es
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Ir al canal en Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

El canal Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 381 suscriptores, ocupando la posición 5 584 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 199 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 381 suscriptores.

Según los últimos datos del 03 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 21, y en las últimas 24 horas de -7, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 21.13%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 9.50% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 250 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 462 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 16.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 04 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 381
Suscriptores
-724 horas
+117 días
+2130 días
Atraer Suscriptores
julio '26
julio '26
+2
en 0 canales
junio '26
+123
en 2 canales
Get PRO
mayo '26
+111
en 6 canales
Get PRO
abril '26
+345
en 4 canales
Get PRO
marzo '26
+61
en 2 canales
Get PRO
febrero '26
+70
en 6 canales
Get PRO
enero '26
+199
en 7 canales
Get PRO
diciembre '25
+135
en 6 canales
Get PRO
noviembre '25
+436
en 3 canales
Get PRO
octubre '25
+680
en 7 canales
Get PRO
septiembre '25
+91
en 4 canales
Get PRO
agosto '25
+295
en 5 canales
Get PRO
julio '25
+246
en 5 canales
Get PRO
junio '25
+159
en 1 canales
Get PRO
mayo '25
+141
en 2 canales
Get PRO
abril '25
+551
en 7 canales
Get PRO
marzo '25
+156
en 3 canales
Get PRO
febrero '25
+112
en 4 canales
Get PRO
enero '25
+296
en 7 canales
Get PRO
diciembre '24
+243
en 3 canales
Get PRO
noviembre '24
+695
en 10 canales
Get PRO
octubre '24
+743
en 7 canales
Get PRO
septiembre '24
+64
en 1 canales
Get PRO
agosto '24
+198
en 4 canales
Get PRO
julio '24
+419
en 12 canales
Get PRO
junio '24
+289
en 3 canales
Get PRO
mayo '24
+459
en 4 canales
Get PRO
abril '24
+522
en 6 canales
Get PRO
marzo '24
+341
en 1 canales
Get PRO
febrero '24
+339
en 4 canales
Get PRO
enero '24
+509
en 8 canales
Get PRO
diciembre '23
+141
en 2 canales
Get PRO
noviembre '23
+276
en 1 canales
Get PRO
octubre '23
+456
en 3 canales
Get PRO
septiembre '23
+103
en 0 canales
Get PRO
agosto '23
+144
en 0 canales
Get PRO
julio '23
+180
en 0 canales
Get PRO
junio '23
+104
en 0 canales
Get PRO
mayo '23
+85
en 0 canales
Get PRO
abril '23
+209
en 0 canales
Get PRO
marzo '23
+62
en 0 canales
Get PRO
febrero '23
+478
en 0 canales
Get PRO
enero '23
+416
en 0 canales
Get PRO
diciembre '22
+188
en 0 canales
Get PRO
noviembre '22
+357
en 0 canales
Get PRO
octubre '22
+579
en 0 canales
Get PRO
septiembre '22
+132
en 0 canales
Get PRO
agosto '22
+166
en 0 canales
Get PRO
julio '22
+145
en 0 canales
Get PRO
junio '22
+110
en 0 canales
Get PRO
mayo '22
+137
en 0 canales
Get PRO
abril '22
+335
en 0 canales
Get PRO
marzo '22
+86
en 0 canales
Get PRO
febrero '22
+68
en 0 canales
Get PRO
enero '22
+195
en 0 canales
Get PRO
diciembre '21
+117
en 0 canales
Get PRO
noviembre '21
+251
en 0 canales
Get PRO
octubre '21
+370
en 0 canales
Get PRO
septiembre '21
+118
en 0 canales
Get PRO
agosto '21
+262
en 0 canales
Get PRO
julio '21
+270
en 0 canales
Get PRO
junio '21
+133
en 0 canales
Get PRO
mayo '21
+145
en 0 canales
Get PRO
abril '21
+177
en 0 canales
Get PRO
marzo '21
+431
en 0 canales
Get PRO
febrero '21
+83
en 0 canales
Get PRO
enero '21
+307
en 0 canales
Get PRO
diciembre '20
+5 656
en 0 canales
Fecha
Crecimiento de Suscriptores
Menciones
Canales
03 julio0
02 julio+2
01 julio0
Publicaciones del Canal
"ታሪክን ለትውልድ የማሻገር ተራው የኔ ነው "" ከ ሰኔ 26-28 ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ  አለም አቀፍ ገቢ ማሰባሰብያ ቀጥታ ስርጭት ላይ ሁሉም ኢትዮጵያዊ እንዲረባረብ  ጥሪ ቀረበ መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን(አራዳ ጊዮርጊስ )   በሁሉም ባንኮች 1423

2
+1
Sin texto...
1 397
3
Sin texto...
1 919
4
# ወደ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ገዳም መንፈሳዊ ጉዞ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ በጸሎት፣ በጾም፣ በትሕትና፣ በትዕግሥት እና በፍቅር ሕይወቷን ለእግዚአብሔር የሰጠች ታላቅ ቅድስት ናት። ሕይወቷ ለእኛ የን
# ወደ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ገዳም መንፈሳዊ ጉዞ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ በጸሎት፣ በጾም፣ በትሕትና፣ በትዕግሥት እና በፍቅር ሕይወቷን ለእግዚአብሔር የሰጠች ታላቅ ቅድስት ናት። ሕይወቷ ለእኛ የንስሐ፣ የጽናት እና የእምነት ትምህርት የምትሰጥ ሕያው ምሳሌ ነው። በዚህ መንፈሳዊ ጉዞ ወደ ቅድስቷ ገዳም በመጓዝ፣ የተቀደሱ አሻራዎቿን እና የተጋድሎ ስፍራዎቿን በቅርብ ይጎበኛሉ። ### በጉዞው የሚጎበኙ መንፈሳዊ እና ታሪካዊ ስፍራዎች ✥ ቅድስቷ በእጇ የተከለቻቸውን አጸዶች። ✥ ለ3 ቀንና 3 ሌሊት በጸሎት የቆየችበትን ጎጆ። ✥ በረጅም ጊዜ በጸሎትና በተጋድሎ የቆየችበትን የጸሎት ስፍራ። ✥ ከ800 ዓመታት በላይ የቆዩ የገዳሙን ታሪካዊ ቅርሶች። ✥ በብዙ ፈተናዎች ውስጥ ቆመው እስከ ዛሬ የደረሱ ታሪካዊ ዛፎችንና የገዳሙን ቅርሶች። ### ከቅድስቷ ሕይወት የምንማረው * ጸሎት ሰውን ወደ እግዚአብሔር ያቀርባል። * ትዕግሥትና ትሕትና የቅድስና መንገድ ናቸው። * ለሌሎች የምናደርገው ምልጃና ፍቅር በእግዚአብሔር ዘንድ ታላቅ ዋጋ አለው፤ ቅድስቷም ለሰው ሁሉ ምሕረት እንዲሆን ጸልያለች። እርስዎም ከእኛ ጋር ይህን መንፈሳዊ ጉዞ ይቀላቀሉ። የቅድስቷን ገድል በተከናወነበት ስፍራ ይመልከቱ፣ በጸሎት ይሳተፉ፣ መንፈሳዊ በረከትንም ይቀበሉ። ትኬት ለማግኘት 0922872768 0924866375 0926580604
2 102
5
+9
Sin texto...
