ru
Feedback
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ

Открыть в Telegram

Every one comment us about the informations that we are uploading. you are also very wellcommed to give us nominations which helps us to improve our capability with regard to the concerns of the organization.

Больше
1 484
Подписчики
Нет данных24 часа
+47 дней
+2230 день
Архив постов
በአዲስ አበባ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር በከፍተኛ የህዝብ ተሳትፎና በልዩ ትኩረት እየተከናወነ ነው፡፡ በዋና ከተማዋ አዲስ አበባ የተጀመረው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ስራ በተገቢውና ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ እየተከናወነ ይገኛል። ለተከላው ስራ የሚሆኑ ዘርፈ ብዙና ለተለያዩ ጠቀሜታዎች የሚውሉ የችግኝ ዝርያዎች በበቂ ሁኔታ ተዘጋጅተዋል። እስካሁን በተከናወኑ ተመሳሳይ ስራዎች የተገኙ ጠቃሚ ተሞክሮዎችንና ልምዶችን መሰረት በማድረግ፣ የመንግስት ልዩ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ በመሆኑ ዘንድሮ የሚተከሉ ችግኞች የመጽደቅ እድላቸው ከፍተኛ እንዲሆን ተደርጎ መዘጋጀቱ ታውቋል። ይህንን ታላቅ ሀገራዊ ጥሪ ተከትሎ ሰፊው የመዲናዋ ህብረተሰብ በንቃትና በከፍተኛ ተነሳሽነት እየተሳተፈበት ይገኛል። ከተማችን አዲስ አበባም ለጉዳዩ ትልቅ ቦታ በመስጠት የሚጠበቅባትን ድርሻ በብቃት እየተወጣች ትገኛለች። ይህ ንቅናቄ ቆንጆ፣ ፅዱና አረንጓዴ አካባቢን ከመፍጠር ባለፈ፣ የችግኝ ተከላንና እንክብካቤን በህብረተሰቡ ዘንድ ወደ ዘላቂ ባህል የመቀየር ትልቅ ምዕራፍ ላይ መደረሱን በተግባር እያሳየ ነው። የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ለአካባቢ ጥበቃ ብቻ ሳይሆን፣ ህዝቡ በተግባርና በመንፈስ እርስ በእርሱ እንዲቀራረብና አንድነቱን እንዲያጠናክር ከፍተኛ ድርሻ እያበረከተ ነው። በማንኛውም ሀገር ላይ ዘላቂ ለውጥ ሊመጣ የሚችለው ህዝቦች በሀገራቸው ጉዳይና በልማት ስራዎች ላይ በባለቤትነት ስሜት ቀጥተኛ ተሳታፊ መሆን ሲችሉ ብቻ እንደሆነ በተጨባጭ እየታየበት ያለ ሂደት ነው። ይህ የአረንጓዴ ልማት ንቅናቄ አዲሱ ትውልድ በሀገሩ ጉዳይ ላይ ንቁ፣ ተቆርቋሪና ግንባር ቀደም ተሳታፊ እንዲሆን በማድረግ ረገድ ያለው ሚና ከፍተኛ ነው። ወጣቱ ትውልድ ዛሬ በሚያኖረው አረንጓዴ አሻራ የነገዋን ውብና ለኑሮ ምቹ ሀገር የመገንባት ታሪካዊ ሀላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል።

በመዲናዋ የተጀመረዉ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር እንደቀጠለ ነዉ፡፡ በከተማችን አዲስ አበባ የተጀመረዉ የ2018/19 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ የክረምት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በሁሉም ክ/ከተሞች
