MIRAF ACADEMY AYAT BRANCH
Ir al canal en Telegram
This channel is for Miraf Academy Ayat branch educational purpose.
Mostrar más5 953
Suscriptores
+224 horas
+97 días
+1630 días
Archivo de publicaciones
Grade 12 mock exam practice New URL for Addis Ababa mock3.ethernet.edu.et
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተናዎች የሚሰጡበት ጊዜ ይፋ ሆናል፡፡
(ግንቦት 13/2018 ዓ.ም) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 የትምህርት ዘመን ከተማ አቀፍ የ6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና እና የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና የሚሰጥበት ጊዜ ይፋ ሆናል፡፡
በዚህ መሰረትም ከተማ አቀፍ የ6ኛ ክፍል የአንደኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ፈተና ሰኔ 8 ፣ 9 እና 10/2018 ዓ.ም እንዲሁም የ8ኛ ክፍል የመካከለኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት ፈተና ሰኔ 11 እና 12/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሚሰጥ ይሆናል፡፡
ከሰኔ 8 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም በሚሰጠው በዚህ ከተማ አቀፍ ፈተና በ6ኛ ከፍል 84,882 ተማሪዎች 199 የመፈተኛ ጣቢያዎች እንዲሁም በ8ኛ ከፍል 86,808 ተማሪዎች 201 የመፈተኛ ጣቢያዎች ፈተናዉን ለመውሰድ ተመዝግበዋል፡፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
Repost from Addis Ababa Education Bureau
+3
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በ2018 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ፣ የ8ኛ እና የ6ኛ ክፍል የሁለተኛ ሴሚስተር ከተማ አቀፍ ሞዴል ፈተና መስጫ ጊዜ ሰሌዳ
(ግንቦት 6/2018 ዓ.ም)
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
ሰላም እንዴት ዋላችሁ
📖የ6ኛ፤ 8ኛና 12ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ የሞዴል ፈተና የቀን ለውጥ ተደርጎበታል፡፡
👉🏻ከግንቦት 12-14/2018 ቀናት መካከል የምሰጥ ይሆናል በዚህ ልክ ትምህርት ቤቶች ፕሮግራማቸውን እንድያዘጋጁ ይደርግ፡፡
መልካም ቀን፡፡
ለውድ የምዕራፍ አካዳሚ ቤተሰቦች:-
ውድ የምዕራፍ ቤተሰቦች ልጆቻችን የሶስተኛውን ሩብ ዓመት ትምርህታቸውን በተሳካ ሁኔታ አጠናቀው የአራተኛ ሩብ ዓመትን በመከታተል ላይ ይገኛሉ ።ስለሆነም የፊታችን እሁድ ግንቦት 09/2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30_6:30 ሰዓት የመምህራን እና የወላጆች የገጽ ለገጽ ውይይት (Open house Conference ) በሁሉም ግቢና የክፍል ደረጃ የሚካሄድ ስለሆነ ወላጆች ስለተማሪዎቹ የት/ት አቀባበልና ስነ-ምግባር ከመምህራን ጋር ውይይት በማድረግ እና ገንቢ አስተያየታችሁን በማስቀመጥ የሶስተኛውን ሩብ ዓመት ውጤት እንድትወስዱ ስንል በአክብሮት ለማሳወቅ እንወዳለን ።
ት/ቤቱ!
ለምዕራፍ አካዳሚ ቤተሰቦች በሙሉየ4ኛውን ሩብ ዓመት ክፍያ ያላጠናቀቃችሁ ቤተሰቦች እስከ ሚያዚያ 16/2018 ዓ.ም ድረስ እንድታጠናቅቁ በድጋሚ እያሳሰብን ክፍያ የምትፈጽሙባቸው ባንኮች ዘወትር በስራ ቀናትና ሰዓት በት/ቤቱ ግቢ ውስጥ ሙሉ የባንክ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን በአክብሮት እናሳውቃለን ። ት/ቤቱ!
ዛሬ ሐሙስ 11:00 ጀምሮ ከምዕራፍ አካዳሚ በመቄዶንያ ዩትዩብ ይከታተሉ።
www.youtube.com/@Mekedonia
👆ይህን ቻናል አሁኑኑ Subscribe በማድረግ ሁላችሁም ነገ Like👍እያደረጋችሁ ስማችሁንና ክፍላችሁን Comment ላይ እየፃፋችሁ እንዲሁም መቄዶንያን እንደምትደግፉ እየገለፃችሁ እንድትከታተሉ ከወዲሁ እናሳውቃለን።
1️⃣ ከምዕራፍ አካዳሚ ጀሞ ቅርንጫፍ ለመቄዶንያ ድጋፍ ለማድረግ የተከፈተ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000748156357
(ከት/ቤቱ አቶ እንዳለማዉ ጌቴ እና ከመቄዶንያ ያብስራ ቢሆነኝ)
2️⃣ ከምዕራፍ አካዳሚ ሀያት ቅርንጫፍ ለመቄዶንያ ድጋፍ ለማድረግ የተከፈተ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000748164638
(ከት/ቤቱ አቶ አብርሃም አንለይ እና ከመቄዶንያ ያብስራ ቢሆነኝ)
፤ አሁኑኑ ይርዱ!
ለምዕራፍ አካዳሚ ቤተሰቦች በሙሉጉዳዩ :- የ2018 ዓ.ም የመጨረሻውን ሩብ ዓመት ክፍያን ይመለከታል ውድ ወላጆች የአገልግሎት ክፍያችሁን በጊዜው እና በሰዓቱ እየፈጸማችሁ እዚህ ስላደረሳችሁን እጅግ እያመሰገንን የ2018 ዓ.ም የመጨረሻው ሩብ ዓመት ክፍያ የሚፈጸመው ከመጋቢት 28/2018 ዓ.ም እስከ ሚያዚያ 16/2018 ዓ.ም መሆኑን አውቃችሁ ከወዲሁ እንድታጠናቅቁ ስንል በአክብሮት ለማሳሰብ እንወዳለን። ት/ቤቱ!
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታይ የምዕራፍ አካዳሚ ቤተሰቦች በሙሉ እንኳን ለ1,447ኛው ዒድ- አልፈጥር በዓል በሠላም አደረሳችሁ !! አደረሰን !!! በዓሉ የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅር፣ የመተሳሰብ እና የደስታ ይሁንላችሁ።
ዒድ-ሙባረክ !!!
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
