ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Ir al canal en Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Mostrar más2 945
Suscriptores
+1624 horas
+127 días
+37730 días
Archivo de publicaciones
በአባታችን በታላቁ ሰማዕቱ ጀኔራል አሳምነው ፅጌ መታሰቢያ ቀን በሃሳብና በፓለቲካዊ ብስለት የሚመራው ጀብደኛው ምኒልክ ዕዝ 106ኛ ኮር 31ኛ-ሰንጥቅ ክፍለጦር የተሃድሶ ፕሮግራም አካሄዱ!
ከህልውናው የጦርነት ትንቅንቅ ባሻገር የእያንዳንዱን የፋኖ የግንዛቤ እድገት እና የባለ-ራዕይነት ጥበብን በማስረፅ የክፍለጦር አባላቶችን የተሃድሶ ስልጠና ተሰቷል። ይህ ፕሮግራም ትውልድንና ሀገርን ለሚረከብ ሀይል የመሪነትንና የሃላፊነትን አፅናፍ በማሳየት ለአሸናፊነት የሚያበቃን ቁልፍ የሀሳብ መንገዶች ተዘክረውበታል።
በፕሮግራሙ ላይ የአፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሃላፊ አርበኛ ብርሃን አረጋ ተገኝተው ከአማራ ፋኖ ለአማራ ህዝብ ምን ይጠበቃል? ህዝቡስ ምን ማድረግ አለበት? የህልውና ትግላችንን ለማሳካትና አሸናፊዎች ለመሆን ምን ይጠበቅብናል? ተሃድሶውስ ምን ያህል ትግላችንን ያስፈልገዋል? በሚሉ ቁልፍ አጀንዳዎች ላይ ሰፊ ትንታኔ የሰጡ ሲሆን በተሃድሶ መድረኩ አዎንታዊ አንድምታ ተችሯቸዋል።
ትውልድ ተረካቢን ሀይል ከፖፕሊዝም (ከስሜት) አስተሳሰብ ወደ አሰላሳይ እና ምክኒያታዊ ትውልድ ለመቀየር የተሃድሶው ስልጠና መሰጠቱ ለታጋዩ ትግልን በኢኮኖሚ እቅድ፣በድፕሎማሲ መስመርና በፖለቲካዊ ልዕልና ለህዝቦች ሁሉ የሚጠቅም አስተዳደርን ለመመስረት የሚጠቅም ስልጠና ነው ሲሉ የክፍለጦሩ አመራርና አባላት ተናግረዋል። ትግልንና ታጋይን ለመጠበቅ ከዘመኑ የእድገት አድማስ እኩል የሚስፈነጠር ትውልድን በአስተሳሰብ ልህቀት ማብቃት ከጦርነት ባሻገር ለህልውናችን ወሳኝ እርምጃ መሆኑን መተማመን ላይ በመደረሱ የተሀድሶው ስልጠና ተሰቷል።
መዳረሻውን ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ሕዝብ የሕልውና ተጋድሎ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 106ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ሰኔ 16/2018 ዓ/ም
🎯 አስመሳይ ሁላ!
(አዲሱ ደረበ)
ፋኖዎቻችን በአገዛዙ የጥይት አረር ከመመታታቸው በፊት፣ መጀመሪያ እዚህ ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ ነው ደጋግመን የምንገ*ድላቸው። አዎ፣ ጨክነን ደጋግመን ገድለ*ናቸዋል!
ስንፈልግ በየጎጡ ተቧድነን ስማቸውን እያጠፋን፣ ሲያሻን የጥፋት ኃይልና ወያኔ እያልን ታርጋ እየለጠፍንባቸው፣ ደስ ካለንም ከጠላት እኩል እንዲ*መቱና እንዲ*ገደሉ ዘመቻ እየከፈትንባቸው ያለነው የዚሁ የማኅበራዊ ሚዲያ ጉዶች አይደለንምን? ጠ*ላት ከፊትና ከኋላ ከቦ ከሚያስጨንቃቸው ይልቅ፣ እኛ ከጀርባ ሆነን ገመናቸውን ስንገልጥና ምሽጋቸውን ለጠላት አሳልፈን ስንሰጥ እንውላለን። እንዲህ ስናደርግ ነፍስና ሥጋቸው እንደሚላቀቅ እያወቅን እንኳ የማንራራላቸው፣ ከየት እንደበቀልንና ወደ የት እንደምናደግ የማንታወቅ አግድም አደጎች በየፊናችን የትየለሌ ነን። ልክ እንደ ድመት የራሷን ልጆች ጨክና እንደምትበላ፣ እኛም የራሳችንን አርበኞች አሳልፈን የምንሰጥ ወለፈንዲዎች ምድራችንን ሞልተናታል።
