en
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Open in Telegram

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Channel Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 15 381 subscribers, ranking 5 584 in the Religion & Spirituality category and 2 199 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 15 381 subscribers.

According to the latest data from 03 July, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 21 over the last 30 days and by -7 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 21.13%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 9.50% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 3 250 views. Within the first day, a publication typically gains 1 462 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 16.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 04 July, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

15 381
Subscribers
-724 hours
+117 days
+2130 days
Posts Archive
#መፃጕዕ፤ አራተኛው ሳምንት አራተኛው ሳምንት መፃጕዕ ይባላል፡፡ በመፃጕዕ የተሰየመው የእርሱ ስህተት ለእኛ ትምህርት፥ ተግሳጽ እንዲሆነን እንጂ፤ በዚህ ሳምንት የሚታሰበው ጌታችን ሕሙማን መፈወሱን፣ ሙት ማስነሳቱንና ስለ ረቂቁ የነፍስ ደዌ ስለ ኀጢአትና ስለ ድኅነታችን የሚያዘክር ምስጋና ይቀርብበታል፡፡ ማቴ. 8፥1-37፣ ማር. 7፥13-37፣ ሉቃ. 17፥1-9፣ ዮሐ. 5፥1-18 በቤተክርስቲያን በሽተኞች በሦስት ስያሜ ይጠራሉ፡- ፨ #በሽተኛ፤ የዕለት ሕመም ወይም እስከ አንድ ዓመት የታመመ ሰው፡፡ ፨ #ድውይ፤ እስከ አምስት ዓመት ሕመሙ የቆየበት፡፡ ፨ #መፃጕዕ፤ ከአምስት ዓመት በላይ ሕመሙ የጸናበት፤ ሲሆን ድውይ፥ በሕመም የሚማቅቅ፥ የዐልጋ ቊራኛ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ #መፃጕዕ የተባለው ስለሕመሙ #38_ዓመታት_መጽናት_እንጂ ስሙ አይደለም፡፡ በዕብራይስጥ ቤተ ሳይዳ ትርጕሙ /የምሕረት ቦታ/፤ በግእዙ ቀላየ አባግዕ (የበጎች መዋኛ) በተባለች ምጥምቃት ዘጵሩጳጥቄ በምትባል የጠበል መጠመቂያ ኩሬ ዳር የውኃውን መንቀሳቀስ እየጠበቁ በሽተኞች፥ እውሮች፥ አንካሶች፥ ልምሾች፥ ሰውነታቸው የሰለለ የደረቀና ያበጠ ብዙ ድውያን ሕዝብ ይተኙ ነበር፡፡ ከእግዚአብሔር የተሰጠውን የምሕረት ፈውስ ይዞ በሳምንት አንድ ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ውኃውን ባርኮ ሲሄድ ቀድሞ የገባው በሽተኛ ይፈወስ ነበር፡፡ ተስፋ ሳይቈርጥ ለ38 ዓመታት ድኅነትን እየጠበቀ በሕመሙም እተሰቃየ በዚያ የተኛ አንድ ሰው ነበር፡፡ ጌታችን ይህን ሁሉ ዓመት እንደተሰቃየ አውቆ ድኅነት ሊሰጠው ወዶ መጣ፡፡ ‹‹ልትድን ትወዳለህን?