1 946
6
ሰኔ ፳፬ #አባ_ሙሴ_ጸሊም በሰማዕትነት አረፈ ሰዎች ከገድሉ የተነሣ ይህን ቅዱስ ያደንቁታል እርሱ  አስቀድሞ መንግሥተ ሰማያትን ገፍቷት ነበረና እርሱ በሥጋው  ጠንካራ በሥራውም ኃይለኛ ነበር ይበላና ይጠጣ ይቀማና ያመነዝር ነበር ይገድልም ነበር ማንም ሊቋቋመው አይችልም ነበር። አንድ በግ በአንድ ጊዜ ጨርሶ እንደሚበላና አንድ ቀን ወይን ጠጅ እንደ ሚጠጣ ስለ እርሱ ተነግሮአል። እርሱም ፀሐይን ለሚያመልኩ ሰዎች አገልጋይ ነበረ ብዙ ጊዜም ወደ ፀሐይ እያንጋጠጠ ፀሐይ ሆይ አንተ አምላክ ከሆንክ አነጋግረኝ ይል ነበር ደግሞም በልቡ የማላውቅህ ሆይ ራስህን አሳውቀኝ ይል ነበር። ከዚህም በኋላ በአስቄጥስ ገዳም ያሉ መነኰሳት እግዚአብሔርን ያውቁታል ያዩታልም እያሉ ሲነጋገሩ ሰዎችን ሰማቸው። ያን ጊዜም ተነሣ ሰይፉንም ታጥቆ ወደ አስቄጥስ ገዳም ሔደ በደረሰም ጊዜ አባ ኤስድሮስን አገኘው አባ ኤስድሮስም ፈራው ሙሴ ጸሊምም እውነተኛውን አምላክ ታሳውቁኝና ታስረዱኝ ዘንድ  ወደ እናንተ መጣሁ አለው አባ ኤስድሮስም ወደ አባ መቃርስ ወስዶ አገናኘው። እርሱም ተቀብሎ ሃይማኖትን አስተ ማረው እንዲህም አለው ታግሰህ የማስተምርህን ከጠበቅህ እግዚአብሔርን ታየዋለህ። ከዚህም በኋላ የክርስትና ጥምቀትን አጥምቆ አመነኰሰው ከብዙዎች ገድለኞች ቅዱሳን ይልቅ ብዙና ጽኑዕ ገድልን መጋደል ጀመረ። ሰይጣንም አስቀድሞ ሲሠራው በነበረ በመብልና በመጠጡ በዝሙቱም ይዋጋው ነበረ እርሱም በራሱ ላይ የሚደርስበትን ሁሉ ለአባ ኤስድሮስ ይነግረው ነበር እርሱም አጽንቶ ሊሠራው የሚገባውን ያስተምረው ነበር። ከገድሉ ብዛትም የተነሣ አረጋውያን መነኰሳት በሚተኙ ጊዜ ቤቶቻቸውን በመዞር ውኃ መቅጃዎችን ወስዶ ውኃ መልቶ በየቤታቸው ደጃፍ ያኖር ነበር። ውኃው ከእነርሱ ሩቅ ነበረና እንዲህም እያደረገ በመጋደል ለብዙ ዘመናት ኖረ። ሰይጣንም በእርሱ ቀንቶ በእግሩ ውስጥ አስጨናቂ የሆነ አመታትን መታው ተኝቶም እየተጨነቀ ብዙ ቀን ታመመ ከዚህም በኋላ የመታውና የሚፈታተነው ሰይጣን እንደሆነ ዐውቆ ሥጋው በእሳት ተለብልቦ እንደ ደረቀ ዕንጨት እስቲሆን ድረስ ተጋድሎውንና አገልግሎቱን አበዛ። እግዚአብሔርም ትዕግሥቱን አይቶ ከደዌው ፈወሰው የሰይጣንንም ጦር ከእርሱ አራቀለት የመንፈስ ቅዱስም ጸጋ አደረበት ወደርሱም አምስት መቶ ወንድሞች መነኰሳት ተሰበሰቡ በእነርሱም ላይ አበምኔት ሆነ። ከዚህ በኋላ ቅስና ሊሾሙት መረጡት በቤተ መቅደስም በሊቀ ጳጳሳቱ ዘንድ ባቆሙት ጊዜ ሊቀ ጳጳሳቱም አልፈቀደም ነበር፤ አረጋውያኑንም ይህን ጠቋራ ለምን አመጣችሁት ከዚህ አውጡት አላቸው፤ #እርሱም "መልክህ የከፋ ጠቋራ ሆይ፣ መልካም አደረጉብህ" በማለት ራሱን እየገሠጸ ወጣ ከዚህ በኋላ ዳግመኛ ሊቀ ጳጳሳቱ ጠራውና እጁን በላዩ ጭኖ ቅስና ሾመው እንዲህም አለው ሙሴ ሆይ እነሆ በውስጥም በውጭም ሁለመናህ ነጭ ሆነ። በአንዲትም ዕለት ቅዱሳን አረጋውያን ወደርሱ መጡ በእርሱም ዘንድ ውኃ አልነበረም እርሱም ከበዓቱ ብዙ ጊዜ ወጣ ገባ ይል ነበር ከዚህ በኋላም ብዙ ዝናም ዘንሞ ጒድጓዶችን ሁሉ ሞላ። አረጋውያንም ለምን ብዙ ጊዜ ወጣ ገባ ትል ነበር ብለው ጠየቁት እርሱም እግዚ አብሔርን ውኃ ካልሰጠኸኝ ቅዱሳን አገ ልጋዮችህን ምን አጠጣቸዋለሁ እለው ነበር፤ በቸርነቱም ዝናምን ልኮልን ውኃን አገኘን አላቸው። በአንዲትም ዕለት አባ ሙሴ ከአረጋውያን ጋራ ወደ አባ መቃርስ ሔደ አባ መቃርስም የሰማዕትነት አክሊል ያለው ከእናንተ ውስጥ አንዱን እነሆ አያለሁ አላቸው አባ ሙሴም አባቴ ሆይ በሰይፍ ይገደል ዘንድ አለው የሚል ጽሑፍ አለና ብሎ መለሰ። ከዚህም በኋላ የበርበር ሰዎች መጡ አባ ሙሴም ከእርሱ ጋራ ያሉትን መነኰሳት እነሆ የበርበር ሰዎች ደረሱ መሸሽ የሚፈልግ ይሽሽ አላቸው እነርሱም አባታችን አንተስ አትሸሽምን አሉት እርሱም #በሰይፍ የገደለ በሰይፍ ይገደላል ስለሚለው የእግዚእብሔር ቃል እነሆ ያቺን ቀን ለብዙ ዘመናት ስጠብቃት ኖሬአለሁ አላቸው። ወዲያውኑም የበርበር ሰዎች ገብተው በሰይፍ ገደሉት መሸሽ ስላአልፈለጉ ከእርሱ ጋራ ሰባት መነኰሳትም ተገደሉ አንዱ ግን ከምንጣፍ ውስጥ ተሠወረ የእግዚአብሔርንም መልአክ እየ በእጁም አክሊል ነበር እርሱም ቆሞ ይጠብቅ ነበር። ይህንንም ባየ ጊዜ ከተሠወረበት ወጣ፤ የበርበር ሰዎችም ገደሉት የሰማዕትነ ትንም እክሊል ተቀበለ። ወንድሞች ሆይ ከሀዲና ነፍሰ ገዳይ ቀማኛና ዘማዊ  የነበረውን ለውጣ ደግ አባት መምህርና የሚያጽናና ለመነኰሳትም ሥርዓትን የሠራ ካህን እንዳደረገችው በሁሉም አብያተ ክርሰቲያን ስሙ እንዲጠራ እንዳደረገችው #የንስሐን_ኃይሏን_ተመልከቱ። ሥጋውም በአስቄጥስ ገዳም ደርምስ በተባለ ቦታ ለዘላለም ይኖራል ከእርሱም ብዙዎች ድንቆችና ተአምራት ይታያሉ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። #ሰኔ #፳፬ ፤ #በዓለ_ዕረፍቱ_ለአቡነ_ሙሴ_ጸሊም_፡፡ #በአገራችን_በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የአቡነ_ሙሴ_ጸሊም_በዓለ_ዕረፍት_ክብረ_በዓል_የሚከበርባቸው_ጥንታውያን #፪ (ሌሎች ያልጠቀስናቸው ካሉ ጨምሩበት፡፡) ፩. ግብጽ ሰሜን ምዕራብ ኒትሪያን በረሐ ባራሞስ እመቤታችን ገዳም፤ (የቅዱስ አባ ሙሴ ጸሊምና የመምህሩ የቅዱስ አባ ኤስድሮስ የከበረ ዐፅማቸው በክብር ያረፈበት) አድራሻ፤ ግብጽ ሃገር፥ ሰሜን ምዕራብ ኒትሪያን በረሐ፥ ባራሞስ እመቤታችን ገዳም፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ → ግብጽ → ሰሜን ምዕራብ ኒትሪያን በረሐ፡፡ ፪. ሐመር ቡስካ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ወአቡነ ሙሴ ገዳም፤ አድራሻው፤ ደቡብ ኦሞ ሀገረ ስብከት፥ ሐመር፥ ቡስካ ተራራ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. አየር ጤና አውቶቡስ ተራ → አርባ ምንጭ → ሐመር → ቡስካ፤ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958
1 938
7
http://t.me/finotehiwott+5
http://t.me/finotehiwott
4 295
8
ሰኔ 21  ሰኔ ጐልጐታ ወሕንፀተ ቤተክርስቲያን እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስተ ቅዱሳን ለድንግል ማርያም ሰኔ ጐልጐታና ሕንፀተ ቤተ ክርስቲያን (ለመጀመሪያ ጊዜ ቤተ ክርስቲያን ለታነጸበት) ክብረ በዓል በሰላምና በጤና አደረሰን አደረሳችሁ፡፡ ‹‹ሰኔ ጐልጐታ ፤ ችግር የምትፈታታ፡፡›› ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያም በዚህች  ቀን (ሰኔ 21) ልጇን ወዳጇን ጐልጐታ በሚባል ቦታ ላይ እንባዋ እንደ ጅረት እስኪፈስ ድረስ ለኃጥአን ምሕረትን ለምናዋለች:: ጌታችንም ‹‹ስምሽን የጠራውን፤ በቃል ኪዳንሽ ያመነውን ሁሉ እምርልሻለሁ፡፡›› ብሎ ቃል ኪዳን ሰጥቷታል፡፡ ሰኔ ጐልጐታን ተመልከት ✤✤ ሕንፀተ ቤተ ክርስቲያን፤ ሰኔ 21 ከእመቤታችን #33ቱ በዓላት አንዱ ሲኾን፤ ሕንጸተ ቤተክርስቲያን ይባላል፡፡ በሐዲስ ኪዳን የመጀመሪያዋ ቤተክርስቲያን በአምላክ እናት ስም የታነጸችው በዚሁ እለት በሰኔ 20 ቀን ነው፡፡ አናጺውም ደግሞ እራሱ ባለቤቱ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሲሆን፤ ቦታው በፊልጵስዩስ ነው፤ ቤተክርስቲያኗ የተሰየመችው