Emmaus - ኤማሁስ
Open in Telegram
ይህ የኤማሁስ ሚዲያ እና ፕሬስ ቻናል ነው። በዚህ ቻናል ኦርቶዶክሳዊ ነገረ መለኮት ላይ ትኩረት ያደረጉ ርእሰ ጉዳዮች የሚቀርቡበት ሲሆን ከተከታታዮቻችን የሚመጡ ጥይቄዎችንም በዋናነት የምንቀበልበት ነው።
Show more3 006
Subscribers
+324 hours
+277 days
+18030 days
Posts Archive
3 006
ጌታን ሲከተሉት የነበሩ አይሁድ "ከሰማይ የወረደ እውነተኛ የሕይወት እንጀራ እኔ ነኝ" የሚለውን የጌታ ቃል በሁለት ምክንያት ለመቀበል ተቸግረው ነበር። ለጊዜው ፍላጎታቸው ምድራዊውን ምግብ አበርክቶ የሚያበላቸው ሰው ነው፡፡ ሁለተኛው እንዴት ሥጋውን ለመብልነት ሊሰጣቸው እንደሚችል ማሰብ አልቻሉም። በዚህ ትምህርቱ " እንዴት ልንከተው እንችላለን" ብለውም ጥለውት ሄዱ። ይኼንን የወንጌል ክፍል ለማየት ሞክረናል። አድምጡት
https://youtu.be/Dt2XogkyzFk?si=m15uIes48_xP5kNO
3 006
ከክርስትና በፊት የነበረው አረማዊው ዓለም (pagan world) ድሆች ፣ ሕሙማን እና አካል ጉዳተኞች በአማልክቱ የተረገሙ እንደሆኑና ርኅራኄ እንደማይገባቸው ያምን ነበር። ለእነዚህ የተገለሉ የማኅበረሰብ ክፍሎች መራራት ለአረማዊው ዐለም እንግዳ የሆነ፣ የክርስትና ግን መሠረታዊ ተፈጥሮ ነበር። ክርስቲያኖችም ከአረማውያኑ የሚለዩበት ልዩ መታወቂያቸው ይህ ለተቸገሩትና ልዩ ልዩ ደዌ ለጸናባቸው ሰዎች የሚያሳዩት ፍቅር ርኅራኄና እንክብካቤ ነበር። በጥንታዊቷ ቤተክርስቲያን ለነበሩ ክርስቲያኖች ምጽዋት እንደ አማራጭ በጎ ስራ (virtue) የሚደረግ አልነበረም። ይልቁንም ክርስቲያን ያደረጋቸው መሠረታዊ ማንነታቸው እንጂ። በዛሬው ቆይታችን ይህንን የጥንቷ ቤተክርስቲያን ስለነዳያን የነበራትን አቢዮታዊ አቋም ፣ ዛሬ ካለው መረዳትና ልምምድ ጋር በስፋት ለማነጻጸር ሞክረናል። መልካም ቆይታ።
https://youtu.be/cy9mYo1cFw0?si=3FKQyHXn4yO_Nnvj
3 006
የ ኢንስታግራም ገጻችን
https://www.instagram.com/emmaus_media_?igsh=cWJ3M3Q1ejZieXNo&igsi=cWJ3M3Q1ejZieXNo
የቲክቶክ ገጻችን
https://www.tiktok.com/@emmaus054/video/7676170894560988437?_r=1&u_code=ekg2c7m7e717c9&preview_pb=0&sharer_language=en&_d=eifh2gmaah41ce&share_item_id=7676170894560988437&source=h5_m×tamp=1787250284&user_id=7510151602943329336&sec_user_id=MS4wLjABAAAA64MMnP0kx7RXge9hDTtImUc5cP_jS7hleAbHhbkjqgNqelnEN_DKhKx_WSapnSSr&social_share_type=0&utm_source=copy&utm_campaign=client_share&utm_medium=android&share_iid=7665441516542396180&share_link_id=f41236b9-b556-4c8c-b454-45db40c75e0e&share_app_id=1233&ugbiz_name=MAIN&ug_btm=b8727%2Cb2878&sp_root_share_link_id=f41236b9-b556-4c8c