ሞዴሎችን ወደ ኤጀንሲው አለመቀበል የተለመደ አሠራር መሆኑንም ጠቅሰዋል። ### በሥራ ሰበብ የተፈጠረ ጥገኝነት አናያ ሞዴል የመሆን ዕድል እንዳላት ኤፕስቲን መንገሩን ቀጠለ። ኤምሲ2 (MC2) ከተባለ የሞዴሎች ተቋም መሥራች ዣን-ሉክ ብሩኔል ጋር አስተዋወቃት (ኤፕስቲን ተቋሙን በገንዘብ እንደሚደግፍ ግን አልነገራትም)። ተቋሙ አሁን ላይ በማያሚ እና ኒው ዮርክ ያሉትን ቅርንጫፎች የዘጋ ሲሆን፤ እስራኤል የሚገኘው ቅርንጫፍ ከኤፕስቲን ጋር ግንኙነት እንደሌለው ገልጿል። በዚህ ኤጀንሲ በኩል ምንም ሥራ እንዳላገኘች አናያ ትናገራለች። ነገር ግን ቀጥታ ለሥራ ለመመዝገብ ወደ ፓልም ቢች እንድትሄድ በወኪሏ ይነገራታል። ፓልም ቢች ስትሄድም ኤፕስቲን ብዝበዛውን ቀጠለ። ከዚያም የሞዴልነት ኢንዱስትሪ ስለመሞቱ እና እሷም ስኬታማ ስላልሆነች ከእሱ ጋር እንድትሠራ ጠየቃት። *"እኔ እውነተኛ ቢዝነስ አስተምርሻለሁ። ወደ ተለያዩ ቦታዎች ትጓዣለሽ፤ በመላው ዓለም ጠቃሚ ሰዎችን ትተዋወቂያለሽ"* አላት። አናያ የኤፕስቲን ረዳት ሆኖ መሥራት ምኞቷ አልነበረም፤ ስለ ንግድም ምንም እንዳላስተማራት ትናገራለች። ኤፕስቲን ሥራ እስከሚሰጣት ከመጠበቅ ውጭ አማራጭ አልነበራትም። ስትጠብቅም ምንም ሳታደርግ በመቀመጧ ያሸማቅቃት ነበር። አንዳንዴ ስልክ የማንሳት ወይም የመጣውን እንግዳ ማንነት የመናገር ተራ ሥራ ይሰጣታል። የኤፕስቲን ረዳቶች ሰባቱንም ቀን ለ24 ሰዓት በሥራ ላይ እንዲሆኑ ይጠበቃል። አናያ ለምሳ ከሰው ጋር በተገናኘች ወቅት ኤፕስቲን እንዴት እንደተበሳጨ እና ያለ እሱ ፈቃድ እንዳትወጣ እንዳስጠነቀቃት ታስታውሳለች። አናያ ኤፕስቲን ላይ ሙሉ በሙሉ ጥገኛ ሆነች። ስትታመም "የጤና መድኅንሽ እኔ ነኝ" ይላታል። የባንክ አካውንት አልነበራትም፤ ቤት እንዳትከራይም የግል ሰነዶች አልነበሯትም። ማንሀተን ካለው ቤት የተወሰነ ጊዜ እንዳባረራትና "የት እንደምትኖሪ አስቢ" እያለ ማስፈራራቱን ትናገራለች። ይህም ቁጥጥሩን የሚያጠናክርበት መንገድ ነበር። ከዓመታት በኋላ በቪዛዋ ምክንያት ክፍያ ያስፈልጋት ስለነበር የተወሰነ ደመወዝ ይሰጣት ጀመር። "አትጨነቂ፤ ሁሌም እደግፍሻለሁ" እያለ ወሲባዊ ብዝበዛውን ቀጠለ። ኤፕስቲን አቅሙን እና እነማንን እንደሚያውቅ ያሳያት ነበር። ሳራ ኬለንም በተመሳሳይ *"ከእሱ በሚጻረር መንገድ መሄድ ሕይወቴን እንደሚያስከፍለኝ እንዳውቅ አድርጓል"* በማለት በአሜሪካ ምክር ቤት ቀርባ ተናግራለች። *"ቤተሰብ አልነበረኝም፤ ገንዘብ አልነበረኝም፤ አልተማርኩም። የተሻለ እንደሚገባኝ አላወቅኩም ነበር"* ስትልም ገልጻለች። ### የብዝበዛው መረብ እና ሥነ-ልቦናዊ ቁጥጥር አንድ የኤፕስቲን ተባባሪ ሠራተኛ ያመለጠችበትን ወቅት አናያ ታስታውሳለች። ለአናያ ስትደውልላት ግን ፍርሃት ገባት፤ ስልኩን ኤፕስቲን ስለሚከታተል ማውራታቸውን እንዳይደርስበት ሰጋች። ኤፕስቲን የግል መርማሪ ቀጥሮ ሠራተኛዋን እንዲከታተል አደረገ፤ 700 ሺህ ዶላር እዳ እንዳለባትም ይናገር ነበር። ኤፕስቲን እያስተላለፈ የነበረው መልዕክት "አምልጣችሁ ብትጠፉ እዳ ስለሚኖርባችሁ አሳድጄ እይዛችኋለሁ" የሚል ነው። ኤፕስቲን ሴቶቹን ያሰረው በእዳ ብቻ አይደለም። አናያን የእርቃን ምሥሏ እንዳለው ያስታውሳት ነበር። በአንድ ወቅት ረዳት ሠራተኞቹን በአጠቃላይ ከወገባቸው በላይ እርቃናቸውን ሆነው በደስታ ሲዘልሉ እንዲቀረጽ አደረገ። *"አሁን ከእኔ በተቃራኒው አትቆሙም"* እንዳላቸውም ታስታውሳለች። *"ቪድዮ ለመቀረጽ ፈቃድ አልሰጠንም ማለት አይችሉም። ማስረጃዎች የሚሰበስብበት መንገድ ነበር"* ትላለች። ሳራ ኬለን በምክር ቤት በሰጠችው ቃል፤ ኤፕስቲን የሠራተኞቹን ራስን የመግዛት አቅም በማፈራረስ የተካነ ነበር። "የምስጋና ደብዳቤ" በሚል ኢሜል እንዲልኩለት ያደርጋል። አናያ "አመሰግናለሁ" ማለት ብቻ በቂ ላይሆን እንደሚችል በማሰብ ትፈራ ነበር። *"እነዚህ ኢሜሎች ያስፈለጉት 'በየጊዜው እያመሰገናችሁኝ ከሆነ እንዴት እኔን ልትገዳደሩ ትችላላችሁ' ለማለት ይመስለኛል።"* ሠራተኞቹ እርስ በራሳቸው እንዲጣሉም ያደርግ ነበር። *"ሰነፍ እና እርባና ቢስ ስለሆንሽ ተናዳብሻለች"* ብሎ ስለ አንደኛዋ ሴት ለሌላኛዋ ይነግራል። *"እኔ ግን አንቺን ነው የምደግፈው"* ሲልም ክፍፍል ይፈጥራል። ሴቶቹ ትስስር እንዳይፈጥሩ በማድረግ በቀላሉ መቆጣጠር የሚችልበትን መረብ ዘርግቷል። አካል የሚያጎድል ቀዶ-ሕክምና አናያ ሆዷ ላይ ጠባሳዎች ይታያሉ። ወጣት ሳለች ትንሽ ንቅሳት ነበራት። ኤፕስቲን ንቅሳቱን እንድታጠፋው ዶክተር ይዞ መሄዱን ትናገራለች። በጨረር ንቅሳቱን ማጥፋት ጊዜ ስለሚወስድ ንቅሳቱ ያለበት ቆዳ እንዲነሳ ኤፕስቲን አዘዘ። *"ይሄን ማሰብ የምችለው እኔ ብቻ ነኝ"* ማለቱን ታስታውሳለች። ቀዶ ሕክምናው ጠባሳ ጥሎባታል። ከዓመት በኋላ በውጤቱ ደስተኛ ስላልሆነ ድጋሚ ቀዶ ሕክምና እንዲደረግላት ወስኗል።
79
7
## "ማስፈራሪያ፣ ቁጥጥር፣ አካል የሚያጎድል ቀዶ ሕክምና" - በጄፍሪ ኤፕስቲን ለዓመታት ብዝበዛ የደረሰባት ሴት ታሪክ የወሲብ ወንጀለኛው ጄፍሪ ኤፕስቲን በሞተበት ሳምንት አናያ (ስሟ ተለውጧል) በሯ ተንኳኳ። ኒው ዮርክ የሚገኘውን ቤቷን ያንኳኳው የኤፕስቲን ወንድም ማርክ ነበር። ማርክ ቤቱን ጥላ መሄድ እንዳለባት እንደነገራት ትገልጻለች። በኒው ዮርክ፣ ማንሀተን የሚገኘው ቤቷ ኤፕስቲን ጥቃት ያደረሰባቸውን ሴቶች የሚያኖርበት ነበር፤ አናያም ወዲያውኑ ከቤቱ ወጣች። ማርክ ግን ወንድሙ ኤፕስቲን ጥፋቶች ስለመፈጸሙ እንደማያውቅ ይናገራል። > "ለዓመታት ጥቃት ሲደርስብኝ እንደነበር አሁንም ለማመን እቸገራለሁ። ቤቱ ውስጥ ታስሬ አልተቀመጥኩም አይደል? ቤቱ ተቆልፎብኝ አልኖርኩም አይደል? ምናልባት ሰንሰለቱ አይታይ ይሆናል እንጂ አስሮኝ ነበር።" - አናያ > ኤፕስቲን ሕጻናትን ለወሲብ ንግድ በማዘዋወር ክስ ቀርቦበት ሳለ እ.አ.