𝑚𝑢𝑠𝑡𝑒𝑓𝑎 A𝑝𝑜𝑙𝑜𝖌𝑒𝑡𝑖𝑐𝑠 🥷
Open in Telegram
እዚህ ቻናል ላይ እስልምና ላይ ለሚነሱ እያንዳንዱ ጥያቄዎች እና ብዥታዎች በማምጣት በጠንካራ ማስረጃ መልስ እንሰጥበታለን ኢንሻ አላህ☪️ስለማንኛውም ሀሳብ አስቴት በዚ➢ @mustefa_1_2 ያካፍሉን
Show more7 927
Subscribers
-1124 hours
-467 days
-11930 days
Posts Archive
so ሰላም ናቹ አንድ ቻናል አለ መግዛት የምፈልጉ አናግሩኝ ወደ 17k subscribers ያለው መግዛት የምፈልጉ በዚ➾@mustefa_1_2 አናግሩኝ
መልሱ ✅በ3 ይከፈላሉ
✅«የቂያማ ምልክቶችና አይነቶች
የቂያማ ምልክቶች ሲባል ቂያማ ከመምጣቱ በፊት መቃረቡን የሚጠቁሙ ክስተቶች ማለት ነው፡፡
✅«አላህ እንዲህ ይላል‼️
{ فَهَلْ يَنْظُرُونَ إِلَّا السَّاعَةَ أَنْ تَأْتِيَهُمْ بَغْتَةً فَقَدْ جَاءَ أَشْرَاطُهَا } (محمد : 18)
‹‹ሰዓቲቱንም ድንገት የምትመጣባቸው መኾንዋን እንጅ ይጠባበቃሉን? ምልክቶችዋም በእርግጥ መጥተወል፡፡›› ሙሐመድ 18
✅«የቂያማ ምልክቶች በሶስት ይከፈላሉ‼️
➊ .ራቅ ያሉ ምልክቶችና ተፈፅመው ያበቁ ናቸው፡፡
በዚህ ክፍል ውስጥ ከሚካተሉ ምልክቶች አንዱ የነብዩﷺ መላክ ነው፡፡ አነስ ኢብን ማሊክ በአስተላለፉት ሀዲስ ነብዩﷺ የመሀልና የአመልካች ጣታቸውን በማያያዝ እኔና ቂያማ እንዲህ ተቀራርበን ተላኩ፡፡” ብለዋል
ከዚህ ክፍል ውስጥ የጨረቃ መሰንጠቅ ይጠቀሳል፡፡
#አላህ እንዲህ ይላል
{ اقْتَرَبَتِ السَّاعَةُ وَانْشَقَّ الْقَمَرُ } (القمر : 1)
«ሰዓቲቱ (የትንሣኤ ቀን) ተቃረበች፤ ጨረቃም ተገመሰ፡፡›› 📚አል ቀመር 1
ሂጃዝ ውስጥ የተቀሰቀሰ እሳት ነበልባል ቡስራ ድረስ መታየቱ፡፡ ቡኻሪና ሙስሊም ከአቡ ሑረይራ በአስተላለፉት ሀዲስ ነብዩﷺ እንዲህ ብለዋል
« لا تقوم الساعة حتى تخرج نار من أرض الحجاز تضيء أعناق الإبل ببصرى »
«ቂያማ ከመቆሙ በፊት ሂጃዝ ላይ እሳት ተነስቶ ቡስራ ያሉ ግመሎች አንገት ላይ የነበልባሉ ነፀብራቅ ይታያል፡፡”
📚ቡኻሪ 7118 ሙስሊም 29ዐ2
ነብዩﷺ ባሉት መሰረት ይህ እሳት በጁማደል አኺር ወር በስድስት መቶ ሃምሳ አራተኛ የሒጅራ አመት በመዲና በስተምስራቅ አካባቢ ተነስቶ ከፍተኛ ንዳድ የተፈጠረ ሲሆን የሻም ህዝቦች የእሳቱን ብርሃን እንደተመለከተ እንዲሁም የቡስራ ህዝብ በእሳቱ ብርሃን የግመሎችን አንገት እንዳዩ ታሪክ ዘግቧል፡፡
