es
Feedback
Finote Hiwot ዹቀጹኔ ደብሚ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብሚ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኀል ቀተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቀት

Finote Hiwot ዹቀጹኔ ደብሚ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብሚ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኀል ቀተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቀት

Ir al canal en Telegram

ዹቀጹኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቀት ነሐሮ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠሚተ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram Finote Hiwot ዹቀጹኔ ደብሚ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብሚ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኀል ቀተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቀት

El canal Finote Hiwot ዹቀጹኔ ደብሚ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብሚ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኀል ቀተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቀት (@finotehiwott) en el segmento lingÌístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 381 suscriptores, ocupando la posición 5 584 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 199 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el МевіЎПЌП, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 381 suscriptores.

Según los últimos datos del 03 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 21, y en las últimas 24 horas de -7, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 21.13%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 9.50% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 3 250 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 462 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 16.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“ዹቀጹኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቀት ነሐሮ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠሚተ።”

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 04 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

15 381
Suscriptores
-724 horas
+117 días
+2130 días
Archivo de publicaciones
#መፃጕዕፀ አራተኛው ሳምንት አራተኛው ሳምንት መፃጕዕ ይባላል፡፡ በመፃጕዕ ዹተሰዹመው ዚእርሱ ስህተት ለእኛ ትምህርት፥ ተግሳጜ እንዲሆነን እንጂፀ በዚህ ሳምንት ዚሚታሰበው ጌታቜን ሕሙማን መፈወሱን፣ ሙት ማስነሳቱንና ስለ ሹቂቁ ዚነፍስ ደዌ ስለ ኀጢአትና ስለ ድኅነታቜን ዚሚያዘክር ምስጋና ይቀርብበታል፡፡ ማቮ. 8፥1-37፣ ማር. 7፥13-37፣ ሉቃ. 17፥1-9፣ ዮሐ. 5፥1-18 በቀተክርስቲያን በሜተኞቜ በሊስት ስያሜ ይጠራሉ፡- ፚ #በሜተኛፀ ዚዕለት ሕመም ወይም እስኚ አንድ ዓመት ዚታመመ ሰው፡፡ ፚ #ድውይፀ እስኚ አምስት ዓመት ሕመሙ ዚቆዚበት፡፡ ፚ #መፃጕዕፀ ኚአምስት ዓመት በላይ ሕመሙ ዚጞናበትፀ ሲሆን ድውይ፥ በሕመም ዚሚማቅቅ፥ ዹዐልጋ ቊራኛ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ #መፃጕዕ ዚተባለው ስለሕመሙ #38_ዓመታት_መጜናት_እንጂ ስሙ አይደለም፡፡ በዕብራይስጥ ቀተ ሳይዳ ትርጕሙ /ዚምሕሚት ቊታ/ፀ በግእዙ ቀላዹ አባግዕ (ዚበጎቜ መዋኛ) በተባለቜ ምጥምቃት ዘጵሩጳጥቄ በምትባል ዹጠበል መጠመቂያ ኩሬ ዳር ዹውኃውን መንቀሳቀስ እዚጠበቁ በሜተኞቜ፥ እውሮቜ፥ አንካሶቜ፥ ልምሟቜ፥ ሰውነታ቞ው ዹሰለለ ዹደሹቀና ያበጠ ብዙ ድውያን ሕዝብ ይተኙ ነበር፡፡ ኚእግዚአብሔር ዹተሰጠውን ዚምሕሚት ፈውስ ይዞ በሳምንት አንድ ጊዜ ዚእግዚአብሔር መልአክ ውኃውን ባርኮ ሲሄድ ቀድሞ ዚገባው በሜተኛ ይፈወስ ነበር፡፡ ተስፋ ሳይቈርጥ ለ38 ዓመታት ድኅነትን እዚጠበቀ በሕመሙም እተሰቃዚ በዚያ ዹተኛ አንድ ሰው ነበር፡፡ ጌታቜን ይህን ሁሉ ዓመት እንደተሰቃዚ አውቆ ድኅነት ሊሰጠው ወዶ መጣ፡፡ ‹‹ልትድን ትወዳለህን?›› ብሎ ጠዚቀው፡፡ መጠዹቁ ፍጹም ዹሰውን ሥጋ እንደተዋሐደ ሲያጠይቅ ነው፡፡ በተጚማሪም በዕለተ ዐርብ ‹‹ራሱ አዳነኝ እንጂ መቌ አድነኝ አልኩት!›› ብሎ ለመክሰስ ምክንያት እንዳያገኝ ጠዚቀው፡፡ ‹‹ጌታ ሆይ ውኃው በተናወጠ ጊዜ በመጠመቂያው ውስጥ ዚሚያኖሚኝ ሰው ዚለኝም›› አለው፡፡ ‹‹እንዲህ ያለው ዹ30 ዓመት ጎልማሳ ነውና አንስቶ ይጚምሚኛል›› ወይም አምስት ገበያ ዚሚያህል ሕዝብ ይኹተለው ነበርና ‹‹ኚእነርሱ መካኚል አዞልኝ ወደ መጠመቂያው ይጚምሚኛል›› ብሎ ነው እንጂ እንዲሁ ይፈውሰኛል ብሎ አልነበሚም፡፡ ጌታ ግን ለመዳን መውደዱን ተመልክቶ ‹‹ተነሳና አልጋህን ተሾክመህ ሒድ›› አለው፡፡ ኚእግዚአብሔር ዘንድ ዹሚገኘው ፍጹም ድኅነት ነውና ወዲያው ሰውዹው ዳነፀ አልጋውንም ተሾክሞ ሔደ፡፡ ያን ሰውም ጌታቜን በምኵራብ አገኘውና እነሆ ድነሃልፀ ግን ኹዚህ ዚባሰ እንዳያገኝህ ዳግመኛ እንዳትበድል እወቅ አለው፡፡ አልጋውንም ተሾክመህ ሂድ ያለው 38 ዓመት ዚተሞኚመቜው ጠንካራና ዚብሚት አልጋ ስለተሞኚመ ፍጹም መዳኑ እንዲታወቅ ነው፡፡ መጻጕዕ ዹተፈወሰው በእለተ ቀዳሚት ስለነበሚ ፀ በሰንበት ይህን ስላደሚገ አይሁድ ኢዚሱስን ያሳድዱት፣ ሊገድሉትም ይፈልጉ ነበር፡፡ በሜተኛው ዚተደሚገለትን ተአምር ሚስቶ በዕለተ ዐርብ ጌታን ኚሰሰውፀ በጥፊም መታው ወዲያው እጁ ሰለለ፡፡ #ቅዱስ_ያሬድም ጌታቜን ሰንበትን ለዕሚፈት ስለፈጠራትፀ ሕሙማንን በመፈወስ (#ዚመቶ አለቃውን ልጅ በመፈወስ ማቮ. 8፥1-15ፀ #ዚዕውራንን ዓይኖቜ በማብራት ማቮ. 20፥24-30ፀ ዮሐ. 9ፀ #ሜባ ዹነበሹውን በመፈወስ) #በዕለተ_ሰንበት_ኚበሜታ቞ው_እንዲያርፉ_አደሚገ፡፡ በእኛ በሰው ልጆቜ ላይ በሜታ በተለያዚ ምክንያት ይመጣል፡፡ † በኃጢአት ምክንያት ዚሚመጣ በሜታ፡፡ ዘኍ. 21፥4-9 † ዚእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ ይገለጥ ዘንድ ዚሚመጣ በሜታ አለ፡፡ ዮሐ. 9፥13 † ሰዎቜ ኚእግዚአብሔር ዋጋ እንዲያገኙበት ኚዲቢያሎስ ዚሚመጣ ዹፈተና በሜታ አለ እንደ ጻድቁ ኢዮብ፡፡ መጜ.ኢዮብ † ሰዎቜ በተሰጣ቞ው ጾጋ እንዳይታበዩ ማሳወቂያ ዹሚሆን በሜታ አለፀ እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ራስ ምታት፡፡ † ዹበደለውን ዚሚቀጣበት በሜታ አለፀ እንደ ሳዖል አጋንንት አድሮበት ይሰቃይ ነበር፣ ዚመጻጕዕ እጁ ዹሰለለው በሁለተኛ በደሉ ነው፡፡ † ያልታመመው እግዚአብሔርን እንዲያመሰግን፥ ዚታመመው ምሕሚትን እንዲለምን ዚሚመጣ በሜታ አለ፡፡ #share Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem

ዚሰንበት ት/ት ቀታቜን ዹ2 ዓመታት ጥያቄ ዛሬም #_በብጹዕ_አቡነ_መልኹጾዮቅ_ዚአዲስ_አበባና_ዚጉራጌ_አህጉሹ_ስብኚት_ሊቀ_ጳጳስ ዹሰ/ት/ቀቱ ጥያቄ #_ዚመጚሚሻ_ውሳኔ_አገኘ #_ውሳኔው ዚመጣው በ10/07/2013 ዓ.ም ቢሆንም አፈጻጞሙን ሰላማዊ በሆነ መልኩ በሜምግልና እንዲያልቅ ስንጥር እስኚዛሬ ድሚስ ውሳኔውን ሳናሳውቃቜሁ ቆይተናል ****************************** በ29/06/2013 ዓ.ም ሰ/ት/ቀቱ ፣ዚአጥቢያው ምዕመናን ፣ ዚአጥቢያ ሰንበት ት/ት ቀቶቜ ፣ ዚአካባቢው ወጣቶቜ በጋራ በመሆን ወደ ሐገሹ ስብኚት በመሄድ ጥያቄያቜንን ማቅሚባቜን ይታወቃል፡፡ ብጹዕነታ቞ውም በቃል ማብራሪያ ዚቀሚቡትን ሃሳቊቜ በተገቢው መንገድ ኚተመለኚቱና ኹሰሙ በኋላ ዚማያዳግም ውሳኔ ለመስጠት በአካልም ሄጄ ማዚት አለብኝ ብለው ደብራቜን ላይ በመገኘት ዚደብሩ አስተዳደርና ማኅበሹ ካህናት ዚሚሉትን አማራጮቜ እንዲሁም በሰንበት ት/ት ቀታቜን በኩል ዚቀሚቡ አማራጮቜንም በአካል ተዘዋውሹው ኚተመለኚቱ በኋላ በ10/07/13 ዓ.ም በደብዳቀ #ቁጥር 3008/13/2013 ለደብራቜን በተጻፈ ደብዳቀ ሰንበት ት/ት ቀቱ #_በመደበኛነት_ዹመዋዕለ_ሕጻናቱ_ግቢ_እንዲሰጠው ፣ በመዋዕለ ሕጻናት ውስጥ በመማር ላይ ዚሚገኙት ሕጻናት እንዳይበተኑ ደብሩ ቊታ አፈላልጎ ዚመማርያ ቊታ እንዲያመቻቜላ቞ው ተወስኗል፡፡ #_ብጹዕ_አባታቜን ዚብጹዕነትዎ ቡራኬ ይደርብንና በዚካቲት 29/2013 ዓ.ም ፡- ኹ 2ዓመታት በላይ በሰ/ት/ቀቱና በደብሩ አስተዳደር መካኚል ዹቆዹውን አለመግባባት ለአንዮና ለመጚሚሻ ጊዜ አመራር ና ውሳኔ እንዲሰጡን ለመጠዹቅ ወደ ሃገሹ ስብኚትዎ ስንመጣ ምንም እንኳ ለአቀቱታቜን እንግዳ ቢሆኑም ዚሚመሩት ሃገሹ ስብኚት ዚቀተክርስቲያኒቱን ቜግሮቜ ለመፍታት ቁርጠኛ መሆኑን ባሳዚ መልኩ ኚሁለታቜንም ወገን ቜግሩን በዝርዝር ኚመስማት ባለፈ ሳይውሉ ሳያድሩ ደብራቜን ድሚስ ተገኝተው ሁሉንም በአይንዎ ተመልክተው ቆራጥ አመራር እና ፈጣን ውሳኔ ስለሰጡን ለእርስዎ ለብጹዕ አባታቜን ያለን ክብርና አድናቆት ታላቅ ነው፡፡ በሁሉም ዚቀተክርስቲያናቜን ቜግሮቜ ይህ አይነት ቆራጥ አመራርና ውሳኔ ያስፈልጋልና ኹዚሁ አንጻር ዚወሰዱትን እርምጃ ዹሃገሹ ስብኚቱን ገጜታ በእጅጉ ኹፍ አድርጎ ያሳዚ ነውና #_ምስጋናቜን_ይድሚሶት፡፡ እግዚአብሔር ሹጅም ዕድሜና ሰፊ ጀና ይስጥልን፡፡ ዹሃገሹ ስብኚታቜን ዋና ስራ አስኪያጅ #_መምህር_አካለወልድ_ተሰማ እንዲሁም ዋና ጾሐፊ #_መ/ር_ታዲዮስ እና ዹሃገሹ ስብኚቱ ዚሰንበት ት/ት ቀቶቜ ማደራጅያ ዋና ክፍል ሃላፊ #_መ/ር_ዳዊት ወደ ሀገሹ ስብኚቱ በአመራርነት ኚመጣቜሁበት ጊዜ ጀምሮ በእኛና በደብሩ መካኚል ይቀርቡ ዚነበሩትን ተደጋጋሚ አቀቱታዎቜ ሳትሰለቹ በመስማት ውሳኔ ሰጥታቜኋል፡፡ በተጚማሪም ያሉትን ቜግሮቜ በውይይት እንዲፈቱ ትልቁን ድርሻ ተወጥታቜኋልና ምስጋናቜን ዹላቀ ነው፡፡ #_ዹአ.