es
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Ir al canal en Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

El canal Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 413 suscriptores, ocupando la posición 5 577 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 192 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 413 suscriptores.

Según los últimos datos del 13 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 71, y en las últimas 24 horas de -3, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 25.53%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 9.38% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 933 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 446 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 23.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 14 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 413
Suscriptores
-324 horas
+357 días
+7130 días
Archivo de publicaciones
ሥርዐተ ማኅሌት ዘወርኀ ጽጌ (‹ዘላይ ወዘታች› ቤት)፤ ፬ኛ ሳምንት፥ዘጥቅምት ፲፰፤

‹‹ ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡›› ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት በወርኃ ነሐሴ ፳/፳፻፲፣በመስከረም ፲፪ና ፲፫/፳፻፲ ዓ.ም. ጋብቻችሁን ለፈጸማችሁ የደብራችን አገልጋይና የሰ/ት/ቤታችን አባላት * ሙላት ተሾመ * ዲ.ን ዐሥራት ለይኩን * ይትባረክ ሙላቱ ከደመቀች ሽፈራው * መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ የፈጸማችሁትን ጋብቻ፤ የይስሐቅንና የርብቃን ጋብቻ የባረከ አምላክ፤ የትዳር ሕይወታችሁን ይባርክላችሁ፤ እመብርሃን በአማላጅነቷ አትለያችሁ፤ ቅ/ገብርኤል ከፊት ይምራችሁ ከኋላ ይከተላችሁ፡፡ ✤ ‹‹ጌታን እንዲወዱና በአካልም ይሁን በመንፈስ በባሎቻቸው ደስ እንዲሰኙ ለእህቶች ንገራቸው፡፡ ልክ እንደዚሁ ጌታ ቤተ ክርስቲያንን እንደወደደ ሚስቶቻቸውን እንዲወዱ ለወንድሞች በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ንገራቸው፡፡›› ቅዱስ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ ለፖሊካርፐስ በላከው መልእክቱ ✤ ከተጋባችሁ በኋላ ባልና ሚስት አንድ አካል ናችሁ እንጂ ሁለት ስላይደላችሁ በፍጹም ልባችሁ እርስ በእርሳችሁ ተፋቀሩ፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ሌላ ወንድ ወይም ሌላ ሴት አትፈልጉ ይልቁንም በተቻላችሁ መጠን አንዳችሁ ሌላውን ደስ አሰኙ፤ በመረዳዳትና በፍጹም ፍቅር ኑሯችሁን ሁሉ አሳምሩ፡፡>> ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ ዘርአያዕቆብ፡፡

በወርኀ ነሐሴና መስከረም የተመረቃችሁ እንኳን ደስ አላችሁ፡፡ 1ኛ. ኪሩቤል ቴዎድሮስ፤ በኮምፒውተር ሳይንስ ዲግሪ፤ ከአኵሱም ዩኒቨርሲቲ 2ኛ. ኪሩቤል ጀቤሳ፤ በኮሙኒኬሽን ኢንጂነሪንግ ዲግሪ፤ ከአ.አ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት 3ኛ. ፈለቀች አሰፋ፤ በአካውንቲንግ ዲግሪ፤ ከአድማስ ዩኒቨርሲቲ 4ኛ. አልማዝ በቀለ፤ በሚድዋይፈሪ ዲግሪ፤ ከዳግማዊ ምኒልክ የጤና ሳይንስ ኰሌጅ 5ኛ. አክሊሉ ደስዬ፤ በማኔጅመንት ዲግሪ (በከፍተኛ ማዕረግ በሜዳልያ ተሸላሚነት)፤ ከጌጅ ኰሌጅ 6ኛ. ራሔል ተሾመ፤ በአካውንቲንግ በዲግሪ፤ 7ኛና 8ኛ) የሺሃረግና ሙሴና አስካለ ሙሴ፤ በቡዝነስ አድሚንስትሬሽን በማስተርስ፤ ከሲፒዩ ኰሌጅ /ፎቶዎቹ ተሰባስበው እጃችን እስኪገቡ በዘግየቱ ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡/

✤ ብዙዎቻችን ከማናውቃቸው ነገሮች መካከል(የአቡነ አረጋዊ በሶ እምነት)፤ ና የጥቅምት 14 ክብረ በዓልን በወፍ በረር፤ ፨ የአቡነ አረጋዊ በሶ እምነት፤ በዓመት አንድ ጊዜ ጥቅምት 14 በደብራችን በሚበሩት በቅዱስ ገብረ ክርስቶስ አቡነ አረጋዊና ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር ክብረ በዓል ላይ በሶ ይሰጣል ይኸውም የበሶ እምነት ብዙዎችን ፈውሷል፤ በሶ የአቡነ አረጋዊ እምነት የኾነበት ምክንያጥ በታላቁ ገዳም በደብረ ዳሞ የመናንያኑ ምግብና ወደዚሁ ቦታ ለሚሄዱ ምዕመናን እንደ እምነት ተደርጎ የሚሰጥ በመኾኑ ነው፡፡ በነገራችን ላይ ደብራችን መጀመሪያ ሲመሠረት ይቀድሱና ያወድሱ የነበሩት የደብረ ዳሞ ገዳም መነኰሳት ናቸው፡፡ ዘንድሮ የበሶ እምነት ያመለጣችሁ ለከርሞ ያድርሰን፡፡ ✤ የጥቅምት 14 ክብረ በዓልን በወፍ በረር ስንቃኘውዋይዜማው ማኅሌቱ ሰዐታቱና ኪዳኑ ከተከናወነ በኋላ፤ ታቦቱ ወጥቶ በዐውደ ምሕረት በቆመበት ሰዐት፤ ✣ የደብራችን ሊቃውንት፤ የደብሩን ቀለም የኾነውንና ልብን የሚመስጠውን (ብፁዓን አበዊነ አረጋዊ ሙሴ ወገብረ ክርስቶስ፤ ዘበምድር መነኑ ዘበሰማያት ዴገኑ ዘበሰማያት) የሚለውን ሲወረቡ ✣ የደብራችን የሕፃናት ክፍል የሰ/ት/ቤት አባላት ደግሞ ‹‹ዘእምደብረ ደናግል አባ ኤልያስ፤ ወትሩፈ ምግባር አረጋዊ ዘውገ ሙሴ ወገብረ ክርስቶስ›› የሚለውን ወረበዋል፡፡ ✣ የተሰጠው ትምህርት፤ ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፡፡ ማቴ. 5፤ በመጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ፡፡ (የቅዱሳንን ታሪክ እንዲሁም ቅዱሳኑን አሁን ካለንበት ኹኔታ አንጻር እያመሳጠሩ /የቀድሞዎቹ ቅዱሳን ከሌላ ሃገራት ወደ ኢትዮጵያ ለጽድቅ ተሰደው ሲመጡ እኛ ደግሞ ዛሬ ለሥጋችን እንሰደዳለን፤ ቅዱሳን ዘር ብሔር (ቦታ ሀገር) ሳይለቻው ክርስቲያንን ወደዋል አስተምረዋል እኛ ደግሞ ሁሉ ነገራችን በዘርና በብሔር ላይ ኹኗል፤ ታዲያ ቅዱሳኑ እንዴት አያዝኑብን፤ ……… በማለት አስተምረውናል፡፡ ✤ በማታ የሰርክ ጕባኤ (የረቡዕ ልዩ የሠርክ ጕባኤ) ላይ ትምህርተ ወንጌል በመምህር ጳውሎስ መልክአ ሥላሴ ‹‹›› አሁን ካለንበት የዘመናችን በተለይም የሃገራችን ኹኔታ ጋር እያገናዘቡና እያመሳጠሩ አስተምረዋል፤ ዝማሬም በዘማሩ ቡሩክና በሲስተር ሄለን ቀርቧል፡፡ /በነገራችን ላይ የማታ የሰርክ ጕባኤ ላይ የሰዐትና መርሐ ግብር ማስተካከያ ቢደረግ ብላችሁ የሰጣችሁትን አስተያየት ግምት በማስገባት የማስተካከል ሥራ እየተሠራ ነው፤ በዚህም ምክንያ ጕባኤው 2፡05 ላይ ተጠናቋል፡፡)

