uz
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Kanalga Telegram’da o‘tish

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት analitikasi

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 413 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 5 577-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 192-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 413 obunachiga ega bo‘ldi.

13 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 71 ga, so‘nggi 24 soatda esa -3 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 25.53% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 9.38% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 933 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 446 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 23 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 14 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 413
Obunachilar
-324 soatlar
+357 kunlar
+7130 kunlar
Postlar arxiv
ሥርዐተ ማኅሌት ዘወርኀ ጽጌ (‹ዘላይ ወዘታች› ቤት)፤ ፬ኛ ሳምንት፥ዘጥቅምት ፲፰፤

‹‹ ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡›› ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት በወርኃ ነሐሴ ፳/፳፻፲፣በመስከረም ፲፪ና ፲፫/፳፻፲ ዓ.ም. ጋብቻችሁን ለፈጸማችሁ የደብራችን አገልጋይና የሰ/ት/ቤታችን አባላት * ሙላት ተሾመ * ዲ.ን ዐሥራት ለይኩን * ይትባረክ ሙላቱ ከደመቀች ሽፈራው * መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ የፈጸማችሁትን ጋብቻ፤ የይስሐቅንና የርብቃን ጋብቻ የባረከ አምላክ፤ የትዳር ሕይወታችሁን ይባርክላችሁ፤ እመብርሃን በአማላጅነቷ አትለያችሁ፤ ቅ/ገብርኤል ከፊት ይምራችሁ ከኋላ ይከተላችሁ፡፡ ✤ ‹‹ጌታን እንዲወዱና በአካልም ይሁን በመንፈስ በባሎቻቸው ደስ እንዲሰኙ ለእህቶች ንገራቸው፡፡ ልክ እንደዚሁ ጌታ ቤተ ክርስቲያንን እንደወደደ ሚስቶቻቸውን እንዲወዱ ለወንድሞች በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ንገራቸው፡፡›› ቅዱስ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ ለፖሊካርፐስ በላከው መልእክቱ ✤ ከተጋባችሁ በኋላ ባልና ሚስት አንድ አካል ናችሁ እንጂ ሁለት ስላይደላችሁ በፍጹም ልባችሁ እርስ በእርሳችሁ ተፋቀሩ፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ሌላ ወንድ ወይም ሌላ ሴት አትፈልጉ ይልቁንም በተቻላችሁ መጠን አንዳችሁ ሌላውን ደስ አሰኙ፤ በመረዳዳትና በፍጹም ፍቅር ኑሯችሁን ሁሉ አሳምሩ፡፡>> ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ ዘርአያዕቆብ፡፡

በወርኀ ነሐሴና መስከረም የተመረቃችሁ እንኳን ደስ አላችሁ፡፡ 1ኛ. ኪሩቤል ቴዎድሮስ፤ በኮምፒውተር ሳይንስ ዲግሪ፤ ከአኵሱም ዩኒቨርሲቲ 2ኛ. ኪሩቤል ጀቤሳ፤ በኮሙኒኬሽን ኢንጂነሪንግ ዲግሪ፤ ከአ.አ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት 3ኛ. ፈለቀች አሰፋ፤ በአካውንቲንግ ዲግሪ፤ ከአድማስ ዩኒቨርሲቲ 4ኛ. አልማዝ በቀለ፤ በሚድዋይፈሪ ዲግሪ፤ ከዳግማዊ ምኒልክ የጤና ሳይንስ ኰሌጅ 5ኛ. አክሊሉ ደስዬ፤ በማኔጅመንት ዲግሪ (በከፍተኛ ማዕረግ በሜዳልያ ተሸላሚነት)፤ ከጌጅ ኰሌጅ 6ኛ. ራሔል ተሾመ፤ በአካውንቲንግ በዲግሪ፤ 7ኛና 8ኛ) የሺሃረግና ሙሴና አስካለ ሙሴ፤ በቡዝነስ አድሚንስትሬሽን በማስተርስ፤ ከሲፒዩ ኰሌጅ /ፎቶዎቹ ተሰባስበው እጃችን እስኪገቡ በዘግየቱ ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡/