አ_ሰ/ት/ቀቶቜ_አንድነት_ዚስራ_አመራር_አባላት ምንም እንኳ ኃፊነታቜሁ ቢሆንም ኚእኛም በላይ ጉዳዩን ዚራሳቜሁ አድርጋቜሁ ሙሉ ጊዜያቜሁን ሰጥታቜሁ ይህ ውሳኔ እንዲገኝ ያበሚኚታቜሁት አስተዋጜኊ ለታሪክ ዚሚቀመጥ ነውና #_እናመሰግናቜኋለን፡፡ በደብራቜን ዹጠፋው ሰላም እንዲመለስ ተቆርቁራቜሁ ልትሞመግሉን ዚመጣቜሁ አባቶቜና ወንድሞቜ ሹጅም እድሜና ጀና ይስጣቜሁ በሜማግሌነት ያኑራቜሁ፡፡ዚአጥቢያቜን ወጣቶቜና ምዕመናን እንዲሁም በቅርብ ዚምትገኙ ሰንበት ት/ት ቀቶቜ በተለይ ( ወልደ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ #ፍቁሹ_እግዚእ ሰ/ት/ቀት ፣ #ገነተ_ጜጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰ/ት/ቀት ፣ #ምስካዚ_ኅዙናን ተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቀት ፣ ደብሚ ታቊር ቅዱስ ሚካኀል ሰ/ት/ቀት ፣ ደብሚሲና ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ዕፀ ጳጊስ ሰ/ት/ቀት) ዹሰ/ት/ቀቱ ጉዳይ ዹኛም ጉዳይ ነው ያገባናል ይመለኹተናል ብላቜሁ ለሰጣቜሁን ድጋፍ እና ለተወጣቜሁት ኃላፊነት ሁሉ ኚልብ እናመስግናለን፡፡ #_ውድ_ዚደብራቜን_አባቶቜ በተገኘው ውሳኔ አሾናፊና ተሾናፊ ዹለም ይልቁንም ቋሚ ዚህጻናትና ወጣቶቜ መማርያ ቊታ ውሳኔ ተሰጠበት እንጂ ፡፡ ክርክራቜን ደግሞ ዹሰ/ት/ቀቱ ዚመማርያ ቊታ ኹዚህ ይልቅ ያኛው ይሻላል ዹሚል ዚአባትና ዹልጅ ነው፡፡ ብጹዕነታ቞ው ደግሞ ይህንን ክርክር ለአንዮና ለመጚሚሻ ጊዜ ለመወሰን ዹሚመለኹተውን ሁሉ አናግሹው በአካልም ቊታው ድሚስ ተገኝተው ዚመጚሚሻ ፠ ግራ ቀኙ በደንብ ዚታዚበት ፀ ሁሉንም ዚማይጎዳ ውሳኔ ሰጥተዋል፡፡ ይህ ውሳኔ ለ3ኛ ጊዜ ዚመጣ ዉሳኔ ነው ፡፡ ስለሆነም ኹዚህ በኃላ በመካኚላቜን ዹተፈጠሹውን አለመግባባት በፍጹም እርቅ አስወግደን ውሳኔውን በጋራ ተሚባርበን አስፈጜመን ደብራቜንን ወደ ቀደመ ሰላሙ እንድንመልሰው ሰ/ት/ቀቱ ዛሬም ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ ስለ ሁሉም ነገር ክብር #_ለመድኃኔዓለም! #share Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem

#ዹሊቀ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቀተ ክርስቲያን ተቃጥሏል #በዹሹር ተራራ እዚነደደ ነው በዹሹር ተራራ ዹሹር ቅዱስ ቎ዎድሮስ 
 ዹዹሹር ሩላሮና ዹዹሹር በአታለማርያም ገዳም ደን እዚነደደ ነው ፡፡ እሣቱ ሰው ሰራሜ መሆኑ ኚምስሉ መሚዳት ይቻላል፡፡ ቀተ ክርስቲያንን እስኚ መሠሚቷ ድሚስ ፈጜሞ አፍርሱ ዚሚሉትን ጎስቋሎቜን ዹሚበቀላቾው አምላካቜን ብፁዕ ነው፡፡ /መዝ. 136/ xበጀውኃ ኹተማ ዹሚገኝ ዹሊቀ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቀተ ክርስቲያን እዚነደደ ነው ሰሜን ሞዋፀኚሞዋ ሮቢት አለፍ ብሎ #በጀውኃ ኹተማ ዹሚገኝ #ዹሊቀ_ሰማዕት_ቅዱስ_ጊዮርጊስ_ቀተ_ክርስቲያን_ተቃጥላል:: ካህናቱ ታርደዋል ፣ ምእመናንም ታርደዋል ፣ ዚክርስቲያን መኖሪያ ቀቶቜ ወድመዋል። #መዝሙሹ ዳዊት 73ፀ ‹‹#መቅደስህንም_በእሳት_አቃጠሉፀ 
 #አቀቱ_ተነስ_በቀሌንም_ተበቀል፡፡›› ስለ ቅድስት ቀተክርስቲያን እንጞልይ ‹‹ሥጋንም ዚሚገድሉትን ነፍስን ግን መግደል ዚማይቻላ቞ውን አትፍሩ!ፀ ይልቅስ ነፍስንም ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ ዚሚቻለውን ፍሩ:: ማቮ. 10፥28:: ። #share Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem

Finote Hiwot ዹቀጹኔ ደብሚ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብሚ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኀል ቀተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቀት - Estadísticas y analítica del canal de Telegram @finotehiwott