አ በ2019 ሞቷል። ኤፕስቲን ሰዎች ተታልለው ወይም ተገድደው አባል የሚሆኑበት ቡድን (Cult) መሪ እንደነበር አናያ ታምናለች፤ እሷም የዚሁ ቡድን አባል ነበረች። አናያ ኤፕስቲን ለዓመታት ተጎጂዎችን እንዴት ይዞ እንዳቆየ ለቢቢሲ ተናግራለች። ኤፕስቲንን የሚረዱ ብዙ ሴቶች እንደነበሩም ገልጻለች። የሚያኖራቸው ኤፕስቲን ሲሆን ያለማቋረጥ ያገለግሉታል። ከዚህም ባሻገር ወሲባዊ ጥቃት ያደርስባቸው ነበር። ሥራ ታገኛላችሁ በሚል ማታለያ ተስበው ኤፕስቲንን ሲቀርቡ ሕይወታቸውን ይቆጣጠረዋል። ማንኛውንም ድክመት ካገኘባቸውም ይጠቀምበታል። ገንዘባቸውን ከመቆጣጠር ባሻገር ከማን ጋር እንደሚገናኙ ይወስናል፤ በሥነ-ልቦናም ያንቋሽሻቸዋል። ሰውነታቸውን አባዜ እንዳለበት ሰው አጥብቆ ይቆጣጠር እንደነበርና አላስፈላጊ የሆነ እንዲሁም መልክን የሚያጠፋ ቀዶ ሕክምና እንዲያደርጉ ያስገድዳቸው እንደነበር አናያ ታስታውሳለች። የኤፕስቲን ረዳት ሠራተኛ የነበረችው ሳራ ኬለን ከአናያ ጋር ተመሳሳይ ምስክርነት ትሰጣለች። ለአሜሪካ ምክር ቤት በሰጠችው ቃል፤ ኤፕስቲን ለረዳት ሠራተኞቹ ራሱን የሚያቀርበው ሊያድናቸው እንደመጣ ሰው አድርጎ ነው። > "ሰዎች በራሳቸው ያላቸውን የመወሰን አቅም እና ኃይል ማክሰም ይችላል። ይህም እሱ ላይ የበለጠ እንዲንጠለጠሉ ያደርጋል።" - ሳራ ኬለን > እንዲህ ባለ ባህሪ ያላቸው ሰዎች የሚያታልሉት ልጆችን ብቻ እንደሆነ ቢታመንም፣ አዋቂዎችንም ሊያስት እንደሚችል የሥነ-ልቦና ባለሙያዋ ዶ/ር ታራ ኩዊን-ክሪሎ ይናገራሉ። በማስገደድ የሚቆጣጠሩ ሰዎች ጉዳት ካደረሱባቸው ጋር አብረው የሠሩት ባለሙያዋ፣ የትኛውም ሰው ተጋላጭ ሊሆን እንደሚችል ያስረዳሉ። ### ዒላማ ተደርጎ መጠመድ ኤፕስቲን እ.አ.አ በ2008 ታዳጊ ሴትን በመበዝበዝ ተከስሷል። የማሳጅ ሠራተኛ እንደምትሆን ነግሮ በማታለል ቤቱ ወስዷታል። ከዚያ በኋላ በሩሲያ እና በምሥራቅ አውሮፓ የሚኖሩ አዋቂ ሴቶችን ማጥመድ ጀምሯል። አናያ እንደምትለው እሷ እና ሌሎችም ኤፕስቲን የመለመላቸው ሴቶች ታዳጊ ይመስሉ ነበር። አናያ ያደገችው ሩሲያ ውስጥ ነው። ወላጆቿ "ስኬት የምታገኚው በትምህርት ነው" እያሉ በጥብቅ ቁጥጥር ነው ያሳደጓት። ነገር ግን ውስን የሥራ ዕድል ብቻ ስለነበር ዲግሪዋን ይዛ ሞዴል ለመሆን ከአገሯ ወጣች። በአውሮፓ እንደ ፌንዲ እና ሻኔል (Chanel) ላሉ ቅንጡ ብራንዶች ሠርታለች። ጓደኞች እና የሚደግፏት ወዳጆች ነበሯት። ቤተሰቧን ባሻት ጊዜ ሄዳ መጠየቅ ትችልም ነበር። ከኤፕስቲን ጋር የተገናኘችው በ20ዎቹ ዕድሜ ሳለች ፓሪስ ወደሚገኝ ኤጀንሲ ሄዳ ነው። በዚያም ሞዴሎች የሚመለምል ዳንኤል ሲያድ የሚባል ሰው ተዋወቀች። "በሞዴሎች ዓለም ባልተለመደ ሁኔታ ብሩህ አእምሮ እንዳላት" ዳንኤል ነገራት። የፋሽን ቢዝነስ ውስጥ ከሚያውቀው ሰው ጋር ሊያስተዋውቃት እንደሚፈልግም አሳመናት፤ ይህ ሰው ኤፕስቲን ነበር። ወደ ኤጀንሲው ባትሄድ ኖሮ ምን ሊፈጠር እንደሚችል አዘውትራ ታስባለች። ዒላማ እንደተደረገችም ታምናለች። "ሁሉንም ነገር ቀድመው ነው ያዘጋጁት። ዳንኤል ሰው አዘዋዋሪ ነው" ትላለች። የዳንኤል ስም በኤፕስቲን ሰነዶች ውስጥ ከሺህ ጊዜ በላይ ተጠቅሷል (የአሜሪካ መንግሥት ያለፈው ታኅሣሥ የኤፕስቲን ሰነዶችን ይፋ ለማድረግ መወሰኑ ይታወሳል)። የዳንኤል ጠበቃ አስተያየት መስጠት እንደማይችል ቢናገርም፣ ከዚያ በፊት እንደገለጸው ግን ኤፕስቲን አደገኛ መሆኑን አያውቅም ነበር። አናያ ለመጀመሪያ ጊዜ ኤፕስቲንን የተዋወቀችው 18 ክፍሎች ባሉት የፓሪስ መኖሪያው ውስጥ ነው። ቢል ክሊንተንን ጨምሮ ከሌሎች የዓለም መሪዎች ጋር የተነሳቸው ፎቶዎች በቤቱ ተሰቅለዋል። በክፍሉ ሌሎች ሁለት ሴቶች ስለነበሩ አናያ ምቾት ተሰማት። አንዷ ሴት ሩሲያዊት ስትሆን፣ ሌላዋ የቀድሞው የኤፕስቲን የሴት ጓደኛ የነበረች ምሥራቅ አውሮፓዊት ናት። አናያ ልብሷን እንድታወልቅ እና ሰውነቷ ለሞዴሊንግ ይሆን እንደሆነ ለመቃኘት ኤፕስቲን ጠየቀ። በውስጥ ሱሪዋ ብቻ ሆና ቆመች። ኤፕስቲን "ሰውነቷ ጥሩ አቋም ላይ ስላልሆነ ስፖርት መሥራት እንድትጀምር" እንደነገራት እና "ሰነፍ" እንዳላት ታስታውሳለች። ሞዴሎች እንዲህ ያለ አስተያየት እንደሚሰጣቸው ታውቅ ስለነበር፣ ጠንክራ ከሠራች ከትክክለኞቹ ሰዎች ጋር እንደሚያስተዋውቃት አመነች። ኤፕስቲን ስለ ቤተሰቦቿ እና ምን እንደሚያስደስታት ጠየቃት። "ለምን ሞዴል መሆን እንደፈለግኩ እና በሕይወት ምን ማሳካት እንደምፈልግ ጠየቀኝ። እንዲህ ያሉ ጥያቄዎች በሞዴሎች ዓለም የተለመዱ አይደሉም" ትላለች። በርካታ ሴቶች ለቢቢሲ እንደገለጹት ኤፕስቲን የሚያስደስታቸውን ነገር የሚጠይቃቸው ኋላ ላይ መረጃውን እነሱን ለመጉዳት ስለሚጠቀምበት ነው። ኤፕስቲን "ጎበዝ ልጅ መሆንሽን ማየት እችላለሁ። ተጠራጣሪም ነሽ። እኔ አብሬሽ መተኛት አልፈልግም" እንዳላት ታስታውሳለች። ይሄንን ስትሰማ ዘና ማለት ጀመረች። "ይሄ ሰው ድንቅ ነው። የውስጤን ማወቅ ይችላል" ብላ አሰበች። ### ረዘም ያለ የ"ምልመላ" ሒደት ይሄ ሁሉ የምልመላው መጀመሪያ ነበር። ለወራት ያህል የቀጠለ ሒደት ሲሆን፣ ለአናያ ብዙ እውነት የማይሆኑ ቃሎች እየተገቡላት ነበር። ለአንድ ዓመት ያህል ኤፕስቲን የሚፈልገው ዓይነት ሰውነት እንዲኖራት ያለመታከት ትሠራ ጀመር። የኤፕስቲን ዋና አጋዥ ሠራተኛ ሌዝሊ ግሮፍ የዕለት ከዕለት ውሎ መዝገቡን ትቆጣጠር ነበር፤ አናያም ምን ላይ እንደደረሰች የሚገልጽ ኢሜል ትልካለች። ኤፕስቲንም አናያ እርቃኗን ፎቶ ተነስታ እንድትልክ እና ይሄንን ለማድረግ "ዐይን አፋር" መሆን እንደሌለባት በመግለጽ ጫና ያሳድር ነበር። ቃል እንደገባውም አናያን 'ኔክስት ኤጀንሲ' (Next Agency) ከተባለ የሞዴል ተቋም ኃላፊ ፌዝ ኬትስ ጋር አገናኛት። የተነጋገሩት ለ30 ደቂቃ ሲሆን ውጤቱን ኤፕስቲን እንደሚያሳውቃት ተነገራት። ሆኖም፣ የሞዴል ኤጀንሲው አናያ "ለኒው ዮርክ ገበያ ብቁ ስላልሆነች እንደማይፈልጋት" እና የሰውነት ቅርጿ "የተስተካከለ" እንዳልሆነ እንደገለጸ ኤፕስቲን ነገራት።
64
8
የፍትሕ ሚኒስቴርን የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገፆችን እና ድረ-ገፅን ይቀላቀሉ Website https://www.justice.gov.et Facebook https://www.facebook.com/MOJEthiopia/ (x) Twitter https://x.com/MOJEthiopia YouTube channel https://youtube.com/@fdreministryofjustice...3701... Telegram https://t.me/fdreattorneyGeneral_externabo
1
9