✤ ብዙዎቻችን ከማናውቃቸው ነገሮች መካከል(የአቡነ አረጋዊ በሶ እምነት)፤ ና የጥቅምት 14 ክብረ በዓልን በወፍ በረር፤ ፨ የአቡነ አረጋዊ በሶ እምነት፤ በዓመት አንድ ጊዜ ጥቅምት 14 በደብራችን በሚበሩት በቅዱስ ገብረ ክርስቶስ አቡነ አረጋዊና ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር ክብረ በዓል ላይ በሶ ይሰጣል ይኸውም የበሶ እምነት ብዙዎችን ፈውሷል፤ በሶ የአቡነ አረጋዊ እምነት የኾነበት ምክንያጥ በታላቁ ገዳም በደብረ ዳሞ የመናንያኑ ምግብና ወደዚሁ ቦታ ለሚሄዱ ምዕመናን እንደ እምነት ተደርጎ የሚሰጥ በመኾኑ ነው፡፡ በነገራችን ላይ ደብራችን መጀመሪያ ሲመሠረት ይቀድሱና ያወድሱ የነበሩት የደብረ ዳሞ ገዳም መነኰሳት ናቸው፡፡ ዘንድሮ የበሶ እምነት ያመለጣችሁ ለከርሞ ያድርሰን፡፡ ✤ የጥቅምት 14 ክብረ በዓልን በወፍ በረር ስንቃኘውዋይዜማው ማኅሌቱ ሰዐታቱና ኪዳኑ ከተከናወነ በኋላ፤ ታቦቱ ወጥቶ በዐውደ ምሕረት በቆመበት ሰዐት፤ ✣ የደብራችን ሊቃውንት፤ የደብሩን ቀለም የኾነውንና ልብን የሚመስጠውን (ብፁዓን አበዊነ አረጋዊ ሙሴ ወገብረ ክርስቶስ፤ ዘበምድር መነኑ ዘበሰማያት ዴገኑ ዘበሰማያት) የሚለውን ሲወረቡ ✣ የደብራችን የሕፃናት ክፍል የሰ/ት/ቤት አባላት ደግሞ ‹‹ዘእምደብረ ደናግል አባ ኤልያስ፤ ወትሩፈ ምግባር አረጋዊ ዘውገ ሙሴ ወገብረ ክርስቶስ›› የሚለውን ወረበዋል፡፡ ✣ የተሰጠው ትምህርት፤ ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፡፡ ማቴ. 5፤ በመጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ፡፡ (የቅዱሳንን ታሪክ እንዲሁም ቅዱሳኑን አሁን ካለንበት ኹኔታ አንጻር እያመሳጠሩ /የቀድሞዎቹ ቅዱሳን ከሌላ ሃገራት ወደ ኢትዮጵያ ለጽድቅ ተሰደው ሲመጡ እኛ ደግሞ ዛሬ ለሥጋችን እንሰደዳለን፤ ቅዱሳን ዘር ብሔር (ቦታ ሀገር) ሳይለቻው ክርስቲያንን ወደዋል አስተምረዋል እኛ ደግሞ ሁሉ ነገራችን በዘርና በብሔር ላይ ኹኗል፤ ታዲያ ቅዱሳኑ እንዴት አያዝኑብን፤ ……… በማለት አስተምረውናል፡፡ ✤ በማታ የሰርክ ጕባኤ (የረቡዕ ልዩ የሠርክ ጕባኤ) ላይ ትምህርተ ወንጌል በመምህር ጳውሎስ መልክአ ሥላሴ ‹‹›› አሁን ካለንበት የዘመናችን በተለይም የሃገራችን ኹኔታ ጋር እያገናዘቡና እያመሳጠሩ አስተምረዋል፤ ዝማሬም በዘማሩ ቡሩክና በሲስተር ሄለን ቀርቧል፡፡ /በነገራችን ላይ የማታ የሰርክ ጕባኤ ላይ የሰዐትና መርሐ ግብር ማስተካከያ ቢደረግ ብላችሁ የሰጣችሁትን አስተያየት ግምት በማስገባት የማስተካከል ሥራ እየተሠራ ነው፤ በዚህም ምክንያ ጕባኤው 2፡05 ላይ ተጠናቋል፡፡)