ደግሞ በእመቤታችን ስም ነው፤ ጥንተ ነገሩስ (ታሪኩ) እንደምን ነው ቢሉ፤ ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና አምላካችን መደኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርቱን ‹‹ሑሩ ወመሐሩ ኵሎ አሕዛበ፤ አሕዛብን ሁሉ ሒዱና አስተምሩ፡፡›› /ማቴ. 28፥19/ ባላቸው ቃል መሠረት ሐዋርያት በወንጌል ያርሷት ዘንድ በዕጣ ተካፍለዋታል:: የሰው ልጅ ድኅነቱ የሚፈጸመው ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ሲቀበል ነውና (ዮሐ. 6፥ 56) አበው ሐዋርያት ቊርባንን በተመረጡ ሰዎች ቤት እያዘጋጁ ቀድሰው  ያቆርቡ ነበር:: በመጀመሪያ በጽርሐ ጽዮን፣ቀጥሎም በተለያዩ ሰዎች ቤት እንዲህ ይከናወን ነበር፡፡ ለጸሎት ሥራ ደግሞ አንዳንዴ ምኵራበ አይሁድን ይጠቀሙ ነበር:: እየቆየ ሲሔድ ግን ከአሕዛብ ያመኑ ሰዎች ቊጥር እጅጉን በመብዛቱ /በተለይ ቅዱስ ዻውሎስ ያሳመናቸው ለጸሎት እያሉ ወደ ጣዖት ቤት መግባት አመጡ::/ በዚህ ምክንያት መምህራን ሕዝቡን ‹‹ካመናችሁ በኋላ እንዴት ወደ ጣዖት ቤት ትገባላችሁ?›› ቢሏቸው ‹‹እኛ ምን እናድርግ! የምንጸልይበት ቤት የለን››ሲሉ መለሱላቸው:: ነገሩ ሲያያዝ ከደጋጉ ሐዋርያት ዻውሎስና በርናባስ ደረሰ:: ወዲያውኑ አንዳንድ ወንድሞች ቤት ‹‹ለምን አናንጽም?›› ብለው ነበር:: ቅዱስ ዻውሎስ ግን ‹‹ሊቀ ሐዋርያቱ ሳይፈቅድ አይሆንም›› አለ:: (ለዚህ ነው ዛሬም ሊቀ ዻዻስ ካልፈቀደ ቤተክርስቲያን የማይታነጸው፡፡) ከዚያ ቅዱሳን ዻውሎስና በርናባስ ሐዋርያቱ ወዳሉበት ሔደው ነገሩን ለቅዱስ ዼጥሮስ አስረዱ:: ሊቀ ሐዋርያቱ ቅዱስ #ዼጥሮስም ‹‹የጌታችን ፈቃዱመኾኑን እናውቅ ዘንድ ተያይዘን ሱባዔ እንግባ›› ብሎ አዋጅ ነገረ:: በዓለም ያሉ ክርስቲያኖች ሁሉ በአንድ ልብ ሱባዔ ገቡ:: በሱባዔያቸው መጨረሻም ክብር ይግባውና ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በኪሩቤል ጀርባ ላይ ሆኖ እልፍ አእላፍ መላአክትን አስከትሎ በግርማ ወደ እነርሱ ወረደ፤እመቤታችን በቀኙ ነበረች፡፡ ኹሉንም ሐዋርያት በሩቅም በቅርብም ያሉትን ደቀ መዛሙርቱን በደመና ጠቅሶ ፊልጵስዩስ በሚባል ሃገር ሰበሰባቸው፡፡ ከዚያም በስተምሥራቅ ከከተማ ወጣ ወዳለ ሥፍራ ወሰዳቸው፡፡ በዚያም ተራርቀው የነበሩ 3 ደንጊያዎች ነበሩ፡፡ 3ቱንም ድንጋዮችን በተአምራት አቀራርቦ አንሥቶ ጎተታቸው፡፡ ድንጋዮቹም እንደሰም ተለጠጡ፣ እንደ ግድግዳም ሆኑ፡፡ ቁመቱን ወርዱን መጥኖ ለሐዋርያቱ ሰጣቸው፡፡ እነርሱም እሳት እንዳየው ሰም በእጃቸው እየለመለሙ (እየሳቡ) ቁመቱን 24፥ ወርዱን 12 ክንድ አድርገው ዕጽብት፥ ግርምት የምትኾን 3 ክፍል ያላትን የመጀመሪያዋን ቤተክርስቲያን በ52 ዓ/ም ሰኔ 20 ቀን አነጹ፡፡ ዳግመኛም የብርሃን ምሰሶ ወረደ፤ ጌታችንም በሰማያዊቷ ኢየሩሳሌም አምሳያ አድርጎ አነጻት፤ ሁለንተናዋም ተጠናቀቀ፡፡ ከዚህም በኋላ ጌታችን ለሐዋርያቱ ‹‹እንግዲህ እናንተም እንዲህ አድርጋችሁ ሥሩ፡፡›› ብሏቸው ዐረገ፡፡ ✜ በማግስቱ ሰኔ 21 ዕለት ደግሞ ለስም አጠራሩ ጌትነት ይሁንና ጌታችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አእላፍ መላእክትን፣ ሰማያውያን ቅዱሳንን እና እናቱን ቅድስት ድንግል ማርያምን ይዞ ወረደ:: ሐዋርያቱ አብዛኞቹ እዛው ሲጸልዩ አድረው ነበርና ጌታችን ከቅዳሴው በፊት 2 ነገሮችን አሳየ፤ አስቀድሞ ቤተክርስቲያኗን በድንግል እናቱ ስም አክብሮ ሥርዐተ ቤተክርስቲያንን አሳየ:: ቀጥሎ ደግሞ ሊቀ ሐዋርያት ቅዱስ ጴጥሮስን ከመካከል አቁሞ ‹‹አርሳይሮስ›› ሲል ሾመው:: ይኼውም የዓለም ሁሉ ሊቀ ዻዻሳት (ፓትርያርክ) ማለት ነው:: በዚህ ጊዜ ቅዱሳን መላእክት ‹ ‹‹አክስዮስ››(አክዮስ)እያሉ 3 ጊዜ አሰምተው ጮሁ:: አክዮስ ማለት በግዕዙ ‹‹ይደልዎ›› በአማርኛው ደግሞ ‹‹ይገባዋል፤ ያስምርለት›› እንደ ማለት ነው:: ጌታችን ይህን ከከወነ በኋላ ይቀድስ ዘንድ ጀመረ:: አማናዊት ማኅደሩን ድንግል ማርያምን መንበር አድርጎ፣ ቅዱስ ጴጥሮስ እንደ ተራዳኢ ካህን ቆሞ፣ ቅዱስ እስጢፋኖስ ሠራኢ ዲያቆን ኾኖ፣ ሐዋርያት ድንግልን ከበው፣ መላእክተ ብርሃን በክብራቸው ቆመው ጌታችን ቀድሶ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለወዳጆቹ አቀበለ:: በዚያች ዕለት በፍጡር አንደበት ተከናውኖ ሊነገር የማይችል ደስታ ተደረገ:: ከቅዳሴ በኋላ ጌታችን ሐዋርያትን አዘዛቸው:: ‹‹ከዚህ ቀን ጀምሮ በመላው ዓለም በእናቴ በማርያም ስም አብያተ ክርስቲያናትን አንጹ፤ ይህችን  እለት የሚያከብራትን አከብረዋለሁ::›› ብሏቸው ከድንግል እናቱና ከመላእክቱ ጋር ዐረገ:: ✤✤ ሥርዐተ ማኅሌቱ እንደየደብራችሁ ይትበሃል ትጠሙበበት ዘንድ የሁለቱንም (የላይ ቤት የግምጃ ቤትና የታች ቤት የበአታን) አብነት አስቀምጠንላችኋል፤ በቢጫ የተቀለመው የላይ ቤት (የግምጃ ቤት) አብነትን ለምትከተሉ አድባራት ሲኾን፤ ሰማያዊ የተቀለመው ደግሞ የታች ቤትን (የበዓታን) የአቋቋም ይትበሃል ለምትጠቀሙ ሲኾን፤ ሁለቱም የላይ ቤቱና ያየታች ቤቱ የሚተባበሩበት ላይ ደግሞ ዘግምጃ ቤት ወዘበዓታ ብለን በፈዛዛ ጥቁር አስቀምጠንላችኋል፡፡ መልካም ማኅሌት፨ ኦ አበው ወእማት አኃው ወአኃት ኢትርስዑነ በጸሎተክሙ (በዘጸለይክዋ በዝንቱ ሥርዐተ ማኅሌት) ለትምህርተ ቤትነ ቀ.ደ.ሰ.መድኀኔዓለም ወደ.ት.ቅ.ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት፡፡ ✼ የድንግል እመቤታችን ልመናዋ ክብሯ፣ ጣዕመ ፍቅሯና በረከቷ በሁላችን ላይ ይደርብን:: /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958
3 595
9
Sin texto...
4 466
10
Sin texto...
4 171
11
Sin texto...
5 232
12
http://t.me/finotehiwott+5
http://t.me/finotehiwott
6 412
13
ጠየቀችው፡፡ ለጊዜው ‹‹በእኛ በመላእክት ዘንድ እንዲህ አይደለም›› ብሎ ሊሸነግላትና አቋሟን ሊያስቀይራት ሞከረ። ከቤቷ ያለ የቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ላይ ያለውን ምልክት አብራርታ የእርሱ ግን ከዛ ጋር አንድነት እንደሌለው አረጋገጠችበት፡፡  በመቀጠልም ከቤቷ ላለው ለቅዱስ ሚካኤል ሥዕል እጅ እንዲነሣ ጠየቀችው፡፡ በዚህ ጊዜ መልኩ ወደ ትክክለኛ ሰይጣናዊ ማንነቱ ተለወጠና ጨለማ ለብሶ እየዛተ አነቃት፡፡ ቅድስት አፎምያም የከበረ መልአክ ቅዱስ ሚካኤልን "ድረስልኝ" እያለች በጠራችው ጊዜ መልአኩም ፈጥኖ በመድረስ ከሰይጣን እጅ አዳናት፡፡ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958
4 722
14
የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ለሰይጣኑ ተገቢውን ቅጣት ሰጥቶ ቅድስት አፎምያን ባረካት፡፡ የዕረፍት ቀኗ በዚህ ቀን መሆኑን ነግሮ ቤቷን እንድታዘጋጅ አዘዛት፡፡ የበዓሉን ዝግጅት አከናውና ሥጋ ወደሙን ተቀብላ ኤጲስ ቆጶሱንና ካህናቱን እንደየመዓርጋቸው ጠርታ በቤቷ አክብራ ተቀበለቻቸው፡፡ ለነዳያንና ለጾም አዳሪዎች በኤጲስ ቆጶሱና በካህናቱ እጅ ገንዘቧን መጽውታ መንገዷን አሳመረች፡፡ ስለ ኃጢአቷ እንዲጸልዩላት ተማፅና በፊታቸው ተንበርክካ ጸለየች፡፡ ባሏ ያሠራላትን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል አቅፋ ስማ ከተማጸነች በኋላ ሰኔ 12 ቀን በሰላም ዐረፈች፡፡ #፬. ቅዱስ ላሊበላን ወደ ሰማያት ማሳረጉን፤ ወደፊት ውቅር አብያተ ክርስቲያናትን እንደሚያንጽ ጌታችን የነገረውና የሕንጻዎቹን አሠራር ዝርዝር የነገረው በዚሁ እለት ነው፡፡ ባሕራንም መልእክቱን ለማድረስ ዘጠኝ ቀን ተጉዞ የአንድ ቀን ጎዳና ሲቀረው እነሆ ክቡር የሚሆን የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል በንጉሥ ጭፍራ አምሳል በፈረስ ተቀምጦ ወደሱ ደረሰና ወዴት እንደሚሄድ ጠየቀው፡፡ ባሕራንም ‹‹ከአንድ ባለጸጋ ሰው የተጻፈ ደብዳቤ ይዤ እርሱን ለማድረስ ዕገሊት ወደምትባል አገር እሄዳለሁ›› አለው። ንዑድ ክቡር የሚሆን ቅዱስ ሚካኤልም "እስኪ የመልእክቱን ደብዳቤ አሳየኝ?" አለው፡፡ ባሕራንም ‹‹ጌታዬ ለማንም አታሳይ ብሎኛል›› አለው፡፡ መልአኩም ‹‹እሺ ያም ባይሆን እንደተጠቀለለ አሳየኝ›› አለው፡፡ ባሕራንም አሳየው፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም በሞቱ ደብዳቤ ላይ እፍ ቢልበት የሞቱን ትእዛዝ አጥፍቶ የሕይወት ትዕዛዝ ጽፎበታል፡፡ በደብዳቤው ላይ የተጻፈውን የሞት መልእክት ደምስሶ ‹‹ከእኔ ከባለጸጋ ዕገሌ የተጻፈ›› ይልና ‹‹ይህን መልእክት ይዞ ለመጣሰው ዕገሊት የምትባለዋን ልጄን አጋቡት (ዳሩለት) በዱር የተሰማራውን ከብቴን ፥ በቤት ያለውን ሀብቴን በጠቅላላው የሚንቀሳቀስና የማይንቀሳቀስ ንብረቴን በሙሉ አውርሼዋለሁና እኔ እስክመጣ ድረስ አትጠብቁ በሄድኩበት ሀገር የምቆይበት ጉዳይ አለኝና፤ በቤቴና በንብረቴ ላይ ሙሉ ሥልጣን ሰጥቼዋለሁና የወደደውን ያደርግ ዘንድ አትከልክሉት ስለዚህም በእኔና በአንተ መካከል የምንተዋወቅበትን ምልክት አድርጌበታለሁ›› የሚል ጽሑፍ ጻፈበት "እንግዲህ ወደ ባለጸጋው ቤት ሂድና ይህን መልእክት አድርስ አለው፤ ባሕራንም ‹‹እሺ ጌታዬ እንዳዘዝከኝ አደርጋለሁ›› ብሎ ጉዞውን ቀጠለና የዚያን የባለፀጋ ቤት እየጠየቀ ከደረሰበት በኋላ ደብዳቤውን ለሹሙ ሰጠው። ያም ሹም ደብዳቤውን ተቀብሎ ሲያነብ የታተመበት ማኅተም ዕውነተኛ መሆኑን ካረጋገጠ በኋላ በቤተ ክርስቲያን ደንብ የባለጸጋውን ልጅ አጋባው፣ የሠርጉንም በዓል እስከ ፵ ቀን ድረስ በታላቅ ደስታ አከበሩ። ከሠርጉም በዓል ፍጻሜ በኋላ ያ ባለጸጋ ሰው ከሄደበት አገር ወደ ሀገሩ ተመልሶ ገባና በቤቱ አካባቢ ሲደርስ የደስታና የዘፈን ድምፅ ስለሰማ "ይህ የምሰማው ድምፅ ምንድነው?" ሲል ጠየቀ፡፡ ሰዎቹም ‹‹ባሕራን የተባለ ጐበዝ ካንተ ዘንድ ልጄን ዳሩለት የሚል ትእዛዝ አምጥቶ ልጅህን አግብቶ በሠርጉ ምክንያት ይዘፍናሉ ይደሰታ፤ እነሆ እየበሉና እየጠጡ በቀንና በሌሊት እየዘፈኑ ሲደሰቱ ፵ ቀን ሆኗቸዋል በመልእክትህም እንዳዘዝከው ገንዘብህን የወንድና የሴት ባሮችህን በጠቅላላው የሚንቀሳቀስና የማይንቀሳቀስ ንብረትህን ሁሉ በሙሉ አስረክበውታል›› አሉት። ያም ባለጸጋ ያህን ቃል በሰማ ጊዜ ከድንጋጤው የተነሳ በታላቅ ቃል በመጮኽ ከመሬት ላይ ተከስክሶ ሞተና ነፍሱን አጋንንት ተረክበው ወደ ሲኦል አወረዷት። ከዚህም በኋላ ባሕራን የተባለ ያ ጐልማሳ የቅዱስ ሚካኤልን በዓል በየወሩ እያከበረ ዝክሩን እየዘከረ ይኖር ጀመር። በዚያን ጊዜ በጉዞ ላይ ሳለ ተገልጾለት የሞቱን መልእክት ወደ ሕይወት የለወጠለት ቅዱስ ሚካኤል እንደሆነም አወቀ ተረዳ። ንዑድ ክቡር የሚሆን የመላእክት ሁሉ አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ያደረገው ተአምር ሊቈጥሩት የማይቻል ብዙ ስለሆነ በኛም ላይ ኃይለ ረድኤቱ አድሮብን ይኑር እስከ ዘላለሙ ድረስ አሜን፡፡ #፭. አፎምያን ያዳነበት ቅድስት አፎምያ ሀገሯ ኪልቅያ ነው፡፡ ባለቤቷ አስተራኒቆስ መስፍነ ኪልቅያ ነበረ፡፡ በየወሩ በ29 ቀን የጌታችንን የልደቱን፣ ወር በገባ በ21 የእመቤታችንንና ወር በገባ በ12 የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያደረጉ ነዳያንን ይጎበኙ ነበር፡፡ ባለቤቷ አስተራኒቆስ ከዚህ ዓለም የሚያርፍበት ጊዜ እንደደረሰ ባወቀ ጊዜ ይሰጡት የነበረውን ምጽዋት እና የሦስቱን በዓላት መታሰቢያ ማድረግ እንዳታስታጕል ከአደራ ጋር አዘዛት፡፡ እርሷም የመልአኩን የቅዱስ ሚካኤልን ሥዕል ያሥልላት ዘንድ ባለቤቷን ጠይቃ አሠርቶ ሰጣት፡፡ በከበረ ቦታም አኖረችው፡፡ ባሏ ካረፈ በኋላ ያዘዛትን መንፈሳዊ ሥራ ከወትሮው አስበልጣ መሥራት ቀጠለች፤ ከሀብቷ ከንብረቷ እየሰጠች እየመጸወተች በጾም ፥ በጸሎት ተወስና ትኖር ነበር፡፡ ሰይጣን ለምቀኝነት አያርፍምና ደግ መነኵሴ መስሎ አጋንንትን መነኰሳይያት አስመስሎ መጥቶ ከደጅ ሆኖ አስጠራት፡፡ እርሷም ‹‹ከቤት ገብታችሁ በቅዱስ ሚካኤል ሥዕል ፊት ጸልዩልኝ›› አለቻቸው፡፡ ሰይጣናቱም ‹‹እኛማ በነግህ ጸልየናል?›› አሏት፡፡ ቀጥሎም ሰይጣን ‹‹...እንደው አንቺ ግን ይህ ሁሉ ጾም ጸሎት ምን ያደርገልሻል? ሀብትሽን ሰጥተሸ መጨረስሽስ ስለምንድን ነው? በዚያ ላይ አንቺ ስትደክሚ የሚደግፍሽ ፥ ስታረጂ የሚጦርሽ ልጅ የለሽም ሁለተኛ ማግባት ኃጢአት መስሎሻልን? እነ አብርሃም እነ ዳዊት ከብዙ ሴቶች ብዙ ልጆች ወልደው የለምን? አሁንም ቤት ሰሪ፥ ጎመን ዘሪ ልጅ ያስፈልግሻልና ባል አግቢ፣ እሺ በይኝ›› አላት፡፡ ቅድስት አፎምያም ‹‹አባ ቆብህ መልካም ነበር ንግግርህ ግን ክፉ ነው፣ አትጹሚ፥ አትጸልዩ ያልከኝ፤ ጌታ ምጽዋትን መጽውቱ ብሎ የለምን? ሁለተኛ ባል አግቢ ማለትንስ ከምን አገኘኸው? ርግቦች እንኳን ባሎቻቸው ከሞቱባቸው ከሌላ ወንድ አይቀርቡም፤ ታዲያ ጥንት በንጽሕና ሊኖር የተፈጠረ ሰው ሁለተኛ አላገባም ቢል ዕዳ ፍዳ ሊሆንበት ነውን?›› ብላ ሞገተችው፡፡ የሰው ልጆች ጠላት የሆነው ሰይጣንም በመልካም አገልግሎት ስትበረታ አይቷታልና ዝም ብሎ ሊተዋት አልወደደም፡፡ ከላይ እንዳየነው በመጀመሪያ ባል ሳታገባ ማገልገሏን ትታ ሌላ ባል አግብታ ልጅ ወልዳ እንድትኖር በብዙ ማባበል ጠየቃት፡፡ ባሏ መንግሥተ ሰማያትን ስለወረሰ ምንም ምጽዋት እንደማይሻ አስመስሎ ነገራት፡፡ ቅድስት አፎምያ ግን ዳግመኛ ትዳር ላለመመሥረት ቃል ኪዳን እንደገባች ርግብንና ዖፈ መንጢጥን አብነት አድርጋ እነርሱ እንኳ በሕይወት ዘመናቸው ከአንድ ባል ውጪ ሌላ ባል እንደማያውቁ በመጥቀስ አሳቡን እንደማትቀበለው ገለጸችለት፡፡  ሰይጣንም አስመሳይ መሆኑ አላዋጣ ሲለው ማንነቱን ቀይሮ ሊያንቃት ቢሞክር የእግዚአብሔርንና የቅዱስ ሚካኤልን ስም ጠርታ አባረረችው፡፡ እርሱም ተመልሶ መጥቶ እንደሚያጠፋት ዝቶባት እንደአቧራ በኖ እንደ ጢስም ተኖ ጠፋ፡፡ በሰኔ 12 ቀን የቅዱስ ሚካኤልን መታሰቢያ እያዘጋጀች ሳለች ሰይጣን ብርሃናዊ መልአክ መስሎ መጣ፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል እንደሆነ ገልጾ የመጀመሪያውን የመሰለ ከንቱ ምክሩን አሰማምሮ አቀረበላት፡፡ አሳቡንም የእግዚአብሔር ፈቃድና አሳብ እንደሆነ አድርጎ ለማሳመን ቅድስት አፎምያም በእግዚአብሔር ኃይል ጸንታ በቅዱስ ሚካኤልም ተራዳኢነት ታምና ‹‹የእግዚአብሔር መልአክ ከሆንክ መንፈሳዊ ማረጋገጫህ የሆነው የመስቀል ምልክት የታለ?›› በማለት በምድራዊ ንጉሥና በጭፍራው መካከል የሚኖርን የጋራ መግባቢያ መንገድ ዋቢ አድርጋ
3 348
15
#ሰኔ_፲፪   በዓለ ተዝካሩ #ለቅዱስ_ሚካኤል ሊቀ መላእክት #ወቅዱስ_ላሊበላ  #ቅዱስ_ሚካኤል_አፎምያንና_ባሕራንን_ያዳነበት_እለእስክንድሮስ_ቅዳሴ_ቤቱን_ያከበረበትና_የቅዱስ_ላሊበላ_ዕረፍቱ_ነው፡፡    #ሰኔ_፲፪ #መከበሩ_ስለምንድን_ነው_ቢሉ_፤ ከጽንፍ እስከ ጽንፍ የሚበር፤ ንሥረ አርያም የሚባል፥ ውዳሴው እንደ ማር የጣፈጠ፥ ንዑድ ክቡር የሆነ ፥ የመላእክት ሁሉ አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ፭ት ነገሮችን የፈጸመበት እለት ነው  እንዲሁም  የሌሎችም ቅዱሳን መታሰቢያ ቀናቸው  (ቅዱስ ላሊበላን ወደ ሰማያት ነጥቆ ወስዶ ያሳየበት) ፡፡ ሚካኤል ፭ት ነገሮችን የፈጸመበት እለት ነው  እነርሱም፤    #share ፠፩. በዓለ ሲመቱ ለቅዱስ ሚካኤል፤ ፠፪. ባሕራንን ያዳነበት፤ ፠፫. የአስተራኒቆስ ሚስት ቅድስት አፎምያን ያዳነበት፤ በዓለ እረፍቷም በዚሁ እለት ነው፤ ፠፬. በግብፅ ሃገር ፓትርያርክ እለ እስክንድሮስ ቅዳሴ ቤቱን ያከበረበት፤ ፠፭. ቅዱስ ላሊበላን ወደ ሰማያት ነጥቆ ወስዶ ያሳየበት፤ ፠ ሐናፄ መቅደስና በሰማያት ያለ ምሥጢርን የተመለከተ ቅዱስ ላሊበላ ንጉሠ ነገሥት ዘኢትዮጵያ በዓለ ዕረፍቱ ነው፤ ፠67ኛ ሊቀ ጳጳስ ቄርሎስ ሊቀ ዻዻሳት ዘእስክንድርያ እረፍቱ ነው፤ ፠የእስክንድርያ 6ኛ ሊቃነ ጳጳሳት አባ ዮስጦስ (ወንጌላዊና ሐዋርያው ቅዱስ ማርቆስ የክርስትና ጥምቀትን ያጠመቀው፥ ዲቁናና ቅስናን የሾመው) እረፍቱ ነው፡፡ ማብራሪያ፤ #፩. ቅዱስ ሚካኤል በፈቃደ እግዚአብሔር ከዲያብሎስ ጋር ተዋግቶ ያሸነፈበት፤ አምላክነትን ሽቶ በወደቀው በዲያብሎስ ምትክ ሊቀ መላእክት ሆኖ የተሾመበት እለት በመሆኑ ነው፡፡ ቀድሞ ከ100 ነገደ መላእክት ኃይላት የሚባሉ የ10 ነገደ መላእክት አለቃ ነበር፤ በዚህች ቀን ግን የኃይላት አለቅነቱን እንደያዘ አጋእዝት የተባሉትንና ሳጥናኤል(ሰማልያል) ይመራቸው ለነበሩት 10 ነገዶች በተጨማሪ አለቃ ኾኗል፤ እንዲሁም በአጠቃላይ ለሌሎችም 100 (99ኝ) ነገደ መላአክት አለቃ ሁኗል፡፡ ልዑል ውእቱ ልዑለ መንበር ያሰኘውም ይኸው ነው፡፡ #፪. ቅዳሴ ቤቱ የተከበረበት፤ ፓትርያርክ እለ እስክንድሮስ /312 - 326/ በግብፅ ሃገር ንግሥት ክሌዎፓትራ ‹‹ሳተርን›› ለሚባለው ያሠራችውንና ጣዖት ይመለክበት የነበረውን ቤተ ጣዖትን አፍርሶ በቦታው ላይ ቤተ ክርስቲያን ሠርቶ ታቦተ ሚካኤልን አግብቶ በዓሉን በታላቅ ክብር ያከበረበት እለት ነው፡፡ #፫. ባሕራንን ያዳነበት ሊቀ ጳጳሳት እለ እስክንድሮስ የተሠራውን የቅዱስ ሚካኤልን በዓል ከሚያከብሩ ምእመናንን አንዱ የባሕራን አባት ነበር፡፡ እርሱም እግዚአብሔርን የሚፈራ ወር በገባ በየዐሥራ ሁለቱ ቀን የቅዱስ ሚካኤልን ዝክሩን የሚዘክርና ይልቁንም በኅዳር ፲፪ትና በሰኔ ፲፪ት ቀን በታላቅ ክብር የሚያከብር አንድ ሰው ነበር፤ በዚህ ሰው ላይ ላይ ጥላቻ ያደረበትና ርኅራኄ የሌለው አንድ ባለጸጋ ጐረቤት ነበረው፡፡ የቅዱስ ሚካኤልን በዓል በሚያከብርበት ጊዜ ሁሉ ይዘብትበት ይሳለቅበት ነበር፡፡     ይህ እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰውም በዚህ ዓይነት በጐ ሥራ ብዙ ጊዜ ከኖረ በኋላ ከዚህ ዓለም ድካም ያርፍ ዘንድ የሞቱ ጊዜ ቀረበ። ሚስቱንም ጠርቶ ‹‹በጐ ስራ ከመሥራት ለድኃ ከመመጽወት ቸል አትበይ! የቅዱስ ሚካኤልንም በዓል በየወሩ ከማክበር አትቦዝኝ፤ ይልቁንም በኅዳር ፲፪ትና በሰኔ ፲፪ት  ቀን ከፍ ባለ ሥነ ሥርዓት እንድታከብሪ አደራ እልሻለው›› አላት፡፡ በሚሞትበትም ጊዜ ሚስቱ ፀንሳ ነበር። ይህም ደገኛ ሰው በሰላም ዐረፈና ፍጹም መንግሥተ ሰማያትን ወረሰ። ሚስቱም የመውለጃዋ ሰዓት በደረሰ ጊዜ ታላቅ ጭንቅ ላይ ኾነች እርሷም መልአኩን ቅዱስ ሚካኤል እንዲደርስላት ተማጸነችው በሰላምም ተገላገለች፡፡ መልኩ በጣም ያማረ ልጅ ወለደች። የእግዚአብሔር መልእክተኛ ቅዱስ ሚካኤልም ከሰማይ ወርዶ ያን ሕፃን ባረከውና ‹‹ቸርነት ርኅራኄ የሌለውን የዚህን ባለጸጋ ገንዘብና ሀብት እርሻውንም ሁሉ ይህ ሕፃን እንዲወርስ እግዚአብሔር አዟል›› አለ። ያን ጊዜ ያ ባለጸጋ በሴትዮዋ ቤት መስኮት አጠገብ ሆኖ ሁኔታውን ሁሉ ይመለከት ነበርና ይህን ነገር በሰማ ጊዜ ልቡ በታላቅ ሐዘን ተነካ፤ ሕፃኑንም የሚገድልበትን ምክንያት ይፈልግ ጀመር፡፡ ነገር ግን እግዚአብሔር በቅዱስ ሚካኤል ጸሎት ብላቴናውን ከክፉ ነገር ሁሉ ይጠብቀው ነበር። ብላቴናውም ዐሥር ዓመት በሆነው ጊዜ እናቱ በጣም ችግር ፀናባት፡፡ ባለጸጋው እኔ ጋር ተንከባክቤ ላሳድገው ብሎ ከእናቱ ከተቀበለ በኋላ፤ በልጅ ቁመት ልክ ሳጥን አሠርቶ ሕፃኑን በሣጥኑ ውስጥ አግብቶ በላዩ ላይ ቆለፈበትና ሣጥኑን ወስዶ ከባሕር ጨመረው፤ እንዲሁም የሣጥኑን ቁልፍ መክፈቻ አብሮ ወረወረው። ነገር ግን በእግዚአብሔር ፈቃድ ያ ሣጥን ሳይሰጥም በባሕሩ ላይ እየተንሳፈፈ ከዚያች አገር ርቃ ወደምትገኝ የባሕር ወደብ ደረሰ። በባሕሩ አካባቢ በጎቹን አሰማርቶ የሚጠብቅ አንድ ሰው ነበርና ያንን ሣጥን ባየው ጊዜ ከባሕሩ አወጣውና ወደ ቤቱ ወስዶ ሣጥኑን ቢከፍተው ያ ባለ ፀጋ ሊገድለው ያሰበውን ሕፃን በሣጥኑ ውስጥ አገኘው።  ባየውም ጊዜ እጅግ ተደስቶ በባሕር ውስጥ ስላገኘው ስሙን "ባሕራን" ብሎ ሰየመውና እንደ ልጁ አድርጐ ይንከባከበው ዘንድ ወሰነ፡፡ ከባሕራን ሀገር የበግ ጠባቂው አገር የዐሥር ቀን ጐዳና የሚያስኬድ ርቀት ነበረው። ከብዙ ዓመታት በኋላ ያ ባለ ጸጋ ሰው ለንግድ ከሀገሩ ወጣ፡፡ በጉዞውም ላይ ሳለ ፀሐይ ስትገባ ከዚያ የበግ ጠባቂው ዘንድ ደረሰ። በግ ጠባቂውንም ‹‹ወንድሜ ሆይ ባንተ ዘንድ የማድርበት ቢኖር ታሳድረኝ ዘንድ እለምንሃለው፣ ኪራዩንም እከፍልሃለው›› ብሎ ጠየቀውና ያ በግ ጠባቂ ወደ ቤቱ አስገባው። ባለጸጋውም ገብቶ ጥቂት ካረፈ በኋላ በግ ጠባቂው ያን ብላቴና ባሕራን ብሎ ሲጠራው በሰማ ጊዜ ‹‹ልጅህ ነውን?›› ብሎ ጠየቀው። በግ ጠባቂውም ‹‹አዎን ይህ አሁን ጐልማሳ ሆኖ የምታየው ወጣት ገና ሕፃን ሆኖ ሳለ በሣጥን ተከቶ ከባሕር ውስጥ ተጥሎ አግኝቼው ወስጄ አሳድጌዋለሁና ልጄ ነው›› አለው። ባለጸጋውም በባሕር ውስጥ የጣለው ሕፃን መሆኑንም ስላወቀ ይህንን ነገር በሰማ ጊዜ ፈጽሞ ደነገጠ፤ ይገድለውም ዘንድ ፈለገ፡፡ በበነጋውም መንገዱን ለመሄድ ሲዘጋጅ ልዩ ልዩ ምክንያት (ሰይጣናዊ ሐሳብ) በመፍጠር በግ ጠባቂውን ‹‹ወንድሜ ሆይ አንድ የማስቸግርህ ጉዳይ አለኝ ይኸውም በቤቴ የረሳሁት ነገር ስላለ ሄዶ መልእክት ያደርስልኝ ዘንድ ይህን ብላቴና እንድትሰጠኝ ነው የድካሙንም ዋጋ ሃያ ወቄት ወርቅ እከፍላለሁ›› አለው። ያም በግ ጠባቂ ስለ ወርቁ ስጦታ ደስ በመሰኘት ያን ጐልማሳ ጠርቶ ‹‹ልጄ ባሕራን ሆይ ይህ ክቡር ሰው ለሥራ ጉዳይ ወደ ቤቱ ሊልክህ ይፈልጋልና መልእክቱን አድርስለት እግዚአብሔር በሰላም ያግባህ›› ሲል ጠየቀው፡፡ ልጁም ‹‹እሺ መልካም ነው አባቴ ሆይ ያዘዝከኝን ሁሉ ለመፈጸም ዝግጁ ነኝ›› አለው። ከዚህም በኋላ ያ ባለጸጋ ‹‹ይህችን የመልእክት ደብዳቤ ይዞ ወደ አንተ የመጣውን ስሙ ባሕራን የተባለውን መልእክቷ በደረሰችህ ጊዜ ፈጥነህ ግደለው፤ ገድለህም ሬሣውን ከጉድጓድ ጣለው እኔ በሰላም ተመልሼ እስክመጣ ድረስ ማንም ማን ይህን ምሥጢር አይወቅ›› የሚል ጽሑፍ ለሹሙ ጽፎ አዘጋጀ፤ በአገልጋዩ (በሹሙ)ና በእርሱ መካከል የሚተዋወቁበትን ማኅተም በደብዳቤው ላይ አትሞ ለባሕራን ሰጠው፡፡ ለመንገዱም የሚሆነው ስንቅ ሰጥቶ ላከው።
2 069
16
+9
Sin texto...
2 779
17
፲፭. ተንታ ደብረ ብርሃን ቅዱስ ሚካኤል፤ (ንጉሥ ሚካኤል በሚያስደንቅ ሁኔታ ያሠሩት) አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሃገረ ስብከት፥ አምባሰል፥ ተንታ ወረዳ፥ ጠዓት ቀበሌ፥ እሜገኝ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ጻድቃኔ፡፡ ፲፮. አጃና ቅዱስ ሚካኤል፤ (በቀስተ ደመና ጠበል አጥማቂው) አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ተጉለት፥ አጃና፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ጻድቃኔ → አጃና፡፡ ፲፯. ቦንብ አርግፍ ቅዱስ ሚካኤል (ሰሜን ወሎ ሀ/ስብከት፤ የጁ ወልዲያ) ፲፰. ቦረዳ ቅዱስ ሚካኤል ፲፱. ዋሻ ቅዱስ ሚካኤል (ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፣ ኢቲሳ) ፳. አንኮበር ቅዱስ ሚካኤል (ሰሜን ሸዋ ሀ/ስብከት) ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከበርባቸው_ #፻፱ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ 1.. ግሸን ደብረ ከርቤ ቅዱስ ሚካኤል ጎሚስታው ሚካኤል (ትግራይ) እንዳ ቅዱስ ሚካኤል (ትግራይ) መቀለ ቅዱስ ሚካኤል 5. ጾረና ቅዱስ ሚካኤል (ኤርትራ) አለም ገና ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል (አለም ገና፤ ሰበታ መስመር) ደብረ ዘይት /ቢሾፍቱ/ ደብረ አሚን ቅዱስ ሚካኤል ዱከም ቅዱስ ሚካኤል ናዝሬት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል 10. ድሬዳዋ ቅዱስ ሚካኤል ጭሮ አሰበ ተፈሪ ቅዱስ ሚካኤል (ድሬዳዋ፥ አሰበ ተፈሪ) ሻሸመኔ ቅዱስ ሚካኤል (ክርስቲያኖች ስለ ሃማኖቶቻው በ2015 ዓ.ም. ሰማዕታት የሆኑበት) አርባ ምንጭ ላከ ኢየሱስና ሚካኤል ዲላ ቅዱስ ሚካኤል 15. አሰላ ደብረ ሰላም ቅድስ ሚካኤል ጂጂጋ ቅዱስ ሚካኤል ሚዛን ቴፒ ደብረ ኀይል ቅዱስ ሚካኤል ቦንጋ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል ኢሉባቦር ሌንቃ ቅዱስ ሚካኤል 20. እነሞርና ኤነር ወረዳ ቅዱስ ሚካኤል (ጉራጌ ሀ/ስብከት) አሰቦት ደብረ ወገግ ቅዱስ ሚካኤል (ምሥ. ሀረርጌ ሀ/ስብከት) ሽንቁሩ ቅዱስ ሚካኤል ኩክ የለሽ ዛሪያ ቅዱስ ሚካኤል ጅሩ ሞቶሎኒ ቅዱስ ሚካኤል (ጅሩ አርሴማ ውስጥ) 25. መንዝ ይገም ቅዱስ ሚካኤል መሐል ሜዳ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል የሲጠር ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል (መንዝ ቀያ ገብርኤል ወረዳ) ወንጪት ቅዱስ ሚካኤል (በነብር የሚጠበቅ) ሸዋሮቢት ጫሬ ቅዱስ ሚካኤል 30. ወልዲያ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ኮምቦልቻ ቅዱስ ሚካኤል ደሴ ጢጣ ደብረ ሲና ቅዱስ ሚካኤል ራያ ቆቦ ቅዱስ ሚካኤል ደብረ ማርቆስ ዋሻው ቅዱስ ሚካኤል 35. ደብረ ማርቆስ አጠገብ ብዕርና ቅዱስ ሚካኤል ደምበጫ ቅዱስ ሚካኤል መርዓዊ ደብረ ኀይል ቅዱስ ሚካኤል ባሕር ዳር ድባንቄ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል አዘዞ አይራ ቅዱስ ሚካኤል 40. ዛራ ቅዱስ ሚካኤል (ባሕር ዳር አጠገብ ሐሙሲት) ጉመር ደብረ ኅሩያን ቅዱስ ሚካኤል ካምባ ቅዱስ ሚካኤል ሳንቃ ወይራ ቅዱስ ሚካኤል ዳስ ዓምባ ቅዱስ ሚካኤል ላሐ ቅዱስ ሚካኤል ጊራራ ቅዱስ ሚካኤል መለኮዛ ቅዱስ ሚካኤል ዋይሎ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ጣፎ ጪኤሚሰ ሚካኤል (ለገጣፎ) 50. ለኩ ከታ ደብረሳህል ቅዱስሚካኤል ካቴድራል አጣራ ሚካኤል ሐረር ሚካኤል ገፈርሳ ሚካኤል ጂማ ደብረ ሣህል ሚካኤል 55. የዶፋ ሚካኤል ሽንኮራ የሚገኘው አዋሮ ሚካኤል (አምቦ ከተማ) ሐርቡ ሰንጣ ቅዱስ ሚካኤል (ወለጋ፥ ሆሮ ጉዱሩ፥ አበ ደንጎሮ ወረዳ፤ #ቀዳሽም_አስቀዳሽም_የለሌው ቀብር ስኖር ብቻ የሚከፈት) ደብረ ገሊላ ሚካኤል (ዱከም) 60. ደደሩ ሚካኤል ቶጫ ሚካኤል (በዳውሮ) ገንዶ ሚካኤል (በዳውሮ) ባሌ ሚካኤል (በዳውሮ) ተፒ ሚካኤል(ተፒ) 65. አረካ ሚካኤል (ወላይታ) ዘንዘልማ ቅዱስ ሚካኤል (ባሕር ዳር አጠገብ) ቦዲቲ መካነ ትጉሃን ቅዱስ ሚካኤል እኩቲ ሚካኤል (ካፋ ዞን፥ ዴቻ ወረዳ) ወልቂጤ ቅዱስሚካኤል 70. ሁልባራቅ ቅዱስ ሚካኤል (ስልጤ ዞን) ጋራው ሚካኤል (ባሌ ጎባ) ወልመራ ደብረ መዊዕ ሚካኤል ቦንጋ ሚካኤል ኩጢ ሚካኤል 75. ኩቲ ሚካኤል (ከቦንጋ ከተማ አጠገብ) የካ ሚካኤል ሸኮ ሚካኤል (ቤንች፥ ሸኮ ዞን፥ ሸኮ ወረዳ) ጭሪይ ሚካኤል (ክፍል) ፀጉር ሚካአኤል (የዲቲዉ) 80. ኬላ ሚካኤል (ደቡብ ሶዶ ፥ ክስታኔ) ደሉ /ሻመን /ሚካኤል ዬህታ ሚካኤል ሸሬብ ሚካኤል ጉስ ሚካኤል 85. ዝፍት ሚካኤል (አሪ ዞን፥ ሴሜን አሪ ወረዳ) ጣጤሳ ሚካኤል ጡጤ ሚካኤል ጡሪ ሚካኤል ወቀራ ሚካኤል 90. ዛዳ ሚካኤል ኮዶ ሚካኤል ኤዞ ሚካኤል ቦሮዳ ሚካኤል ሊሻና ሚካኤል 95. ዶቃማ አ/ም ሚካኤል (ጋሞ ሀገረ ስብከት) ሻለኛ ሚካኤል (ሰሜን ሸዋ፥ ዥማ ዳር) ቃንቆ ሚካኤል። ባሺ ቅዱስ ሚካኤል (ካፋ /ቦንጋ፥ ጨታ ወረዳ) ጆሌ ሚካኤል 100. አባዜቦ ሚካኤል (መቄት) ደምበኣታ ሚካኤል ጨሞ ሚካኤል የጫ ሚካኤል አገዮ ሚካኤል 105. የባርዛው ሚካኤል የሳዝጋው ሚካኤል የላሃው ሚካኤል ድባና ሚካኤል አበርጉት ሚካኤል 110. ንፋሦ ሚካኤል ጠሎ ዋሻ ሚካኤል ዳዩ ሚካኤል የቦርገላው ሚካኤል አዋሽ አርባ ቅዱስ ሚካኤል (አፋር) 115. ጋራ ጎዶ ደብረ ምሕረት ሚካኤል ሞጆ ሚካኤል አዳማ (ናዝሬት) ሚካኤል መቂ ሚካኤል ቦኩ ሚካኤል 120. ቆቃ ሚካኤል ኩርፋ ሚካኤል ተጉለ ሚካኤል ዓይንማይ ሚካኤል አርባምንጭ ሚካኤል 125. ኦለንጭቲ ደ/መ ሚካኤል ሲጋዲ ሚካኤል (ቻግኒ) ፓዌ መንደር አራት ሚካኤል ፓዌ መንደር ሁለት ሚካኤል ለምለም ሚካኤል (#ኩተሬ_አንድ_የኦርቶዶክስ_እምነት_ተከታይ_ያለበት) 130. ቱርሚ ሚካኤል ቡርካመሩ ሚካኤል ላሃ ሚካኤል ሳላይሽ ሚካኤል ስሲማ ሚካኤል 135. ኮይሻ ሚካኤል ቦርገላ ሚካኤል በርዛ ሚካኤል ሳዝጋ ሚካኤል 139. ዶፋ ሚካኤል (ምንጃር) ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #ከኢትዮጵያ_ውጭ_የሚከብርባቸው_ #፪ #ጥንታውያን_ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. ላስ ቬጋስ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ወቅዱስ ዑራኤል ወቅድስት ማርያም ቤ/ን፤ አድራሻ፤ ዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው ሀገረ ስብከት፥ አሜሪካ፥ ላስቬጋስ (USA, 2575 Westwind Rd. Las Vegas, NV 89146)፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቦሌ አየር ማረፊያ → አሜሪካ ላስ ቬጋስ፡፡ ፪. ላስ ቬጋስ ሐመረ ኖኅ ኪዳነ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል እና አቡነ ተክለሃይማኖት ቤ/ክ፤ (USA, 2575 Westwind Rd. Las Vegas, NV 89146) አድራሻ፤ ዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው ሀገረ ስብከት፥ አሜሪካ፥ ላስቬጋስ (USA, 5985 S Lindell Rd, Las Vegas, NV 89118)፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቦሌ አየር ማረፊያ → አሜሪካ ላስ ቬጋስ፡፡ ፫. ጀርመን ዳርምሽታት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ጀርመን ሀገረ ስብከት፥ ዳርምሽታት፤ ትራንስፖርት፤ ከአ.አ. ቦሌ አየር ማረፊያ → ጀርመን፡፡ (ሌሎች ያልጠቀስናቸው ገዳማት ካሉ አሳውቁን) ምንጭ #ዋልድባዋሊ ገጽ
1 203
18
፴፩. ደብረ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስና መካነ ጎልጎታ ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አረዳ ክፍለ ከተማ፥ ሰባራ ባቡር፥ ራስ ደስታ ዳምጠው ሆስፒታል አጠገብ (አርበኞች መንገድ)፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ → በዊንጌት አስኮ /ሩፋኤል ፊንሐስ/ ታክሲ → ዮሐንስ፡፡ ፴፪. ኮልፌ ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ዊንጌት፥ ጠሮ፥ አራት መንታ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ → ዊንጌት → ጠሮ፡፡ ፴፫. ሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ ገዳም፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ልኳንዳ፥ ፈጥኖ ደራሽ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መርካቶ → ኮልፌ አጣና ተራ → ልኳንዳ → (በስተግራ ባለው አስፓልት በእግር 5 ደቂቃ ፈጥኖ ደራሽ ማሰልጠኛ)፡፡ ፴፬. ቃሌ ተራራ ደብረ መድኀኒት አቡነ ሀብተ ማርያም ወቅድስት ልደታ ወቅድስት አርሴማ ገዳም፤ አድራሻው፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ አስኮ፥ ካኦ ጄጄ ዱቄት ፋብሪካ፥ ቃሌ ተራራ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መርካቶ) → አስኮ፤ ፴፭. ማኅደረ መለኮት ወይብላ ቅድስት ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ የሺ ደበሌ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → መርካቶ → የሺ ደበሌ፡፡ ፴፮. ቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ገርጂ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ገርጂ፡፡ ፴፯. ኮተቤ ደብረ ልዳ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቅድስት ኪዳነ ምሕረትና አቡነ ሀብተ ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ኮተቤ፥ ካራ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ኮተቤ (ካራ) ፴፰. ረጲ መካነ ጎልጎታ መድኃኔ ዓለም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ካራ ቆሬ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ አራዳ → አለም ባንክ → ካራቆሬ (ረጲ)፡፡ ፴፱. ፉሪ ደብረ ኀይል ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ጋራ ኦዳ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ጋራ ኦዳ፡፡ ፵. ሐመረ ወርቅ ማርያምና አርሴማ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ወርቁ ሰፈር፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ቃሊቲ → ወርቁ ሰፈር፡፡ ፵፩. ቶታል ደብረ ገነት ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ሰፈረ ገነት፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መርካቶ) → ሰፈረ ገነት፡፡ ፵፪. ቦሌ ቡልቡላ ምስካበ ቅዱሳን አባ ሳሙኤል ዘዋልድባና ቅዱስ አማኑኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ቡልቡላ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ሳሪስ አቦ → ቡልቡላ መድኀኔ ዓለም (ኮንዶሚኒየም)→ ወደ ላይ በአስፓልቱ የ5 ደቂቃ የእግር መንግድ፡፡ ወይም፤ ከቦሌ መድኃኔ ዓለም → ቡልቡላ (በአዲሱ መንገድ) ፵፫. ደብረ ዐባይ ቅድስት አርሴማ ወቅዱስ ሚካኤል ወመርቆሬዎስ ወአቡነ ሀብተ ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ አለም ባንክ፥ ግራር፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ጦር ኄሎች → አለም ባንክ → ግራር፡፡ ፵፬. አቃቂ መንበረ ሕይወት መድኀኔ ዓለም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ አቃቂ፥ ጋራው መድኃኔዓለም፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ቃሊቲ → አቃቂ፡፡ ፵፭. ሣሎ ደብረ ፀሐይ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሣሎ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(መገናኛ) → ቃሊቲ → ሣሎ፡፡ ፵፮. ቤተል) ደብረ ይድራስ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ቤተል፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ ሸዋ ዳቦ ቤት (ጦር ኀይሎች) → ቤቴል፡ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #በኢትዮጵያና_በዓለም_አቀፍ_ደረጃ_የሚከበርባቸው_ጥንታውያን #፳ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ ፩. #እየላ_ቅዱስ_ሚካኤል፤ (#የ3 #ሺህ_ዓመታት_ባለታሪክ፤ ከታቦተ ጽዮን ጋራ በ980 ከክ.ል.በ. ታቦቱ የመጣ፤ መሥዋዕተ ኦሪት ይቀርብበት የነበረ፤ አቡነ ሰላማ ከሣቴ ብርሃን መጥቶ የባረከው) ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ላሊበላ → ግዳን (እየላ)፡፡ ፪. ሰሜን ትግራይ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል፤ (መሥዋዕተ ኦሪት ይቀርብበት የነበረ) አድራሻው፤ ሰሜን ትግራይ ሀገረ ስብከት፥ ሰሜን ትግራይ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎሃ ጽዮን ወይም ደብረ ማርቆስ በሚለው መኪና ዐባይ በረሃ ላይ መውረድ፤ ፫. ዘጌ ወንጀጣ ቅድስ ሚካኤል፤(መሥዋዕተ ኦሪት ይቀርብበት የነበረ) አድራሻው፤ ባሕር ዳር ሀገረ ስብከት፥ ዘጌ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ባሕርዳር → ዘጌ (20 ኪ.ሜ) ፬. ጎሐ ጽዮን ቅዱስ ሚካኤል፤ (በ4ኛው ክፍለ ዘመን በአብርሃ ወአጽብሃ ዘመን የተሠራ) አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሰላሌ ፍቼ ሀገረ ስብከት፥ ጎሐ ጽዮን፥ ዐባይ በረሃ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎሃ ጽዮን ወይም ደብረ ማርቆስ በሚለው መኪና ዐባይ በረሃ ላይ መውረድ፤ ፭. ሸኖ ጎልባ ደብረ ሣሕል ቅዱስ ሚካኤል ደብር፤ (በአብርሃ ወአጽብሃ ዘመን የተመሠረተ) አድራሻ፤ ሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት፥ ሰኖ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ሸኖ፡፡ ፮. መላሃይዘንጊ ቅዱስ ሚካኤል፤ (በ8ኛው ክፍለ ዘመን የታነጸ) አድራሻው፤ ሰሜን ሸዋ ሰላሌ ፍቼ ሀገረ ስብከት፥ ጎሐ ጽዮን፥ ዐባይ በረሃ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎሃ ጽዮን ወይም ደብረ ማርቆስ በሚለው መኪና ዐባይ በረሃ ላይ መውረድ፤ ፯. ላስታ ላሊበላ ቤተ ሚካኤል፤ (በ11ኛው ክፍለ ዘመን በቅዱስ ላሊበላ የታነፀ፥ ከ11ዱ የላስታ ላሊበላ ፍልፍል ሕንጻዎች አንዱ) አድራሻው፤ ላስታ ሀገረ ስብከት፥ ላሊበላ ከተማ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ላሊበላ፡፡ ፰. ገርዓልታ ዋሻ ቅዱስ ሚካኤል፤ አድራሻው፤ ትግራይ ሀገረ ስብከት፥ ገርዓልታ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → መቀለ → ገርዓልታ፡፡ ፱. ሚካኤል ዓምባ፤ (በ11ኛው ክፍለ ዘመን የታነጸ) አድራሻው፤ ትግራይ ሀገረ ስብከት፥ ውቅሮ፥ (በመቀለና በአዲግራት መሃል)፥ አጽቢ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ውቅሮ → አጽቢ፤ ፲. ባሕር ዳር ሽንብጥ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ (በ13ኛው ክፍለ ዘመን የተመሠረተ) አድራሻ፤ ምዕራብ ጎጃም ባሕር ዳር ሀገረ ስብከት፥ ባሕር ዳር ከተማ፥ ቀበሌ 13 ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ባሕር ዳር ከተማ → ሆስፒታል በሚል ታክሲ (ዲፖ ጋር)፡፡ ፲፩. እስቴ አበርጉት ቅዱስ ሚካኤል ፤ (በአፄ ዓምደ ጽዮን ዘመነ መንግስት በልጃቸው በአቡነ ፊልሞና የተሠራ ታሪካዊ ጠበል ያለበት) አድራሻ፤ ደቡብ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ እስቴ ወረዳ፥ ደስኳ አጋማች ቀበሌ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → እስቴ፡፡ ፲፪. በሮ ደብረ ሰላም ቅዱስ ሚካኤል፤ በ16ኛው መ/ክ/ዘመን መጨረሻ የተመሠረተ አድራሻ፤ ደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት፥ ሳይንት ወረዳ ታክሲ፤ ከአ.አ. ጉርድ ሾላ አውቶቡስ ተራ → ደሴ → አማራ ሳይንት፡፡ ወይም፤ ከጎጃም በመርጠሉ ማርያም → አማራ ሳይንት ፲፫. ጎንደር ፊት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ በአፄ ፋሲለደስ ዘመነ መንግሥት ተመሠረተ፤ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር፡፡ ፲፬. ጎንደር አጣጣሚ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ማዕከላዊ ጎንደር ሃገረ ስብከት፥ ጎንደር ከተማ፤ ታክሲ፤ ከአ.አ. መርካቶ አውቶቡስ ተራ → ጎንደር፡፡
1 290
19