የጋራ ንብረት ባለሀብትነት (Joint ownership) መግቢያ በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግሥት አንቀፅ 40(1) መሠረት ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ዜጋ የግል ንብረት ባለቤት የመሆን መብት እንዳለው በግልፅ ተደንግጎ ይገኛል። ይኸውም ዜጎች በጉልበታቸው፣ በመፍጠር ችሎታቸው ወይም መዋዕለ-ንዋያቸውን አፍስሰው ያፈሩት ተጨባጭ የሆነና ተጨባጭነት ሳይኖረው ዋጋ ያለውን ነገር ያጠቃልላል። የንብረት መብት ለሕዝብ ጥቅም አስፈላጊ ሆኖ ካልተገኘ በስተቀር ንብረት የማፍራት በንብረት የመጠቀም ወይም የሌሎችን ዜጎች መብቶች እስካልተቃረነ ድረስ ንብረትን የመሸጥ፣ የማውረስ ወይም በሌላ መንገድ የማስተላለፍ መብቶችን ያካትታል። በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገ መንግስት አንቀፅ 40 (3) መሰረት የገጠርም ሆነ የከተማ መሬትናና የተፈጥሮ ሀብት የባለቤትነት መብት የመንግሥትና የሕዝብ ብቻ እንደሆነ የተደነገገ ቢሆንም ከእነዚህ በሕገ መንግሥቱ እና በሌሎች ሕጎች ገደብ ከተደረገባቸው የንብረት ዓይነቶች ውጭ ያሉ የንብረት አይነቶችን ሁሉም ዜጋ በግሉም ሆነ በጋራ ባለሀብትነት ሊይዝ ይችላል። በዚህ ጽሐፍ የጋራ ባለሀብትነትን ምንነት፣ ምንጮች፣ ወሰን፣ ዓይነት፣ መብትና ግዴታዎች፣ የጋራ ሀብትን ስለማስተዳደር እና የጋራ ባለሀብትነት ቀሪ ስለሚሆንባቸው ሁኔታዎች አጠር ባለ መልኩ ዳሰሳ ተካሂዷል። የጋራ ንብረት ባለሀብትነት ምንነት እና ምንጭ የጋራ ባለቤትነት ማለት ሁለት እና ከዚያ በላይ የሆኑ ሰዎች በተወሰነ ጊዜ በአንድ ንብረት ላይ የሚመሰርቱት አንድ የባለቤትነት አይነት ነው፡፡ በሁለትና ከዚያም በላይ ባሉ ሰዎች መካከል የጋራ ባለሀብትነት ግንኙነት አለ ለማለት የጋራ ባለሀብቶች ነን በሚሉት ሰዎች መካከል የባለቤትነት ጥቅም (ownership interest) ያላቸው ሰዎች መሆንና የጋራ ባለሀብትነታቸው በተመሳሳይ ንብረት ላይ የተመሰረተ መሆን ይኖርበታል፡፡ የጋራ ባለቤትነት በንብረት ሕግ የሚመራ ሲሆን እንደ ሽርክና (በንግድ ሕግ የሚመራ) እና የባልና ሚስት የጋራ ሀብት (በቤተሰብ ሕጉ የሚመራ) ከመሳሰሉት ሀብት በጋራ ከሚተዳደርባቸው ሁኔታዎች ይለያል፡፡ የጋራ ባለሀብትነት መብት በሁለት እና ከዚያ በላይ በሆኑ ሰዎች መካከል በሚደረግ ውል ወይም ከሕግ ሊመነጭ ይችላል፡፡ ሰዎች የጋራ ባለቤትነት በስምምነትና በሙሉ ፍቃዳቸው እንዲመሰርቱ ሕግ ቅድሚያ ይሰጣል፡፡ ይህንንም ከፍትሐብሔር ሕግ አንቀጽ 1258 ድንጋጌ ለመረዳት ይቻላል፡፡ በሌላ በኩል ለምሳሌ ከአንድ ሰው በላይ በባለቤትነት ተይዘው የነበሩ ንብረቶች በሚቀላቀሉበት (በሚዋሃዱበት) ጊዜ መልሶ እንደነበሩ ለማድረግ የማይቻል ወይም ከፍተኛ ኪሳራ የሚያስከትል በሚሆንበት ጊዜ ሕግ የቀድሞ ባለሀብቶችን ለተቀላቀለው ወይም ለተዋሃደው ነገር የጋራ ባለቤት እንደሚያደርጋቸው ከፍ/ብ/ሕ/ቁ 1183 ድንጋጌ መገንዘብ ይቻላል። በሌላ በኩል አንቀጽ 1060 (2) ድንጋጌን የተመለከትን እንደሆነ የጋራ ባለሀብትነት ከሰዎች ስምምነት ባለፈ ከሕግም ሊመነጭ እንደሚችል በሚገባ ያስገነዝበናል። የጋራ ባለሀብቶች መብትና ግዴታዎች በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1260 መሠረት አንድ የጋራ ባለሀብት ያለውን ድርሻ የመሸጥ፣ በእዳ መያዣነት የመስጠት፣ በስጦታ የመስጠት ወዘተ መብት አለው፡፡ የጋራ ባለሀብቶች ባላቸው ድርሻ ላይ በብቸኝነት የማዘዝ መብታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ በጋራ በተያዘው ነገር ላይ የሌሎችን መብት በማይጎዳ ሁኔታ በነገሩ የመጠቀምና የፍሬውም ባለቤት የመሆን መብት ያላቸው ስለመሆኑ ከፍ/ብ/ሕ/ቁ 1263 እና 1264 ንባብ መረዳት ይቻላል፡፡ ከጋራ ባለሀብቶች መብትና ግዴታ ጋር በተያያዘ አጽንኦት ሊሰጠው የሚገባው አንኳር ጉዳይ የጋራ ባለሀብቶች ንብረቱ ላይ ያላቸውን መብት ተግባራዊ የሚያደርጉት የሌላኛውን የጋራ ባለሀብት መብት በማይጎዳ ሁኔታ መሆን እንደሚገባው ነው ፡፡ የጋራ ሀብት አስተዳደር የጋራ ንብረት አስተዳደር በዋናነት በጋራ ባለሃብቶች ሥምምነት የሚከናወን ሲሆን በፍትሐብሔር ሕጉ የተቀመጡት ድንጋጌዎች ሊተገበሩ የሚችሉት በጋራ ባለሀብቶች መካከል የንብረታቸውን አስተዳደር አስመልክቶ የመተዳደሪያ ደንብ በማይኖርበት ወቅት ወይም የመተዳደሪያ ደንቡ ቢኖርም ጉድለት ያለበት ወይም አስገዳጅ ከሆኑ የሕጉ ድንጋጌዎች በሚጋጭበት ወቅት ነው፡፡ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1265 (1) እና ተከታይ ድንጋጌዎች መሠረት በአስተዳደራዊ ጉዳዮች ሁሉም የጋራ ባለሀብቶች ተሳትፎ የማድረግ መብት አላቸው፡፡ የጋራ ንብረቱ የዕለት ተዕለት አሥተዳደራዊ ውሳኔ የጋራ ባለሀብቶች በተሳተፉበት በአብላጫ ድምፅ ይወሰናል፡፡ ይሁን እንጅ ድምፅ የሚቆጠረው ባለው የድርሻ ልክ ነው፡፡ በመሆኑም ውሳኔ ለማሳለፍ የንብረቱን ከግማሽ በላይ ድርሻ ያላቸው ባለሀብቶች ድምፅ መስጠት ያለባቸው ስለመሆኑ ከፍ/ብ/ሕ/ቁ 1265(2) ድንጋጌ መገንዘብ ይቻላል። ሌላው በፍ/ብ/ሕ/ቁ1266 መሠረት የጋራ ንብረት የሆነውን ነገር ለመሸጥ፣ ለማስተላለፍ፣ በዋስትና ለማስያዝ እና የተመደበበትን አገልግሎት ለመለወጥ የሁሉም የጋራ ባለሀብቶች የሙሉ ድምፅ ስምምነት ያስፈልጋል። ይሁን እንጂ ይህ ድንጋጌ ቢኖርም አንድ የጋራ ባለሀብት የጋራ ንብረት የሆነውን ተንቀሳቃሽ ወይም የማይንቀሳቀስ ነገር በጨረታ እንዲሸጥ ወይም እንዲከፋፈል እንደ ቅደም ተከተላቸው ፍርድ ቤት አቤቱታ ሊያቀርብ እንደሚችል በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1271 እና 1272 ስር ተደንግጓል። ሌላው ንብረቱን ለማስተዳደር የሚወጣው ወጪን በተመለከተ ባለሀብቶች ባላቸው ድርሻ ልክ የሚሰራጭ/የሚከፋፈል ነው፡፡ የጋራ ባለሀብትነት ቀሪ መሆን የጋራ ባለሀብትነት በተለያዩ ምክንያቶች ቀሪ ሊሆን እንደሚችል ከፍትሐብሔር ሕጉ መረዳት የሚቻል ሲሆን ለአብነትም የሚከተሉት ሁኔታዎች የጋራ ባለሀብትነቱን ቀሪ ያደርጉታል፡፡ * የጋራ ባለሀብቱ ድርሻውን ለሌሎቹ ባለድርሻዎች በነፃ ፈቃዱ የለቀቀ እንደሆነ (የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1262 እና 1191) * የጋራ ሀብቱ ክፍፍል (partition) ሲደረግ (የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1264) * ተቃራኒ ስምምነት ቢኖርም የሚንቀሳቀስ ንብረት ሲሆንና የጋራ ባለሀብቱ በሚያቀርበው ጥያቄ ንብረቱ በግልፅ ሀራጅ ሲሸጥ (የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1264) * የጋራ ሀብቱ የማይንቀሳቀስ ሆኖ ተቃራኒ ስምምነት ከሌለና ለመከፋፈል የማይቻል ከሆነ ወይም ንብረቱን መሸጥ ተስማሚ አይደለም ተብሎ በፍርድ ቤት ካልተወሰነ በስተቀር የጋራ ሃብቱ ሲሸጥ ወይም ሲከፋፈል (የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1272) * የጋራ ባለሀብቶቹ በራሳቸው ስምምነት ውላቸው እንዲቀር ሲያደርጉ ወይም ሕጉ በሚያዘው መሠረት የጋራ ሃብቱ ክፍፍል ሲጠናቀቅ፡፡ ለምሳሌ የጋራ ሃብቱ የውርስ ሃብት በሚሆንበት ጊዜ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1079 እና ተከታዮቹ መሠረት የንብረቱ ክፍፍል ሲጠናቀቅ * ንብረቱ ሲበላሽ ወይም ሀልዎቱ (መኖሩ) ሲጠፋ፣ በሕግ መሠረት ሀብትነቱ ለሌላ ሰው ሲተላለፍ (የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1188፣ 1889) የጋራ ባለሀብትነት ቀሪ ይሆናል፡፡ ማጠቃለያ በአጠቃላይ በሕግ የተቀመጡ ገደቦች እንደተጠበቁ ሆኖ ሁሉም ዜጋ በግሉም ሆነ በጋራ ንብረት የማፍራት እና ከንብረቱ የሚገኝን ጥቅም የመጠቀም መብቱ የተጠበቀ ሲሆን በጋራ ባለሀብትነት የሚያዙ ንብረቶች ደግሞ በጋራ ባለንብረቶቹ መካከል የጋራ የሆነ የጥቅም እና ግዴታ ቁርኝት የሚፈጥሩ ናቸው፡፡ በንቃተ ሕግና ሥልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ
79
10
የፋይናንስ አገልግሎት የሕግ መድብል እና የፍትሐ ብሔር ፍትሕ ፖሊሲ ዝግጅት የአፈጻጸም ደረጃ ተገመገመ **************************** የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ፍትሕ ሚኒስቴር የሕግና ፍትሕ አገልግሎት ዘርፍ የፋይናንስ አገልግሎት የሕግ መድብል ረቂቅ ዝግጅትና የፍትሐ ብሔር ፍትሕ ፖሊሲ የማዘጋጀት ሥራዎች የደረሱበት የአፈፃጸም ደረጃ ተገምግሟል። በውይይቱ ላይ እንደተብራራው፣ አዲሱ የንግድ ሕግ (አዋጅ ቁጥር 1243/2013) ከ60 ዓመታት በላይ ሲያገለግል የነበረውን የቀድሞ የንግድ ሕግ ተክቶ በሥራ ላይ ሲውል፣ የባንክ ሥራ፣ የገንዘብ ሰነዶች እና የመድን ዘርፎች ካላቸው ልዩ የሕግ ይዘትና ባህሪ አንጻር ከንግድ ሕጉ ተነጥለው በልዩ የፋይናንስ አገልግሎት የሕግ መድብል (Financial Service Code) እንዲመሩ ተወስኗል። ይህንን ተከትሎም ከመነሻ ጥናቱ ጀምሮ ባለድርሻ አካላትን ያካተተ አርቃቂ ኮሚቴ ተዋቅሮ ሲሠራበት የቆየ ሲሆን፣ ሕጉን የማርቀቅ ሥራው በ2018 በጀት ዓመት እንደ አንድ ዋና የትኩረት አቅጣጫ ተይዞ በከፍተኛ ትኩረት ሲከናወን መቆየቱ ተመላክቷል። በመድረኩ የአርቃቂ ኮሚቴ አባላት በበጀት ዓመቱ የተከናወኑ ዝርዝር ተግባራትንና ቀሪ ሥራዎችን ያቀረቡ ሲሆን፣ ተያይዞም የፋይናንስ አገልግሎት የሕግ መድብልን የማውጣት ዋና ዓላማ ኢትዮጵያ በመድንና በባንኪንግ ዘርፍ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትን እንድትጎናጸፍ እንዲሁም ዘርፈ ብዙ ለውጦችን የሚመራ ጥራት ያለው የሕግ ማዕቀፍ ለመፍጠር መሆኑን ተገንዝቧል። በሌላ በኩል፣ አገራችን በፍትሐ ብሔር ፍትሕ ዘርፍ የጀመረችውን የሪፎርም ሥራ በውጤታማነት ለመምራት እና ዘመናዊ የፍትሕ ሥርዓት ለመገንባት ከፍተኛ ፋይዳ ባለው የፍትሐ ብሔር ፍትሕ ፖሊሲ ዝግጅት ሥራ ላይም ግምገማ ተደርጓል። ፖሊሲውን ለማዘጋጀት ፍርድ ቤቶችን ጨምሮ የተለያዩ ባለድርሻ አካላትን ያካተተ ኮሚቴ ተዋቅሮ መነሻ ጥናት ሲሠራ መቆየቱ የተገለጸ ሲሆን፣ ባለፈው በጀት ዓመት የመነሻ ጥናቱ ለባለድርሻ አካላት ቀርቦ ውይይት ከተደረገበት በኋላ በተገኙት ግብዓቶች መሠረት ጥናቱን በማጠናቀቅ ፖሊሲውን የማዘጋጀት ሥራ ሲከናወን መቆየቱ ተመላክቷል። በመጨረሻም በቀጣይ የሁለቱንም ተግባራት ቀሪ ሥራዎች ውጤታማና ጥራቱን በጠበቀ መልኩ በአጭር ጊዜ ውስጥ በማጠናቀቅ ረቂቆቹ ለሕዝብና ለባለድርሻ አካላት ቀርበው ሰፊ ውይይት እንዲደረግባቸው አቅጣጫ በመስጠት ውይይቱ ተጠናቋል። የፍትሕ ሚኒስቴርን የማህበራዊ ሚዲያ ትስስር ገፆችን እና ድረ-ገፅን ይቀላቀሉ Website https://www.justice.gov.et Facebook https://www.facebook.com/MOJEthiopia/ (x) Twitter https://x.com/MOJEthiopia YouTube channel https://youtube.com/@fdreministryofjustice...3701... Telegram https://t.me/fdreattorneyGeneral_externabo
110
11
Hawassa University Journal of Law (HUJL) Volume 10, July 2026
161
12
የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባኤ አደረጃጀት ሥልጣንና ተግባር እንደገና ለመወሰን የወጣ የማሻሻያ አዋጅ ቁጥር 251/2015
335
13