የሰ/ት/ቤታችን የሕፃናት ክፍል አባላት ለጥቀምት 14 ለበዓሉ ተስማሚ የኾነውን ወረብ እያቀረቡ፡፡
የሰ/ት/ቤታችን የሕፃናት ክፍል አባላት ለጥቀምት 14 ለበዓሉ ተስማሚ የኾነውን ወረብ እያቀረቡ፡፡

ጥቅምት 14፤ ✤ ቅዱስ ገብረክርሰቶስ በዓለ እረፍቱ፤ ✤ በጋዛ ምድር ኢትዮጵያዊውን ጃንረባ ባኮስን ያጠመቀው ረድኡ ሐዋርያ ቅዱስ ፊሊጶስ ዕረፍቱ ነው፡፡ ✤ አቡነ አረጋዊ ወደ ደብረ ዳሞ በዘንዶ የወጡበት፤ ✤ ቅዱስ ሙሴ እግዚአብሔር በዓለ ዕረፍታቸው ነው፡፡ ✤✤ ጥቅምት 14 በአ.አ. ክብረ በዓል የሚከበርባቸውን አብያተ ክርስቲያናት እንጠቁማችሁ፡፡ ✤ በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም ቤተክርስቲያን (የቅዱስ ገብረ ክርስቶስ አቡነ አረጋዊና ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር ታቦት በድርብነት ከጥንት ጀምሮ ይከብራል) ✤ ለእኛ ለኢትዮጵያውያን ባለውለታችን የኾነውና ለመጀመሪያ ጊዜ በሐዲስ ኪዳን የእግዚአብሔርን ቃል የተናገረን፤ የክርስትና ጥቀምት አባትና አጥማቂያችን ከ72ቱ አርድዕት አንዱ የኾነው ቅዱስ (ሐዋርያው) ፊልጶስ በሀገራችንን ውስጥ ብቸኛ በኾነውና በአ.አ ኮልፌ አጠና ተራ በሚገኘው ቤ.ክ. ደብረ ምጥማቅ ቤ.ክ በዓለ ዕረፍቱ ይከበራል፡፡ ✤ በደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤ.ክ /ዘነበ ወርቅ/ ✤ በመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን (የአቡነ አረጋዊ ታቦት በድርብነት ይገኛል) ✤ በሽሮ ሜዳ መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን (የአቡነ አረጋዊ ታቦት በድርብነት ይገኛል) ✤ በደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤ.ክ. (የአቡነ አረጋዊ ታቦት በድርብነት ይገኛል)

ዘጥቅምት ፲፩፤ ሥርዐተ ማኅሌት ዘወርኀ ጽጌ (‹ዘላይ ወዘታች› ቤት) (፯ኛ ዙር ዓመት፤ ፫ኛ ሳምንት፥ ዘጥቅምት ፲፩) በዓለ ቅድስት ሐና ወጲላግያ ወቅዱስ ኢያቄም ወያሬድ፡፡ ✤ ልዩ አዋጅ ዘወርኃ ጽጌ ✤  የማኅሌቱ ሥርዐት የላይ ቤት (የጎንደር መካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም አብነት) እና የታች ቤት (የጎንደር ደብረ ኀይል ዑራኤል ወደብረ ጥበብ በዓታ ለማርያምን አብነት) የሚያደርግ ሲኾን፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ የማኅሌት ቁመትም የላይ ቤትን አብነት የተከተለ ሲኾን፤ የዚቁ ወረብ ግን የደብሩን የራሱን (የሸዋን) የተከተለ ነው፤  የላይ ቤት ቁመት የሚቆሙ አድባራት ዘግምጃ ቤት የሚለውን እንዲከተሉ፤ የታች ቤትን ቁመት የሚቆሙ አድባራት ዘበዓታ የሚለውን እንዲከተሉ እያሳሰብን፡፡ የዚቁ ወረብን ግን የቀጨኔ ደብረ ሰላም የቤቱን ቀለም አስቀድመን ቀጥሎ ደግሞ ዓዲ (ወይም) በማለት የጎንደርን ስላስቀመጥነው እንደ ደብራችሁ ይትበሃል መርጣችሁ እንድትጠቀሙበት ኹሉንም አስቀምጠነዋል፡፡