+3
በመዲናዋ የተጀመረዉ የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር እንደቀጠለ ነዉ፡፡ በከተማችን አዲስ አበባ የተጀመረዉ የ2018/19 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ የክረምት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በሁሉም ክ/ከተሞች የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን ባሳተፈ መልኩ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ የዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር እንደ ሀገር “ተስፋን እንትከል” በሚል መርህ ቃል በክቡር ጠ/ሚኒስትር አብይ አህመድ ከተበሰረ በኋላ መዲናችን አዲስ አበባም የክረምት የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩን የተለያዩ የመዲናዋ የህብረተሰብ ክፍሎችን በንቅናቄ መልክ አስተባብራ በማሳተፍ እየተገበረች ትገኛለች፡፡ በዘንድሮ የአረንጓዴ አሻራ የክረምት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ የሆኑ ችግኞች የመዲናዋን የአየር ንብረት ሁኔታ ግምት ዉስጥ ባስገባ መልኩ እየተተከሉ ሲሆን በተለይም ለሀገር በቀል ዛፎች ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራበት ይገኛል፡፡ በሌላ በኩል የችግኞቹ ስብጥር የጥላ፤ለምግብነት የሚዉሉ የፍራፍሬ፤ የዉበት፤ለመድኃኒትነትና ለቅመማ ቅመም አገልግሎት የሚዉሉ የችግኝ ዓይነቶች ታሳቢ ተደርገዋል፡፡ መዲናዋ የአለም አቀፍ የአረንጓዴ ሽፋን ስታንዳርድ ላይ ለመድረስ እየተቃረበች የምትገኝ ሲሆን በሚቀጥሉት ጥቂት ዓመታት አሁን ካለችበት 24 በመቶ ወደ 30 በመቶ የአረንጓዴ ሽፋን ግቧ ለመድረስ ደፋ ቀና እያለች ትገኛለች፡፡

የአረንጓዴ ዐሻራ ሳይንሳዊ እውነታዎች ***** የደን ሽፋንን ማሳደግ የውኃን መኖር፣ ጥራትና ተደራሽነት በከፍተኛ ደረጃ እንደሚያሻሽል በርካታ ሀገራዊና ዓለም አቀፋዊ ጥናቶች ያመክታሉ። በኢትዮጵያ በስፋት እየተተገበረ ያለው የአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ-ግብር እና የችግኝ ተከላ ሥራዎችም ከዘላቂ የውኃ ሀብት ልማትና ጥበቃ ጋር ቀጥተኛና ሳይንሳዊ ቁርኝት እንዳላቸው የዘርፉ ባለሙያዎች ያስረዳሉ። ከተለያዩ አካባቢያዊና ሃይድሮሎጂያዊ ጥናቶች በመነሳት፣ ችግኝ መትከል ለዘላቂ የውኃ ሀብት ጥበቃ ያለውን ከፍተኛ ፋይዳ እንደሚከተለው ማጠቃለል ይቻላል፡- 1. የከርሰ-ምድር ውኃን መሙላትና ማከማቸት የሳይንስ እውነታዎች እንደሚያመለክቱት፤ የዛፎች ሥሮች የአፈርን መዋቅር በማላላትና ቀዳዳዎችን በመፍጠር የዝናብ ውኃ በቀላሉ ወደ መሬት ውስጥ እንዲሰርግ ያደርጋሉ። በዚህ ሂደት ዝናብ በሚዘንብበት ወቅት ውኃው ከመሬት ወለል ላይ በጎርፍ መልክ ፈስሶ ከመባከን ይልቅ ወደ ከርሰ-ምድር በመግባት ተፈጥሯዊ የውኃ ማጠራቀሚያዎችን ይሞላል። ይህም ምንጮችና ጉድጓዶች በበጋ ወቅት እንኳ ሳይደርቁ ቀጣይነት ያለው ውኃ እንዲያመነጩ ያደርጋል። 