## የይምሰል ውል (Simulated Contract) በኢትዮጵያ ህግ እና በሰበር ችሎት ውሳኔዎች ዕይታ መግብያ: የውል ግንኙነቶች በሀገራችን የፍትሐብሔር ህግ መሰረት በነፃ ፍላጎት፣ በህጋዊ ምክንያት እና ግልፅ በሆነ ስምምነት ላይ ሊመሰረቱ ይገባል። ይሁን እንጂ በተለያዩ ምክንያቶች ተዋዋይ ወገኖች እውነተኛ ፍላጎታቸውን ለመሸሸግ በማሰብ የይምሰል ወይም የማስመሰያ ውሎችን (Simulated Contracts) ሲያደርጉ ይስተዋላል። ### የይምሰል ውል ምንነት የይምሰል ውል ማለት ተዋዋይ ወገኖች በውስጣቸው የተስማሙበትን እውነተኛ ስምምነት (Counter deed ወይም Back letter) ከሶስተኛ ወገኖች፣ ከመንግስት ወይም ከህግ ለመሸሸግ በማሰብ ለውጭው ማህበረሰብ የተለየ የማስመሰያ ውል (Simulated Contract) ሲያዘጋጁ የሚፈጠር የህግ እውነታ ነው። በኢትዮጵያ ፍትሐብሔር ህግ ቁጥር 1994 ድንጋጌ መንፈስ መሰረት፣ ተዋዋዮቹ የገቡት የማስመሰል ውል የሶስተኛ ወገኖችን መብት የሚነካ ሆኖ በተገኘ ጊዜ ሶስተኛ ወገኖች ተቃውሞ ሊያነሱ እንደሚችሉ ተደንግጓል። ### የሰበር ችሎት ውሳኔዎች የይምሰል ውልን የሚተረጉሙበት አግባብ የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በተለያዩ መዝገቦች ላይ የይምሰል ውልን በተመለከተ አስገዳጅ የህግ ትርጉሞችን ሰጥቷል፡- * የማስመሰያ ውልን በማስረጃ ስለማረጋገጥ፡ በሰ/መ/ቁ 58087 ላይ ችሎቱ እንዳብራራው፣ አንድ ውል በማስመሰል የተሰራ ወይም የሀሰት ነው የሚል ክርክር ሲቀርብ የውል አዋዋይ ፊት የተደረገ ነው በሚል ብቻ የጽሁፍ ማስረጃ መቅረብ አለበት ተብሎ አይታለፍም። ክርክሩ የሰነዱን እውነተኛነት የሚፈታተን በመሆኑ፣ ፍርድ ቤቶች እውነተኛ የሽያጭ ውል ወይም የሽሽግ ውል (Counter deed) መኖሩን በሰው ምስክር ጭምር በሚገባ ማጣራት እንዳለባቸው አስቀምጧል። ሆኖም ፍርድ ቤቶች ዝም ብለው በዳኝነት ግንዛቤ (Judicial Notice) ብቻ ውልን ማፍረስ እንደሌለባቸው ተብራርቷል። * የእውነተኛው ውል ተፈፃሚነት፡ በሰ/መ/ቁ 117719 በተሰጠው ውሳኔ፣ ተዋዋይ ወገኖች በተለያዩ ቀናት ያደረጓቸው ውሎች በሚኖሩበት ጊዜ፣ የግራ ቀኙ ትክክለኛ ሀሳብ ያረፈበት እና እውነተኛው ውል የቱ እንደሆነ በፍርድ ቤት ተጣርቶ ከተረጋገጠ በኋላ ተፈፃሚነት ሊያገኝ የሚገባው ይኸው እውነተኛው ውል እንጂ የይምሰል ውሉ አለመሆኑን አረጋግጧል። * ፍርድን ለማሸሽ የሚደረጉ የይምሰል ውሎች፡ በሰ/መ/ቁ 207446 ላይ እንደተወሰነው፣ ንብረትን በሚመለከት በፍርድ ቤት ክርክር መኖሩን እያወቁ የትዳር አጋር በሆነ ሰው ስም የሚደረግ የሽያጭ ግብይት በእውነት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን ሆነ ተብሎ ፍርድ እንዳይፈፀም ለማድረግ የሚደረግ ያልተገባ የይምሰል ውል መሆኑ ታምኖ ውድቅ ተደርጓል። * የጋራ ንብረትን ለማሸሽ የሚደረጉ የማስመሰል ውሎች፡ በሰ/መ/ቁ 223825፣ ባል ሚስት በሌለችበት ጊዜ ጋብቻን በማፍረስ ንብረትን ለዘመድ ሸጦ ከጥቂት ቀናት በኋላ መልሶ በስጦታ መቀበሉ፣ ንብረቱን ከእጅ ሳያወጡ ለይስሙላ የሚደረግ የንብረት ማሸሽ ውል መሆኑን ቢያሳይም፣ መብቱ የተነካበት ወገን እነዚህ የይምሰል ውሎች በቅድሚያ በፍርድ ቤት መዝገብ ዳኝነት ጠይቆ እስካላስፈረሳቸው ድረስ በውርስ ማጣራት ሂደት ብቻ ውሎቹን ቀሪ ማድረግ እንደማይቻል ተወስኗል። * ከውል ውጪ ባለ ግንኙነት (አላግባብ መበልጸግ) ላይ ያለው ዕይታ፡ በሰ/መ/ቁ 218394 ላይ ችሎቱ እንዳስቀመጠው፣ ግራ ቀኙ ያደረጉት ውል እውነተኛ የኪራይ ውል መሆኑ እየታወቀ፣ አንደኛው ወገን ግዴታውን ስላላሟላ ብቻ ውሉን ወደ አላግባብ መበልጸግ (Unjust Enrichment) ማዕቀፍ በመውሰድ መወሰን አይቻልም። በግልፅ የሽያጭ ውል የለም ከተባለ የኪራይ ውሉን የማስመሰል ውል (Simulated contract) ነው ሊባል አይችልም። ### በይምሰል ውል የሚመጡ ህጋዊ ውጤቶች * በተዋዋዮች መካከል፡ በፍትሐብሔር ህግ መሰረት በተዋዋዮች መካከል ሁልጊዜም አስገዳጅነት የሚኖረው የተደበቀው እውነተኛ ስምምነት (Counter deed) እንጂ ለውጭ ሰዎች የሚታየው የማስመሰያ ውል አይደለም። * በሶስተኛ ወገኖች ላይ፡ የማስመሰያ ውሉን አምነው በቅን ልቦና ከገቡ ሶስተኛ ወገኖች ላይ የተደበቀውን እውነተኛ ውል በመጥቀስ መቃወም አይቻልም። ሆኖም የይምሰል ውሉ የሶስተኛ ወገኖችን (ለምሳሌ አበዳሪዎችን ወይም የትዳር አጋርን) መብት ለመጉዳት የተደረገ ከሆነ፣ መብታቸው የተነካባቸው ወገኖች የይምሰል ውሉ እንዲፈርስላቸው ፍርድ ቤትን መጠየቅ ይችላሉ። ### ህብረተሰቡ ሊወስዳቸው የሚገቡ ጥንቃቄዎች የይምሰል ውሎች ለጊዜው ጥቅም የሚያስገኙ ቢመስሉም የኋላ ኋላ ውስብስብ ለሆኑ የህግ ክርክሮች እና የንብረት መጥፋት ይዳርጋሉ። በመሆኑም ህብረተሰቡ የሚከተሉትን ጥንቃቄዎች ማድረግ ይኖርበታል፡- * ግልፅነትን መከተል፡ ማንኛውንም ግብይት ሲያደርጉ ለግብር ማሸሽ፣ ለንብረት መደበቅ ወይም ለሌላ ህገ-ወጥ አላማ በማሰብ ትክክለኛ ያልሆነ የገንዘብ መጠንን በውል ላይ ከመፃፍ መቆጠብ ያሻል። * የንብረት ታሪክን ማጣራት፡ በተለይም መሬት እና ቤቶችን ሲገዙ፣ ንብረቱ ላይ የፍርድ ቤት እገዳ፣ የባንክ ዕዳ ወይም የባልና ሚስት ክርክር አለመኖሩን ከሚመለከተው አካል በሚገባ ማጣራት ያስፈልጋል። ከቤተሰብ አባላት ወይም ከባለአክሲዮኖች ጋር በሚደረግ አጠራጣሪ ሽያጭ ውስጥ አለመግባት ይመከራል። * ህጋዊ ዳኝነትን በወቅቱ መጠየቅ፡ መብትዎን የሚነካ የይምሰል ውል መደረጉን ሲያውቁ፣ ጉዳዩን በዝምታ ከማሳለፍ ወይም በሌላ ሂደት (ለምሳሌ በውርስ ማጣራት) መፍትሄ ይገኛል ብሎ ከመጠበቅ ይልቅ፣ ውሉ እንዲፈርስ በወቅቱ ስልጣን ላለው ፍርድ ቤት አቤቱታ ማቅረብ ህጋዊ መብትን ለማስከበር ወሳኝ ነው። የፍትሐብሔር ህጋችንም ሆነ የሰበር ችሎት አስገዳጅ ውሳኔዎች የሚያስተምሩን ዋናው መርህ፣ ህግ እውነተኛ ፍላጎትን እንጂ ማጭበርበርን እና ማስመሰልን ከለላ እንደማይሰጥ ነው። ቻናላችንን ለመቀላቀል ይህንንhttps://t.me/j_f125 ሊንክ ያስፈንጥሩ! በቻናላችን ላይ በምናቀርባቸው ህግ ነክ ጉዳዮችና ዜናዎች ላይ ሀሳብ፣ ጥቆማና ማንኛውንም አይነት ህግ ነክ ጥያቄዎችን ማቅረብ ሲፈልጉ  ይህንን https://t.me/justice_forum_bot የቴሌግራም ቦት ሊንካችንን በማስፈንጠር ሊያገኙን ይችላሉ. ​Chaanalii keenyatti makamuuf liinkii kana https://t.me/j_f125 tuqaa! Chaanalii keenya irratti dhimmoota seeraa fi oduuwwan dhiyeessinu ilaalchisee yaada, eeruu fi gaaffiiwwan seeraa kamiyyuu dhiyeessuu yoo barbaaddan, liinkii bootii Telegraamii keenya kana https://t.me/justice_forum_bot tuquun nu argachuu dandeessu.