›› ብሎ ጠየቀው፡፡ መጠየቁ ፍጹም የሰውን ሥጋ እንደተዋሐደ ሲያጠይቅ ነው፡፡ በተጨማሪም በዕለተ ዐርብ ‹‹ራሱ አዳነኝ እንጂ መቼ አድነኝ አልኩት!›› ብሎ ለመክሰስ ምክንያት እንዳያገኝ ጠየቀው፡፡ ‹‹ጌታ ሆይ ውኃው በተናወጠ ጊዜ በመጠመቂያው ውስጥ የሚያኖረኝ ሰው የለኝም›› አለው፡፡ ‹‹እንዲህ ያለው የ30 ዓመት ጎልማሳ ነውና አንስቶ ይጨምረኛል›› ወይም አምስት ገበያ የሚያህል ሕዝብ ይከተለው ነበርና ‹‹ከእነርሱ መካከል አዞልኝ ወደ መጠመቂያው ይጨምረኛል›› ብሎ ነው እንጂ እንዲሁ ይፈውሰኛል ብሎ አልነበረም፡፡ ጌታ ግን ለመዳን መውደዱን ተመልክቶ ‹‹ተነሳና አልጋህን ተሸክመህ ሒድ›› አለው፡፡ ከእግዚአብሔር ዘንድ የሚገኘው ፍጹም ድኅነት ነውና ወዲያው ሰውየው ዳነ፤ አልጋውንም ተሸክሞ ሔደ፡፡ ያን ሰውም ጌታችን በምኵራብ አገኘውና እነሆ ድነሃል፤ ግን ከዚህ የባሰ እንዳያገኝህ ዳግመኛ እንዳትበድል እወቅ አለው፡፡ አልጋውንም ተሸክመህ ሂድ ያለው 38 ዓመት የተሸከመችው ጠንካራና የብረት አልጋ ስለተሸከመ ፍጹም መዳኑ እንዲታወቅ ነው፡፡ መጻጕዕ የተፈወሰው በእለተ ቀዳሚት ስለነበረ ፤ በሰንበት ይህን ስላደረገ አይሁድ ኢየሱስን ያሳድዱት፣ ሊገድሉትም ይፈልጉ ነበር፡፡ በሽተኛው የተደረገለትን ተአምር ረስቶ በዕለተ ዐርብ ጌታን ከሰሰው፤ በጥፊም መታው ወዲያው እጁ ሰለለ፡፡ #ቅዱስ_ያሬድም ጌታችን ሰንበትን ለዕረፈት ስለፈጠራት፤ ሕሙማንን በመፈወስ (#የመቶ አለቃውን ልጅ በመፈወስ ማቴ. 8፥1-15፤ #የዕውራንን ዓይኖች በማብራት ማቴ. 20፥24-30፤ ዮሐ. 9፤ #ሽባ የነበረውን በመፈወስ) #በዕለተ_ሰንበት_ከበሽታቸው_እንዲያርፉ_አደረገ፡፡ በእኛ በሰው ልጆች ላይ በሽታ በተለያየ ምክንያት ይመጣል፡፡ † በኃጢአት ምክንያት የሚመጣ በሽታ፡፡ ዘኍ. 21፥4-9 † የእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ ይገለጥ ዘንድ የሚመጣ በሽታ አለ፡፡ ዮሐ. 9፥13 † ሰዎች ከእግዚአብሔር ዋጋ እንዲያገኙበት ከዲቢያሎስ የሚመጣ የፈተና በሽታ አለ እንደ ጻድቁ ኢዮብ፡፡ መጽ.ኢዮብ † ሰዎች በተሰጣቸው ጸጋ እንዳይታበዩ ማሳወቂያ የሚሆን በሽታ አለ፤ እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ራስ ምታት፡፡ † የበደለውን የሚቀጣበት በሽታ አለ፤ እንደ ሳዖል አጋንንት አድሮበት ይሰቃይ ነበር፣ የመጻጕዕ እጁ የሰለለው በሁለተኛ በደሉ ነው፡፡ † ያልታመመው እግዚአብሔርን እንዲያመሰግን፥ የታመመው ምሕረትን እንዲለምን የሚመጣ በሽታ አለ፡፡ #share Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem

የሰንበት ት/ት ቤታችን የ2 ዓመታት ጥያቄ ዛሬም #_በብጹዕ_አቡነ_መልከጸዴቅ_የአዲስ_አበባና_የጉራጌ_አህጉረ_ስብከት_ሊቀ_ጳጳስ የሰ/ት/ቤቱ ጥያቄ #_የመጨረሻ_ውሳኔ_አገኘ #_ውሳኔው የመጣው በ10/07/2013 ዓ.ም ቢሆንም አፈጻጸሙን ሰላማዊ በሆነ መልኩ በሽምግልና እንዲያልቅ ስንጥር እስከዛሬ ድረስ ውሳኔውን ሳናሳውቃችሁ ቆይተናል ****************************** በ29/06/2013 ዓ.ም ሰ/ት/ቤቱ ፣የአጥቢያው ምዕመናን ፣ የአጥቢያ ሰንበት ት/ት ቤቶች ፣ የአካባቢው ወጣቶች በጋራ በመሆን ወደ ሐገረ ስብከት በመሄድ ጥያቄያችንን ማቅረባችን ይታወቃል፡፡ ብጹዕነታቸውም በቃል ማብራሪያ የቀረቡትን ሃሳቦች በተገቢው መንገድ ከተመለከቱና ከሰሙ በኋላ የማያዳግም ውሳኔ ለመስጠት በአካልም ሄጄ ማየት አለብኝ ብለው ደብራችን ላይ በመገኘት የደብሩ አስተዳደርና ማኅበረ ካህናት የሚሉትን አማራጮች እንዲሁም በሰንበት ት/ት ቤታችን በኩል የቀረቡ አማራጮችንም በአካል ተዘዋውረው ከተመለከቱ በኋላ በ10/07/13 ዓ.ም በደብዳቤ #ቁጥር 3008/13/2013 ለደብራችን በተጻፈ ደብዳቤ ሰንበት ት/ት ቤቱ #_በመደበኛነት_የመዋዕለ_ሕጻናቱ_ግቢ_እንዲሰጠው ፣ በመዋዕለ ሕጻናት ውስጥ በመማር ላይ የሚገኙት ሕጻናት እንዳይበተኑ ደብሩ ቦታ አፈላልጎ የመማርያ ቦታ እንዲያመቻችላቸው ተወስኗል፡፡ #_ብጹዕ_አባታችን የብጹዕነትዎ ቡራኬ ይደርብንና በየካቲት 29/2013 ዓ.ም ፡- ከ 2ዓመታት በላይ በሰ/ት/ቤቱና በደብሩ አስተዳደር መካከል የቆየውን አለመግባባት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ አመራር ና ውሳኔ እንዲሰጡን ለመጠየቅ ወደ ሃገረ ስብከትዎ ስንመጣ ምንም እንኳ ለአቤቱታችን እንግዳ ቢሆኑም የሚመሩት ሃገረ ስብከት የቤተክርስቲያኒቱን ችግሮች ለመፍታት ቁርጠኛ መሆኑን ባሳየ መልኩ ከሁለታችንም ወገን ችግሩን በዝርዝር ከመስማት ባለፈ ሳይውሉ ሳያድሩ ደብራችን ድረስ ተገኝተው ሁሉንም በአይንዎ ተመልክተው ቆራጥ አመራር እና ፈጣን ውሳኔ ስለሰጡን ለእርስዎ ለብጹዕ አባታችን ያለን ክብርና አድናቆት ታላቅ ነው፡፡ በሁሉም የቤተክርስቲያናችን ችግሮች ይህ አይነት ቆራጥ አመራርና ውሳኔ ያስፈልጋልና ከዚሁ አንጻር የወሰዱትን እርምጃ የሃገረ ስብከቱን ገጽታ በእጅጉ ከፍ አድርጎ ያሳየ ነውና #_ምስጋናችን_ይድረሶት፡፡ እግዚአብሔር ረጅም ዕድሜና ሰፊ ጤና ይስጥልን፡፡ የሃገረ ስብከታችን ዋና ስራ አስኪያጅ #_መምህር_አካለወልድ_ተሰማ እንዲሁም ዋና ጸሐፊ #_መ/ር_ታዲዮስ እና የሃገረ ስብከቱ የሰንበት ት/ት ቤቶች ማደራጅያ ዋና ክፍል ሃላፊ #_መ/ር_ዳዊት ወደ ሀገረ ስብከቱ በአመራርነት ከመጣችሁበት ጊዜ ጀምሮ በእኛና በደብሩ መካከል ይቀርቡ የነበሩትን ተደጋጋሚ አቤቱታዎች ሳትሰለቹ በመስማት ውሳኔ ሰጥታችኋል፡፡ በተጨማሪም ያሉትን ችግሮች በውይይት እንዲፈቱ ትልቁን ድርሻ ተወጥታችኋልና ምስጋናችን የላቀ ነው፡፡ #_የአ.