es
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Ir al canal en Telegram

📈 Análisis del canal de Telegram የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

El canal የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 14 442 suscriptores, ocupando la posición 6 042 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 328 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 14 442 suscriptores.

Según los últimos datos del 28 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 550, y en las últimas 24 horas de 26, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 37.47%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 10.23% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 5 412 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 477 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 33.

📝 Descripción y política de contenido

No se ha proporcionado la descripción del canal.

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 29 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

14 442
Suscriptores
+2624 horas
+1347 días
+55030 días
Archivo de publicaciones
የነገረ ሰብእ ትምህርት ጉድለት የወለደው አገራዊ ቀውስ በቤተ ክርስቲያን ትምህርት ነገረ ሰብእ (አንትሮፖሎጂ) አንደኛው የጥናት ዘርፍ ነው። ይህ የጥናት ዘርፍ ስለ ሰው አፈጣጠርና ክብር የሚናገር ነ
የነገረ ሰብእ ትምህርት ጉድለት የወለደው አገራዊ ቀውስ በቤተ ክርስቲያን ትምህርት ነገረ ሰብእ (አንትሮፖሎጂ) አንደኛው የጥናት ዘርፍ ነው። ይህ የጥናት ዘርፍ ስለ ሰው አፈጣጠርና ክብር የሚናገር ነው። ስለ ፍጥረት አመጣጥ የሚናገረው የመጽሐፍ ቅዱስ የመጀመሪያው መጽሐፍ ኦሪት ዘፍጥረት ሰው በእግዚአብሔር አርአያና ምሳሌ የተፈጠረ ክቡር ፍጡር መሆኑን ይነግረናል። ሊቀ ነቢያት ሙሴ ስለ አፈጣጠሩ ሲተርክልንም “እግዚአብሔርም አለ፤ ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌያችን እንፍጠር፤ የባሕር ዓሦችንና የሰማይ ወፎችን፣ እንስሳትንና ምድርን ሁሉ፣ በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ይግዙ፡ እግዚአብሔርም ሰውን በመልኩ ፈጠረ፤ በእግዚአብሔር መልክ ፈጠረው፤ ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው” (ዘፍ. ፩፡፳፮-፳፯) ይለናል። የሚወዱትን እንግዳ ሁሉን አዘጋጅቶ እንደሚጠሩት እግዚአብሔርም ለሰው የሚያስፈልገውን ሁሉ አስቀድሞ ካዘጋጀ በኋላ ሰውን የፍጥረት መደምደሚያና መካተቻ አድርጎ ፈጥሮታል። እግዚአብሔር ሌሎች ፍጥረታትን በኀልዮ (በማሰብ) እና በነቢብ (በመናገር) ሲፈጥራቸው ሰውን ግን በእጁ ሠርቶታል። “እግዚአብሔር አምላክ ሰውን ከምድር አፈር አበጀው፤ በፊቱም የሕይወት እስትንፋስን እፍ አለበት፤ ሰውም ሕያው ነፍስ ያለው ሆነ” (ዘፍ. ፪፡፯) የተባለው ለዚህ ነው። ስለሆነም ሰው ክብሩና ልእልናው ከፍ ያለ ነው። ማንበብ ይቀጥሉ... 👇👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/የነገረ-ሰብእ-ትምህርት-ጉድለት-የወለደው/ የነገረ ሰብእ ትምህርት ጉድለት የወለደው አገራዊ ቀውስ (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

በሰንበት ት/ቤቶች ታሪክ የመጀመሪያ የሆነው የ ፲፪ኛ ክፍል የተማሪዎች ምርቃት መርሐ ግብር ተካሄደ ቅዳሜ ጥቅምት 3 ቀን 2016ዓ.ም ፤ (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሰንበት ት/ት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ በሰንበት ት/ት ቤቶች አንድነት የመጀመሪያ የሆነውና በሙከራ ትግበራ ላይ በነበረው ሥርዓተ ትምህርት መሠረት የተማሩና በ2015ዓ.ም 12ኛ ክፍል ደርሰው ምዘናውን የወሰዱ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች የምርቃት መርሐ ግብር ተከናወነ። ጥቅምት 3 ቀን 2016 ዓ.ም በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በበዓለ ወልድ አዳራሽ በተደረገው በዚህ ጉባኤ የምስራቅ አውስትራሊያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እንዲሁም የመላው ኢትዮጵያ ገዳማት መምሪያ ኃላፊ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል የሆኑት ብፁዕ አብነ ሉቃስ ፤ የሰንበት ት/ት ቤቶች ማደራጃ መምሪያው ኃላፊ መጋቤ ብርሃናት ቆሞስ አባ ተክለ ያሬድ ጎርጎርዮስ፤ የሰንበት ት/ት ቤቶች ማደራጃ መምሪያው ምክትል ኃላፊ መጋቤ ሐዲስ ፀጋ ወልደ ትንሳኤ፤ የሀገረ አቀፍ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ም/ ሰብሳቢ ዲ.ን ስንታየሁ ምስጋናውና የየደብራቱ መምህራን፣ ተመራቂዎችና በርካታ የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች እንዲሁም የተማሪ ወላጆች ተገኝተዋል። በመርሐ ግብሩ የሰንበት ት/ት ቤቶች ማደራጃ መምሪያው ኃላፊ መጋቤ ብርሃናት ቆሞስ አባ ተክለ ያሬድ ጎርጎርዮስ በፀሎት ያስከፈቱ ሲሆን ወቅቱን የተመለከቱ ዪሬዳዊ ዝማሬዎች መነባንብና ወረብ ቀርቧል። የሰንበት ት/ት ቤቶች ማደራጃ መምሪያው ምክትል ኃላፊ መጋቤ ሐዲስ ፀጋ እንዲሁም በሀገር አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ም/ሰብሳቢ ዲ.ን ስንታየሁ የእንኳን ደስ አላቹ መልዕክትና ቀጣይ የሥርዓተ ትምህርቱ አቅጣጫ ላይ ንግግር አድርገዋል። በመርሐ ግብሩ ለሰንበት ትምህርት ቤቶች የተዘጋጀው ሥርዓተ ትምህርት የመጀመርያ የ12ኛ ክፍል ምርቃት መደረጉ ፍሬ የማፍራቱ ማሳያ መሆኑ የተጠቀሰ ሲሆን በቀጣይ በአዲስ አበባና በሌሎች አህጉረ ስብከቶች የትግበራ ክትትሉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተነግሯል። በመቀጠልም "ይህንን መልካም ሥራ እንድንሰራ መንፈስ ቅዱስ ጠራን" የሚለውን የቅዱስ ጳውሎስ መልዕክት መሠረት በማድረግ ቆሞስ አባ ተክለ ያሬድ ጎርጎርዮስ ቃለ እግዚአብሔርን አስተምረዋል። በመጨረሻም ለተመራቂ ተማሪዎች ምስክር ወረቀት ያበረከቱት የምስራቅ አውስትራሊያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እንዲሁም የመላው ኢትዮጵያ ገዳማት መምሪያ ኃላፊ እና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ብፅዕ አቡነ ሉቃስ ቃለ ምዕዳን እና ቡራኬ የሰጡ ሲሆን በመልዕክታቸው " የቤተ ክርስቲያን ሙሽራ ሆናቹ ክርስቶስን እንድትጠብቁ፣ ወደ ዓለም ስትሔዱ በተኩላው እንዳትወሰዱ ተጠንቀቁ" ሲሉ አባታዊ መልዕክት በማስተላለፍ በፀሎት የመርሐ ግብሩ ፍፃሜ ሆኗል። (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

🔔🔔🔔🔔🔔🔔 💫💫💫💫 🔔🔔🔔🔔🔔 💫💫💫💫 🔔🔔🔔🔔🔔 💫💫💫💫 🔔🔔🔔🔔🔔 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!! "ልጅን በሚኼድበት መን
+3
🔔🔔🔔🔔🔔🔔 💫💫💫💫 🔔🔔🔔🔔🔔 💫💫💫💫 🔔🔔🔔🔔🔔 💫💫💫💫 🔔🔔🔔🔔🔔 በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!!!  "ልጅን በሚኼድበት መንገድ ምራው፤ በሸመገለም ጊዜ ከርሱ ፈቀቅ አይልም።" {ምሳሌ 22፥6}     በሚል መሪ ቃል የተዘጋጀ በ2015 ዓ.ም በሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ትምህርታቸውን  ተከታትለው  ያጠናቀቁ እና በሀገረ ስብከት በብሔራዊ ደረጃ ምዘና ተደርጎላቸው ያለፉ  #የ4ኛ , #የ6ኛ እና #የ10ኛ ክፍል #ከ4500 በላይ ተማሪዎች የዕውቅና መስጠት መርሐ ግብር የዝግጅት ሥራ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ታዳሚዎቻችንን በመጠባበቅ ላይ እንገኛለን!!! #ጥቅምት_4_2016_ዓ_ም  #ከቀኑ_7_00_ሰዓት_ጀምሮ  #በደብረ_ምጥማቅ_ሰዓሊተ_ምህረት_ቅድስት_ማርያም_እና_ቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ_ካቴድራል        #በዕለቱ_ሁላችሁም_ተጋብዛችኋል!!! #ኑ_ተማሪዎቻችንን_በጋራ_እንመርቅ #ሰዓት_ይከበር #መቅረት_ያስቆጫል 💢የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት💢 ++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ 🔔🔔🔔🔔🔔🔔 💫💫💫💫 🔔🔔🔔🔔🔔 💫💫💫💫 🔔🔔🔔🔔🔔 💫💫💫💫 🔔🔔🔔🔔🔔

"ሰውስ ዘመኑ እንደ ሣር ነው፤ እንደ ዱር አበባ እንዲሁ ያብባል፤ ነፋስ በነፈሰበት ጊዜ ያልፋልና፥ ስፍራውንም ደግሞ አያውቀውምና።" መዝ 102(103) ፡ 16 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩ
"ሰውስ ዘመኑ እንደ ሣር ነው፤ እንደ ዱር አበባ እንዲሁ ያብባል፤ ነፋስ በነፈሰበት ጊዜ ያልፋልና፥ ስፍራውንም ደግሞ አያውቀውምና።" መዝ 102(103) ፡ 16 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU - Estadísticas y analítica del canal de Telegram @eotcgssu21