328
14
ቻናላችንን ለመቀላቀል ይህንንhttps://t.me/j_f125 ሊንክ ያስፈንጥሩ! በቻናላችን ላይ በምናቀርባቸው ህግ ነክ ጉዳዮችና ዜናዎች ላይ ሀሳብ፣ ጥቆማና ማንኛውንም አይነት ህግ ነክ ጥያቄዎችን ማቅረብ ሲፈልጉ  ይህንን https://t.me/justice_forum_bot የቴሌግራም ቦት ሊንካችንን በማስፈንጠር ሊያገኙን ይችላሉ. ​Chaanalii keenyatti makamuuf liinkii kana https://t.me/j_f125 tuqaa! Chaanalii keenya irratti dhimmoota seeraa fi oduuwwan dhiyeessinu ilaalchisee yaada, eeruu fi gaaffiiwwan seeraa kamiyyuu dhiyeessuu yoo barbaaddan, liinkii bootii Telegraamii keenya kana https://t.me/justice_forum_bot tuquun nu argachuu dandeessu.
260
15
ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ የኢፌዲሪ የፍትሕ ሚኒስቴር በሕግ የተጣለበትን ኃላፊነት በላቀ ለመወጣት ይችል ዘንድ የአምስት ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ በማውጣት የአሰራር እና የአደረጃጀት ማሻሻያዎችን አድርጓል። በአዲሱ አደረጃጀት መሠረት ባሉ የተለያዩ ማስተባበሪያዎች፣ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች፣ ዳይሬክቶሬቶች ተመድበው ለመስራት ፍላጎቱ እና ተነሳሽነቱ ያላቸው እና ከዚህ በታች የተመላከቱ መስፈርቶችን የሚያሟሉ የሕግ ባለሙያዎችን በዐቃቤ ሕግነት ለመቅጠር ይህ ማስታወቂያ ወጥቷል። በመሆኑም ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 30 ቀናት ውስጥ በተወዳዳሪነት መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እናስታውቃለን። አስፈላጊ የሆኑ መስፈርቶች፡ ኢትዮጵያዊ የሆነ/የሆነች እና በኢትዮጵያ የሚኖር /የምትኖር ፤ ለሕገ መንግስቱ እና ለሕግ የበላይነት ተገዢ የሆነ/የሆነች ፤ የየትኛውም የፖለቲካ ድርጅት አባል ያልሆነ/ያልሆነች ፤ በታታሪነቱ/ቷ ፣ በታማኝነቱ/ቷ ፣ በሥነ-ምግባሩ/ሯ መልካም ስም ያተረፈ/ች መሆኑን/ኗን ይማርበት/ ትማርበት ከነበረበት ዩኒቨርሲቲ ወይም ከሚኖሩበት አካባቢ ካለ የመንግስት ተቋም ማስረጃ ማቅረብ የሚችል /የምትችል ፤ የወንጀል ቅጣት ሪከርድ የሌለበት/ባት ፤ የፌዴራል መንግስቱን የሥራ ቋንቋ የሚችል/የምትችል ፤ እንደ አስፈላጊነቱ የሚሰጠውን የጽሁፍም ይሁን የቃል ወይም ሁለቱንም ፈተና መውሰድ እና ማለፍ የሚችል /የምትችል፤ የሥራ መደብ፡ (ዐቃቤ ሕግ) ዐቃቤ ሕግ ደረጃ ሦስት ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ፡ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋም በሕግ ትምህርት በመጀመሪያ ዲግሪ በ2018 ዓ.ም የተመረቀ /የተመረቀች፤ የመመረቂያ ነጥብ (Cumulative GPA) 3.6 ከዚያ በላይ ያለው/ ያላት፣ የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ውጤት 85 ፐርሰንታይል እና ከዛ በላይ በማምጣት ፈተናውን ያለፈ/ያለፈች፤ ብዝሃነት፣ ሴት እና አካል ጉዳተኛ ተወዳዳሪዎችን እናበረታታለን፤ የሥራ ልምድ - 0 አመት ብዛት -25 የምዝገባ ሁኔታ፡- http://www.justice.gov.et በሚለው የተቋሙ ዌብሳይት ክፍት የሥራ ቦታ በሚለው ሥራ ባለው ማስፈንጠሪያ ወይም https://forms.gle/rWi1n6wi8HYYZubc7 በመጠቀም የሚጠይቀውን መረጃ በመሙላት እና ማስረጃዎችን በማያያዝ መመዝገብ ይቻላል። የምዝገባ ቀን፡- ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 30 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ፤ ማስታወሻ፡- ተወዳዳሪዎች ሲመዘገቡ ሊያሟሏቸው የሚገባቸው ሰነዶች፡- 1. ኢትዮጵያዊ መሆናችሁን የሚገልጽ መታወቂያ/ፓስፖርት እና ብሔራዊ መታወቂያ በpdf scan የተደረገ፤ 2. ዋና የትምህርት ማስረጃ (student copy) ጨምሮ በpdf scan የተደረገ ፤ አጠቃላይ የመመረቂያ አማካይ ውጤት CGPA እና የመውጫ ፈተና ውጤትን Exit Exam የሚገልጽ የትምህርት ማስረጃ፣ 3. ከሚኖሩበት አካባቢ ካለ የመንግስት ተቋም ወይም ከተመረቁበት የትምህርት ተቋም የመልካም ሥነ ምግባር ማስረጃ፣ ለበለጠ መረጃ ፡- በስራ ሠዓት በስልክ ቁጥር ፡- +251-15-15-7432 በመደወል፤ እንዲሁም በኢሜል አድረራሻ፡- mojprosecutorsadministration@justice.gov.et ወይም mojpublicprosecutorsa@gmail.com ላይ በመፃፍ ማግኘት ይችላሉ። የኢፌዲሪ ፍትሕ ሚኒስቴር
422
16
Mirga Abbaa Qabiyummaa (Holding Right) Jechuun Maal Jechuudha? Maal Maal of Keessatti Qabata? ============================================================ Qabiyyee lafaa ilaalchisee mirga abbaa qabeenyummaa kan ummataa fi mootummaa ta’uu fi namoonni ykn lammiileen dhuunfaa mirga abbaa qabiyummaa fi/ykn ittifayyadamaa qofa akka qabaatan Heera Mootummaa kwt 40(1-3) fi labsiileen qabeenya lafaa bulchuuf began keessattis tumamee argama.  Namni dhuunfaa mirgi qabiyyee lafaa irratti qabaachuu danda’u mirga abbaa qabiyyummaa (holding right) fi mirga ittafyyamuu (use right) qofa eega ta’ee Mormon kun maal akka ta’an immoo Seerota Lafa Bulchiinsa keessatti ibsamee argama.  Haaluma kanaan mirga abbaa qabiyyummaa jechuun gabaabumatti mirga laficha qabachuu ykn kan isaati jedhamuu  yoo ta’u Innis fkn kanneen Labsii Lkk 248/2015 kwt 22 jalatti tareeffaman hammata. Akka fakkeenyaattis;  Laficha haala karoora ittifayyadama lafaatiin misoomsuu fi ittifaayyadamuu ykn waan seera qabeessa ta’e kamiiyyuu irratti raawwachuu, Seeraan ala Lafa isaa irraa mirga buqqa’uu dhabuu fi faayidaa ummataaf kan barbaadamu yoo ta’es adeemsa seeraa hordofee dursa beenyaa gahaa argachuun qofa ta’uu ( isa dhiyeenya kana hooggansi wayii dubbate jedhamu otuu hintaane isuma seerri jedhu qofa dubbachaa jirra), Mirga kireessuu, dhaalchisuu fi ykn kennaan dabarsuu, Mirga yoo barbaade wabummaan qsbsiisee ittiin liqeefdachuu  Mirga qabeenya irratti horachuu, walitti aanfachuu, waljijjiiruu fi, Mirga qabeenya laficha irratti horate akkaataa seeraan eeyyamameen dabarsuu fa’a kan of keessatti qabatudha. Gaa’illi malee mirga itti fayyadamaa (use right) qofa namni qabu lafichatti tajaajilamuu irraan kan hafe mirgoota olitti tarreeffaman kanneen hunda kan hinqabne waan ta’eef mirgi abbaa qabiyyummaa fi mirga itti fayyadamaa garaagara akka ta’e kan agarsiisudha. Mirgi itti fayyadamaa mirgoota abbaan qabiyyummaa hammatu keessaa isa tokko qofa akka ta’e hubatamuu qaba. https://t.me/speaklawinabsentia
272
17
Ethiopian_Journal_of_Federal_Studies_The_Legal_and_Practical_Challenges.pdf
242
18