➋ . መካከለኛ የቂያማ ምልክቶች ሲሆን የተከሰተ ወደፊት የሚከተቱ ምልክቶች ናቸው፡፡ ከነዚህ ውስጥ ለምሳሌ፡-
የሴት ባሪያ ጌታዋን መውለድና የታረዙ ድሆች በፈጣን ጊዜ ውስጥ ለግንባታ መፎካከር፡፡
📚ሙስሊም በዘገቡት የጅብሪል ሀዲስ
« قال فأخبرني عن الساعة ؟ قال : ما المسئول عنها بأعلم من السائل . قال : فأخبرني عن أماراتها ، قال : أن تلد الأمة ربتها ، وأن ترى الحفاة العراة العالة رعاء الشاء يتطاولون في البنيان »صحيح مسلم برقم (8)
«ጅብሪል ለነብዩﷺ ቂያማ እለት መች እንደሚመ ንገርኝ ሲላቸው ተጠያቂ ከጠያቂ ይበልጥ ስለዚህ አያውቅም አሉት በማስከተል እንግዲያውስ ስለምልክቶቿ ንግሩኝ ሲላቸው እንዲህ ሲሉ ነገሩት ሴት ባሪያ ጌታዋን መውለድ፣ ጫማ ያልነበረው የታረዘ ድሃ እረኛ የነበሩ ለግንባታ መሽቀዳደም፡፡”
📚(ሙስሊም 8)
ነቢይ ነኝ የሚሉ ሰላሳ ውሸታሞች መምጣት፡፡ አቡሑረይራ በአስተላለፉት ሀዲስ ነብዩﷺ እንዲህ ብለዋል
« لا تقوم الساعة حتى يبعث دجالون كذابون قريبا من ثلاثين كلهم يزعم أنه رسول الله » رواه البخاري برقم (3609)
«ቂያማ ከመከሰቱ በፊት ወደሰላሳ የሚሆኑ ውሸታሞች ነቢይ ነኝ በማለት ብቅ ይላሉ፡፡” (ቡኻሪ 36ዐ9)
➌ .ታላላቅ ምልክቶች
እነዚህ ምልክቶች መከሰታቸውን ተከትሎ ቂያማ ይቆማል።
#ሀዛ ወላሁ አዕለም
ተሳተፉፉ የሁለቱም ጥያቄ መልስ ነገ ይጠብቁኝ በተብራራ ሁኔታ ከቁርአን ከሀዲስ የተብራራ መልስ ይኖረዋል ኢሻአላህ ተሳተፉ
አፍቅሬ ተከዳሁ፣ አምኜ ተገፋሁ፣ ተስፋ አርጌ አጣሁ አትበል፡፡ ከሱ ከምትጣበቂ ከአላህ ተጣበቂ፡፡ ተወኝ፣ ረሳኝ፣ ጣለኝ… አትበሉ፡፡ አላህ ብቻ አይጣላችሁ፡፡ እሱ ካልጣለን ዓለም ሁሉ ቢጥለን ምንም አንሆንም።ከሰው ሳይሆን ከአላህ ብዙ ጠብቁ፡፡ ከፈጠራችሁ እንጂ ከሰው ብዙ ተስፋ አታድርጉ፡፡ አላህ ከሰውም ከሀብትም ብዙ ብዙ አለው፡፡
በተከታታይ ስናየው የነበረው እርእስ ዛሬም ስንቀጥል ዛሬ የምንመለከተው➾የመጨረሻው ነብይ መሆናቸው ኢሻአላህ ወደ ብሀላ ይለቀቃል ኢሻአላህ
አረቦች እንዲህ ይላሉ።
" الصمت أبلغ من الكلام " «አንዳንዴ ዝምታ ከንግግር ይበልጣል»
" الصمت زينة للعالم وستر للجاهل" ዝምታ የጥበበኛ ሰው ጌጥ፣ የሰነፍ ሰው ደግሞ መከለያ (መሸሸጊያ) ነው።ስለዚህ በነገሮች ላይ ፊትናን ላለመጫር እስከ ግዜው ዝምታን መርጠናል።
