Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览
频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 413 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 577,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 192 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 413 名订阅者。
根据 13 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 71,过去 24 小时变化为 -3,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.53%。内容发布后 24 小时内通常能获得 9.38% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 933 次浏览,首日通常累积 1 446 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 23。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 14 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
15 413
订阅者
-324 小时
+357 天
+7130 天
帖子存档
ሥርዐተ ማኅሌት ዘወርኀ ጽጌ (‹ዘላይ ወዘታች› ቤት)፤
፬ኛ ሳምንት፥ዘጥቅምት ፲፰፤
‹‹ ሁለቱም አንድ አካል ይኾናሉ፤ ይህ ነገር ጥልቅ፤ ረቂቅ ምሥጢር ነው፤ እኔም ለክርስቶስና ለቤተ ክርስቲያን ምሳሌ አድርጌ እናገረዋለሁ፡፡›› ሃይማኖተ አበው ዘስምዓት
በወርኃ ነሐሴ ፳/፳፻፲፣በመስከረም ፲፪ና ፲፫/፳፻፲ ዓ.ም. ጋብቻችሁን ለፈጸማችሁ የደብራችን አገልጋይና የሰ/ት/ቤታችን አባላት
* ሙላት ተሾመ
* ዲ.ን ዐሥራት ለይኩን
* ይትባረክ ሙላቱ ከደመቀች ሽፈራው
* መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ የፈጸማችሁትን ጋብቻ፤
የይስሐቅንና የርብቃን ጋብቻ የባረከ አምላክ፤ የትዳር ሕይወታችሁን ይባርክላችሁ፤ እመብርሃን በአማላጅነቷ አትለያችሁ፤ ቅ/ገብርኤል ከፊት ይምራችሁ ከኋላ ይከተላችሁ፡፡
✤ ‹‹ጌታን እንዲወዱና በአካልም ይሁን በመንፈስ በባሎቻቸው ደስ እንዲሰኙ ለእህቶች ንገራቸው፡፡ ልክ እንደዚሁ ጌታ ቤተ ክርስቲያንን እንደወደደ ሚስቶቻቸውን እንዲወዱ ለወንድሞች በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም ንገራቸው፡፡›› ቅዱስ አግናጥዮስ ምጥው ለአንበሳ ለፖሊካርፐስ በላከው መልእክቱ
✤ ከተጋባችሁ በኋላ ባልና ሚስት አንድ አካል ናችሁ እንጂ ሁለት ስላይደላችሁ በፍጹም ልባችሁ እርስ በእርሳችሁ ተፋቀሩ፡፡ ከዛሬ ጀምሮ ሌላ ወንድ ወይም ሌላ ሴት አትፈልጉ ይልቁንም በተቻላችሁ መጠን አንዳችሁ ሌላውን ደስ አሰኙ፤ በመረዳዳትና በፍጹም ፍቅር ኑሯችሁን ሁሉ አሳምሩ፡፡>> ኢትዮጵያዊው ፈላስፋ ዘርአያዕቆብ፡፡
በወርኀ ነሐሴና መስከረም የተመረቃችሁ እንኳን ደስ አላችሁ፡፡
1ኛ. ኪሩቤል ቴዎድሮስ፤ በኮምፒውተር ሳይንስ ዲግሪ፤ ከአኵሱም ዩኒቨርሲቲ
2ኛ. ኪሩቤል ጀቤሳ፤ በኮሙኒኬሽን ኢንጂነሪንግ ዲግሪ፤ ከአ.አ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት
3ኛ. ፈለቀች አሰፋ፤ በአካውንቲንግ ዲግሪ፤ ከአድማስ ዩኒቨርሲቲ
4ኛ. አልማዝ በቀለ፤ በሚድዋይፈሪ ዲግሪ፤ ከዳግማዊ ምኒልክ የጤና ሳይንስ ኰሌጅ
5ኛ. አክሊሉ ደስዬ፤ በማኔጅመንት ዲግሪ (በከፍተኛ ማዕረግ በሜዳልያ ተሸላሚነት)፤ ከጌጅ ኰሌጅ
6ኛ. ራሔል ተሾመ፤ በአካውንቲንግ በዲግሪ፤
7ኛና 8ኛ) የሺሃረግና ሙሴና አስካለ ሙሴ፤ በቡዝነስ አድሚንስትሬሽን በማስተርስ፤ ከሲፒዩ ኰሌጅ
/ፎቶዎቹ ተሰባስበው እጃችን እስኪገቡ በዘግየቱ ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡/
✤ ብዙዎቻችን ከማናውቃቸው ነገሮች መካከል(የአቡነ አረጋዊ በሶ እምነት)፤ ና የጥቅምት 14 ክብረ በዓልን በወፍ በረር፤
፨ የአቡነ አረጋዊ በሶ እምነት፤
በዓመት አንድ ጊዜ ጥቅምት 14 በደብራችን በሚበሩት በቅዱስ ገብረ ክርስቶስ አቡነ አረጋዊና ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር ክብረ በዓል ላይ በሶ ይሰጣል ይኸውም የበሶ እምነት ብዙዎችን ፈውሷል፤ በሶ የአቡነ አረጋዊ እምነት የኾነበት ምክንያጥ በታላቁ ገዳም በደብረ ዳሞ የመናንያኑ ምግብና ወደዚሁ ቦታ ለሚሄዱ ምዕመናን እንደ እምነት ተደርጎ የሚሰጥ በመኾኑ ነው፡፡ በነገራችን ላይ ደብራችን መጀመሪያ ሲመሠረት ይቀድሱና ያወድሱ የነበሩት የደብረ ዳሞ ገዳም መነኰሳት ናቸው፡፡ ዘንድሮ የበሶ እምነት ያመለጣችሁ ለከርሞ ያድርሰን፡፡
✤ የጥቅምት 14 ክብረ በዓልን በወፍ በረር ስንቃኘውዋይዜማው ማኅሌቱ ሰዐታቱና ኪዳኑ ከተከናወነ በኋላ፤ ታቦቱ ወጥቶ በዐውደ ምሕረት በቆመበት ሰዐት፤
✣ የደብራችን ሊቃውንት፤ የደብሩን ቀለም የኾነውንና ልብን የሚመስጠውን (ብፁዓን አበዊነ አረጋዊ ሙሴ ወገብረ ክርስቶስ፤ ዘበምድር መነኑ ዘበሰማያት ዴገኑ ዘበሰማያት) የሚለውን ሲወረቡ
✣ የደብራችን የሕፃናት ክፍል የሰ/ት/ቤት አባላት ደግሞ ‹‹ዘእምደብረ ደናግል አባ ኤልያስ፤ ወትሩፈ ምግባር አረጋዊ ዘውገ ሙሴ ወገብረ ክርስቶስ›› የሚለውን ወረበዋል፡፡
✣ የተሰጠው ትምህርት፤ ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፡፡ ማቴ. 5፤ በመጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ፡፡ (የቅዱሳንን ታሪክ እንዲሁም ቅዱሳኑን አሁን ካለንበት ኹኔታ አንጻር እያመሳጠሩ /የቀድሞዎቹ ቅዱሳን ከሌላ ሃገራት ወደ ኢትዮጵያ ለጽድቅ ተሰደው ሲመጡ እኛ ደግሞ ዛሬ ለሥጋችን እንሰደዳለን፤ ቅዱሳን ዘር ብሔር (ቦታ ሀገር) ሳይለቻው ክርስቲያንን ወደዋል አስተምረዋል እኛ ደግሞ ሁሉ ነገራችን በዘርና በብሔር ላይ ኹኗል፤ ታዲያ ቅዱሳኑ እንዴት አያዝኑብን፤ ……… በማለት አስተምረውናል፡፡
✤ በማታ የሰርክ ጕባኤ (የረቡዕ ልዩ የሠርክ ጕባኤ) ላይ ትምህርተ ወንጌል በመምህር ጳውሎስ መልክአ ሥላሴ ‹‹›› አሁን ካለንበት የዘመናችን በተለይም የሃገራችን ኹኔታ ጋር እያገናዘቡና እያመሳጠሩ አስተምረዋል፤ ዝማሬም በዘማሩ ቡሩክና በሲስተር ሄለን ቀርቧል፡፡ /በነገራችን ላይ የማታ የሰርክ ጕባኤ ላይ የሰዐትና መርሐ ግብር ማስተካከያ ቢደረግ ብላችሁ የሰጣችሁትን አስተያየት ግምት በማስገባት የማስተካከል ሥራ እየተሠራ ነው፤ በዚህም ምክንያ ጕባኤው 2፡05 ላይ ተጠናቋል፡፡)