የሰኔ 12 የቅዱስ ሚካኤል ክብረ በዓል (በአ.አ፣ በሀገራችን በኢትዮጵያ እና በዓለም አቀፍ ባሉ) ከሚከበርባቸው በርካታ ገዳማትና አድባራት 208ቱን እንጠቁምዎ፡፡ (ምንጭ ፤ ዋሊ ገጽ) ሰኔ ፲፪ የቅዱስ ሚካኤል እና የቅዱስ ላሊበላን በዓል በየት ሊያከብሩ ዐስበዋል? #ቅዱስ_ሚካኤል_አፎምያንና_ባሕራንን_ያዳነበት_እለእስክንድሮስ_ቅዳሴ_ቤቱን_ያከበረበትና_የቅዱስ_ላሊበላ_ዕረፍቱ_ነው፡፡ #በመላው_ዓለም_ክብረ_በዓሉ_የሚከበርባቸው_ #፪፻፰ #ገዳማትና_አድባራት፡፡ (ሌሎች ያልጠቀስናቸው ገዳማት ካሉ አሳውቁን) ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #በአዲስ_አበባ_የሚከብርባቸው_ #፵፮ #ገዳማትና_አድባራት፡፡፡ ፩. የካ ደብረ ሣህል ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (በኦሪት ዘመን መሥዋዕተ ኦሪት ይሰዋበት የነበረ፥ ዋሻ ቤተ ክርስቲያኑ በ4ኛው ክ/ዘመን በአብሃ ወአጽብሃ ዘመን የተመሠረተ) (የቅዱስ ላሊበላም በዓለ ዕረፍት በማኅሌት በወረብ ጨምር ሳይቀር የሚከበርበት ነው) አድራሻው፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ሾላ መገናኛ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(4 ኪሎ) → ሾላ መገናኛ፤ ፪. አንቀጸ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (ራስ ካሳ ሚካኤል) (ጭቁኑ) /የቅዱስ ላሊበላ ታቦትም አብሮ ይከብራል/፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ራስ ካሳ ታክሲ፤ ከ4ኪሎ(ከ6 ኪሎ) → ፈረንሳይ፡፡ ፫. ደብረ መዊዕ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (አዲሱ ሚካኤል) አድራሻ፤ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ፥ መርካቶ አውቶቡስ ተራ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(4ኪሎ) → መርካቶ አውቶቡስ ተራ፡፡ ፬. አፍሪካ ኅብረት ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ (ወህኒ ቤት) (ከርቸሌ) አድራሻ፤ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ፥ ቡልጋርያ (ከርቸሌ) (አፍሪካ ኅብረት)፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ቄራ፡፡ ፭. ኮተቤ (ሲኤምሲ) (አልታድ) ደብረ ጽባሕ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ /ሳጠራው/ (ቀድሞ ኮተቤ አሁን ሲኤምሲ) አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ካራ አሎ ፥ አባዶ አጠገብ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ሲኤምሲ፡፡ ፮. መካኒሳ ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ መካኒሳ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → መካኒሳ፡፡ ፯. ላፍቶ ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ላፍቶ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ላፍቶ፡፡ ፰. ቤተል ደብረ ኢዮር ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ፥ ቤተል፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ጦር ኃሎች → አየር ጤና፡፡ ወይም፤ ከፒያሳ ሸዋ ዳቦ ቤት → አለም ባንክ/ኤር ጤና/፡፡ ፱. ኤረር በር መካነ ሰላም ቅዱስ ሚካኤልና ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ጎሮ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ (ፒያሳ) → ጎሮ፡፡ ፲. መንበረ ክብር ቅዱስ ሚካኤል ወአቡነ ተክለ ሃይማኖትና ቅድስት አርሴማ ገዳም፤ (የራስ መኰንን ደን /ጋራው /ጫካው/ /ጽድ/ ሚካኤል/) አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ ቀጨኔ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ(ከመርካቶ)(ከአዲሱ ገበያ) → ቀጨኔ፡፡ ፲፩. አያት ጨፌ ኢያሪኮ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ (በ1980ዓ.ም ጽላቱ ከነ ድርሳናቱ ተቀብሮ የተገኘበት) አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ወረዳ 9፥ ጎሮ ሰፈር፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ጎሮ፡፡ ፲፪. ካራ ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ሚካኤል፥ 24ቱ ካህናተ ሰማይና ማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አባዶ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → አባዶ ፲፫. ቦሌ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ቦሌ ሚካኤል፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ቦሌ ሚካኤል፡፡ ፲፬. የካ አባዶ ገ/አ/ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ አባዶ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → አባዶ ፲፭. ምሥራቀ ፀሐይ ዳንሴ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ወረዳ 10 ከጉራራ ከፍ ብሎ፤ ታክሲ፤ ከጊዮርጊስ (4 ኪሎ) (6 ኪሎ) → ፈረንሳይ → ጉራራ፡፡ ፲፮. ወረገኑ ቅዱስ ሚካኤልና አቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ሩዋንዳ አጠገብ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ (ቦሌ) → ወረገኑ፡፡ ፲፯. ቃሊቲ ሰፈረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሰፈረ ገነት፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ቃሊቲ → ሰፈረ ገነት፡፡ ፲፰. ንቡ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ሃራብሳ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ቱሉ ዲምቱ → ንቡ ሚካኤል፡፡ ፲፱. ጀሞ (መካኒሳ) ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ጀሞ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (ሜክሲኮ) → ጀሞ፡፡ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ ꔰ #እንዲሁም_በአዲስ_አበባ_በአንድነት_ተሠሩ_በሚከተሉት_አብያተ_ክርስቲያናት_ይከበራል፤ ፳. ጽርሐ ጽዮን ሐዋርያትና ጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ልደታ ክፍለ ከተማ፥ ጎላ (ኢምግሬሽን ጀርባ)፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል (ኢምግሬሽን)፡፡ ፳፩. ደብረ ናዝሬት ቅዱስ ዮሴፍና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ዮሴፍ፥ ደጃዝማች መርዕድ መንገድ፥ ቀለበት መንገድ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ከላጋር (ከፒያሣ) (ከ4 ኪሎ) (ከቦሌ)(ከመገናኛ) → ቃሊቲ መናኸሪያ /በቀለበት መንገድ/ ወይም፤ ከሳሪስ አቦ → ቦሌ /በቀለበት መንገድ/ ፳፪. ጀሞ ምዕራፈ ቅዱሳን አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ነፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ፥ ጀሞ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (ሜክሲኮ) → ጀሞ፡፡ ፳፫. ቃሊቲ ደብረ ቊስቋም ማርያምና ደብረ ገነት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ሰፈረ ገነት፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ (መገናኛ) → ቃሊቲ → ሰፈረ ገነት፡፡ ፳፬. ኮተቤ ማኅደረ ቅዱሳን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ የካ ክፍለ ከተማ፥ ሎቄ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ሎቄ፡፡ ፳፭. ፉሪ መካነ ቅዱሳን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ እና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ፥ ለቡ፥ ፉሪ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ለቡ፡፡ ፳፮. ቂሊንጦ መካነ ፍስሐ ቅዱስ ሚካኤልና በዓታ ለማርያም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ ቂሊንጦ ኮዬ ዐደባባይ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ቱሉዲምቱ፡፡ ወይም፤ ከፒያሳ → ቃሊቲ → ቂሊንጦ፡፡ ፳፯. ቱሉ ዲምቱ ደብረ ሰላም ቅዱስ ጊዮርጊስና ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ፥ አቃቂ ኬላ አጠገብ፤ ታክሲ፤ ከመገናኛ → ቱሉዲምቱ፡፡ ወይም፤ ከፒያሳ → ቃሊቲ → ቱሉዲምቱ፡፡ / ©#ገዳማትና_አድባራት #Monasteries_and_Churches / #እንዲሁም_በድርብነት_በሚከተሉት_አብያተ_ክርስቲያናት_ይከበራል፤ ፳፰. መንበረ ልዑል ቅዱስ ማርቆስ ወቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ጉለሌ ክፍለ ከተማ፥ 6 ኪሎ ዐደባባይ፤ ታክሲ፤ ከጊዮርጊስ → 6 ኪሎ (ማርቆስ)፡፡ ፳፱. ደብረ ሰላም ቅዱስ እስጢፋኖስ ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ቦሌ ክፍለ ከተማ፥ ገርጂ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ቦሌ በሚል ታክሲ → መስቀል ዐደባባይ፡፡ ፴. ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያምና ደብረ መድኃኒት መድኀኔ ዓለም ቤ/ክ፤ አድራሻ፤ ልደታ ክፍለ ከተማ፥ ልደታ፤ ታክሲ፤ ከፒያሳ → ሜክሲኮ → ጦር ኃይሎች በሚለው ታክሲ → ልደታ፡፡
1 993
20
Sin texto...
2 718