ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Open in Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Show more2 955
Subscribers
+1424 hours
+247 days
+38330 days
Posts Archive
‹‹እናንተ ውጡ፤ እኛ መውጣት አንችልም›› የጀግኖቹ የመጨረሻ ቃል!
ለዓላማ ታምኖ በጀግንነት መውደቅ፤ የአማራ ፋኖ የአባቶቹ ውርስ ነው።
ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ እዝ የተሰጠ መግለጫ፦
የአማራ ሕዝብ የተከፈተበትን ሥርዓታዊ የዘር ማጥፋት ጦርነት ለመቀልበስ በጽናት እየተዋጋ ያለው የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ፤ በጠላት ብልጽግና አገዛዝ ላይ ተደጋጋሚ ክንዱን እያሳረፈ፤ የድል ግስጋሴውን አስጠብቆ ይገኛል፡፡
በዚህ መራራ እና ፈተናው ብዙ በሆነው የህልውና ትግል ላይ፤ የአማራ ፋኖ በርካታ ተግዳሮቶችን በጽናት እያለፈ፤ ውድ እና ጀግና ልጆቹም በጀግንነት የህይወት መስዋዕት እየከፈሉ፤ የድል ጉዞውን አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ እዝ፤ ከመቼውም ጊዜ በላይ የአንድነት ሂደቱን እያጠናቀቀ ይገኛል፡፡ ይህ የፋኖ አንድነት ያሳሰበውና የጭቆና አገዛዝነት ዘመኑ ማብቂያ መሆኑን የተረዳው ጠላት ኦህዴድ/ብልጽግና አገዛዝ፤ የዘወትር የአማራ ሕዝብ የስቃይ ምንጭ የሆነውንና ለአገዛዙም የጥቃት ዓላማ ዋና ምርኩዝ የሆነውን የብአዴን መዋቅር እንዲሁም ሰርጎ ገብ ሀይሉን ተጠቅሞ በርካታ ሠራዊት በሜካናይዝድ መሣሪያ አጅቦ ወደ ማዕካለዊ ጎንደር ደንቢያና ማክሰኝት ዙሪያ ዘመቻ ከፍቶ ነበር፡፡
ጠላት በከፍተኛ ዝግጅትና በጀት፤ እንዲሁም በመንገድ መሪ ምርኩዙ ብአዴን እየተመራ የፋኖ መሪዎችን ለመክበብ ባደረገው ውጊያ፤ በርካታ የጠላትን ሠራዊት አንበርክከው የተሰው ውድ የአማራ ልጆች፤ ለወጡለት ዓላማ እና አደራ ለሰጣቸው ሕዝብ ታምነው የክብር መስዋዕት ሆነዋል፡፡
የጠላት ሠራዊት ከፍተኛ ሀይል ይዞ ያደረገውን ከበባ ለመስበር በተደረገው ብርቱ ትንቅንቅ፤ ውድ የአማራ ልጆች የሆኑት መሪዎቻችን፤ አርበኛ አማረ አቸነፍ ታደገ፣ አርበኛ ሳምሶን አማረ፣ አርበኛ መቶ አለቃ አበራ አግማስ፣ አርበኛ ሥጦት ጀምበር እና አርበኛ አትርሳው ገበያውን ጨምሮ፤ ሌሎች ጀግኖች የትግል አጋሮቻችን ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም በክብር ተሰውተዋል፡፡ በጀግኖች መስዋዕት መሆን እዛችን የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን እየገለጸ፤ ጀግኖቹ የተሰውለትን ዓላማ ከግብ ለማድረስ፤ መላው የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ እዝ አመራርና ሠራዊት፤ ቃል እነገባለን፡፡
ጀግኖቹ በመጨረሻው የተጋድሏቸው ሰዓት፤ ‹‹እኛ መውጣት አንችልም፤ የአማራን ሕዝብ እኛ ሞተን ልናድነው ስለሆነ ትግላችንን የጀመርነው ለወጣንለት ዓላማ ታምነን እንሰዋለን፡፡ አንድ ጥይት እስኪቀረን ድረስ እንፋለማለን እናንተ ወደኋላ ሁኑና ትግሉን አድኑ፡፡ አንድነቱን በጉጉት ለሚጠብቀው ወገናችን እንድታበስሩት በመጨረሻዋ እስትንፋሳችን ላይ ቆመን አደራ እንላችኋለን›› በማለት ነበር የመጨረሻ ቃላቸውን ለመሪዎቻቸውና ለትግል አጋሮቻቸው በማስተላለፍ የተሰናበቱን፡፡ ጀግኖቹ በቃላቸው መሠረት ህልቆ መሳፍርት የጠላትን ሠራዊት ከአፈር ከቀላቀሉ በኋላ፤ ለአማራ ሕዝብ ህልውና እና ነፃነት ሲሉ በጀግንነትና በክብር ተወስተዋል፡፡
ይህ የጀግኖች ወንድሞቻችን የክብር መስዋዕትነት፤ ሠራዊታችን የወጣለትን ዓላማ ከዳር ለማድረስ የበለጠ የሚያነሳሳን እንጂ፤ ትግላችንን የሚያዳክም፤ በሠራዊታችን ላይም የስነ ልቦና ስብራት እንደማያደርስ ልናረጋግጥላችሁ እንወዳለን፡፡
የጀግና ፍጻሜው በጀግኖች ሜዳ እንጂ፤ ለጠላቱ እጁን በመስጠት የሚጠናቀቅ ታሪክ የለውም፡፡ በጀግኖች ወንድሞቻችን መስዋዕት መክፈል፤ መሪር ሀዘን ቢሰማንም፤ ወንድሞቻችን ለተሰውለት ዓላማ እና የአማራ ፋኖ ለወጣለት የትግል ዓላማ፤ በጽናት በመፋለም፤ የአማራን ሕዝብ ስቃይና መከራ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እናስቆማለን፡፡
