ar
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

الذهاب إلى القناة على Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

إظهار المزيد
2 940
المشتركون
-1524 ساعات
+287 أيام
+37030 أيام
أرشيف المشاركات
የጠላት ኮማንደሮችና የጦር ኦፊሰሮች ያለቁበት የወለጋው ትንቅንቅ! በአፋብን ወለጋ (ቢዛሞ)አንሻ ሰይድ ዕዝ ከጌጤ ግርማ መብረቅ ክ/ጦር፣ ከታፈረ አለሙ ሳተናው ክ/ጦር፣ ከአንገር ጉትን ክ/ጦርና ከአበጀ ጥበቡ ነበልባል ክ/ጦር የተወጣጡ አርበኞች በወሰዱት እርምጃ የጠላት ብልፅግና ኃይልን አከርካሪ ሰብረው አንፀባራቂ ድል መቀዳጀታቸውን ዕዙ በሕዝብ ግንኙነት መምሪያው በኩል ለመረብ ሚዲያ በላከው መረጃ አስታውቋል። በአንሻ ሰይድ ዕዝ የአበጀ ጥበቡ ነበልባል ክ/ጦር አርበኞች ጉትን ከተማ ዙሪያ በፈፀሙት የቆረጣ ሽምቅ ጥቃት በርካታ ወታደሮችን መደምሰስ ችለዋል። በምስራቅ ወለጋ ዞን መነሻውን ከአንገር ጉትን ከተማ አድርጎ ወደ ሊሙ ወረዳ ፊጥበቆ በመግባት ንፁኋን ላይ ጭፍጨፋ ለመፈፀም ሲገሰግስ በነበረ የጠላት ጦር ላይ ነው የደፈጣ ጥቃቱ የተፈፀመው። የአበጀ ጥበቡ ነበልባል ክ/ጦር አርበኞች፡ ከአንገር ጉትን ከተማ በቅርብ ርቀት ልዩ ስሙ መንደር 4 ላይ የጠላት ጦርን ሁለት ሦስት ቦታ ላይ ቆርጠው በወሰዱት እርምጃ፡ አንድ ኮማደር፣ አንድ ኦፌሰር፣ አንድ መቶ አለቃ የሚኒሻ ጠርናፊን ጨምሮ ከ15 በላይ ወታደሮች ሲገደሉ፡ በርካቶች ከከባድ እስከ ቀላል ሲቆስሉ፡ ቀሪው የጠላት ኃይል ሙትና ቁስለኛውን አዝረክርኮ አርቁምቢ መንደር አንድ ተብሎ ወደሚጠራው አከባቢ መፈርጠጡን ነው ዕዙ ለመረብ ሚዲያ በላከው መረጃ ያስታወቀው። በዚህ የፋኖ የማድረግ አቅምና ፍፁም ጀግንነት በታየበት የቆረጣ ማጥቃት፡ ከተደመሰሱ የአገዛዙ ወታደሮች በተጨማሪ፡ በርካታ የጦር መሣሪያዎችና ሌሎች ወታደራዊ ቁሳቁሶች በፋኖ ቁጥጥር ስር ውለዋል። ቀሪ የጠላት ንብረቶችም እንዲወድሙ መደረጋቸው ተረጋግጧል። በሌላ ግንባር፡ በዕዙ ስር ከጌጤ ግርማ መብረቅ ክ/ጦርና ከታፈረ አለሙ ሳተናው ክ/ጦር የተወጣጡ አርበኞች በቅንጅት በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አቤደንጎሮ ወረዳ ቱሉጋና ከተማ በነበረ የጠላት ጦር ላይ በወሰዱት እርምጃ በርካታ ወታደሮችን ደምስሰው አመርቂ ድል አስመዝግበዋል። አርበኞቹ በድሽቃና በብሬን ሽፋን ታግዘው የጠላት የቁም ምሽጎችን ጭምር የሰበሩ ሲሆን፡ የጠላት ጦርን አከርካሪ በመስበር በርካቶችን ደምስሰው ልዩ ልዩ የጦር መሣሪያዎችን ማርከው ታጥቀዋል። በተመሣሣይ፡ በምስራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ ውስጥ ንፁኋንን በመጨፍጨፍ ላይ በነበረ የጠላት ኃይል ላይ በአይሻ ሰይድ ዕዝ ስር ጀብደኞቹ የአንገር ጉትን ክ/ጦር አርበኞች በወሰዱት እርምጃ፡ በርካታ ጠላትን ደምስሰው ቀጠናውን መቆጣጠራቸው ታውቋል። በዚህ ተጋድሎ ሙትና ቁስለኛ ከተደረገው የጠላት ጦር በተጨማሪ፡ አገዛዙ የአማራን ሃብት ንብረት እየዘረፈ በተሽከርካሪ ሲጭንበት የነበረው ክሬን በፋኖ መማረኩንም አይሻ ሰይድ ዕዝ በሕዝብ ግንኙነት መምሪያው በኩል ለመረብ ሚዲያ በላከው መረጃ ገልጿል። ለዘመናት በስርዓታዊ የዘር ማጥፋት ዘመቻ ሲማቅቅ የኖረው የወለጋ-ቢዛሞ አማራ ህዝብ  በብልፅግና አገዛዝ የተጋረጠበትን የህልውና አደጋ ለመመከት ተደራጅቶ ጠላቶቹ ላይ የእሳት መዓት እያወረደ ይገኛል። እራስን ከእልቂት የመታደግ ተፈጥሯዊ መብቱን ተጠቅሞ የተደራጀውና ብሶት የወለደው ጀግናው የአይሻ ሰይድ ዕዝ ሠራዊት ብርቱ የሆነ የፀረ ማጥቃት እርምጃ በመውሰድ የሕዝቡን ሕልውና ለማረጋገጥ የሚያደርገውን ተጋድሎ አጠናክሮ ቀጥሏል።