2. ለአነስተኛ አርሶ አደሮች የውኃ አማራጭ መፍጠር በኢትዮጵያ እየተከናወነ ያለው የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር፣ በዝናብ ላይ ብቻ ጥገኛ የነበረውን ባህላዊ የግብርና ሥራ በመቀየር ውኃን አቁሮ በዓመት ከሁለት እስከ ሦስት ጊዜ ለማምረት የሚያስችሉ ሁኔታዎችን እየፈጠረ ይገኛል። በተለይም በአነስተኛ ማሳ ላይ ለሚከናወኑ የእርሻ ተግባራት አርሶ አደሮች የውኃ አማራጮችን እንዲያገኙ፣ በአቀበታማ መሬቶች ላይ ዛፍ መትከልና መንከባከብ ውኃን አስቀርቶ ለመጠቀም ሁነኛ መፍትሔ እንደሆነ ባለሙያዎች ይመክራሉ። 3. የጎርፍ አደጋንና የገጽታ ፍሰትን መቀነስ የዛፎች ቅጠሎችና ቅርንጫፎች የዝናብ ጠብታዎች በቀጥታ መሬት ላይ የሚያርፉበትን ኃይል ይቀንሳሉ። የደረቁ ቅጠሎችና ዕፅዋት ደግሞ በምድር ላይ የሚፈሰውን ውኃ ፍጥነት ይገቱታል። ይህም ከፍተኛ የጎርፍ አደጋን ከመከላከል ባለፈ፣ ውኃው ረጋ ብሎ ወደ መሬት እንዲሰረጽ ጊዜ ይሰጠዋል። ይህ ሂደት የወንዞችን መደበኛ የውኃ ፍሰት መጠን ዓመቱን ሙሉ የተመጣጠነ እንዲሆን ያደርጋል። 4. የአፈር መሸርሸርን መከላከልና የግድቦችን ዕድሜ ማራዘም የዛፎች ሥሮች አፈርን አጥብቀው የመያዝ ተፈጥሯዊ ባሕርይ አላቸው። ይህም በዝናብና በጎርፍ ምክንያት የሚመጣን የአፈር መሸርሸር በከፍተኛ ሁኔታ ይቀንሳል። በዚህም ወደ ወንዞች፣ ሐይቆችና ሰው ሠራሽ የውኃ ግድቦች የሚገባውን የደለል መጠን ይገታል። ይህም እንደ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብና ሌሎች የሃይድሮ-ኤሌክትሪክና የመስኖ ግድቦች የውኃ የመያዝ አቅማቸው እንዳይቀንስና የዕድሜ ዘመናቸው እንዲረዝም ያደርጋል። 5. ተፈጥሯዊ የውኃ ማጣሪያ የደን ሥነ-ምህዳር እንደ ተፈጥሯዊ የውኃ ማጣሪያ ያገለግላል። በጎርፍ አማካኝነት የሚመጡ የተለያዩ ኬሚካሎችን፣ አፈርና ቆሻሻዎችን የዛፍ ሥሮችና የአፈር ውስጥ ተሕዋሲያን በመምጠጥና በማጥለል ወደ ወንዞችና ሐይቆች የሚገባውን ውኃ ንጹሕ ያደርጉታል። ይህ አሠራር ለመጠጥ ውኃ የሚወጣውን የማጣሪያ ወጪ በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሳል። 6. የአካባቢን እርጥበትና የዝናብ ዑደትን መጠበቅ ዛፎች ከመሬት ውስጥ የሳቡትን ውኃ በቅጠሎቻቸው አማካኝነት ወደ አየር ያስወጣሉ፤ ይህ ሳይንሳዊ ሂደት ትራንስፒሬሽን ይባላል። ይህ ሂደት በአየር ላይ ያለውን እርጥበት በመጨመር የደመና ምስረታንና የአካባቢን የዝናብ ዑደት ያፋጥናል። ደኖች የራሳቸውን ዝናብ የመሳብና የአየር ንብረትን የማቀዝቀዝ ከፍተኛ ተፈጥሯዊ አቅም አላቸው። በአጠቃላይ የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር የደን ሽፋንን በማሳደግ ረገድ የሚጫወተው ሚና፣ የውኃ ሀብትን ከተፈጥሯዊ ምንጩ (ከዝናብና ከከርሰ-ምድር) ጀምሮ እስከ መጨረሻው መዳረሻ (ግድቦችና ወንዞች) ድረስ በዘላቂነት ለመጠበቅና ለማስተዳደር የሚደገፍ ቀዳሚ ሳይንሳዊ መፍትሔ መሆኑን ጥናቶች ያረጋግጣሉ።

የመዲናዋ የአረንጓዴ መሰረተ ልማት ስራዎችን በቴክኖሎጂ ለማዘመን የሚያስችል ስልጠና ተሰጠ፡፡ የከተማ ዉበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ጋር በመተባበር የመዲናዋን የአረንጓዴ መሰ
+3
የመዲናዋ የአረንጓዴ መሰረተ ልማት ስራዎችን በቴክኖሎጂ ለማዘመን የሚያስችል ስልጠና ተሰጠ፡፡ የከተማ ዉበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ጋር በመተባበር የመዲናዋን የአረንጓዴ መሰረተ ልማት ስራዎች ወቅቱን በዋጀ ቴክኖሎጂ ለማዘመን የሚያስችል  ስልጠና ከማዕከልና ከክ/ከተማ ለተዉጣጡ የዘርፉ ባለሙያዎች  ሰጥቷል፡፡ በስልጠናዉ ማመስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የከተማ  ዉበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታደለ አለሙ “በበላይነት የምንመራዉን የአረንጓዴ መሰረተ ልማት ስራዎችን ዘመኑ በደረሰበት ቴክኖሎጂ አስደግፈን በማላቅ ቀጣይነቱን ማረጋገጥ ይኖርብናል ያሉ ሲሆን ለተግባራዊነቱም ባለሙያዉ ከቴክኖሎጂ አጠቃቀሙ ጋር በተገቢዉ መንገድ መተዋወቅ አለበት” ብለዋል፡፡ በአዲስ መልክ የለማዉ ቴክኖሎጂ የመዲናዋን የአረንጓዴ መሰረተ ልማት ስራዎችን ልማት፤እንክብካቤ፤ቁጥጥርና አገልግሎት አሰጣጥን ለማቀላጠፍ እና ለማዘመን እንዲሁም የአረንጓዴ መሰረተ ልማቶችን በተሻለ መንገድ ለማስተዳደር ከማስቻሉም በላይ ኃላፊነትን በአግባቡ ባለመወጣት ለሚከሰተዉ ክፍተት ተጠያቂነትንም ያሰፍናል ተብሏል፡፡ ቴክኖሎጂዉ የወረቀት ስራን ከመቀነስ ባለፈ የሀብትን ፤የጉልበትንና የጊዜን ብክነት ይቀንሳል የተባለ ሲሆን ወደ ተክኖሎጂዉ የምናስገባዉን መረጃ ትክክለኛነት ማረጋገጥ እንደሚገባና በየጊዜዉ ተከታትለን ለዉጦችን በማድረግ ማዘመን (update) ማድረግ እንደሚገባ ተገልጿል፡፡ በመጨረሻም የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ታደለ አለሙ የዘርፉ ባለሙያዎች የቴክኖሎጂ አጠቃቀሙን በተገቢዉ መንገድ እስኪረዱት ድረስ ልምምድ ማድረግ እንዳለባቸዉ ያሳሰቡ ሲሆን ቴክኖሎጂዉ በግልም የምንሰራቸዉን ስራዎች ያቀላጥፍልናል ብለዋል፡፡

ቢሮዉ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ገመገመ፡፡ የከተማ ዉበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት የቢሮዉ አመራሮችና ሰራተኞች በተገኙበት ገምግሟል፡፡ በዓመቱ ታቅደዉ የተከናወኑ አበይት ተግባራት ሪፖርት የቀረበ ሲሆን በሪፖርቱ ታቅደዉ የተተገበሩ ጠንካራ ጎኖች፤ የተገኙ ዉጤቶች፤የታዩ ክፍቶች፤የተወሰዱ መፍትሄዎች እና የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን የዳሰሰ ሪፖርት በቢሮዉ የዕ/በ/ዝ/ ግምገማ ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ደግሰዉ መንግስቱ ቀርቧል፡፡ በሪፖርቱ የ2017/18 የአረንጓዴ አሻራ የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በቅንጅት በመሰራቱ ከዕቅድ በላይ ማሳካት መቻሉ፤በኮሪደር ልማቱ የስራ ባህልን በመቀየር 24/7 በተሰራዉ ስራ አመርቂ ዉጤት መገኘቱ፤ ምቹ የስራ አካባቢን በመፍጠር አገልግሎት አሰጣጥ ማቀላጠፍ መቻሉ፤የቴክኖሎጂ አጠቃቀም ላይ ጥሩ ጅምሮች መኖራቸዉ፤ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ መስራት