-b454-45db40c75e0e&link_reflow_popup_iteration_sharer=%7B%22click_empty_to_play%22%3A1%2C%22dynamic_cover%22%3A1%2C%22follow_to_play_duration%22%3A-1.0%2C%22profile_clickable%22%3A1%7D&panel_source_v2=share_panel&share_enter_from=personal_homepage&item_author_type=1&enable_checksum=1&sp_level=1&sp_root_u=ekg2c7m7e717c9&sp_root_d=eifh2gmaah41ce
3 006
የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ዋና የትምህርት ምንጭ የሆነው የአብነት ትምህርት ቤት በየአመቱ በሺህ የሚቆጠሩ ተማሪዎችን በመምህርነት አስመርቆ ያወጣል። እነዚህ ተማሪዎች የሚማሩት ትምህርትና ከሦስት እና ከአራት መቶ አመት በፊት የነበሩት ሊቃውንት የተማሩበት መንገድም ሆነ የተማሩት ትምህርት ይዘት ተመሳሳይ ነው። ብዙዎች ይህን ትውፊትን እንደማስጠበቅ አድርገው ይረዱታል። የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያንን ቤተክርስቲያን አድርጎ ያቆያት ዋና ቁምነገርም ይህ እንደሆነ ያስባሉ። ወደፊትም ቤተክርስቲያኒቱን ለመጠበቅ የትምህርት መንገዳችንም ሆነ ትምህርታችን መነካት የለበትም ይላሉ። ነገር ግን እዚህ ጋር መሠረታዊ የሆነ ጥያቄ ይነሳል። ከአብነት ትምህርት ቤት የሚወጡ መምህራን ከዘመኑ ጋር መራመድና ዘመኑ የሚሠራበትን ፍልስፍና ያለማወቃቸው ነገር ነው። የማያውቁትን ሕመም ደግሞ ማዳን እንደማይቻል ግልጽ ነው። የመምህራን ዋና ተልእኮ ደግሞ የዘመኑን መንፈስ ማንበብና መፈወስ መቻል እስከሆነ ድረስ ትምህርታችንም ሆነ የትምህርት መንገዳችን ላይ ጥያቄ ማንሳታችን የግድ ይሆናል። ከየኔታ ኃይለማርያም ጋር ይህንን ጉዳይ በተመለከተ ደፈር ብለን ለመወያየት ሞክረናል። መልካም ቆይታ።
https://youtu.be/84qnUpLiPeg?si=sA22oVkx2kT9njo_
3 006
በዚህኛው ክፍል ባለፉት ሁለት ወራት ስለ ገዳማዊ ሕይወት እና ምንኩስና የተሰጡ አስተያየቶችን ለመቃኘት ሞክረናል። ሲሰጡ የነበሩ አስተያየቶች ስላለንበት ደረጃ ምን ይነግሩናል? ምን ዓይነት የቤት ሥራስ ከፊታችን ይጠብቀናል?...የሚሉትን ርእሰ ጉዳዮች ለማንሣት ሞክረናል። እንደ ሁልጊዜው ሁሉ እንድታደምጡ፣ አስተያየታችሁንም እንድታካፍሉ ጋብዘናል
እነሆ ክፍል ሁለት
https://youtu.be/5lxbXfsp6pc?si=AzFaWBkWLIUQRDo1
3 006
ታላቁ አባት ቅዱስ አትናቴዎስ በአባ እንጦንስ የምንኩስና ሕይወት እጅጉን ተማርኮ ነበር። "አባ እንጦንስ ለመላዋ ግብጽ የተሰጠ መድኀኒት ነው' እስከ ማለትም ደርሶ ነበር። ክቡርየሆነው ይህ የምንኩስና ገድል የእኛ ቤተ ክርስቲያን ታሪክመገለጫ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡ አሁን ግን ምን እየተባለ ነው? ችግሩን እንዴት እንረዳው? ለመፍትሔውስ ምን መደረግ አለበት የሚሉትን በሁለት ክፍል ለማንሣት ሞክረናል።
እነሆ ክፍል አንድ
https://youtu.be/AQ_z48j-rEQ?si=vau7PCj7ECGXLSfd