🚀የስራ ዕድል: የኢፌዲሪ ፍትሕ ሚኒስቴር ዐቃቤ ሕግ የሥራ ዕድል ለ2018 ዓ.ም የሕግ (LLB) ተመራቂዎች🚀 ✨የሕግ ትምህርት ተመራቂ ነዎት? በመንግስት ተቋም የሙያ ሕይወትዎን ለመጀመር እና በፍትሕ ሥርዓቱ ውስጥ ተግባራዊ ሚና ለመጫወት ዝግጁ ከሆኑ፣ የኢፌዲሪ ፍትሕ ሚኒስቴር ለዐቃቤ ሕግ ደረጃ 3 አዲስ ተመራቂዎችን እየቀጠረ ነው። የሚያገኙት; 🔹በመንግስት ተቋም የሙያ ጉዞዎን የመጀመር ዕድል 🔹በፍትሕ ዘርፍ ተግባራዊ የሥራ ልምድ 🔹የሙያ እድገትና የረጅም ጊዜ የሥራ እድል 🔹ለሕግ የበላይነት እና ለፍትሕ ሥርዓት ቀጥተኛ አስተዋጽኦ ማን ማመልከት ይችላል? 🔸በ2018 ዓ.ም በሕግ (LLB) የተመረቁ 🔸3.6 እና ከዚያ በላይ CGPA ያላቸው 🔸Exit Exam 85 Percentile እና ከዚያ በላይ ያስመዘገቡ 🔸0 ዓመት የሥራ ልምድ ያላቸው 🔸ኢትዮጵያዊ ዜጋ የሆኑ 🔸የሕጉንና የሥነ-ምግባር መስፈርቶችን የሚያሟሉ 🔸ሴት እና አካል ጉዳተኛ ተወዳዳሪዎች ይበረታታሉ የሚያስፈልጉ ሰነዶች: 📌ብሔራዊ መታወቂያ 📌የትምህርት ማስረጃ (Student Copy) 📌አጠቃላይ የመመረቂያ አማካይ ውጤት CGPA 📌የExit Exam ውጤት 📌ከሚኖሩበት አካባቢ ካለ የመንግስት ተቋም ወይም ከተመረቁበት የትምህርት ተቋም የመልካም ሥነ ምግባር ማስረጃ 🎯የሥራ መደብ፡ (ዐቃቤ ሕግ) ዐቃቤ ሕግ ደረጃ ሦስት  ✍ብዛት: 25 🔗ለማመልከት: https://forms.gle/rWi1n6wi8HYYZubc7 📞ለበለጠ መረጃ ይደውሉ፡- +251-15-15-7432 (በስራ ሠዓት) 📝ምዝገባው የሚያበቃበት ቀን: ከማስታወቂያው ቀን ጀምሮ 30 ተከታታይ ቀናት "ይህ ለእርስዎ ካልሆነ፣ እባክዎን ፍላጎት ላላቸው ለሌሎች ያካፍሉ."🙏
71
19
ibsa fi xiinxaala seeraa lakk/MWFD/246230 ta'e irratti qopheessine akka armaan gadiitti isiniif qoodnee jirra waan ta'eef nu hordofaa! Qabiyyee tokko irratti Kaartaa dacha hojjechuu fi bu'aa isaa Lakk. G/I. 246230 | Bitootessa 25 bara 2018 B.A. 1. Seensaa fi Akkaataa Dhimmi itti Dhufe Xiinxalli seeraa kun kan xiyyeeffatu hiika seeraa dirqisiisaa Mana Murtii Waliigalaa Federaalaatti Dhaddacha Ijibbaataa 3ffaa abbootii seeraa 7n taa'ame, Lakk. Galmee 246230 Bitootessa 25 bara 2018 B.A. kenne irrattidha. Dhimmi kun qabiyyee lafa magaalaa tokko irratti waraqaan ragaa qabiyyee lafaa (kaartaan) dacha kennamuusaa hordofee falmii mirga abbaa qabeenyummaa ka'e ilaallata. Falmiin kun kan eegale himataa (Waldaa Ijaarsa Mana Jireenyaa Odaa Baliinaa) fi himatamtoota (Namoota dhuunfaa kaartaan kennameef fi qaamolee bulchiinsa lafaa) gidduuttidha. Waldichi lafa ka.mee 5220 kennameefii miseensota 29f qoodaa osoo jiruu, bulchiinsichi lafuma kana irraa kutee namoota dhuunfaa biroof kaartaa kennuu isaatii fi namoonni dhuunfaa kunis ijaarsa waan geggeessaniif walitti bu'iinsi uumameera. 2. Adeemsa Manneen Murtii Jalaa Manni Murtii Aanaa Magaalaa Adaamaa "kaartaa irratti kaartaa kennuun seeraan ala waan ta'eef, tilmaamni ijaarsa ijaaramee kaffalamee qabiyyichi waldaadhaaf haa gadi lakkifamu" jechuun murteessee ture. Haa ta'u malee, dhimma kana ol'iyyannoon kan ilaale Manni Murtii Ol'aanaa Godina Addaa Adaamaa, Seera Hariiroo Hawaasaa kwt 1179 fi murteewwan ijibbaataa kanaan duraa bu'uura godhachuun, namoonni dhuunfaa kun ijaarsa kan raawwatan mormii malee waan ta'eef waldichi mirga hin qabu jechuun murtee mana murtii jalaa diigeera. Dhaddachi Ijibbaataa Mana Murtii Waliigalaa Oromiyaa gama isaatiin, Hojii Gaggeessaan waldichaa mormii gochaa akka ture mirkaneeffachuun murtee mana murtii ol'aanaa diigee murtee mana murtii aanaa cimsiseera. 3. Gaaffii Seeraa Ijoo (Qabxii) Dhaddacha Ijibbaataa Qabxiin ijoo dhaddachichi qabate: Qaama aangoqabuun bakka tokkotti waraqaan ragaa qabiyyee lafaa (kaartaan) dacha kennamee qaamni tokko ijaarsa yoo gaggeesse, qaama kamtu mirga dursa argata? kan jedhudha. 4. Murteewwan Dirqisiisoo Kanaan Duraa Diigamuu Lakk. G/I. 186946 Diigamuu Kanaan dura Lakk. G/I. 186946 irratti hiikni dirqisiisaan kenname "Lafa tokko irratti namoonni garaa garaa lama waraqaa ragaa qabiyyee (kaartaa) qabaatanii inni tokko mana yoo ijaare, inni kaan diigi naaf jedhee gaafachuu hin danda'u" kan jedhu ture. Adeemsi kun dursee ijaaruu (Possession through construction) irratti kan xiyyeeffate ture. Haa ta'u malee, ejjennoon kun murtee ammaa kanaan diigameera. Dhaddachichi murtee dirqisiisaa biraa (abbootii seeraa 7n taa'ame) Lakk. G/I. 242314 irratti kenname caqasuun, qabiyyee nama biraa irratti ijaarsa raawwachuun bu'uura SHH kwt 1178 fi 1179tiin ijaarsichaaf (gamochichaaf) malee lafachaaaf mirga akka hin argamsiifne mirkaneesseera. Kanaafuu, yeroo kaartaan dacha/irratti-tuqaan qunnamu, dursee ijaaruun qofa mirgi fooyya'aan argamuu hin danda'u. 5. Bu'uura Seeraa fi Xiinxala Murtichaa Dhaddachichi yaada baasaa seeraa fi tumaalee ifa ta'an hojiirra oolcheera. Ogeeyyii seeraaf xiyyeeffannoo guddaa kan barbaadu Labsii Galmee Qabiyyee Lafa Magaalaa Lakk. 818/2006 keewwata 43(1) hiikuudha. Keewwatni kun namoonni lama qabiyyee tokko irratti mirga yoo qabaatan, namni jalqaba mirga isaa galmeessise dursa argata jechuun ifatti kaa'eera. Mirgi dursa argachuu kan murtaa'u tartiiba galmee isaatiin malee lafacha irratti dafanii ijaaruun ykn karaa seeraan ala ta'een kaartaa baasuudhaan miti. Kaartaan dogoggoraa kennamuusaatiin miidhaa qaqqabuuf itti-gaafatamummaan mootummaa bu'uura SHH kwt 1198 fi Labsii 818/2006 keewwata 40tiin kan keessummeeffamu ta'a. 6. Murtee Cuunfaa Dhumarrattis, dhaddachichi hiika seeraa dirqisiisaa haaraa armaan gadii kenneera: • Hiikni dirqisiisaan Lakk. G/I 186946 irratti kenname diigameera. • Qabiyyee magaalaa tokko irratti waraqaan ragaa qabiyyee (kaartaan) tokkoo ol namoota garaa garaaf dacha ta'ee (tuqatee) kennamee yoo argame, abbaa qabeenyummaa lafachaatiif dursi kan kennamu nama jalqaba galmeessiseefidha.