መቻሉ፤በሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን መረጃዎችን በአግባቡ ለህ/ሰቡ ተደራሽ ማድረግ መቻሉ፤ የበጎ አድራጎት እና ኢንሸቲቪ ሥራዎች አበረታች መሆናቸዉ፤ህብረተሰቡን የልማቱ አካል በማድረግ ረገድ ዉጤታ ስራዎች መሰራታቸዉ፤በወንዝና ወንዝ ዳርቻ ስራዎች አበረታች ስራዎች መሰራታቸዉ፤በዘላቂ ማረፊያ ጥሩ ለዉጥ መታየቱ በሪፖርቱ ከተዳሰሱ ጠንካራ ጎኖች መካከል ናቸዉ፡፡ በሌላ በኩል የተወሰኑ ስራዎች በተቀመጠላቸዉ የጊዜ ሰሌዳ አለመከናወን፤ለቀዳማይ ልጅነት የተለዩ ቦታዎች መሬት ባንክ በመግባታቸዉ ስራዉን በአግባቡ ለመጀመር መቸገር፤ ለመስክ ስራዎች ተሽከርካሪ እጥረት፤ የበጀት እጥረት፤የአረንጓዴ ቦታዎች የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ በሚጠየቀዉ ልክ አለመዉጣት ከነበሩ ተግዳሮቶች መካከል የተጠቀሱ ናቸዉ፡፡ በቀጣይነት የእንክብካቤ ስራዎችን ማጠናከር፤ህብረተሰቡ የልማቱ አካል እንዲሆን ይበልጥ መስራት፤ በቀጣይ በ2018/19 የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መረሃ ግብር ስራዎችን አጠናክሮ ማሰቀጠል፤የለሙ አረንጓዴ ቦታዎች፤የወንዝ ዳርቻ እንክብካቤና ዘላቂነት ማረጋገጥ፤በኮሪደር ስራ የተጀመሩትን አጠናከሮ ማስቀጠል፤ የአረንጓዴ ልማት ቦታዎችን የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ማዉጣት እና ኮፕ 32ን በተመለከተ የቅደመ ዝግጀት ስራዎችን አጠናክሮ ማሰቀጠል ሊሆን እንደሚገባ በሪፖርቱ ተመላክተዋል፡፡ ከተሳታፊ ሰራተኞች የተለያዩ ጥቄዎችና አስተያየቶች የተሰነዘሩ ሲሆን ማብራሪያ  ለሚሹ ጉዳዮች የቢሮዉ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፀሐይ ጌታሁን እና የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ  ታደለ አለሙ ከመድረክ ምላሽና ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን የቢሮዉ ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፀሐይ ጌታሁን የቀጣይ የስራ አቅጣጫ  በመስጠት መድረኩን አጠቃልለዋል ፡፡

ወቅቱን የጠበቀ የስነ-ተዋልዶ ስልጠና መሰጠቱ አምራች ና ጤናማ የሆነ ሰራተኛ በመገንባት ረገድ ድርሻው የጎላ መሆኑ ተገለፀ። የከተማ ዉበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ከአዲስ አበባ ከተማ ጤና ቢሮ ጋር በ
+6
ወቅቱን የጠበቀ የስነ-ተዋልዶ ስልጠና መሰጠቱ አምራች ና ጤናማ የሆነ ሰራተኛ በመገንባት ረገድ ድርሻው የጎላ መሆኑ ተገለፀ። የከተማ ዉበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ ከአዲስ አበባ ከተማ ጤና ቢሮ ጋር በመተባበር ለሰራተኞቹ በኤች አይ ቪ ኤድስ ሜይንስትሪሚንግ ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል፡፡ በበስልጠናዉ የኤች አይ ቪ ኤድስ ዋና ዋና መተላለፊያ እና መከላከያ መንገዶች ላይ ሰፋ ያለ ገለፃ የተደረገ ሲሆን በተለይም ባህሪያዊ ፤ባዮሎጂካል እና ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ምክንያቶች