ማን ይናገር የነበረ ፥ ማን ያርዳ የቀበረ‼️ አይበገሬዋ አርበኛ አይናዲስ ዋለልኝ ከሰላማዊ የአደባባይ የህዝብ ጥያቄ እስከ አብዮታዊ የትጥቅ እንቅስቃሴ የትግል አበርክቶ በጥቂቱ ፦ ትላንት በጨለማው ዘመን የአማራን ፓለቲካዊ አጀንዳ ወደ አደባባይ ይዞ መቅረብ ይቅርና "አማራ ነኝ!" ብሎ ለመናገር አብዛኛው በሚሽኮረመምበት ወቅት ፣ከባድ ማህበራዊ ድባቴ ውስጥ በነበርንበት ወቅት ፣ብዙኅኑ ከአገዛዙ ጎን ተሰልፎ በሚያሸርግድበት ወቅት የህዝብን አጀንዳ ፣በህዝባችን ላይ እየደረሰ ያለውን በደልና ግፍ በጥቅሉ የህልውና ስጋትና አደጋ በንጉስ ተክለሃይማኖት አደባባይ ይዞ በመውጣት በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀስ ጀግና እህታችን ናት። የአማራ ህዝብን አብዮት ለመውለድና አዲሱን ትውልድ የማንቃት፣የማሰልጠን እና በህዕቡ የማደራጀት ወቅት የሚሰጣትን አብዮታዊ ግዳጅ ወይም አደራ በብቃት የተወጣች የሴቶች ቁና ፥ ደፋር ታጋይ ፥ አታጋይ አርበኛ ናት። በዚያም የሰልፉ ዘመን በደብረ ማርቆስ ንጉስ ተክለሃይማኖት አደባባይ በተደረጉ በርካታ መሬት አንቀጥቅጥ አትግደሉን ፣ አታፈናቅሉን ፣ ሞት በቃን ፣ መሳደድ በቃን መፈናቀል በቃን የቤተክርስቲያን መቃጠል ይቁም ፣ የካህናትና የኦርቶዶክስ አማንያን ግድያ ይቁም ወዘተ በሚሉ ተቃውሞ ሰልፎች ከጀግና የደብረ ማርቆስ ወጣቶች ጋር በመሆን የተቃውሞ ሰልፎችን በማዘጋጀት ፣ በመምራት እና የአማራ ህዝብን አጀንዳ በዓለም አቀፍ መድረክ ትኩረት ሳቢ እንዲሆን የአንበሳውን ድርሻ ከተወጡ የንጉስ ተክለሃይማኖት የመንፈስ ልጆች መካከል በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀስ ጀግና የህዝብ ልጅ ናት። በአብዮቱ ዋዜማ ወቅት በአብዮታዊው መሪያችንና ምልክታችን አርበኛ ዘመነ ካሴ ሃሳብ አመንጭነትና ትዕዛዝ "የእሳት ኳሶች!" ማደራጀትና ዝግጁ የማድረግ እጅግ ወሳኝ በሆነው የትግል ምዕራፍ ወቅት ፦እጅግ ውስብስብና ፈታኝ ፣ በስራ ላይ መሳሳት ፣ የመረጃ መሽሎክ ህይወትን ሊያሳጣ በሚችል ፈተና በሚያስከትለው እጅግ ከባድ የትግል ዘመን የተሰጣትን ተልኮ በመቀበል በበርካታ የጎጃም ከተሞች በመንቀሳቀስ ለአብዮቱ እርሾ የሆኑ ከሃያ እስከ ሰላሳ የሚሆኑ የእሳት ኳሶችን የማደራጀት ተግባርን ከሌሎች ወንድሞችን ጋር በመሆን በብቃት የተወጣች አይበገሬ አርበኛ ናት።የእሳት ኳሶች አደረጃጀት ለአብዮቱ መፈንዳት ያበረከተውን የላቀ አስተዋፅኦ በአደረጃጀቱ የተሳተፉ አብሪ ኮከብ ታጋዮችና የተፈፀመውን ጀብዱ ለታሪክ ተመራማሪዎች ጥናት ፥ ምርምር ልተወውና በተጨማሪ የአማራ ህዝባዊ ኃይል (ፋኖ) አባላትን እንዲሁም ንቁና ብቁ የአማራ ወጣቶችን በከተማ ውስጥ ለምናዋልደው አማራዊ አብዮት አንቅቶ ፥ አደራጅቶና አብቅቶ ማዘጋጀት ፤ በበርሃ ውስጥ ሄዶ ላቅ ያለ ዝግጅት የሚያደርገውን የአማራ አብዮታዊ የፋኖ ሀይል በመመልመል "በጎዛም ጭምት በርሃ ፣ በአባይ በርሃ ፣ በአብያ በርሃ ፣ በቡሬ በርሃ " ወዘተ ቦታው ድረስ በመሄድ ቦታ መረጣና ተያያዥ ተግባራትን ለአብዮቱ እጅግ ወሳኝ የሆኑ ስራዎችን የሰራች የዘመናችን ጣይቱ ፥ ሸዋረግ ገድሌ ናት። በአዲሱ ትውልድ ፣ በአዲስ አስተሳሰብና ተስፋ ከሶስት አመታት በፊት በተቀጣጠለው አማራዊ አብዮት በፊት አውራሪ አዝማችነት የንጉስ ተክለሃይማኖትን ከተማ ደብረማርቆስን ከአገዛዙ ነፃ የማውጣት፣ የፀጥታና የፓለቲካ መዋቅሩን የማፈራረስ ወሳኝ ተግባር ላይ አብሪ በመሆን የታገለች፥ያታገለች ጀግና ፣ደፋር አብዮተኛ አርበኛ ናት። አርበኛ አይናዲስ ዋለልኝ ላለፉት ሶስት የትጥቅ ትግል አመታት ከአማራ ህዝባዊ ኃይል (ፋኖ) እስከ የአማራ ፋኖ በጎጃም (አፋጎ) ፤ ከአፋጎ እስከ አፋብኃ ፤ ከአፋብኃ እስከ ግዙፉ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ድረስ ደጋ ወጥታ፣ቆላ ወርዳ ፤ ተራራ ዳገቱን ወጥታ፣ወንዙንና ሸንተረሩን አቋርጣ ፣በዱር ገደሉ አድራ እጅግ ፈታኝ በሆነው የትግል ምዕራፍ ውስጥ ድርጅታችን የሰጣትን አብዮታዊ ግዳጅ በብቃት፣በታማኝነት፣በቅንነት እና በሀቀኝነት ግዳጇን የምትከውን የፅናት ተምሳሌት የሆነች ጀግና መሪ ናት። ጀግናዋ ጓዴ! አይናዲስ ዋለልኝ በአሁኑ ወቅት አንድ አማራዊ ቤታችን በሆነው የአዲሱ ትውልድ ድርጅት የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) የሴቶች ጉዳይ መመሪያ ኃላፊ በመሆን የተሰጣትን አብዮታዊ ግዳጅ ትግል አቆርቋዥ ፣ ከፋፋይ እና አውርቶ አደር የወገንን ዩኒፎርም የለበሱ የሚዲያ ሚሊሾች ጩኸትና ስም ማጥፋት ሳይበግራት ፣ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳትል የተሰጣትን ከባድ ሃላፊነት በልበ ሙሉነት እየሰራች ትገኛለች። እህታለም ፥ ጓዴ ፥ አይናችን አንቺና መሰል ጀግና እህቶቻችን በዚህ ትግል ውስጥ በታሪክ አምድ በትውልዱ የሚዘከር ፣ የሚወደስ እና ጮክ ተብሎ የሚነገር ደማቅ ታሪክ እየሰራችሁ ነው። በርችልን ፥ በርቱልን! ክብር ለሚገባው ክብር መስጠት ያለ ፥ የነበረ ፥ ወደ ፊት የሚኖር አገራዊም ዓለም አቀፋዊም የወል ሃቅ ነው። መበርታት ብቻ! ክፋት ለማንም፣በጎነት ለሁሉም! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ ፣አዲስ ተስፋ! Hailemichael Bayeh

በከባድ መሳሪያ በሞርተር ደብረ ማርያም ቀበሌ ሸማት ጎጥ የአራት (4) የንፁሀን አርሶ አደሮች ቤት ከጥቅም ውጭ አድርገዋል። $$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$ .......ሰኔ 15/2018
+2
በከባድ መሳሪያ በሞርተር ደብረ ማርያም ቀበሌ ሸማት ጎጥ የአራት (4) የንፁሀን አርሶ አደሮች ቤት ከጥቅም ውጭ አድርገዋል። $$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$ .......ሰኔ 15/2018 ዓ.ም የፋኖን ክንድ ብትር መቋቋም ያቃተው የብልፅግናው ወንበር አስጠባቂው በሞርተር ደብረ ማርያም ቀበሌ ሸማት ጎጥ የአራት የንፁሀንን አርሶአደር ቤታቸው የፈረሰባቸው አርሶ አደሮች። 1ኛ.ፍቃዴ መልኬ 2ኛ.ባወቀ ተሹ 3ኛ ልገረው አይቸህ 4ኛ.ጌትነት ፈንታሁን ሲሆኑ ፊት ለፊት ለመግጠም ሞራል የሌለው የብልፅግና አገልጋይ በዛሬው እለትም የተለመደውን የበቀል ጥሙን የአርሶ አደሮችን ቤት አፈርሷል። በዚህ ሊቆም እና ሊሸማቀቅ የሚችል አንድም አማራ እንደሌለ ይኸን ስርአት ከስሩ ነቅለን ለመጣል አስፈላጊውን መስዋት ለመክፈል ዝግጅ መሆናቸውን አርሶ አደሮች ተናግረዋል። የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክፍለ ጦር የ2/ጁ እነሴ ወረዳ ሚዲያና ግንኙነት መረጃውን አጋርቶናል።

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 101ኛ ኮር 35ኛ ክፍለጦር ከስርዓቱ ጨፍጫፊ ጦር በመክዳት ፉኖን የተቀላቀሉትን የሰራዊት አባል የአማራ ፉኖ የትግል አላማን በተመለከተ የፖለ
+1
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 101ኛ ኮር 35ኛ ክፍለጦር ከስርዓቱ ጨፍጫፊ ጦር በመክዳት ፉኖን የተቀላቀሉትን የሰራዊት አባል   የአማራ ፉኖ የትግል አላማን በተመለከተ የፖለቲካ ግንባታ በመስጠት  ወደ አማራ ትግል በፍላጎታቸዉ እንድቀላቀሉ ተደርጓል። ከሰኔ 10 -13  ድረስ ከአብይ አህመድ  ዙፉን ጠባቂነት ወደ ፉኖ ሙሉ ትጥቃችውን ከነፍስ ወከፍ እስከ ቡድን መሳሪያ በመያዝ የተቀላቀሉትን 16 የስራዊት አባላትን ትላንት ሰኔ 14/2018 ዓ.ም የአማራ ፉኖ ብሄራዊ ንቅንቄ ምክትል ህግ መምሪያ ሀላፊ አርበኛ መሀመድ ሞገስ ፡ የአማራ ፉኖን ወቅታዊ የትግል ሁኔታ :ትግሉ የደረሰበትን ደረጃ፣የአማራ ፉኖ በደም እና አጥንቱ ስለመሰረተው መሪ ድርጂት /አፉብን/ የትግል አቋም:የምርኮኛ አያያዝ እና የድርጂታችን የድፕሎማሲ ቅቡልነት እንድሁ ውጊያውን እንዳሸነፍን የሚያመለክቱ ማሳያዎችን እና ጦርነቱንም ያለ ጥርጥር በስኬትና በድል እንደምናሸንፍ ያሉትን መልካም አጋጠሚዎችን እና መሰል ጉዳዮችን ከስራዐቱ ከድተው ፉኖን የተቀላቀሉ የሰራዊት አባላትን  ከላይ በተዘረዘሩት ጉዳዮች የፖለቲካ ግንባታ ሰጥተው ወደ ክፍለጦሩ መደበኛ ሰራዊት እንድቀላቀሉ ተደርገዋል ሲል የ 35ኛ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት መረጃዉን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!! አፋብን ወሎ ቤተ- አማራ ምኒልክ ዕዝ  ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!! ሰኔ 15/2018 ዓ.ም

+4
በሶስቱም አቅጣጫ የአብይ ሰራዊት በየሄደበት ሰብአዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ እያስተናገደ ይገኛል። ============================= .....ሰኔ 15/2018 ዓ.ም በዛሬው እለት መነሻውን በተለያዩ ሶስት አቅጣጫ ከአዴት ከጎንጂ እና ከሞጣ የአማራን አርሶአደር ትጥቅ አስፈታለሁ በማለት የተንቀሳቀሰው የጠላት ሀይል በንስሮች የ201ኛ ኮር 54ኛ ክፍለ ጦር ሻለቃ 3 እና የ102ኛ ኮር 33ኛ ክ/ጦር 5ኛ ሻለቃ የጋራ ጥምረት በመፍጠር ወለቆይ ላይ ጠላት እንደ እባብ ሲቀጠቀጥ አርፍዶ ሙት እና ቁስለኛውን በመያዝ ወደ መጣበት ቀጠና እየተዘረከረከ እንዲመለስ አድርገውታል። በሌላኛው ግንባር ከሞጣ ከተማ በመነሳት በዙ=23 የተደገፈ የማጥቃት ሙከራ ቢያደረግም አይበገሬወች የ54ኛ ክ/ጦር ሻለቃ ሁለት አጋም ውሀ ላይ በተለያዩ አቅጣጫ ገዥ ቦታወችን በመያዝ ጥቃት በመክፈት ዙ=23ቱን በመጣበት እግሩ ተመልሶ ወደ ሞጣ እንዲገባ በማድረግ አንገት አስደፍተው ቁስለኛውን ሸክፎ እንዲመለስ አድርገውታል። አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስተስፋ የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

በ2እጅ እነሴ ወረዳ ወብ ቀንጫሪት ቀበሌ ላይ በወቅታዊ ጉዳዮች ከህዝቡ ጋር ውይይት ተካሄደ። ============================= ሰኔ15/2018 ዓ.ም የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር
+7
በ2እጅ እነሴ ወረዳ ወብ ቀንጫሪት ቀበሌ ላይ በወቅታዊ ጉዳዮች ከህዝቡ ጋር ውይይት ተካሄደ። ============================= ሰኔ15/2018 ዓ.ም የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር በ2እጁ እነሴ ወረዳ ወብ ቀንጫሪት ቀበሌ ህዝብ ጋር ሰኔ 14/2018 ዓ.ም የጋራ ውይይት ተደርጓል። ➺ በፍትህ አሰጣጥ እና የመልካም አስ/ር ➺በፀጥታ ዙሪያ ያሉ ችግሮችን በመለየት ➺የአፋብን ትግል ከየት ወደየት የደረሰበት ሁኔታ እና ህዝባዊ አስተዳደርን ጨምሮ የተገመገመና የወደፊት አቅጣጫ የተቀመጠበት ሲሆን ትግላችን አሁን ላይ የደረሰበትን ሁኔታ አጭር ማብራሪያ በኮሩ እና በክፍለ ጦር አመራሮች የማስረዳት ስራ ተሰርቷል። እናደራጃለን ! እንመክራለን! እንፈፅማለን!! አዲስ ትውለድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ!! አፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

#የአማራ_ፋኖ_ብሄራዊ_ንቅናቄ(አፋብን) በላይ ዘለቀ ዕዝ #ዘመቻ_መቶ_አለቃ_ያለው_አዱኛ እና የመብረቅ ክፍለ-ጦር አመራሮች በጋራ በመሆን ወደተለያዩ የበላሳ አካባቢዎች በመንቀሳቀስ ለተከታታይ 3ቀናት  ከማህበረሰቡ እና በተለያዩ ምክንያት ከአደረጃጀት ውጭ ሲንቀሳቀሱ ከነቀሩ  ሃይሎች ጋር ውይይት ተደረገ ። በተለያየ ምክንያት ከአደረጃጀት ከውጭ ከሆኑ  ሃይሎች ጋር ውይይት የተደረገ ሲሆን በውይይቱ የተለያዩ ጥያቄዎች  ተነስተው በዋናነት የዕዝና የኮር አመራሮች ላይ ችግሮች እንዳሉ ጠቅሰው ችግሮቹ እንዲስተካከሉና ቀጣይ እንዳይደገሙ በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል ያሉ ሲሆን  ጥያቄያቸውን ተቀብለው ውስጣዊ ችግሮቻቸውን በመፍታት በመቅራዊ አደረጃጀቱ እንዲገቡ በማድረግና አንደነትን በማጠንከር ተቋማዊ አሰራርን ተከትለው ህዝባቸውን በቅንነት በታማኝነት እንዲያገለግሉ ተቋማቸውን እንዲጠብቁና ለማይቀረው ድላችን እንዲዘጋጁ ማድረግ ተችሏል። ከማህበረሰቡ ጋር በተደረገ ውይይት የተለያዩ ችግሮችና ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን በዋናነት ድም መመላለስ የሚባል አጉል ባህል በማህበራዊ ሂወታቸው ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰባቸው እንደሆነ ገልፀዋል ። አመራሩም ጥያቄዎችንና ችግሮችን መነሻ በማድረግ ችግሮች በዘላቂነት እልባት አግኝተው ማህበረሰቡ በጋራ እንዲኖር በጋራ እንዲያለማ እርስበርስ መተማመን እንዲፈጠር ለማድረግ ውስጣዊ ችግሮቻችን በዘላቂነት ይፈታልናል ያሉትን የተለያዩ ህጎችን ከማህበረሰቡ ጋር ያወጡ ሲሆን  የገደለ እንዲክስና እንዲታረቁ በማድረግ ድጋሜ መገዳደል እንዳይኖር የሚያደርጉ  ህጎችንም በማውጣት በማህበረሰቡ ውስጥ ያሉ አጉል ባህሎችን በዘላቂነት ለመፍታት ይረዳዘንድ ማህበረሰቡ ከህግ አካላት ጋር  በመሆን ህግ ለማስከበር ዝግጁ እንዲሆን የጋራ ውሳኔ ላይ ተደርሷል ። ክብር ምስጋና ለትግሉ ሰማዕታት 🙏 ህሊናችን በተባበረ ክንዳችን 💪 አማራ በጀግና ልጆቹ ያሸንፋል!! መብረቅ ክፍለ-ጦር ህ/ግንኙነት ክፍል Alazar Dagmawi Tedros

"ጦሩ የማን ነው የበላይ ጥሪት የዘመነ ነው" ይህ ድምፅ የትውልድ ቃልኪዳን ነው ፣ ጦሩ የህዝብ ፣ መሪውም የታሪክ ባለአደራው አርበኛ ዘመነ ካሴ!" ዛሬ በእነዚህ ድንቅ የአማራ ፋኖ ወጣት ሰልጣኞች ድምፅ ውስጥ የሚስተጋባው "ጦሩ የማን ነው?" የሚለው ጥያቄ ተራ ወታደራዊ ጥያቄ ሳይሆን ፣ የሉዓላዊነትና የማንነት ምንጭን የመጠየቅ ጥልቅ ፖለቲካዊ ፍልስፍና ነው። "የበላይ ጥሪት" ሲባል ፣ የጀግናው ደጃዝማች በላይ ዘለቀን ወኔ የታጠቀ ፣ የዘመኑን ፈተና ለመሻገር የተዘጋጀ የቁርጥ ቀን ልጅ መሆኑን ለማብሰር ነው። "የበላይ ጥሪት የዘመነ ነው" የሚለው ስንኝ ደግሞ ከታሪካዊው ደጃዝማች በላይ ዘለቀ የተወረሰውን የላቀ የሞራል ልዕልና እና የዛሬውን ተጨባጭ መሪነት የሚያቆራኝ የታሪክ ድልድይ ነው። አርበኛ ዘመነ ካሴን በዚህ ትውልድ አይን ውስጥ "መሪ" ብቻ ሳይሆን "ምልክት" የሚያደርገው የአመራር ጥበቡ ከኢትዮጵያ ነባር የአርበኝነት ወግ ጋር መቆራኘቱ ነው። እርሱ ከህዝብ ጥልቅ ፍላጎት የሚመነጭን የመሪነት ፀጋን የታጠቀ መሪ ነው። ሰልጣኞቹ "የበላይ ጥሪት" ሲሉ ፣ የአባይ ሸለቆው ነበር የሶማው አንበሳ የደጃዝማች በላይ ዘለቀን ያልተንበረከከ መንፈስ አርበኛ ዘመነ ካሴ ዳግም ህያው አድርጎታል ማለታቸው ነው። ይህ "በላይነት" የስነ-ልቦና የበላይነት ነው ፣ ይህ "በላይነት" የማንነት ኩራት ነው ፣ ይህ "በላይነት" ፍርሃትን አሸንፎ በራስ እግር ላይ የመቆም ፖለቲካዊ ውሳኔ ነው። በዚህ የሰልጣኞች መዝሙር ውስጥ የሚታየው ወታደራዊ ስልጠናን ብቻ ሳይሆን ፣ አንድ ትውልድ ራሱን ከባርነትና ከጭቆና ቀንበር ነፃ ለማውጣት የሚያደርገውን የነፍስ ተጋድሎ ነው። ሰልጣኞቹ የአርበኛ ዘመነ ካሴን ስም ሲጠሩ ፣ ግለሰቡን ለማምለክ ሳይሆን ፣ እርሱ የያዘውን ዓላማና የተሸከመውን የታሪክ አደራ ለማክበር ነው። በፖለቲካዊ ረገድ ፣ አርበኛ ዘመነ ካሴ የዚህን ትውልድ የነፃነት ጥማት ወደ ወታደራዊ ዲሲፕሊንና ወደ ፖለቲካዊ ንቃት የቀየረ የስትራቴጂ ጥበበኛ ነው ፣ ህዝባዊ ንቅናቄን ወደ ተደራጀ ኃይል የመለወጥ ስልታዊ ብቃት አሳይቷል።  ይህ ኃይል ደግሞ መነሻውም መድረሻውም ህዝብ መሆኑን ጦሩ የማን ነው? የህዝብ ነው! የሚለው ምላሽ በግልፅ ያረጋግጣል እዚህ ላይ መሪው አርበኛ ዘመነ ካሴ ፣ የግል ዝናን ሳይሆን የጋራ ድልን ፣ የግል የበላይነትን ሳይሆን የፍትህ የበላይነትን የሚሰብክ የንቅናቄው ማዕከል ሆኖ ይገኛል። አርበኛ ዘመነ ካሴ በዚህ ትውልድ አይን ውስጥ መሪ ብቻ አይደለም ፣ እሱ የተገፋው ድምፅ ፣ የተረሳው ታሪክ እና የነገው ተስፋ ምልክት ነው። አርበኛ ዘመነ ካሴ የዚህ ዘመን የነፃነት ትርክት ቀማሪ፣ የትውልዱ የፅናት ማገዶ እና የታሪክ አደራ ተረካቢ ነው። ዛሬ በአቧራማው የልምምድ ሜዳ ላይ የሚሰማው ድምፅ ፣ ነገ በአገሪቱ የፖለቲካ ጠፈር ላይ የፍትህና የነፃነት ብርሃን ሆኖ መውጣቱ የማይቀር ሃቅ ነው። ታሪክ ራሱን በጀግኖች ትከሻ ላይ ዳግም ይተክላል ፣ ያ ተክል ደግሞ ዛሬ በአርበኛ ዘመነ መሪነትና በፋኖ ቆራጥነት እያቆጠቆጠ ይገኛል። ©Birhanu Chalie Demelash https://www.facebook.com/share/1BMtrRDfpz/

የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮር የ49ኛ ክፍለጦር 2ኛ ሻለቃ በአገዛዙ ሰራዊት ላይ መብራቃዊ ጥቃት ፈፀመ። የ49ኛ ክፍለጦር ሰኔ 14/2018ዓ/ም በተለያየ አቅ
+2
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮር የ49ኛ ክፍለጦር  2ኛ ሻለቃ በአገዛዙ ሰራዊት ላይ መብራቃዊ ጥቃት ፈፀመ። የ49ኛ ክፍለጦር  ሰኔ 14/2018ዓ/ም በተለያየ አቅጣጫ የመጣውን የአገዛዙ ሰራዊት  መብረቃዊ ጥቃት በመሰንዘር ወደ መጣበት እንዲመለስ አድርገዉታል። የጨፍጫፊውና የአምባገነኑ ስርዓት ያለ የሌለ ሀይሉን በመያዝ ጎብየ ከተማ መነሻዉን አድርጎ ቡሆሮ፣ ቃሊም፣ቀይ አፈር፣ ከአሰገዳና ወደ ጭራሮ አምባ እንቅስቃሴ ቢሞክርም የ49ኛ ክፍለጦር 2ኛ ሻለቃ አናብስቶች  በሁሉም ግንባር  የተቀናጀ ዉጊያ በማድረግ ወደ መጣበት ሊመልሱት ችለዋል። ከአናብስቶቹ አፈሙዝ የተረፈዉ የጠላት ኋይል እግር  አዉጭኙን ሲፈረጥጥ በየ ገደሉ ሲንከባለል የዋለ ሲሆን የተቀረዉ  የቆሰለ ጓዱን እንኳን ሳያነሳ ሳያነሳ ወደ ወልዲያ ከተማና ጎብየ ከተማ እየፈረጠጠ ተመልሷል። የ102ኛ ኮር ቃሊም፣ቡሆሮ ፣ሳንቃ ከተማ ሰፊ ቀጠናዎችን በመቆጣጠር የአገዛዙን ወታደር መፈናፈኛ በማሳጣት የአማራ ህዝብ የፖለቲካ ጥያቄ መሆኑን ለብልፅግና ምስለኔዎች ትምህርት የሰጠ አውደ ውጊያ እንደ ነበር የአይን እማኞች ተናግረዋል። በመጨረሻም በቡሆሮና ቃሊም በነበረው አውደ ውጊያ ከ49ኛ ክፍለጦር በተጨማሪ የ11ኛ ክፍለጦር ቃኝ  ጀግኖች ከወንድሞቻቸው ጋር በመሰለፍ የጨፍጫፊውንና የእብሪተኛውን አገዛዝ ወታደር ሙትና ቁስለኛ በማድረግ በቀይ ቀለም ታሪካቸውን ፅፈዋል ሲል የ102ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃዉን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!! አፋብን ወሎ ቤተ- አማራ ምኒልክ ዕዝ  ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!! ሰኔ 15/2018 ዓ.ም

44ኛ ክፍለ ጦር ከቲሊሊ አብስከን ሰከላ እስከ ብር አዳማ ድል ተቀዳጅቷል። ሰኔ 14/2018 ዓ.ም አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 44ኛ ክፍለ ጦር፡ አረመኔው የብልፅግና ስርዓት ጠባቂ መካለከያ ቡድን የ44ኛ ክፍለ ጦርን ቀጠናን በረገጠበት ሰሃት ጀምሮ በተከፈተበት የሶስት ግንባር ዉጊያ የሽንፈት ፅጓ ተጎንጭቷል። ጀብደኛዉ 44ኛ ክፍለ ጦር ከ102ኛ ኮር 33ኛ ክፍለ ጦር ጋር በመጣመር ብር አዳማ አብስከን ላይ በሰሩት ኦብሬሽን ጠላትን ድባቅ በመምታት 9 ክላሽ በመማረክ ብዛት ያለውን የጠላት ሀይል መደምሰስ ችሏል። ሰከላ ወረዳ እኩለ ቀን ላይ በምርኮ የተጀመረዉ ድል በቲሊሊ ወረዳ አሽፋ ላይ ሌላ ድል ተደግሟል። ከቡሬ እንጅባራ ፉነተሰላም ድረስ አለኝ የሚለውን ሃይል በማሰባሰብ የመጨረሻ ዙር መዉጫ ወይም መፈርጠጫና ጊዜ መግዣ በሚል ስሁት እሳቤ 105ኛ ኮር 44ኛ ክፍለ ጦርን ለመክበብ ሙከራ አድርጓል። አቅመቢሱ የብልፅግና ሰራዊት እንደተለከፈ ዉሻ በየ ገጠሩ አካባቢ ያገኘውን ንፁሃን የአማራ ህዝብ ከማንገላታት፣ከመረሸንና ከመዝረፍ ባሻገር ፋኖ ላይ ምንም አይነት ድል እንደማያገኝ በሶስት አመታቱ የትግል ዘመናት በሙሉ ቢያውቅም ሀገር ለቆ ለመፈርጠጥ ጊዜ ያገኝ ዘንድ እያፈሰ ያስገባውን ህፃናት በግዳጅ እንደ ከብት እየነዳ ያመጣው ቢሆንም የ44ኛ ክፍለ ጦር ተርቦች ከባቢዉን ሀይል መልሶ ከበባ በመስራት ሲገርፉት አምሽተዋል። ከጥዋት 5:30 በሶስት ግንባር የተጀመረዉ ዉጊያ አድማሱን እያሰፋ አስከ12:00 ዘልቆ ጠላት አላማዉ ሳይሳካ ከሁለት ደርዘን በላይ ሙትና ቁስለኛ ታቅፏል። የብልፅግና ስርዓት የመጥፊያዉ ሰሃት መድረሱን እርግጠኛ የሆኑ የሰራዊቱ አባላት የመዋጋት ሞራል እንደሌለቸዉ በይፋ እየተናገሩ እየከዱና እየኮበለሉ ወደ ፋኖ እየተቀላቀሉ ህይወታቸዉን እያተረፉ ባለበት በዚህ አጣብቂኝ ሰሃት የቀረዉ ነፍሰ በላ ቡድን እየክለፈለፈ በሚሄድበት ቀጠና ሁሉ የእሳት እረመጥ የሆነዉ ጀግናዉ የአማራ ፋኖ ጭንቅላቱን እያፈረሰ በየ ጥሻዉ ወድቆ እንዲቀር እያደረገዉ ቀጥሏል። ለመክበብ አስበህ ወጠህ አደለም የኮንክሪት ምሽግ  ሰርታችሁ እንዳልተረፋችሁ አውቃችሁ በጊዜ እጃችሁን ስጡ መልዕታችን ነው። አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 105ኛ ኮር 44ኛ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት

ለወረራ ወደ ከሰም የገባው የጠላት ኃይል በፋኖ  ከበባ ውስጥ ገብቶ መውጫ ያጣ ሲሆን ነጎድጓድ ክፍለ ጦር ላለፉት ተከታታይ ወራት በንድፈ ሐሳብና በተግባር ያሰለጠናቸውን የህክምና ባለሙያዎች አስመረቀ!!      ሰኔ 14/2018 ዓ.ም አ.ፋ.ብ.ን  ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ    በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ተጉለት እና ቡልጋ አውራጃ በሀገረ ማርያም ከሰም  ወረዳ በሁሉም የወረዳው የገጠር ቀበሌዎች እና ታዳጊ ከተሞች ፋኖን ለመደምሰስ በሚል ቀቢፀ ተስፋ የተንቀሳቀሰው የአገዛዙ ጥምር ጦር ከፍተኛ ኪሳራ አስተናገደ:: ከተለያዩ የሸዋ አካባቢዎች ኃይል ሰብስቦ በ42 ተሽከርካሪ ጭኖ ያመጣውን ኃይል  በሀገረ ማርያም ከሰም ወረዳ የኃይለማርያም ማሞ ክፍለጦር የፋኖ ኃይል  በሚንቀሳቀሥበት 6 ቀበሌዎች ማለትም በጎርፎ ፤በሥችት፤ በቅዱሥጌ ፤በዬላት እና በዛላ ዘንባባ ቀበሌ መነሻውን  ከወረዳ መዲና ሾላ ገበያ ያደረገ ሲሆን በሌላ አቅጣጫ መነሻውን ምንታምር ከምትባል ከተማ አድርጎ ፋኖዎች ይገኙበታል ብሎ ወዳሰበበት አከርሚት ቀበሌ ቢያመራም ጠላት ባልጠበቀው መልኩ ከበባ ተደርጎበት ሰብዓዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ አስተናግዷል::   ጠላት ያለ የሌለ ሀይሉን ሰብስቦ የፋኖ ኃይሉ ላይ ጥቃት ለማድረስ ቢሞክርም  በአካባቢው የሚንቀሳቀሱት በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ በከሰም ኮር ሥር ያሉት ወንድማማቾቹ የነበልባል ክፍለጦር ቃኚ ሻለቃ እና የሃይለማርያም ማሞ ክፍለጦር ሙሉ የሰራዊት አባላቱ በጋራ በመሆን የጠላትን እቅድ ማክሸፍ ችለዋል::     የጠላት ወራሪ ኃይል የፋኖን ክንድ መቋቋም ሲያቅተው እራሱን ለማዳን ከማጥቃት የውጊያ እቅዱ ወደ መከላከል እንዲገባ ማድረግ የተቻለ ሲሆን ጠላት ተራራማ ቦታዎችን ይዞ የመከላከል ውጊያ እያደረገ ይገኛል:: ጦርነቱ ይህንን ዜና እስካዘጋጅንበት ሰዓት ድረስ የቀጠለ ሲሆን ሌሎች የተጋድሎ ዜናዎችን በነገው ዘገባችን በዝርዝር የምንመለስበት ይሆናል::   በሌላ ዜና የአፋብን አፄ ዘርዓ ያዕቆብ ፩ኛ ኮር ነጎድጓድ ክፍለ ጦር ላለፉት ተከታታይ ወራት በንድፈ ሐሳብና በተግባር ያሰለጠናቸውን የህክምና ባለሙያዎች አስመረቀ!! ​በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ላይ እንደተገለጸው፣ ይህ ሥልጠና በክፍለ ጦሩ ውስጥ ቀደም ሲል የነበረውን የህክምና ባለሙያዎች እጥረት በእጅጉ ለመቅረፍ አስተዋጽኦ እንደሚያደርግ ተጠቁሟል።,​የምረቃ ሥነ ሥርዓቱን በንግግር የከፈቱት የነጎድጓድ ክፍለ ጦር ዋና መሪ አርበኛ አምባሳደር ጌጤ፣ የሥልጠና ተቋሙ “ፕሮፌሰር አስራት የህክምና ቡድን” ተብሎ መሰየሙን ገልጸው፣ ስያሜውም ታላቁን የህክምና ሊቅ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስን ለማሰብና ለማክበር እንደሆነ አስረድተዋል። ​በተጨማሪም የፕሮፌሰር አስራት ወልደየስን የሕይወት ታሪክ በአጭሩ በማቅረብ፣ ለአማራ ሕዝብ የከፈሉትን መስዋዕትነትና አስተዋጽኦ ለታዳሚዎች አብራርተዋል።​በተለያዩ ፕሮግራሞች የታጀበው የምረቃ ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኙት አርበኛ ሞጆ አዳነ የክፍለ ጦሩ የፖለቲካ መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አስር አለቃ  በቃሉ ማሞ የክፍለ ጦሩ የሕዝብ አስተዳደር መምሪያ ኃላፊ እና አርበኛ አብርሃም ዳኛቸው የክፍለ ጦሩ ምክትል ወታደራዊ አዛዥ ለተመራቂዎቹ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት በማስተላለፍ ስለ ምረቃው አስፈላጊነት ሐሳባቸውን አካፍለዋል። ​በተጨማሪም እንግዳ ተናጋሪ ሆነው የተገኙት ዶ/ር አብደላ እድሪስ፣ ለተመራቂዎቹ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈው፣ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ሐኪም፣ ፓይለት፣ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች እና ፖለቲከኛ እንደነበሩ ጠቅሰው፣ ተመራቂዎቹም ሐኪሞችና ወታደሮች እንደመሆናቸው ከማንኛውም አድሎአዊ አሠራር ነፃ ሆነው ሙያቸውን በሥነ ምግባርና በህሊና እንዲያገለግሉ አሳስበዋል። እንዲሁም በአስቸጋሪ ሁኔታዎች ውስጥ ሥልጠናውን ለሰጡት አርበኛ ሀኪም ፍቅረማርያም ታዬ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። ​በመጨረሻም የክፍለ ጦሩ ዋና ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ መስፍን ኃይሉ የቀጣይ ሥራ አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ ለተመራቂዎቹ የምረቃ ሰርተፍኬት ተበርክቶ የምረቃ ፕሮግራሙ ተጠናቋል። ​ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! ​"ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን የአፋብን ሽዋ ጠቅላ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ!!

የብልጽግና "ኮርቻ" ታጣቂ ሃይል በጉና ክፍለ ጦር በምድር ድሮን በሆኑት እስቴ ዴንሳ ብርጌድ ተከታታይ ቀናት ባካሄዱት ተጋድሎ የጠላት ሃይል አከሪካሪውን በመስበር ድል ተቀዳጁ። ======================= ሰኔ 14/2018 አፋብን ሰሜን አማራ ቀጠና በላይ ዕዝ ሜ/ጀኔሬል ውባንተ አባተ፩ኛ ኮሩ ስር ጉና ክፍለ ጦር ልማደኛዋ እስቴ ዴንሳ ብርጌድ በእስቴ ወረዳ ፣ በብሩአደጌ፣ በሸንበቆች፣በጎንደርበር፣ውስጤዱር፣በገናመምቻ፣በጽዮን፣በሾለክት፣በለበጥእስላምአገር፣ በምክሬ ከተማ፣ በደንጎልት ተራራ ማማ ስር በተባሉ ልዩ ቦታዎች የአገዛዙን ሰራዊት በውጫ በግቢያ አስጥተውታል። ወራሪው ሃይል በዙ23፣ በሞርተር ቅንቡላ፣ በዲሽቃ ታግዞ ውጊያ ቢከፍትም የፋኖን ብርቱ ምት መቋቋም ባለመቻሉ ሙት እና ቁስለኛውን እያንጠባጠብ በየ በየገደሉ ቢወሸቅም አይበሬዎች የህዝብ ልጆች የጦር ጠበብቶች ሰብስብ የሆነው እስቴ ዴንሳ ብረሰጌድ ብልፅግናን የማፈራረስ ጉዞ አጠናክረው ቀጥለውበታል። በዚህ ተከታታይ ቀናቶች በተደረጉ አውደ ውጊያዎች ጠላትን በመደምሰስ ምርኮ፣ ለጥፋት ዕቅድ የሚጠቀምበት ተሽከርካሪ አንድ ፖትሮለ መኪና፣ የነፍስ ወከፍ መሳሪያዎች፣ ወታደራዊ ሎጅስቲክ ቁሳቁሶች የዙ23 ተተኳሽ በመማረክ በርካታ አንፀባርቂ ውጤት በማስመዝገብ የኦህዴድ ቡድንን አሸመድምደውት ሰንብተዋል። የድል ጉዞ እንደቀጠለ ነው ...........! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን‼️ አፋብን ሰሜን አማራ በላይ ዕዝ ሜ/ ጀኔራል ውባንተ አባተ፩ኛ ኮር ጉና ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ መምህር ያሬድ ገደፍው

ፋኖ እና የአባት አርበኞች በባሶና ወረና ወረዳ የአገዛዙ ጥምር ጦር ላይ አስደናቂ ርምጃ ወሰዱ ​ ሰኔ 14 ቀን 2018 ዓ.ም ​በአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ፣ ዓፄ ዘርዓያዕቆብ ኮር የነጎድጓድ ክፍለ ጦር ስር የሚንቀሳቀሱት የፋኖ ሰራዊት እና የአባት አርበኞች በትናንትናው ዕለት (ሰኔ 13 ቀን 2018 ዓ.ም) በደብረብርሃን ዙሪያ በሚገኘው ባሶና ወረና ወረዳ ልዩ ስሙ "ጨርቆስ" በተባለ ቦታ ላይ በተደረገ ውጊያ በብልፅግና ጥምር ጦር ላይ ድል መቀናጀታቸውን የግንባር መረጃዎች አስታወቁ። ​ከመንዲዳ እና ከአንጨቆረር ከተሞች በሶስት አቅጣጫዎች የተንቀሳቀሰው የአገዛዙ ሰራዊት፣ የክ/ጦሩ ቃኝወችን እና የአካባቢውን የአባት አርበኞች ከበባ ውስጥ ለማስገባት ሙከራ ያደረገ ቢሆንም፤ያሰበው ሳይሳካለት ቀርቶ እራሱ ከበባ ውስጥ ገብቶ ከሌሊቱ 10:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ቀኑ 06:30 ሰዓት ድረስ በቆየው ከባድ ውጊያ፣ የአገዛዙ ሰራዊት ተገቢ ምት አስተናግዷል። በዚህም ▸ከ10 በላይ የአገዛዙ ሰራዊት አባላት መሞታቸው፣ ▸ከ17 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ከባድ ቁስለኛ መሆናቸው ታውቋል። ▸በተጨማሪም በርካታ ተተኳሽ መሳሪያዎች፣ የብሬን ሸንሸል፣ ወታደራዊ የደንብ ልብሶች እና ሬሽኑ በፋኖ እና በአባት አርበኞች እጅ ገብቷል። ​​የነጎድጓድ ክፍለ ጦር ሪፖርተር ክፍል እንደገለጸው፣ የአገዛዙ ሰራዊት ሽንፈት ከገጠመው በኋላ በጨርቆስ ቀበሌ የሚገኘውን ቤተክርስቲያን ለማቃጠል ሙከራ አድርጓል። ይህንን ድርጊት የተቃወሙና " በልመና የተከላከሉ" የሃይማኖት አባቶች ላይ ድብደባና ዘረፋ የተፈጸመባቸው ሲሆን፣ 4 ንጹሃን ዜጎችም መረሸናቸው ታውቋል። ​ድርጊቱን ተከትሎ የአካባቢው ነዋሪዎች ከፍተኛ ቁጣን የገለጹ ሲሆን፣ ከዚህ በኋላ ራሳቸውን ለመከላከል ትግሉን ወደ "ህዝባዊነት" እንደሚቀይሩት ገልፀዋል ። ምንጭ-የአፄ ዘረያዕቆብ ኮር ህዝብ ግንኙነት ክፍል ክብር ለትግሉ ሰማዕታት ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