316
20
በ"ፍትህ ለሀገሬ" የዩቲዩብ ቻናል አዘጋጅ በሆነችው ሊያ ተረፈ እና በፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኛ በሆኑት አቶ ካሴ መልካም መካከል የተደረገውን ጥልቅ የህግ ውይይት ዋና ዋና ሀሳቦች በማጠናቀር እንደሚከተለው አዘጋጅቼዋለሁ። ## የፍርድ አፈፃፀም እና የንብረት እግድ፡ የህግ እና የተግባር ቅኝት በፍርድ ቤት የሚሰጥ ማንኛውም ውሳኔ ወይም ብይን ዋጋ የሚኖረው በተግባር ሲተረጎም እና ወደ አፈፃፀም ሲቀየር ነው። በ"ፍትህ ለሀገሬ" የዩቲዩብ ቻናል ላይ የተደረገው ይህ ውይይት፣ የፍርድ አፈፃፀም ሂደትን፣ የንብረት እግድን፣ እና ህጉ የሚሰጣቸውን መፍትሄዎች በተመለከተ ሰፊ ግንዛቤን ያስጨብጣል። ### 1. የፍርድ አፈፃፀም ምንነት እና ተግዳሮቶቹ አንድ ግለሰብ ፍርድ ቤት ቀርቦ ከተከራከረ እና ካሸነፈ በኋላ፣ የተሰጠው የፍርድ ወረቀት ብቻውን መብቱን አያስከብርለትም። ፍርዱ መሬት ላይ ወርዶ አሸናፊው የሚገባውን (ገንዘብ፣ ንብረት፣ ወይም መብት) እንዲያገኝ የፍርድ አፈፃፀም (Execution) ሂደት ግድ ይላል። ይሁን እንጂ ይህ ሂደት ቀላል አይደለም። ተሸናፊው ወገን (ባለዕዳው) ንብረቱን በማሸሽ፣ በመደበቅ ወይም የፍርድ ቤቱን ትዕዛዝ ባለማክበር እንቅፋት ሊፈጥር ይችላል። በዚህ ጊዜ የፍርድ ቤቱን ትዕዛዝ ለማስፈፀም አሸናፊው ወገን የፍርድ አፈፃፀም መዝገብ ከፍቶ መንቀሳቀስ አለበት። ### 2. ከክስ በፊት የሚደረግ የንብረት እግድ (ቅድመ-ክስ ማስከበር) ከውይይቱ አንኳር ነጥቦች አንዱ "ክስ ሳይቀርብ ንብረት ማስከበር ይቻላል ወይ?" የሚለው ነው። > የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት (በቅጽ 25) ላይ በሰጠው አስገዳጅ የህግ ትርጉም መሰረት፤ አንድ ሰው መብቱ ከመረጋገጡ ወይም ዋናው ክስ ፍርድ ቤት ከመቅረቡ በፊት እንኳን ንብረት ማሳገድ ይችላል። > ይህ የሚሆነው ከሳሽ ክሱን በሚያዘጋጅበት ጊዜ ተከሳሽ ንብረቱን ሊያሸሽ፣ ሊሸጥ ወይም ሊደብቅ ይችላል የሚል ስጋት ሲኖረው ነው። ይህ አሰራር ከሳሽ ከረጅም የፍርድ ሂደት በኋላ "ባዶ እጁን" እንዳይቀር ትልቅ ዋስትና ይሰጣል። ### 3. በእግድ እና አፈፃፀም የማይነኩ ንብረቶች ህጉ የባለገንዘብን (አሸናፊን) መብት ለማስከበር ቢጥርም፣ በሌላ በኩል ደግሞ የባለዕዳውን መሰረታዊ የመኖር ህልውና አደጋ ላይ አይጥልም። በመሆኑም ሁሉም ንብረት አይታገድም ወይም አይሸጥም። * የጡረታ ገንዘብ፡ አንድ ባለዕዳ ዕዳ ቢኖርበትም የጡረታ አበሉ በፍርድ አፈፃፀም አይታገድም። * መሰረታዊ ፍላጎቶች፡ ለዕለት ተዕለት ኑሮ እጅግ አስፈላጊ የሆኑ አልባሳት፣ የቤት ቁሳቁሶች እና መሰል ንብረቶች ለሐራጅ አይቀርቡም። ### 4. የተቋማት ሚና በፍርድ አፈፃፀም ሂደት የፍርድ አፈፃፀም ስኬታማ የሚሆነው የተለያዩ አካላት በቅንጅት ሲሰሩ ነው። ዳኛ ካሴ መልካም በውይይታቸው እንዳብራሩት የሚከተሉት ተቋማት ቁልፍ ሚና አላቸው፡ * ፖሊስ፡ ትዕዛዝ አልቀበልም የሚልን ሰው በማምጣት፣ ንብረት ሲደበቅ በማስከበር እና የፍርድ ቤት ትዕዛዝን በጉልበት ጭምር በማስፈፀም ረገድ ፖሊስ ትልቅ ኃላፊነት አለበት። * ባንኮች እና የትራንስፖርት ባለስልጣን፡ የገንዘብ ተቋማት የባለዕዳውን አካውንት በማገድ፣ እንዲሁም የትራንስፖርት ባለስልጣን የተሽከርካሪ ስም ዝውውርን በመከልከል የፍርድ አፈፃፀሙን ይደግፋሉ። * የፍርድ አፈፃፀም ጽ/ቤት፡ በፌደራል ፍርድ ቤቶች ስር የተቋቋመው ራሱን የቻለ የአፈፃፀም ዳይሬክቶሬት፣ ሂደቱን ይበልጥ ቀልጣፋ እና ውጤታማ ለማድረግ አጋዥ ሆኗል። ### 5. የሶስተኛ ወገን መብቶች እና የሐራጅ ሽያጭ አንድ ንብረት ታግዶ ለሽያጭ (ለሐራጅ) ሲቀርብ የሶስተኛ ወገኖች መብት ሊነካ ይችላል። * የቀዳሚነት መብት፡ በንብረቱ ላይ ቀድሞ የተመዘገበ መብት (ለምሳሌ በባንክ የተያዘ መያዣ) ካለ፣ ባንኩ ወይም መብት ያለው አካል ቅድሚያ የማግኘት መብቱ የተጠበቀ ነው። * የሐራጅ ሂደት፡ ንብረቱ በግልጽ ጨረታ ለሶስተኛ ወገን ከተሸጠ በኋላ ገንዘቡ ለፍርድ ባለመብቱ (አሸናፊው) ገቢ ይደረጋል። ማጠቃለያ የፍርድ አፈፃፀም ሂደት የፍትህ ስርአቱ የልብ ትርታ ነው። ፍርድ ቤቶች ትዕዛዝ ከመስጠት ባለፈ፣ ያ ትዕዛዝ መሬት ላይ መውረዱን የሚያረጋግጡበት፣ ባለመብቶች የድካማቸውን ፍሬ የሚያገኙበት፣ እንዲሁም የተቋማት የህግ የበላይነትን የማስከበር አቅም የሚፈተንበት ወሳኝ ምዕራፍ ነው።
296