ለበሽታዉ መስፋፋት ዋነኞቹ መሆናቸዉን ከስልጠናዉ መረዳት ተችሏል፡፡ በግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዉ የኤች አይ ቪ ኤድስ ስርጭት በአለም አቀፍ ፤በሀገር፤ እና በከተማ ደረጃ ያለበት አጠቃላይ ሁኔታ የተዳሰሰ ሲሆን በተለይ በአሁኑ ወቅት በከተማችን አዲስ አበባ ስርጭቱ ከሌሎች ክልሎች አንፃር ሲታይ ከፍተኛ መሆኑ በመረጃ በተደገፈ ዳታ ተመላክቷል፡፡ ከግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዉ መረዳት እንደተቻለዉ የኤች አይ ቪ ኤድስ ስርጭት ምንም እንኳ ስለበሽታዉ ከተሜዉ ማህበረሰብ የተሻለ ግብዛቤ ይኖረዋል ተብሎ ቢገመትም ስርጭቱ ግን በተቃራኒዉ በከተሞቸ በስፋት እንደሚታይ ከገለፃዉ መረዳት ተችሏል፡፡ በተለይ መዋቅራዊና ማህበራዊ የመከላከያ ስልቶችን በግለሰብ ፤ በቤተሰብ፤በማህበረሰብ እና በተቋም ደረጃ ተግባራዊ በማድረግ ወቅቱን የጠበቀ የስነ-ተዋልዶ ስልጠና መሰጠቱ አምራች ና ጤናማ የሆነ ሰራተኛ በመገንባት ረገድ ድርሻው የጎላ መሆኑ ተገልጿል። ከተሳታፊ ሰራተኞች የተለያዩ ሃሳቦችና ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን አሰልጣኙ ለተነሱት ጥያቄዎች በቂ ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡

"ተስፋን እንትከል!" በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ የ2018 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ንቅናቄ ተካሄደ። በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የ2018/2019 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ንቅናቄ በዛሬው ተካሂዷል። በዚህ መርሃ ግብር ላይ የከተማ፣ የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራሮች፣ የሃይማኖት አባቶች፣ የጸጥታ አካላት፣የህክምና ባለሞያዎች፣ የተፎካካሪ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ተወካዮች እንዲሁም ከሁሉም ወረዳዎች የተወጣጡ በርካታ የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል። በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ቴዎድሮስ ወ/ሚካኤል እንዳሉት "ዛሬ በክፍለ ከተማችን ወረዳ 06 'ጦጣ ገደል' ተብሎ በሚጠራው ስፍራ የተገኘነው 'ተስፋን እንትከል' በሚል መሪ ቃል የነገዋን ውብ፣ ጽዱ እና አረንጓዴ ኮልፌ ቀራኒዮን ለመገንባት ቃል ኪዳናችንን ለማደስ ነው" ሲሉ ገልጸዋል። ዋና ስራ አስፈፃሚው አክለውም የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ ባለፉት ዓመታት በተግባር ታይቶ አገርን የቀየረ ድንቅ ታሪክ መሆኑን ጠቅሰው፤ በሁሉም ኢትዮጵያውያን የተቀናጀ ርብርብ 48 ቢሊዮን ችግኞችን በመትከል ዓለምን ያስደመመ ታሪክ መሰራቱን አብራርተዋል። እንደ አዲስ አበባ ከተማም ባለፉት ዓመታት 90 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል፣ ቀደም ሲል