የሰ/ት/ቤታችን የሕፃናት ክፍል አባላት ለጥቀምት 14 ለበዓሉ ተስማሚ የኾነውን ወረብ እያቀረቡ፡፡
ጥቅምት 14፤
✤ ቅዱስ ገብረክርሰቶስ በዓለ እረፍቱ፤
✤ በጋዛ ምድር ኢትዮጵያዊውን ጃንረባ ባኮስን ያጠመቀው ረድኡ ሐዋርያ ቅዱስ ፊሊጶስ ዕረፍቱ ነው፡፡
✤ አቡነ አረጋዊ ወደ ደብረ ዳሞ በዘንዶ የወጡበት፤
✤ ቅዱስ ሙሴ እግዚአብሔር በዓለ ዕረፍታቸው ነው፡፡
✤✤ ጥቅምት 14 በአ.አ. ክብረ በዓል የሚከበርባቸውን አብያተ ክርስቲያናት እንጠቁማችሁ፡፡
✤ በቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም ቤተክርስቲያን (የቅዱስ ገብረ ክርስቶስ አቡነ አረጋዊና ሙሴ ብእሴ እግዚአብሔር ታቦት በድርብነት ከጥንት ጀምሮ ይከብራል)
✤ ለእኛ ለኢትዮጵያውያን ባለውለታችን የኾነውና ለመጀመሪያ ጊዜ በሐዲስ ኪዳን የእግዚአብሔርን ቃል የተናገረን፤ የክርስትና ጥቀምት አባትና አጥማቂያችን ከ72ቱ አርድዕት አንዱ የኾነው ቅዱስ (ሐዋርያው) ፊልጶስ በሀገራችንን ውስጥ ብቸኛ በኾነውና በአ.አ ኮልፌ አጠና ተራ በሚገኘው ቤ.ክ. ደብረ ምጥማቅ ቤ.ክ በዓለ ዕረፍቱ ይከበራል፡፡
✤ በደብረ ከዋክብት አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ገብረ ክርስቶስ ቤ.ክ /ዘነበ ወርቅ/
✤ በመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን (የአቡነ አረጋዊ ታቦት በድርብነት ይገኛል)
✤ በሽሮ ሜዳ መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን (የአቡነ አረጋዊ ታቦት በድርብነት ይገኛል)
✤ በደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤ.ክ. (የአቡነ አረጋዊ ታቦት በድርብነት ይገኛል)
ሥርዐተ ማኅሌት ዘጥቅምት ፲፬
ዘጥቅምት ፲፩፤ ሥርዐተ ማኅሌት ዘወርኀ ጽጌ (‹ዘላይ ወዘታች› ቤት)
(፯ኛ ዙር ዓመት፤ ፫ኛ ሳምንት፥ ዘጥቅምት ፲፩)
በዓለ ቅድስት ሐና ወጲላግያ ወቅዱስ ኢያቄም ወያሬድ፡፡
✤ ልዩ አዋጅ ዘወርኃ ጽጌ ✤
የማኅሌቱ ሥርዐት የላይ ቤት (የጎንደር መካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም አብነት) እና የታች ቤት (የጎንደር ደብረ ኀይል ዑራኤል ወደብረ ጥበብ በዓታ ለማርያምን አብነት) የሚያደርግ ሲኾን፤ የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ የማኅሌት ቁመትም የላይ ቤትን አብነት የተከተለ ሲኾን፤ የዚቁ ወረብ ግን የደብሩን የራሱን (የሸዋን) የተከተለ ነው፤
የላይ ቤት ቁመት የሚቆሙ አድባራት ዘግምጃ ቤት የሚለውን እንዲከተሉ፤ የታች ቤትን ቁመት የሚቆሙ አድባራት ዘበዓታ የሚለውን እንዲከተሉ እያሳሰብን፡፡ የዚቁ ወረብን ግን የቀጨኔ ደብረ ሰላም የቤቱን ቀለም አስቀድመን ቀጥሎ ደግሞ ዓዲ (ወይም) በማለት የጎንደርን ስላስቀመጥነው እንደ ደብራችሁ ይትበሃል መርጣችሁ እንድትጠቀሙበት ኹሉንም አስቀምጠነዋል፡፡
ዘጥቅምት ፲፩፤ ሥርዐተ ማኅሌት ዘወርኀ ጽጌ (‹ዘላይ ወዘታች› ቤት)