የሰ/ት/ቤታችን የሕፃናት ክፍል አባላት ለጥቀምት 14 ለበዓሉ ተስማሚ የኾነውን ወረብ እያቀረቡ፡፡
የሰ/ት/ቤታችን የሕፃናት ክፍል አባላት ለጥቀምት 14 ለበዓሉ ተስማሚ የኾነውን ወረብ እያቀረቡ፡፡

ጥቅምት 14፤ ✤ ቅዱስ ገብረክርሰቶስ በዓለ እረፍቱ፤ ✤ በጋዛ ምድር ኢትዮጵያዊውን ጃንረባ ባኮስን ያጠመቀው ረድኡ ሐዋርያ ቅዱስ ፊሊጶስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ✤ አቡነ አረጋዊ ወደ ደብረ ዳሞ በዘንዶ የወጡበት፤ ✤ ቅዱስ ሙሴ እግዚአብሔር በዓለ ዕረፍታቸው ነው፡፡ ✤✤ ጥቅምት 14 በአ.አ. ክብረ በዓል የሚከበርባቸውን አብያተ ክርስቲያናት እንጠቁማችሁ፡፡ ✤ በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም ቤተክርስቲያን (የቅዱስ ገብረ ክርስቶስ አቡነ አረጋዊና ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር ታቦት በድርብነት ከጥንት ጀምሮ ይከብራል) ✤ ለእኛ ለኢትዮጵያውያን ባለውለታችን የኾነውና ለመጀመሪያ ጊዜ በሐዲስ ኪዳን የእግዚአብሔርን ቃል የተናገረን፤ የክርስትና ጥቀምት አባትና አጥማቂያችን ከ72ቱ አርድዕት አንዱ የኾነው ቅዱስ (ሐዋርያው) ፊልጶስ በሀገራችንን ውስጥ ብቸኛ በኾነውና በአ.አ ኮልፌ አጠና ተራ በሚገኘው ቤ.ክ. ደብረ ምጥማቅ ቤ.ክ በዓለ ዕረፍቱ ይከበራል፡፡ ✤ በደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤ.ክ /ዘነበ ወርቅ/ ✤ በመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን (የአቡነ አረጋዊ ታቦት በድርብነት ይገኛል) ✤ በሽሮ ሜዳ መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን (የአቡነ አረጋዊ ታቦት በድርብነት ይገኛል) ✤ በደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤ.ክ. (የአቡነ አረጋዊ ታቦት በድርብነት ይገኛል)

ዘጥቅምት ፲፩፤ ሥርዐተ ማኅሌት ዘወርኀ ጽጌ (‹ዘላይ ወዘታች› ቤት) (፯ኛ ዙር ዓመት፤ ፫ኛ ሳምንት፥ ዘጥቅምት ፲፩) በዓለ ቅድስት ሐና ወጲላግያ ወቅዱስ ኢያቄም ወያሬድ፡፡ ✤ ልዩ አዋጅ ዘወርኃ ጽጌ ✤  የማኅሌቱ ሥርዐት የላይ ቤት (የጎንደር መካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም አብነት) እና የታች ቤት (የጎንደር ደብረ ኀይል ዑራኤል ወደብረ ጥበብ በዓታ ለማርያምን አብነት) የሚያደርግ ሲኾን፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ የማኅሌት ቁመትም የላይ ቤትን አብነት የተከተለ ሲኾን፤ የዚቁ ወረብ ግን የደብሩን የራሱን (የሸዋን) የተከተለ ነው፤  የላይ ቤት ቁመት የሚቆሙ አድባራት ዘግምጃ ቤት የሚለውን እንዲከተሉ፤ የታች ቤትን ቁመት የሚቆሙ አድባራት ዘበዓታ የሚለውን እንዲከተሉ እያሳሰብን፡፡ የዚቁ ወረብን ግን የቀጨኔ ደብረ ሰላም የቤቱን ቀለም አስቀድመን ቀጥሎ ደግሞ ዓዲ (ወይም) በማለት የጎንደርን ስላስቀመጥነው እንደ ደብራችሁ ይትበሃል መርጣችሁ እንድትጠቀሙበት ኹሉንም አስቀምጠነዋል፡፡