እጅግ አሳሳቢ የነበረውን የከተማዋን የአረንጓዴ ሽፋን ማሳደግ መቻሉን ጠቁመዋል። የአዲስ አበባ ከተማ የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ቢሮ አማካሪ አቶ ነጋሽ አረጋ እንደገለጹት ከ8 ዓመታት በፊት 2.8 በመቶ ብቻ የነበረው የአዲስ አበባ ከተማ የአረንጓዴ ሽፋን፣ በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በተጀመረው የንቅናቄ ኢኒሼቲቭ እና በአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ አማካኝነት በአሁኑ ወቅት 24 በመቶ መድረስ መቻሉን ገልፀዉ ዛሬ የሚተከለው ችግኝ ለሀገራችን ምግብ፣ ተስፋና ማረፊያ መሆኑን ተናግረዋል። የክፍለ ከተማው የከተማ ውበትና አረንጓዴ ልማት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዳኛቸው አበበ በበኩላቸው የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ ከተጀመረ ወዲህ የችግኝ ተከላ ባህል መሆኑን አንስተዋል። ባለፉት 7 ተከታታይ ዓመታት በክፍለ ከተማው ብቻ 8.73 ሚሊዮን ችግኞች መተከሉን የገለፁት አቶ ዳኛቸው በዚህም የክፍለ ከተማው የአረንጓዴ ሽፋን እጅግ ዝቅተኛ ከነበረበት 2.8 በመቶ ወደ 22 በመቶ ማሳደግ ተችሏል ብለዋል። የዘንድሮው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር "ተስፋን እንትከል!" በሚል መሪ ቃል የተጀመረ ንቅናቄ በክፍለ ከተማችን 330 ሺህ 816 (ሶስት መቶ ሰላሳ ሺህ ስምንት መቶ አስራ ስድስት) ችግኞች የሚተከሉ ሲሆን በአካባቢ ጥበቃ፣ በምግብ ዋስትና ማረጋገጥና በከተማ ግብርና ላይ የጎላ አስተዋፅኦ ባላቸው የችግኝ ዓይነቶች ላይ ልዩ ትኩረት ተደርጎ እየተሰራም እንደሚገኝ ተገልጿል።

ሰዉ አጠፋዉ፤ ሰዉ አለማዉ!! ፈጣሪ የሰጠንን ቀበና “ሰዉ “ አጠፋዉ ፤ ይህ የተፈጥሮ ስጦታ መጥፋት ቁጭት ያደረበት “ሰዉ “ ደግሞ ቀበናን ዳግም እንደ አዲስ እንዲወለድ አደረገዉ። የቀበና ወንዝ ለ
+2
ሰዉ አጠፋዉ፤ ሰዉ አለማዉ!! ፈጣሪ የሰጠንን ቀበና “ሰዉ “ አጠፋዉ ፤ ይህ የተፈጥሮ ስጦታ መጥፋት ቁጭት ያደረበት “ሰዉ “ ደግሞ ቀበናን ዳግም እንደ አዲስ እንዲወለድ አደረገዉ። የቀበና ወንዝ ለዘመናት በዘፈን እና በትዝታ ብቻ ስሙ ሲነሳና ሲወደስ ኖሮ ዛሬ ግን ዳግም እንዲወለድ አድርጐ አለማዉ!! አርቲስት ፀሀዬ ዮሀንስ “ቢሻን ቀበና” እያለ ብዙዎች እየዋኙ ያደጉበትን የልጅነት ትዝታን ሲቀሰቅስ ፣የክብር ዶ/ር አርቲስት አሊ ቢራ “ቢሻን አዲስ አበባ “ እያለ ሲያደናንቅ በዘመናት ውስጥ ግን ትዝታን ብቻ ተሸክሞ የወንዙ ተፈጥሮዊ ማንነት ጠፍቶ ፣የፍሳሽ መዉረጃና የቆሻሻ መጣያ ሆኖ፣ ጠረኑ አላስጠጋ ብሎ ተረስቶ የኖረ ወንዝ ነበር ። እነሆ እነዚህ የብክለት ፣ የበሽታ ምንጭና የቆሻሻ ማጠራቀሚያ የነበሩትን ወንዞቻችንን ዛሬ ላይ በትጋት እና በላብ እየታከሙ፣ ለነዋሪው ተስፋን ሀሴትን የሚለግሱ የደስታ ምንጭ እየሆኑ ነው፡፡ በአጭር ጊዜ የተገነባው ይህ ድንቅ ፕሮጀክት፣ ከሌሎች የከተማዋ ታላላቅ ፕሮጀክቶች ጋር ተዳምሮ አዲስ አበባን የውበት ማማ አድርጓታል። ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!