ዘላለማዊ ክብር ለጀግኖች ሰማዕታት
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ እዝ
ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም
ጎንደር--- አማራ ---ኢትዮጵያ
ከሠም ፪ኛ ኮር ለተከታታይ ሶስት ቀናት ከጠላት ኃይል ጋር ከፍተኛ ትንቅንቅ አድርጎ ድል ሲቀዳጅ በሌላ በኩል ተስፋ የቆረጠው የአገዛዙ ኃይል በደራ ከፍተኛ ዝርፊያ እና የንፁሃን እገታን ስራዬ ብሎ የዕለተ ከእለት ተግባሩ አድርጎታል::
ሰኔ 16/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ከሠም ኮር ነበልባል ክ/ጦር ከነብሮ ሻለቃ እና ከምኒልክ ሻለቃ በተውጣጣ ኃይል ጠላት ላይ ከባድ ኪሳራ ማድረስ ችሏል። በሁለት የፋኖ ሻለቆች ለሁለት ተከታታይ ቀናት ከወራሪው ኃይል ጋር በተደረገ እልህ አስጨራሽ ውጊያ በምስራቅ ሸዋ ዞን አዳማ ወረዳ በሙኩዬ ቀበሌ ዘልቀው የገቡት የፋኖ ኃይሎች ወራሪው ኃይል ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረስ ችለዋል። በተደረገው እልህ አስጨራሽ ውጊያ የጠላት ኃይል ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ ደርሶበታል:: ይኸውም
.አንድ ከአዳማ ወረዳ የመጣ ከፍተኛ አመራር የሞተ
. አንድ የሙኩዬ ቀበሌ ኮማንደር ፖሊስ የሞተ
.አንድ ሚሊሻ የተማረከ
.አምስት የአገዛዙን ኃይል ቁስለኛ ማድረግ የተቻለ ሲሆን በምርኮ የተገኙ ንብረቶች
. ሁለት ክላሽ ኮፍ
.አንድ ኤምዋን መሳሪያ ገቢ ተደርገዋል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ከሠም ኮር ሀይለማርያም ማሞ ክፍለ ጦር እና ነበልባል ክፍለ ጦር በጥምረት ባደረጉት አውደ ውጊያ ጠላትን ቀጥቅጠው ድል ተቀዳጅተዋል።ከሀገረ ማርያም ከሰም ወረዳና ከምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በኩል ለወረራ እና ለዘረፋ የገባውን የጠላት ኃይል በሀይለ ማርያም ማሞ ከፍለ ጦር ክፉኛ ተመትቶ ወደ መጣበት እዲመለስ ተደርጓል። በዚሕ አውደውጊያ ክፉኛ የተመታው ጠላት ለተከታታይ ሶስት ቀናት በተደረገው እልህ አስጨራሽ ውጊያ ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ኪሳራን አስተናግዶ ወደ መጣበት ተመልሷል። አገዛዙ ቁጥራቸው በውል ያልታወቁትን ቁስለኛቹን ወደ ሀገረማርያም የህክምና ማዕከሉ የላከ ሲሆን የሞቱት አባሎቹን የቻለውን ባገኘበት ቀብሮ ያልቻለውን አስከሬናቸውን ሳይዝ ትቶ መፈርጠጡ ተረጋግጧል።
በሌላ ግንባር ነበልባል ክፍለ ጦር ከ14/10/2018 ጀምሮ ከሀገረ ማርያም ተነስቶ በዮላት እና በቅዱሥጌ ቀበሌ የመጣውን ወራሪ ሰራዊት እንደ አንዳ አመጣጡ ተመቶ የተመለሰ ሲሆን ሥቻት ቀበሌ ላይ ሰፍሮ የነበረውን የጠላት ኃይል ለተከታታይ ሶስት ቀን በተደረገ እልህ አስጨራሽ ውጊያ ወራሪው ኃይል ስቻትን ለቆ እንዲወጣ ተደርጕል::
በሌላ አቅጣጫ በምንታምር በኩል ወደ አክርሚት የገባው የጠላት ኃይል በጀግኖቹ የነበልባል ክፍለ ጦር ቃኚዎች እና አንድ ሻለቃ ባደረጉት አውደ ውጊያ ሰቃዋጮ በምትባል ቀበሌ ላይ የጠላት ኃይል ከፍተኛ ጉዳት ያስተናገደ ሲሆን ጠላት ይዞታውን ለቆ እየሸሸ ይገኛል። ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ድረስ ውጊያው በተለያየ ግንባሮች አሁንም እንደቀጠለ ሲሆን ተጨማሪ የአውደ ውጊያ ዘገባዎችን በቀጣይ ይዘን የምንመለስ ይሆናል::
በሌላ ዜና በደራ እና አካባቢው ህዝባችን ላይ በተፈፀመ ዝርፊያ እና ውንብድና ከ400 በላይ የሚሆኑ የቀንድ ከብቶች ሲዘረፉ፣ ከ84 በላይ ንፁሀን ወገኖች ታግተው መወሰዳቸውን ነዋሪዎች ገለፁ።
በውድቀቱ ዋዜማ ላይ የሚገኘው የብልፅግናው አገዛዝ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሀቤቴ አውራጃ በደራ ጉንዶ መስቀል ወረዳ ነዋሪዎች ላይ መጠነ ሰፊ ግፍና መከራ ማድረሱን አጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን የኦሆዴድ ብልፅግና መራሹ ቡድን ካሰማራው የጃል ሰኚ የሸኔ ትራፊ ወንበዴዎች ጋር በፈፀሙት የጋራ የዝርፊያ ተግባር በወረዳው ስር የሚገኙ የአባጦ ቀበሌ ነዋሪዎችን ከ400 በላይ የሚሆኑ የቀንድ ከብቶችን የዘረፉ ሲሆን ከ84 በላይ ንፁሀን ሰዎችን በማገት መውሰዳቸውን ነዋሪዎች ገልፀዋል።
ትላንት ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም በተፈፀመው የዝርፊያ እና የአጋችነት ተግባር እጅግ አሳፋሪ የሚያደርገው ንብረታቸውን ከወራሪው ለመከላከል የጦር መሳሪያ ይዘው የወጡ የአካባቢው ነዋሪዎችን በመነጠል እና አንድ ላይ በመሰብሰብ አገዛዙ በፈፀመው የድሮን ጥቃት ንፁሓኖቹ ኢላማ እንደሆኑ ተደርጎ 7ቱ ወዲያውኑ ህይዎታቸው ሲያልፍ 11ዱ ቁስለኛ ሆነው ሀብት ንብረታቸውን እንዳይከላከሉ ከመደረጉም ባሻገር ግፍ ተፈፅሞባቸዋል::
አገዛዙ ባሰማራቸው የሸኔ ቡድን በአባጦ ቀበሌ ነዋሪዎች ላይ መጠነ ሰፊ ዝርፊያ እና ወረራ መደረጉን ተከትሎ ነዋሪዎች ባሰሙት የድረሱልን ጥሪ መሰረት የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደ ፅዮን ኮር የአፄ ዳዊት ክፍለ ጦር አሃዶች በፍጥነት ተወርውረው በቦታው ላይ ደርሰው ለመታደግ ባደረጉት ከፍተኛ ጥረት ውስን የኦሮሞ ብሔር ተወላጆችን ከእገታው ቢያስለቅቁም በሁለት አቅጣጫ በብልፅግናው ሰራዊት በተፈፀመበት ከበባና ጥቃት የፋኖ ኃይሉ ወደመከላከል ውጊያ በመግባቱ በአባጦ ቀበሌ የታገቱ ንፁሃን ነዋሪዎች እና የተዘረፈውን ንበራታቸውን ሙሉ በሙሉ ማትረፍ አለመቻሉን ኮሩ ባደረሰን መረጃ ገልጿል።
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ በተደጋጋሚ ጊዜ ባደረገው የማጣራት ስራ በደራ ጉንዶ መስቀልና አጎራባች ወረዳዎች የሚገኘው የብልፅግና አመራሮች ከሸኔ ቡድን ጋር ጥብቅ ቁርኝት እንዳላቸውና የጦር መሳሪያና የተተኳሽ ድጋፍ ጭምር እንደሚያደርግላቸው ያረጋገጠ ሲሆን በተጨማሪም በንፁሀን ወገኖች ላይ የሚፈፀሙ እገታና ዘረፋዎች በቅንጅት እንደሚሰሩ ማሳያ መሆኑን ለሰፊው ህዝባችን መግለፅ እንወዳለን።
''ክብር ለትግሉ ሰማዕታት''
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
በስቦ ማስከዳት አንድ የመከላከያ ሰራዊት አባል ሁለት ዳይሞሊ ክላሽ በመያዝ ፋኖን ተቀላቀለ!
ፀሐይ መውጫ ከተባለ አካባቢ የሚንቀሳቀሰው 16ኛ ክፍለ ጦር የብልፅግና ሰራዊት አባል የነበረው መሰረታዊ ወታደር ድርጅት አማረ አገዛዙን በመቃወም ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ/ም የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር 21ኛ ክፍለ ጦርን ተቀላቅሏል።
የመከላከያ አባሉም ከአሸባሪው ቡድን ጋር አብሮ መቀጠል ሕዝብ እና ሃገርን መክዳት ስለሆነ አብሬ አልቀጥልም በማለት ምሽግ ላይ የነበሩትን ሁለት ሰራዊት አባልን እስከ ወዳኛው በመሽኘት ሁለት ዳይሞሊ ክላሽ፣ 250 የክላሽ ተተኳሽና ሦስት የእጅ ቦምብ በመያዝ የተቀላቀለ ሲሆን የክፍለ ጦሩ ከፍተኛ አመራሮች ባደረጉለት ደማቅ አቀባበልም ደስተኛ መሆኑን አልደበቀም።
መዳረሻው ድል እና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲል የ303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መረጃውን አድርሷል ።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ/ም
አማራ ሳይንት የገባው የጠላት ኃይል ከፍተኛ ጉዳት አስተናገደ:: 136 ወታደሮች ተደመሰሱ!! ጓሜዳ ታዳጊ ከተማንም ነፃ ማድረግ ተችሏል::
6ተኛ ቀኑን በያዘው ትንቅንቅ የአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 47ኛ ክፍለ ጦር ታቦር ተራራ ሻለቃ ፋኖዎች ታላቅ የጦር ሜዳ ጀብዱ ፈጽመዋል:: ጓሜዳን ነፃ ማድረግ የተቻለ ሲሆን ወደ ተድባበ ማርያም ቀጠና ለመግባት ተግተልትሎ የተጓዘው የ11ኛ ዕዝ 204ኛ ኮር ሜካናይዝድ እና እግረኛ ሰራዊት ከፊትም ከጀርባም ጥቃት ተሰንዝሮበት በርካታ አባላቱን ተነጥቋል:: አምበሳ መጫሪያ እና ተሮ ሜዳ በተባሉ ቦታወች የበርካታ ወታሮች አስከሬን የወደቀ ሲሆን ጠላት አስከሬኑን እንኳን ማንሳት የማይችልበት ሁኔታ ውስጥ እስኪገባ ድረስ በታቦር አናብስት ወታደራዊ የበላይነት ተወስዶበታል::
አጅባር የሚገኘው አማራ ሳይንት ሪፈራል ሆስፒታል በጠላት ኃይል ቁስለኞች መጥለቅለቁ ታውቋል:: ይህን ዜና እያጠናከርንበት ባለንበት ቅጽበት እንኳን 3 አምቡላንሶች ቁስለኛ ጭነው ወደ ደሴ መስመር እየተጓዙ በለጩማ ላይ ሲደርሱ ታይተዋል::
በብርሀን ፍጥነት ተድባበ ማርያም እገባለሁ ብሎ በ2 ጄኔራሎች እየተመራ የተንቀሳቀሰው ጠላት የሽንፈት ፅዋን መጎንጨቱን ተከትሎ በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ መነቃቃት የተፈጠረ ሲሆን ጠላትም የፋኖን የማድረግ አቅም ተገንዝቦበታል::
በርሀ ድረስ እገባለሁ በሚል እብሪት በዋሮ ቀጠና በኩል ጭምር ጠላት ተኩስ ቢከፍትም የታቦር አናብስት አሳፍረው መልሰውታል:: የአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 47ኛ ክፍለ ጦር ሼህ ሁሴን ጅብሪል ሻለቃም የተወሰነ ኃይል ወደ አማራ ሳይንት በማሻገር በዋሮ ግንባር ያለውን የጠላት ኃይል ከታቦር አናብስት ጋር በመሆን አይቀጡ ቅጣት ቀጥተውታል::
ጠላት ስፍር ቁጥር የሌለው እግረኛ ሰራዊት እና መድፍን ጭምሮ በርካታ ከባድ መሳሪያዎች ወደ አማራ ሳይንት አስገብቶ የአየር ኃይል ድጋፍም ተደርጎለት ቢፈራገጥም ያሰበውን መፈፀም ሳይችል ቀርቷል:: በዚህ የተበሳጨው ጠላት ሲተኩሰው የነበረው መድፍ የቤት እንስሳትን ጭምር ገድሏል::
ባለፉት 24 ሰአታት በጠላት ላይ የደረሰው ጉዳት እንደሚከተለው ነው:-
የተደመሰሰ - ከ30 በላይ ጠላት
የቆሰለ - ከ50 ያላነሰ ጠላት
በድምሩ ከትናንት ጀምሮ ከ80 በላይ የጠላት ኃይል ከጥቅም ውጭ ተደርጓል:: ሰሞኑን የተደመሰሱት አጠቃላይ ድምር 136 ደርሷል:: ይህ የተረጋገጠ መረጃ ነው:: በየጥሻው ወድቀው የቀሩትን ቁጥር ለማወቅ አልተቻለም::
ምንጭ፦ በአፋብ ምኒልክ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!
የተከበራችሁ የሃይማኖት አባቶች
የተከበራችሁ የአፋብን የድርጅት አመራሮች
የተከበራችሁ የምንሊክ እዝ አመራሮች አባላት
የተከበራችሁ የቴድሮስ ዕዝ አመራሮች እና የሰራዊት አባላት በሙሉ በቅድሚያ እንኳን ለጀግና አባታችን ለጀኔራል አሳምነው ፅጌ ሰባተኛ መታሰቢያ አመት በሰላም አደረሳችሁ እንዲሁም በዚች በተቀደሰች ቀን ለመመረቅ ዝግጁ የሆናችሁ የምንልክ ዕዝ የ105ኛ ኮር የ29ኛ ክፈለጦር ተመራቂ ሰራዊት እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እውዳለሁ
ለተመራቂዎች የቀረበ የትግል ቃል ኪዳን እና የአደራ መልዕክት!
የተከበራችሁ የትግል አጋሮቼ ፤ የነጻነት ታጋዮች እና የዛሬው ቀን የክብር ባለቤቶች እንኳን ለዚህ የቃል ኪዳን ቀን በሰላም አደረሳችሁ። ዛሬ እዚህ የቆማችሁት ለተራ ስልጠና ማጠናቀቂያ አይደለም ዛሬ እዚህ የተሰለፋችሁት ለአማራ ህዝብ ህልውና እና ለነጻነት ዘብ የምትቆሙበትን ታሪካዊ አደራ ለመረከብ ነው። አሳምነው ፅጌ ለአማራ ትግል ምልክት ሆኖ ያለፈው ህይወቱን ሳይሳሳ ለህዝብ ክብር በመስዋዕትነት በመክፈል ነው። እርሱ የለቀቀልን አደራ አማራ ተደራጅቶ ከመጣ እና ኢጎን ጥሎ ለጋራ አላማ ከተሰለፈ ማንም የማይደፍረው ህዝብ እንደሚሆን ነው።
እኛ የአማራ ትግል ታጋዮች እና ሰልጣኞች በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ለአማራ ህዝብ ክብር ነፃነት እና ቀናነት ዋጋ የከፈሉትን ጀግኖች አርአያነት በመከተል የብርጋዴር ጀነራል አሳምነው ፅጌን የትግል ፅናት ያልተሸነፈ መንፈስ እና የአማራነት ፅኑ አቋም መነሻ በማድረግ ይህንን የትውልድ ቃልኪዳን በመገንባት ልክ እንደ አባታችን አሳምነው ፅጌ ትግላችን በምንም አይነት ፈተና በምንም አይነት መከራ ወይም የጠላት ሴራ ወደ ኋላ እንደማይመለስ ቃል ገብተን የትግሉ ዓላማ የአማራን ህዝብ ህልውናና ክብር ማረጋገጥ መሆኑን አምነን እስከ መጨረሻው ጠብታ ደም ድረስ በፅናት መቆም አለብን ።
ብ/ጀ አሳምነው ፅጌ አማራን ከቦታ ቦታ አገናኝቶ በአንድ የትግል ማዕቀፍ ውስጥ እንዳሰባሰበ ሁሉ እኛም በውስጣችን ያለውን ልዩነት አጥበን በጋራ የጠላት ግብ ላይ በማተኮር ለአማራነት የሚቆም አንድ ልብ እና አንድ አላማ ያለው የትግል ሃይል ለመፍጠር ተሰልፈን የአማራነት ትግል የትናንቱ የጀግኖች ታሪክ ብቻ ሳይሆን የዛሬው ትግልና የነገው የልጅ ልጆቻችን ዋስትና መሆኑን ተገንዝበን በጀነራሉ ስም የተገባው ይህ አደራ የህልውናችን መገለጫ እንደሆነ አምነን ፤ ትግሉን ሳይጨርሱ ወደ ኋላ መመለስ እንደሌለብን በሙሉ ልብ ቃል እንገባለን።
እናንተ ዛሬ ከዚህ የትግል ማዕከል ስትመረቁ ከሁሉ በላይ ቅድሚያ የምትሰጡት ከጎታች ኢጎ እና ከራስ ወዳድነት ስሜት መውጣትን ነው። ኢጎ ለታጋይ መርዝ ነውን የራሱን ጥቅም የሚያስቀድም ታጋይ የህዝቡን እንባ ሊያብስ አይችልም። ከዚህ ከንቱ የራስ ስሜት ወጥታችሁ የህዝብን አደራ በትከሻችሁ ላይ ስትጭኑ የትግሉን አላማ በደም ስራችሁ ስትረዱ ብቻ ነው የድል አርማ የምትሆኑት። ከዚህ ጎን ለጎን የድርጅታችሁን አፋብን መዋቅርን መሪን እና ድርጅትን በአክብሮት መያዝ የትግላችሁ መገለጫ ነው። መሪን ማክበር ለትግሉ ስኬት፤ ድርጅትን ማክበር ደግሞ ለትግሉ ህልውና ወሳኝ ነው።
ድርጅት የትግሉ አከርካሪ ነው፤ የድርጅትን ደንብ መሪዎች እና አመራር ማክበር ለህዝብ ትግል ያለዎትን ታማኝነት ማሳያ ነው። ይህ ትግል የሀይማኖት ሳይሆን የማንነት ትግል መሆኑን መገንዘብ ይገባል። የአማራን ህዝብ ህልውና ለመጠበቅ የምናደርገው ይህ ትግል ከማንኛውም እምነት ወይም የሀይማኖት ልዩነት በላይ የሆነ የመኖር እና ያለመኖር የህልውና ትግል ነው። የአማራ ብሄርተኝነትን በፅኑ አለት ላይ ስንገነባ መለያያችን ሳይሆን አንድነታችንን ማዕከል እናደርጋለን፤ ስለዚህም በሀይማኖት አጥር ውስጥ ሳንወሰን እንደ አማራ በማንነታችን ብቻ አንድ ሆነን እንታገላለን። ከዚህም በላይ የትግላችን ከፍተኛው መገለጫ አማራ ለአማራ የመሆንን የተቀደሰ ምልክት በተግባር እውን ማድረግ ነው። አማራ ለአማራ ማለት በአንድነት መቆም እርስ በርስ መተጋገዝ የሌላውን ህመም እንደራስ ህመም መቁጠር እና የጋራ ጠላትን በአንድነት መመከት ማለት ነው። ይህ መፈክር ሳይሆን የህይወት ዘይቤአችሁ ሊሆን ይገባል። እርስ በርሳችሁ ተደጋግፋችሁ ተከባብራችሁ እና ተዋደዳችሁ ስትኖሩ ስትታገሉ የጠላት ሴራ ይረግፋል፤ የህዝባችን ተስፋ ይለመልማል።
የአማራ ብሄርተኝነት እንደ ንፋስ የሚለዋወጥ ሳይሆን እንደ ተራራ የቆመ በታሪክ፤ በባህል ፤ በአንድነት እና በፍትህ መሰረት ላይ የቆመ መሆን አለበት። ይህ ብሄርተኝነት ጠላትን የሚያንቀጠቅጥ ወዳጅን የሚያበረታታ እና ለአማራ ህዝብ የማያናጋ እምነት የሚፈጥር ነው። የብሄርተኝነታችን ፅኑ አለት በእናንተ አርበኝነት በብ/ ጀ አሳምነው ፅጌ መስዋዕትነት እና በህዝባችን አጥንትና ደም የታነጸ ነው። ስለዚህም ይህን እምነት በማንም የማይናወጥ ፅኑ አለት ላይ በመገንባት የጠላትን ጥቃት መመከት እና የክብርን ግንብ መገንባት አለባችሁ። የትግላችን አሻራ የሚቀረጸው በጡንቻ ብቻ ሳይሆን በድርጅታዊ ዲሲፕሊን ፤ በታማኝነት፤ በአንድነት እና በአማራነት ስሜት ነው። ብ/ ጀ አሳምነው ፅጌ የከፈለው መስዋዕትነት እኛን ከፋፋይ እና አሳሳች ከሆኑ የውስጥ ጠላቶች ጠብቆ የድርጅትን ክብር ጠብቀን የህዝብን የነጻነት ጥማት እንድንጠማ አድርጎናል።
እናንተ የዚህ ትግል ተተኪዎች ሆይ የህዝብ አደራ ተሸካሚዎች እና የፍትህ ፀሐይ አድራጊዎች ናችሁ። በመስክ ላይ ስትሰማሩ ከጀርባችሁ የህዝብ ጸሎት እንዳለ በፊታችሁ ደግሞ የነጻነት አላማ እንዳለ አትዘንጉ። የትግሉ አላማ የራስን ስም በታሪክ መዝገብ ላይ ማስፈር ሳይሆን የአማራን ህዝብ ከውርደት እና ከስቃይ ማውጣት ነው። ይህ የተቀደሰ ቃል ኪዳን በቃል ብቻ ሳይሆን በተግባር ይረጋገጣል። በጠላት ፊት እንደ አርማ የቆማችሁት እናንተ የህዝባችሁ የነጻነት ተስፋዎች ናችሁ። የብ/ ጀ አሳምነው ፅጌ መንፈስ የትግሉ ምልክት ሆኖ ከፊታችሁ ይሂድ የከፈለው መስዋዕትነት ለጀግንነታችሁ ዋስትና ይሁን። ከኢጎ ወጥታችሁ ድርጅታችሁን እና መሪዎቻችሁን አክብራችሁ አማራ ለአማራ የሚለውን የትግል ቃል ኪዳን በተግባር እውን አድርጋችሁ ትግሉ የማንነት እንጂ የሀይማኖት አለመሆኑን በጽኑ እምነት ይዛችሁ፤ የአማራን ብሄርተኝነት በፅኑ አለት ላይ አንጻችሁ፤ የህዝብን አደራ በታማኝነት ተሸክማችሁ፤ እስከ መጨረሻው የድል አፋፍ ድረስ በቁርጠኝነት እንደምትጓዝ አንጠራጠርም ። አማራነት በጀግንነት ይፀናል፤ የድርጅት ህግ፣ መሪ እና አደራ በትግላችን ይፈጸማል፤ የአማራ አንድነት በድል ይደመደማል!
የአማራነት ትግል በጀግኖች ደም የጠነከረ ፤በሰልጣኞች ፅናት የዘለቀ እና በውጤት የሚታተም የህዝብ አደራ ነው። በብ/ጀ/ አሳምነው ፅጌ ስም እና አሻራ ትግሉ በድል እስኪጠናቀቅ ወደ ኋላ አንልም።
መቶ አለቃ ዮሴፍ አስማረ
አነሰግናለሁ------------
አባ መላ(ንጉስ ተክለሀይማኖት) የመተከሉ ግንብ!
መተከል በረሃው...... ያ ምድር ያ ቆላ
ታሪክ ይናገራል...... ሲነሳ አባ መላ
በላያ ተናገር...... ቢዝር ወይም ዳንጉር
ደም አጥንት መኖሩን...... ከመተከል አፈር
አባይም ይመስክር...... ይናገር ለጣና
ተክለሃይማኖት ነው...... የአሽመን(መተከል) ዋስትና
ደርቡሽ ሲያገሳ...... ሊያጠፋው ድንበሩን
አዳል ተሰማ ነው...... ያስከበረው ምድሩን
ዋንበራ(ወንበራ) ታውቃለች...... ያን የጦር ማዕበል
የጀግናው ክንድ ነው...... የሀገር ሲሳይ ብል
ድንበሩን አትግፉ...... አትድፈር ርስቱን
አባ መላ አለልህ...... ሚሰብር ወገብን
©Birhanu Chalie Demelash
https://www.facebook.com/share/1BMtrRDfpz/
+3
ራሱን በብቁ ሰራዊት እያደራጀ የሚገኘው ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር 29ኛ ክፍለጦር ለአራተኛ ተከታታይ ጊዜ አዳዲስ ምልምል ሰራዊት አስመረቀ!
ምኒልክ ዕዝ 105ኛ ኮር ከጠላት ላይ ከሚወስደው ተከታታይነት ያለው መብረቃዊ ጥቃት በተጨማሪ ለአማራ ሕዝብ የሕልውና ትግል ራሱን በሰው ሃይል እያጎለበተ ይገኛል። የ105ኛ ኮር አሃድ የሆነችው ነበልባሏ 29ኛ ክፍለጦር ነፃ ቀጠናወችን በመፍጠር ለአማራ ሕዝብ ትግል ትልቅ እመርታ እና ተስፋ የሆነውን በሰው ሃይል ግዙፍ የመሆን እቅድን በንቃት በመተግባር ላይ ናቸው።
105ኛ 29ኛ ክፍለጦር የጠላትን ሃይል በደፈጣ፣ በመደበኛ ውጊያ ፣ በልዩ የከተማ ውስጥ ኦፕሬሽን እንዲሁም በጠላት ውስጥ ሰርጎ በመግባት የአገዛዙን ወታደራዊ እና ፓለቲካዊ አቅም በመገምገም ከውስጡ ፍርክስክሱን በማውጣት ላለፉት አመታት ምትሃታዊ ጀብዱዎቹን እየፈፀመች ትገኛለች። ለሶስት ዙር በብቃት አዲስ የፋኖ አባላትን ማስመረቅ የቻለቺው ክፍለጦሯ ለአራተኛ ጊዜ የኮማንዶ አባላትን በስኬት ማስመረቅ ችላለች።
ለተከታታይ አራት(4) ወራት ከባድ የስልጠና ልምምዶችን ምንም ባልተሟላ የስልጠና ግብዐት በፅናት ላሰለጠኑ አሰልጣኞች እንዲሁም ከባዱን የኮማንዶ ስልጠና ላጠናቀቁ ምሩቅ የሰራዊት አባላት የክፍለጦሯ አመራሮች የከበረ ምስጋና አቅርበዋል። ምልምል የኮማንዶ አባላትም የአማራ ሕዝብን በጀግንነትና በፅናት ለማገልገል ቃል በመግባት የምረቃ ፕሮግራሙ በስኬት ተጠናቋል ሲል የ29ኛ ክፍለጦር ሕዝብ ግንኙነት ዘርፍ ሃላፊ አርበኛ አስማማው ፈንታው መረጃውን አድርሷል።
መዳረሻውን ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ሕዝብ የሕልውና ተጋድሎ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ሰኔ 16/2018 ዓ/ም
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የመጀመሪያ መደበኛ ጉባዔውን አካሄደ
ሰኔ 16/2018 ዓ.ም
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ውስጥ ሲንቀሳቀሱ የነበሩት ሁለቱ ዕዞች አንድነታቸውን እውን ካደረጉበት ቀን ጀምሮ በሸዋ ጠንካራ ድርጅታዊና ተቋማዊ እንቅስቃሴዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የመጀመሪያ ጉባዔውን በማካሄድ የሸዋን አንድነት በጽኑ መሠረት ላይ እያጠናከረ መጓዙን ቀጥሏል።
ይህ ጉባዔ ከሰኔ 9/2018 ዓ.ም እስከ ሰኔ 15/2018 ዓ.ም ለተከታታይ ሰባት (7) ቀናት የተካሄደ ሲሆን፣ በጉባዔው ላይ የዕዙ ጠቅላላ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ተሳትፈዋል። በዚሁ ስብሰባ ላይ ድርጅቱ ከትላንት እስከ ዛሬ እንዲሁም ከዛሬ እስከ ነገ በሚከተላቸው መርሆች ላይ ጥልቅ ግምገማ በማድረግ፣ የታዩ ክፍተቶችን በመንቀስና ለቀጣይ ስኬትን ሊያጎናፅፉ የሚያስችሉ ውሳኔዎችን በማሳለፍ የቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል።
በጉባዔው የተለዩ ዋና ዋና ክፍተቶችና የተወሰዱ ማስተካከያዎች፦
▸ቀደም ሲል የነበሩ የተናጠል ጉዞዎች ህዝብን፣ ሰራዊትንና ደጋፊዎችን ያሳፈሩ፣ ትግሉ በሚፈለገው ፍጥነት እንዳይሄድ ያደረጉና ለጠላት ጊዜ የሰጡ በመሆናቸው ወደፊት እንዳይደገሙ ተደርጓል።
▸የድርጅቱ የአሠራር ክፍተቶች ተገምግመው፣ አንድ ወጥና ሰንሰለቱን የጠበቀ አሠራር እንዲዘረጋ በሚል አቋም ተይዟል።
▸ከጉባዔው ማግስት ጀምሮ የድርጅቱ ወታደራዊና ህዝባዊ መዋቅር ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ እንዲገባ ተወስኗል።
▸የህዝብና የሰራዊት መብቶችን ማክበር ቀዳሚ ተግባር መሆኑ ተረጋግጧል።
በሂደቱም ቀጣይ በትኩረት እንድሰሩ አቅጣጫ የተሰጠባቸው ጉዳዮች :- ▸ድርጅታዊ አሠራርና መርሆዎችን ሙሉ በሙሉ ተፈፃሚ ማድረግ።
▸በህዝባዊ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ አንድ ወጥ አሠራርን መተግበር።
▸የሰራዊቱን ብቃትና ዝግጁነት በስልጠናና ተሃድሶ ወደ መካናይዝድ በማሻሻል ለማይቀረው ድል ማዘጋጀት።
▸ህዝቡ ከትላንት ደጀንነቱ በላቀ መልኩ፣ ለነገው የድል ግስጋሴ በጠንካራና ወጥ አደረጃጀት እንዲዘጋጅ ማድረግ።
አርበኛ ኢ/ር ደሳለኝ ሲያስብ (የዕዙ ዋና መሪ) እንደገለፀው :-ትግሉ ግለቱን ጠብቆ እንዳይሄድ አደናቃፊ የነበረውን ወጥመድ በጥሰነዋል።
ማዕከላዊ ኮሚቴው በሰራዊቱና በህዝቡ ፍላጎት እውን የሆነውን የሸዋ አንድነት በተግባር ለመግለጽ ከመቼውም በላይ በልበ ሙሉነት ሥራ መጀመሩን ገልጿል።
አርበኛ ጠጁ ባበይ (የዕዙ ም/ል መሪ) እንደገለፀው :-ከውስጥም ከውጪም ድላችንን ለሚናፍቅና በአንድነቱ ደስ ለተሰኘው ሁሉ፣ ለምናደርገው አኩሪ የህልውና ተጋድሎ ከጎናችን ትሆኑ ዘንድ ጥሪያችን ተግባራዊ ነው።አንድነታችን እውን ነው።ከዚህ ቡሀላ አንድነትን የሚጠላ ካለ ህዝባችንንና ሰራዊታችንም አይቀበልም በአንድነት ለማይቀረው ድል እንጓዛለን።
በማጠቃለያው፣ የአገዛዙን ዕድሜ ላለማራዘም ዋጋ እየከፈሉ ላሉ ጀግኖች የድል ቀን ከመቼውም በላይ እየቀረበች ስለሆነ አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ መስራት አለብን በማለት ሀሳቡን ገልጿል።።
"ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!"
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!"
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የመጀመሪያ መደበኛ ጉባዔውን አካሄደ
ሰኔ 16/2018 ዓ.ም
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ውስጥ ሲንቀሳቀሱ የነበሩት ሁለቱ ዕዞች አንድነታቸውን እውን ካደረጉበት ቀን ጀምሮ በሸዋ ጠንካራ ድርጅታዊና ተቋማዊ እንቅስቃሴዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል። የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የመጀመሪያ ጉባዔውን በማካሄድ የሸዋን አንድነት በጽኑ መሠረት ላይ እያጠናከረ መጓዙን ቀጥሏል።
ይህ ጉባዔ ከሰኔ 9/2018 ዓ.ም እስከ ሰኔ 15/2018 ዓ.ም ለተከታታይ ሰባት (7) ቀናት የተካሄደ ሲሆን፣ በጉባዔው ላይ የዕዙ ጠቅላላ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት ተሳትፈዋል። በዚሁ ስብሰባ ላይ ድርጅቱ ከትላንት እስከ ዛሬ እንዲሁም ከዛሬ እስከ ነገ በሚከተላቸው መርሆች ላይ ጥልቅ ግምገማ በማድረግ፣ የታዩ ክፍተቶችን በመንቀስና ለቀጣይ ስኬትን ሊያጎናፅፉ የሚያስችሉ ውሳኔዎችን በማሳለፍ የቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል።
በጉባዔው የተለዩ ዋና ዋና ክፍተቶችና የተወሰዱ ማስተካከያዎች፦
▸ቀደም ሲል የነበሩ የተናጠል ጉዞዎች ህዝብን፣ ሰራዊትንና ደጋፊዎችን ያሳፈሩ፣ ትግሉ በሚፈለገው ፍጥነት እንዳይሄድ ያደረጉና ለጠላት ጊዜ የሰጡ በመሆናቸው ወደፊት እንዳይደገሙ ተደርጓል።
▸የድርጅቱ የአሠራር ክፍተቶች ተገምግመው፣ አንድ ወጥና ሰንሰለቱን የጠበቀ አሠራር እንዲዘረጋ በሚል አቋም ተይዟል።
▸ከጉባዔው ማግስት ጀምሮ የድርጅቱ ወታደራዊና ህዝባዊ መዋቅር ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ እንዲገባ ተወስኗል።
▸የህዝብና የሰራዊት መብቶችን ማክበር ቀዳሚ ተግባር መሆኑ ተረጋግጧል።
በሂደቱም ቀጣይ በትኩረት እንድሰሩ አቅጣጫ የተሰጠባቸው ጉዳዮች :- ▸ድርጅታዊ አሠራርና መርሆዎችን ሙሉ በሙሉ ተፈፃሚ ማድረግ።
▸በህዝባዊ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት ላይ አንድ ወጥ አሠራርን መተግበር።
▸የሰራዊቱን ብቃትና ዝግጁነት በስልጠናና ተሃድሶ ወደ መካናይዝድ በማሻሻል ለማይቀረው ድል ማዘጋጀት።
▸ህዝቡ ከትላንት ደጀንነቱ በላቀ መልኩ፣ ለነገው የድል ግስጋሴ በጠንካራና ወጥ አደረጃጀት እንዲዘጋጅ ማድረግ።
አርበኛ ኢ/ር ደሳለኝ ሲያስብ (የዕዙ ዋና መሪ) እንደገለፀው :-ትግሉ ግለቱን ጠብቆ እንዳይሄድ አደናቃፊ የነበረውን ወጥመድ በጥሰነዋል።
ማዕከላዊ ኮሚቴው በሰራዊቱና በህዝቡ ፍላጎት እውን የሆነውን የሸዋ አንድነት በተግባር ለመግለጽ ከመቼውም በላይ በልበ ሙሉነት ሥራ መጀመሩን ገልጿል።
አርበኛ ጠጁ ባበይ (የዕዙ ም/ል መሪ) እንደገለፀው :-ከውስጥም ከውጪም ድላችንን ለሚናፍቅና በአንድነቱ ደስ ለተሰኘው ሁሉ፣ ለምናደርገው አኩሪ የህልውና ተጋድሎ ከጎናችን ትሆኑ ዘንድ ጥሪያችን ተግባራዊ ነው።አንድነታችን እውን ነው።ከዚህ ቡሀላ አንድነትን የሚጠላ ካለ ህዝባችንንና ሰራዊታችንም አይቀበልም በአንድነት ለማይቀረው ድል እንጓዛለን።
በማጠቃለያው፣ የአገዛዙን ዕድሜ ላለማራዘም ዋጋ እየከፈሉ ላሉ ጀግኖች የድል ቀን ከመቼውም በላይ እየቀረበች ስለሆነ አስፈላጊውን ዝግጅት እንዲያደርጉ መስራት አለብን በማለት ሀሳቡን ገልጿል።።
"ክብር ለትግሉ ሰማዕታት!"
"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!"
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የህዝብ ግንኙነት መምሪያ
በአባታችን በታላቁ ሰማዕቱ ጀኔራል አሳምነው ፅጌ መታሰቢያ ቀን በሃሳብና በፓለቲካዊ ብስለት የሚመራው ጀብደኛው ምኒልክ ዕዝ 106ኛ ኮር 31ኛ-ሰንጥቅ ክፍለጦር የተሃድሶ ፕሮግራም አካሄዱ!
ከህልውናው የጦርነት ትንቅንቅ ባሻገር የእያንዳንዱን የፋኖ የግንዛቤ እድገት እና የባለ-ራዕይነት ጥበብን በማስረፅ የክፍለጦር አባላቶችን የተሃድሶ ስልጠና ተሰቷል። ይህ ፕሮግራም ትውልድንና ሀገርን ለሚረከብ ሀይል የመሪነትንና የሃላፊነትን አፅናፍ በማሳየት ለአሸናፊነት የሚያበቃን ቁልፍ የሀሳብ መንገዶች ተዘክረውበታል።
በፕሮግራሙ ላይ የአፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሃላፊ አርበኛ ብርሃን አረጋ ተገኝተው ከአማራ ፋኖ ለአማራ ህዝብ ምን ይጠበቃል? ህዝቡስ ምን ማድረግ አለበት? የህልውና ትግላችንን ለማሳካትና አሸናፊዎች ለመሆን ምን ይጠበቅብናል? ተሃድሶውስ ምን ያህል ትግላችንን ያስፈልገዋል? በሚሉ ቁልፍ አጀንዳዎች ላይ ሰፊ ትንታኔ የሰጡ ሲሆን በተሃድሶ መድረኩ አዎንታዊ አንድምታ ተችሯቸዋል።
ትውልድ ተረካቢን ሀይል ከፖፕሊዝም (ከስሜት) አስተሳሰብ ወደ አሰላሳይ እና ምክኒያታዊ ትውልድ ለመቀየር የተሃድሶው ስልጠና መሰጠቱ ለታጋዩ ትግልን በኢኮኖሚ እቅድ፣በድፕሎማሲ መስመርና በፖለቲካዊ ልዕልና ለህዝቦች ሁሉ የሚጠቅም አስተዳደርን ለመመስረት የሚጠቅም ስልጠና ነው ሲሉ የክፍለጦሩ አመራርና አባላት ተናግረዋል። ትግልንና ታጋይን ለመጠበቅ ከዘመኑ የእድገት አድማስ እኩል የሚስፈነጠር ትውልድን በአስተሳሰብ ልህቀት ማብቃት ከጦርነት ባሻገር ለህልውናችን ወሳኝ እርምጃ መሆኑን መተማመን ላይ በመደረሱ የተሀድሶው ስልጠና ተሰቷል።
መዳረሻውን ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ሕዝብ የሕልውና ተጋድሎ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 106ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ሰኔ 16/2018 ዓ/ም