አ_ሰ/ት/ቤቶች_አንድነት_የስራ_አመራር_አባላት ምንም እንኳ ኃፊነታችሁ ቢሆንም ከእኛም በላይ ጉዳዩን የራሳችሁ አድርጋችሁ ሙሉ ጊዜያችሁን ሰጥታችሁ ይህ ውሳኔ እንዲገኝ ያበረከታችሁት አስተዋጽኦ ለታሪክ የሚቀመጥ ነውና #_እናመሰግናችኋለን፡፡ በደብራችን የጠፋው ሰላም እንዲመለስ ተቆርቁራችሁ ልትሸመግሉን የመጣችሁ አባቶችና ወንድሞች ረጅም እድሜና ጤና ይስጣችሁ በሽማግሌነት ያኑራችሁ፡፡የአጥቢያችን ወጣቶችና ምዕመናን እንዲሁም በቅርብ የምትገኙ ሰንበት ት/ት ቤቶች በተለይ ( ወልደ ነጎድጓድ ቅዱስ ዮሐንስ #ፍቁረ_እግዚእ ሰ/ት/ቤት ፣ #ገነተ_ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰ/ት/ቤት ፣ #ምስካየ_ኅዙናን ተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ቤት ፣ ደብረ ታቦር ቅዱስ ሚካኤል ሰ/ት/ቤት ፣ ደብረሲና ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ዕፀ ጳጦስ ሰ/ት/ቤት) የሰ/ት/ቤቱ ጉዳይ የኛም ጉዳይ ነው ያገባናል ይመለከተናል ብላችሁ ለሰጣችሁን ድጋፍ እና ለተወጣችሁት ኃላፊነት ሁሉ ከልብ እናመስግናለን፡፡ #_ውድ_የደብራችን_አባቶች በተገኘው ውሳኔ አሸናፊና ተሸናፊ የለም ይልቁንም ቋሚ የህጻናትና ወጣቶች መማርያ ቦታ ውሳኔ ተሰጠበት እንጂ ፡፡ ክርክራችን ደግሞ የሰ/ት/ቤቱ የመማርያ ቦታ ከዚህ ይልቅ ያኛው ይሻላል የሚል የአባትና የልጅ ነው፡፡ ብጹዕነታቸው ደግሞ ይህንን ክርክር ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለመወሰን የሚመለከተውን ሁሉ አናግረው በአካልም ቦታው ድረስ ተገኝተው የመጨረሻ ፠ ግራ ቀኙ በደንብ የታየበት ፤ ሁሉንም የማይጎዳ ውሳኔ ሰጥተዋል፡፡ ይህ ውሳኔ ለ3ኛ ጊዜ የመጣ ዉሳኔ ነው ፡፡ ስለሆነም ከዚህ በኃላ በመካከላችን የተፈጠረውን አለመግባባት በፍጹም እርቅ አስወግደን ውሳኔውን በጋራ ተረባርበን አስፈጽመን ደብራችንን ወደ ቀደመ ሰላሙ እንድንመልሰው ሰ/ት/ቤቱ ዛሬም ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡ ስለ ሁሉም ነገር ክብር #_ለመድኃኔዓለም! #share Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem

#የሊቀ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ተቃጥሏል #በየረር ተራራ እየነደደ ነው በየረር ተራራ የረር ቅዱስ ቴዎድሮስ … የየረር ሦላሴና የየረር በአታለማርያም ገዳም ደን እየነደደ ነው ፡፡ እሣቱ ሰው ሰራሽ መሆኑ ከምስሉ መረዳት ይቻላል፡፡ ቤተ ክርስቲያንን እስከ መሠረቷ ድረስ ፈጽሞ አፍርሱ የሚሉትን ጎስቋሎችን የሚበቀላቸው አምላካችን ብፁዕ ነው፡፡ /መዝ. 136/ xበጀውኃ ከተማ የሚገኝ የሊቀ ሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን እየነደደ ነው ሰሜን ሸዋ፤ከሸዋ ሮቢት አለፍ ብሎ #በጀውኃ ከተማ የሚገኝ #የሊቀ_ሰማዕት_ቅዱስ_ጊዮርጊስ_ቤተ_ክርስቲያን_ተቃጥላል:: ካህናቱ ታርደዋል ፣ ምእመናንም ታርደዋል ፣ የክርስቲያን መኖሪያ ቤቶች ወድመዋል። #መዝሙረ ዳዊት 73፤ ‹‹#መቅደስህንም_በእሳት_አቃጠሉ፤ … #አቤቱ_ተነስ_በቀሌንም_ተበቀል፡፡›› ስለ ቅድስት ቤተክርስቲያን እንጸልይ ‹‹ሥጋንም የሚገድሉትን ነፍስን ግን መግደል የማይቻላቸውን አትፍሩ!፤ ይልቅስ ነፍስንም ሥጋንም በገሃነም ሊያጠፋ የሚቻለውን ፍሩ:: ማቴ. 10፥28:: ። #share Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem