es
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

Ir al canal en Telegram

📈 Análisis del canal de Telegram የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

El canal የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 14 454 suscriptores, ocupando la posición 6 042 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 2 328 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 14 454 suscriptores.

Según los últimos datos del 28 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 550, y en las últimas 24 horas de 26, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 37.47%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 10.23% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 5 412 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 477 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 33.

📝 Descripción y política de contenido

No se ha proporcionado la descripción del canal.

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 29 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.

14 454
Suscriptores
+2624 horas
+1347 días
+55030 días
Archivo de publicaciones
"በእሾህ መካከል እንዳለ የሱፍ አበባ፥ እንዲሁ ወዳጄ በቈነጃጅት መካከል ናት።" መኃ 2፡2 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube �
"በእሾህ መካከል እንዳለ የሱፍ አበባ፥ እንዲሁ ወዳጄ በቈነጃጅት መካከል ናት።" መኃ 2፡2 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

የ2016 ዓ.ም ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ የመጀመርያ ቀን በጉራጌ ሀገረ ስብከት። ጥቅምት 2/01/2016 ዓም (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) በጉራጌ ሀገረ ስብከት ሥር የሚገኘው የወልቂጤ ደብረ ብስራት ቅ
+5
የ2016 ዓ.ም ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ የመጀመርያ ቀን በጉራጌ ሀገረ ስብከት። ጥቅምት 2/01/2016 ዓም (የሰ/ት/ቤቶች አንድነት) በጉራጌ ሀገረ ስብከት ሥር የሚገኘው የወልቂጤ ደብረ ብስራት ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ተስፋ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት የ2016 ዓ.ም የትምህርት መርሐ ግብር የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ባዘጋጀው ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ከቅድመ መደበኛ እስከ 12ኛ ክፍል የትግበራ መመርያውን ተከትሎ በ14 ክፍሎች ከ 1000 በላይ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር መጀመሩን አስታወቀ። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የምረቃ መርሐ ግብር እንኳን ደስ አላችሁ! በ2011 ዓ.ም በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሰንበት ትምህርት ቤቶች የተዘጋጀውንና በሁሉም አኅጉረ ስብከት ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ በትግበራ
የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የምረቃ መርሐ ግብር እንኳን ደስ አላችሁ! በ2011 ዓ.ም በሀገር አቀፍ ደረጃ ለሰንበት ትምህርት ቤቶች የተዘጋጀውንና በሁሉም አኅጉረ ስብከት ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ በትግበራ ላይ ያለው ወጥ ሥርዓተ ትምህርት የመጀመርያ ፍሬውን አፍርቶ የቅድመ ሙከራ ትግበራ ከተጀመረባቸው በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ከሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች መካከል በሥርዓተ ትምህርቱ መሠረት 12ኛ ክፍል አስተምረው የደረሱ የሙከራ ትግበራ የመጀመርያው ተማሪዎች በመንበረ ፓትርያርክ በሀገር አቀፍ ደረጃም  በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ማጠቃለያ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ብፁአን ሊቃነ ጳጳሳት ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን መምህራን ተጋባዥ እንግዶች እንዲሁም የተመራቂ ቤተሰቦች በተገኙበት ጥቅምት 3 ከቀኑ 7 ሰዓት ጀምሮ  በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ባለወልድ አዳራሽ በታላቅ ድምቀት ያስመርቃል። እርሶም በእለቱ ተገኝተው የጉባኤው ተሳታፊ ይሆኑ ዘንድ ተጋብዘዋል። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

✥✥✥ ማኅሌተ ጽጌ የእመቤታችን ስደት ✥✥✥ ✥ በቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ መሠረት ከመስከረም ፳፮ እስከ ኅዳር ፮ ያለው ወቅት ዘመነ ጽጌ (የጽጌ/ የአበባ ዘመን) ይባላል፡፡ በዘመነ ጽጌ አበባዎች ያብባሉ፤ ፍሬም ያፈራሉ፤ በዚህም ወቅት ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እመቤታችንን በአበባ፣ ጌታችንን ደግሞ በፍሬ እየመሰሉ ለማመስገንና ለማወደስ በሚያስችል ምሥጢር የጌታን ስደት እንዲዘከር አድርገዋል፡፡ ✥ ማኅሌተ ጽጌ ፡ ማኅሌት የሚለው ቃል የግእዝ ቃል ሲሆን ትርጉሙም ምስጋና ማለት ነው፡፡ ጽጌ የሚለውም የግእዝ ቃል ሲሆን ትርጉሙ አበባ የፍሬ ምልክት ማለት ነው፡፡ ማኅሌት ጽጌ ተብሎ በአንድነት ሲነገር ሲተረጎም ደግሞ የኣበባ ምስጋና ማለት ነው፡፡ ይህም ድንግል ማርያም የማኅጸኗ ፍሬ ኢየሱስ ክርስቶስ በጎ መዓዛ ባላቸው አበባዎችና ፍሬዎች እየተመሰሉ የሚመሰገኑበት ምስጋና ማለት ነው፡፡ እመቤታችን እንዴት ተሰደደች ‹‹ #የኢትዮጵያ_ድንኳኖች_ሲጨነቁ_አየሁ ›› ዕንባቆም 3:7 አስቀድሞ ነቢዩ እንባቆም በተናገረው መሠረት ዓለምን ሁሉ የሚመግብ የሚያጠጣ ጌታን ይዛ ተሰደደች ተራበች ተጠማች የድንግል ትህትና እንደምን ያለ ትህትና ነው? በዛ በአስጨናቂ የስደት ወራት አንድም ቀን የሚያሳድዷትን እንዲያጠፋቸው ወደ ልጇ አለመነችም በጎን የምትለምን እናት ለእኛ ለልጆቿ ፍቅር ትሕትናን ትስጠን ዘንድ ለሰው ልጆች ሁሉ ሩሕሩሕ የምትሆን ለፍጥረት ሁሉ የምታዝን ቤዛዊተ ዓለም ቅድስት ድንግል ማርያም ልጇን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ይዛ ከዮሴፍና ከሶሎሜ ጋር ወደ ግብጽ ተሰደደች፤ ከአባቶቿ ሀገር ወጥታ 3 ዓመት ከ6 ወር በዱር በገደሉ ተንከራተተች። እመቤታችን ከየት ወደ የት ተሰደደች አስቀድሞ በአባቶቻችን ቅዱሳን ነቢያት የተነገሩት ትንቢቶች እንድ እንድፈፀሙ ከኢየሩሳሌም ወደ ግብፅ ተሰደደች ይህም አስቀድሞ ነቢዩ ኢሳይያስ በመንፈሰ እግዚአብሔር እየተቃኘ ቅድስት ድንግል ማርያም የባሕርይ አምላክ ዐማኑኤልን ይዛ ወደ ግብጽ የመሰደዷን ነገር አስቀድሞ ተገልጾለት በምዕ ፲፱፥፩ ላይ፡- ✍️ "እነሆ እግዚአብሔር በፈጣን ደመና እየበረረ ወደ ግብጽ ይመጣል፤ የግብጽም ጣዖታት በፊቱ ይርዳሉ" በማለት ከገነት የተሰደድነውን እኛን ወደ ቀደመ ርስታችን ሊመልሰን እንደመጣ አጠይቋል። ✍️ ጠላታችን ዲያብሎስን ከሰዎች ልብ አውጥቶ ለመስደድ፤ ክብር ይግባውና ወልደ እግዚአብሔር ልመናዋ ፈጥኖ በሚሰማላት "ደመና መፍጠኒት" በተባለች በእናቱ በቅድስት ድንግል ማርያም ጀርባ ታዝሎ ወደ ግብጽ የመሰደዱን ነገር አስቀድሞ ገልጾታል፡፡ ❤️ ይኸውም በቅዱስ ወንጌል እንደተጻፈ ንጉሡ ሄሮድስ ክርስቶስን ለመግደል በፈለገ ጊዜ ቅዱስ ገብርኤል ለአረጋዊዉ ለዮሴፍ በሕልሙ ተገልጾለት "ተንሥእ ወንሣእ ሕፃነ ወእሞ ወጒየይ ውስተ ብሔረ ግብጽ" (ሕፃኑንና እናቱን ይዘኽ ወደ ግብጽ ሽሽ) ባለው ጊዜ ይኽ ኢሳይያስ የተናገረው ትንቢት ሊፈጸም ምልጃዋ ፈጥኖ በሚደርስ "ደመና መፍጠኒት" በተባለች በእናቱ በቅድስት ድንግል ማርያም ጀርባ ታዝሎ ወደ ግብጽ በኼደ ጊዜ የግብጽ ጣዖታት ኹሉ እየተሰባበሩ ሲወድቁ፤ በነርሱ ዐድረው ያስቱ የነበሩ አጋንንት ኹሉ ሸሽተዋል፤ በመኾኑም በዚኽ የነገረ ማርያም አስተምህሮ እመቤታችን "ደመና መፍጠኒት" ወይም "ደመና ኢሳይያስ" ተብላ ተጠርታለች፡፡ አምላካችን እግዚአብሔር ለምን ወደ ግብፅ ሀገር ተሰደደ ✔️ሀ. ስደተ ቅዱሳንን ለመባረክ ወደ ምድረ ግብጽ ተሰደዱ የክርስትና ህይወት የመስቀል ላይ ጉዞ በመሆኑ ክርስቶስን አምነው ለተከተሉት ሁሉ በመከራና በስደት እንደሚያልፍ ጌታችን ኢየሱስ ክርሰቶስ ከዓለም ተመርጠው ለተከተሉት ደቀ መዛሙርቱ ሲያስተምር "እኔን መከተል የሚወድ ቢኖር ራሱን ይካድ መስቀሉንም ተሸክሞ ይከተለኝ" በማለት ተናገረ 《ማቴ. 16፥24》 በዚህም ቃል መሠረት ከቅዱሳን ሐዋርያት ጀምሮ የተነሡ ክርስቲያኖች በብዙ መከራ ውስጥ አለፉ በበረሃ ተሰደዱ፣ በዱር በገደሉ ተቅበዘበዙ በሰይፉ ተመተሩ፣ በድንጋይ ተወገሩ፡፡ ዛሬም ቢሆን በእምነት የተሰደድን የተጨነቅን የምንጸልየው ስደትን ከኛ በፊት በሕጻንነቱ በቀመሰ ስደትን በሚያውቅ አምላክ ፊት ነው፡፡ ✔️ለ. ጣዖታተ ግብጽን ለማጥፋትና ለመደምሰስ ወደ ምድረ ግብጽ ተሰደደ ግብጽ ከነገሥታቶቿ ጀምሮ ጣዖትን የሚያመልኩ አህዛብ ነበሩ፡፡ እነዚህ ጣዖታት ደግሞ የበሬ፣ የላም፣ የአንበሳ፣ የወፍ ምስል አስቀርጸው ያመልኩ ስለነበር ለዚህም ከሙሴና ከአሮን ጸሎት የተነሳ የግብጻውያን የእጃቸው ሥራ መጥፋቱን፣ እግዚአብሔር በናቡከደነጾር አድሮ ወደ ግብጽ መምጣቱን፣ ጣዖታትን ማጥፋቱን የተነበየበት ከመሆኑ በላይ በዘባነ ማርያም ኅዙል /በማርያም ጀርባ ታዝሎ/ በፈጣን ደመና በተመሰለች ከእመቤታችን ጋር ወደ ግብጽ ተሰዷል፡፡ በዚህ ትንቢት ላይ እንደተገለጸው ግብጽ በጣዖታት የተሞላች በመሆኗ የጌታችን ስደት በግብጽ ያሉ ጣዖታትን ለማጥፋት እንዲሆን ተጠቅሷል፡፡ ✔️ሐ . ሰው መሆኑን ለመግለጽ ወደ ምድረ ግብጽ ተሰደደ ኢየሱስ ክርስቶስ አገሩን ሳይለቅ ከሄድሮስ ዓይን መሠወር ይችል ነበር፡፡ ነገር ግን በአምላካዊ ጥበቡ ከሄሮድስ ዓይን ተሰውሮ ቢሆን ሥጋ መዋሐዱ ሰው መሆኑን አይገለጽም ነበር፡፡ በሄሮድስ ዓይን የማይታይ ከሆነ ሥጋን ሳይዋሐድ የተዋሐደ መስሎ የተገለጸ ሥጋና አጥንት የሌለው /ምትሐት/ ነው በተባለም ነበር፡፡ ከአዳም አካል አንድም ያልጎደለው ሙሉ ዳግማዊ አዳም መሆኑን እና የተዋሐደው ሥጋ የሚደማ የሚቆስል በሰይፍም ሆነ በጦር ቢወጋ ጉዳት የሚደርስበት ሰብአዊ ባሕርይ ያለው መሆኑን ለማስረዳት ስደተኛ ሆነ፡፡ ሥጋ የለበሰ ሁሉ ከጠላቱ ማምለጥ የሚችለው ከጠላቱ ፊት ዞር በማለቱ እና በመሸሹ ስለሆነ ጌታም ከጠላቱ ከሄሮድስ ለመሸሽ ሰው እንደመሆኑ ወደ ግብጽ ተሰደደ፡፡ ✔️መ . ዲያብሎስን ለማሳደድ ወደ ምድረ ግብጽ ተሰደደ አዳም ዕፀ በለስን በልቶ ከፈጣሪው ጋር ተጣልቶ ከገነት ከወጣ በኋላ የእግዚአብሔርና የሰው ግንኙነት እየራቀ ሄደ፡፡ ይህን የፈጣሪና የፍጡር መራራቅ ያመጣው ዲያብሎስ ሲሆን በፈጣሪ መራቅ ፈንታ እርሱ መቅረብ ይፈልግ ነበር፡፡ ስለሆነም ፈጣሪው ከሰው ጓሮ ወደ ወጣበት የሰው ልጅ ሳይጠራ መምጣት ወይም መቅረብ ጀመረ፡፡ ዲያብሎስ የአዳምን ልጆች ተቆጣጠራቸው፡፡ ልባቸውን በፍቅረ ጣዖት ሸፍኖ አምልኮተ እግዚአብሔርን እንዳያዩ አደረጋቸው ብዙ የአዳም ልጆችም የአግዚአብሔርን ፈቃድ ሳይሆን የሰይጣንን ፈቃድ ሲፈጽሙ ኖሩ፡፡ ጌታም "አሁን የዚህ ዓለም ገዥ ወደ ውጪ ይጣላል" 《ዮሐ. 12፥31》 በማለት ሰይጣን ዓለሙን ተቆጣጥሮት እንደነበረ ይገልጻል፡፡ እግዚአብሔር ወልድ የሰውንሥጋ በተዋሐደ ጊዜ የፈጣሪና የፍጡር ግንኙነት እንደገና ተመሠረተ፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ አገሩን ለቆ በመውጣቱ ዲያብሎስን ከተቆጣጠረው ከሰው ልቡና አስወጣው ጌታ ከሄሮድስ ፊት እየራቀ ሲሄድ ዲያብሎስም ከሰው ፊት እየራቀ ሄደ፡፡ የጌታ ስደት በተዘዋዋሪ የዲያብሎስ ስደት ሆነ ጌታ የሚቀበለው መከራ ሁሉ ዲያብሎስን በርቀት የሚመታ መሣርያ ነበር፡፡ በመጨረሻም በመስቀል ላይ የሆነው የጌታ ሞት የዲያብሎስ ሞት ሆነ፡፡ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ለዘበቅዱሳኒሁ ይሴባሕ ይእዜኒ ወዘልፈኒ ወለዓለመ ዓለም አሜን ወአሜን ለይኩን ለይኩን። አሜን !!!!!! የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

የአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ የማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተካሄደ ጥቅምት 01/02/2016 (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) የሲዳማ ሀገረ ስብከት መንበረ ጵጵስና ዋና መቀመጫ በሆነው በታላቁ ገዳም በ
+4
የአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት  ትግበራ የማስጀመሪያ መርሐ ግብር ተካሄደ ጥቅምት 01/02/2016 (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) የሲዳማ ሀገረ ስብከት መንበረ ጵጵስና ዋና መቀመጫ በሆነው በታላቁ ገዳም በሀዋሳ ደብረ ምህረት ቅዱስ ገብርኤል ገዳም  መራሔ ድኅነት ሰንበት ትምህርት ቤት አዲሱን ሥርዓተ ትምህርት ለመተግበር የማስጀመሪያ መርሐ ግብር አከናውኗል። ወጥነት ያለው ለሰንበት ትምህርት ቤቶች የተዘጋጀው አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት  ተዘጋጅቶ በሲኖዶስ ጉባኤ ከጸደቀበት ጊዜ ጀምሮ በሁሉም አህጉረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች በመተግበር ላይ ይገኛል።  እንደ መራሔ ድኅነት ሰንበት ትምህርት ቤት ደግሞ ለመጀመሪያ ጊዜ በያዝነው በ2016 ዓ .ም  የትምህርት ዓመት  ለመተግበር በዝግጅት ላይ የቆየ ሲሆን ለትግበራው የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎችን በማሟላት  መስከረም 26/ 2016 ዓ. ም በይፋ አስጀምሮ ። ትግበራው  ቅድመ መደበኛን  ጨምሮ  ከአንደኛ እስከ ስምንተኛ ክፍል ያሉ ተማሪዎችን  በአምስት ክፍል በመክፈል  እንዲሁም የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ  ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የመማር ማስተማር የሚከናወን ይሆናል ። (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) ✍️YouTube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu ✍️ FaceBook 👇 https://www.facebook.com/EOTC.GSSU ✍️Telegram 👇 https://t.me/EOTCNSSU ✍️Website👇 https://eotc-gssu.org/a/ ✍️Twitter👇 https://twitter.com/tibeb_feleg ✍️Tiktok👇 https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion

"ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፤ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና።" ማቴ 5፡10 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube 👇 h
"ስለ ጽድቅ የሚሰደዱ ብፁዓን ናቸው፤ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና።" ማቴ 5፡10 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

የዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ዮናታን እስር ሊቀ ጳጳስ ዮናታን በዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የተልኪና ብራስላቭ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ናቸው። የሀገሪቱ መንግሥት ዩክሬን የ
የዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ዮናታን እስር ሊቀ ጳጳስ ዮናታን በዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የተልኪና ብራስላቭ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ናቸው። የሀገሪቱ መንግሥት ዩክሬን የምትመራበትን ወንጀለኛ መቅጫ ሕግ አንቀጽ 109፣ 110፣ 161 እና 436 (2) በመጥቀስ በአራት ወንጀሎች ጠርጥሬያቸዋለሁ በማለት ክስ ይመሠርትባቸዋል። ጉዳዩን በአግባቡ ለመረዳት ሊቀ ጳጳሱ የተከሰሱባቸው የወንጀል ሕጉ ድንጋጌዎች ምን ምን እንደሚሉ አስቀድመን እንመለከታለን። አንቀጽ 109 በዐመጽ ለውጥ ለማምጣት ወይም ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ለማስወገድ ወይም በኃይል ሥልጣን ለመያዝ የሚፈጸሙ ተግባራት አንቀጽ 110 – የዩክሬንን ሉዓላዊ የግዛት ወሰን ማለፍ ወይም ዳር ድንበሯን ለመለወጥ አስቦ መሥራት አንቀጽ 161 – ዘርን፣ ሃይማኖትን እና ዜግነትን መሠረት በማድረግ ልዩነት መፍጠር አንቀጽ 463 (2) – የጦርነት ፕሮፖጋንዳ መንዛት (ሩሲያ በዩክሬን ላይ የፈጸመችውን የኃይል ወረራ አይቀበሉም፣ ለሕጋዊነቱ ዕውቅና ሰጥተዋል፤ የሩሲያ ወታደሮችን አድንቀዋል) የሚሉ ናቸው። ... ማንበብ ይቀጥሉ ... 👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/የዩክሬን-ኦርቶዶክስ-ቤተ-ክርስቲያን-ሊቀ/ የዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ዮናታን እስር😼 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

ቅድስት አንስጣሲያ ሰማዕት ጥቅምት 1 ዕለተ ዕረፍቷ ነው። የሰማዕቷ ረድኤት በረከት ይደርብን! https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion/video/72887458127822226
ቅድስት አንስጣሲያ ሰማዕት ጥቅምት 1 ዕለተ ዕረፍቷ ነው። የሰማዕቷ ረድኤት በረከት ይደርብን! https://www.tiktok.com/@sundayschoolunion/video/7288745812782222634?is_from_webapp=1&sender_device=pc&web_id=7288000334784579078

"አበቦች በምድር ላይ ተገለጡ፥ የዜማም ጊዜ ደረሰ፥ የቊርዬውም ቃል በምድራችን ተሰማ።" መኃ 2፡12 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️You
"አበቦች በምድር ላይ ተገለጡ፥ የዜማም ጊዜ ደረሰ፥ የቊርዬውም ቃል በምድራችን ተሰማ።" መኃ 2፡12 የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ሰናይ ሌሊት! ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

“ክርስቲያኖች መተት አደረጉብን” መቼም በየዘመኑ የማይሰማ ጉድ የለም። ከመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን አንሥቶ በየሀገሩ ይኖሩ የነበሩ አረማውያን እና አሕዛብ ክርስቲያኖችን ተከራክረው ማሸነፍ እንደማይ
“ክርስቲያኖች መተት አደረጉብን” መቼም በየዘመኑ የማይሰማ ጉድ የለም። ከመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን አንሥቶ በየሀገሩ ይኖሩ የነበሩ አረማውያን እና አሕዛብ ክርስቲያኖችን ተከራክረው ማሸነፍ እንደማይቻላቸው ሲረዱ አንድ መላ ዘይደው ነበር። ይኸውም “ክርስቲያኖች የሰው ሥጋ ይበላሉ” ብለው በማስወራት ስለክርስትና የማያውቁ የሰው ልጆች እንዲርቁ በሌላ በኩልም ሃይማኖቱ ሕገ ወጥ ተብሎ ከምድረ ገጽ እንዲጠፋ ማስደረግ ነበር። ይህም ሐዋርያት ወንጌልን ለመላው ዓለም ለማዳረስ በሚሰማሩባቸው ቦታዎች ሁሉ እንደ በግ እንዲታረዱ የሱ ምክንያት ነበረው። የአረማውያኑ አሳብ መከራውን ተሰቅቀው ሌሎች እንዲሸሿቸው ማድረግ ቢሆንም ውጤቱ ግን በተቃራኒው ነበር። ማንበብ ይቀጥሉ ... 👇👇👇👇👇 https://eotc-gssu.org/a/ክርስቲያኖች-መተት-አደረጉብን/ “ክርስቲያኖች መተት አደረጉብን” የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

"ሴቶች ሙታናቸውን በትንሣኤ ተቀበሉ፤ ሌሎችም መዳንን ሳይቀበሉ የሚበልጠውን ትንሣኤ እንዲያገኙ እስከ ሞት ድረስ ተደበደቡ፤" ዕብ 11፡35 እንኳን ለሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ በዓለ ዕረፍት በሰላም አደ
"ሴቶች ሙታናቸውን በትንሣኤ ተቀበሉ፤ ሌሎችም መዳንን ሳይቀበሉ የሚበልጠውን ትንሣኤ እንዲያገኙ እስከ ሞት ድረስ ተደበደቡ፤" ዕብ 11፡35 እንኳን ለሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ በዓለ ዕረፍት በሰላም አደረሳችሁ! የእናታችን ረድኤት በረከት አማላጅነት በዚህም ዓለም በወዲያኛውም ዓለም ይጠብቀን! የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የዩቲዩብ ቻናልን ሰብስክራይብ ያድርጉ። ✍️Youtube 👇 https://www.youtube.com/@eotc-gssu

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU - Estadísticas y analítica del canal de Telegram @eotcgssu21