ዛሬ አርበኛ አማረ አቸነፍን ጨምሮ ወርቃማና ብርቅዬ ጓዶቻችን ተሰውተውብናል። ልክ እንደ ዛሬው ጀግኖቹ ከተሰው በኋላ ያ የለመድነው የአዞ እምባችን እንደ ጉድ ይፈሳል። አስመሳይነታችንና ምንፍቅናችን በገሀድ ይገለጣል። በሞታቸውና በከፈሉት ክቡር መስዋዕትነት ላይ የገጽታና የላይክ ትርፍ ለመቃረም ሁሉም ይሯሯጣል። ልክ የፋኖ የቅርብ አማካሪና መካሪ እንደነበረ ሁሉ፣ ወይም መሬት ላይ ካሉ የጦር አዛዦች ጋር በቀጥታ ይደዋወላል ለመባል፣ አሊያም ትናንት የፈጸመውን አጥፊነቱን ዛሬ በትግል ባለቤትነት ስም ለመቀየር ሲል እያለቀሰ ሲያስመስል ይውላል። ዛሬ ከመሬት በታች ሆነው ምስክርነት ሊሰጡ የማይችሉትን የሰማዕታት ጓዶቻችንን ምስል እየለጠፈ እማኝ በመጥራት ያላዝናል።
“ምን ብለኸኝ ነበር? ያወራነውን ታላቅ ምስጢር ሁሉ የት ጥለኸው ወደቅህ? ያላንተ እኮ ትግሉ አይሆንልኝም! ትናንት በስልክ ስታወራኝ እየተሰናበትከኝ ነበር ወይ?” እያለ በውሸትና በማስመሰያ ቃላት በቁም ያለውንና የሚሰማውን አማራ ይሸነግላል፣ ያደነዝዛል። መሽቶ ሲነጋ ግን፣ ይሄው አስመሳይ ስብስብ ሌላ በሕይወት ያለና ግንባር ላይ የሚዋደቅ ፋኖ ፈልጎ ስም የማጥፋት ዘመቻ ይከፍታል። አስመሳይ ሁላ! በርካታ ጀግኖቻችንን ከጠላት ጥይት በፊት የብዕር መርዝና የማኅበራዊ ሚዲያ ሴራ ገድሏቸዋል።
የአማራ ሕዝብ እውነተኛ የቁርጥ ቀን ልጆች የሆናችሁና ለእውነት የተሰዋችሁ ብርቅዬ ጓዶቻችን ሆይ፤ እናንተስ ከምድራዊው ውሸትና ክህደት አምልጣችኋል። ፈጣሪ አምላክ ንጹሕ ነፍሳችሁን በገነት ያኑርልን፤ ለእኛም ከዚህ የከፋ አስመሳይነትና የቁም ሞት የሚታደገንን ልቦና ይስጠን።
ድል ለአማራ የህልውና ትግል! 🎯
+1
የአገዛዙ ሰራዊት አሁንም ወደ ጀብደኛዉ ምኒልክ ዕዝ እየኮበለለ ነዉ!!
ዛሬ ሰኔ 15/2018ዓ.ም አልብኮ ወረዳ ካለው አድማ ብተና 26ኛ ሻለቃ አንድ አባል እና ከመከላከያ 36ኛ ክ/ጦር አባል ሙሉ ትጥቃቸውን በመያዝ አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 104ኛ ኮር 25ኛ ክ/ጦርን ተቀላቅለዋል።
አባሎቹም ወደ ፋኖ ሲመጡ በክ/ጦሩ አመራሮች በተደረገላቸው አቀባበል እና እንክብካቤ ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል ሲል የ104ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ መረጃዉን አድርሷል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ!!
ሰኔ:-15/ 2018 ዓ/ም
አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 104ኛ ኮር 25ኛ ክ/ጦር በጠላት ኃይል ላይ መብረቃዊ ጥቃት ፈፀመ።
ሰኔ 15/2018ዓ.ም ከወረኢሉ ወረዳ በወይብላ ማሪምና በቁልቢ ቦታወች አገዛዙ ጥምር ጦር እያለ የሚጠራዉ የአማራን ህዝብ መጨፍጨፊያ ስም በተሰጠው የአብይ አህመድ ዙፋን ጠባቂ ስራዊት ላይ በደፈጣና ስቦ ወደ መግደያ ቦታ በማስገባት የ104ኛ ኮር ቃኝና የ25ኛ ክ/ጦር አንደኛ ሻለቃ አናብስቶች በፈፀሙት መብረቃዊ ጥቃት መቶ አለቃ ፋንታው የተባለ ሻለቃ መሪ ጨምሮ ከ10 በላይ ሰራዊት ሲደመሰስ በርካታ ቁስለኛውን ተሸክሞ ወደመጣበት ፈርጥጦ ተመልሷል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የ104ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ሰኔ 15/2018ዓ.ም
የጠላት ኮማንደሮችና የጦር ኦፊሰሮች ያለቁበት የወለጋው ትንቅንቅ!
በአፋብን ወለጋ (ቢዛሞ)አንሻ ሰይድ ዕዝ ከጌጤ ግርማ መብረቅ ክ/ጦር፣ ከታፈረ አለሙ ሳተናው ክ/ጦር፣ ከአንገር ጉትን ክ/ጦርና ከአበጀ ጥበቡ ነበልባል ክ/ጦር የተወጣጡ አርበኞች በወሰዱት እርምጃ የጠላት ብልፅግና ኃይልን አከርካሪ ሰብረው አንፀባራቂ ድል መቀዳጀታቸውን ዕዙ በሕዝብ ግንኙነት መምሪያው በኩል ለመረብ ሚዲያ በላከው መረጃ አስታውቋል።
በአንሻ ሰይድ ዕዝ የአበጀ ጥበቡ ነበልባል ክ/ጦር አርበኞች ጉትን ከተማ ዙሪያ በፈፀሙት የቆረጣ ሽምቅ ጥቃት በርካታ ወታደሮችን መደምሰስ ችለዋል።
በምስራቅ ወለጋ ዞን መነሻውን ከአንገር ጉትን ከተማ አድርጎ ወደ ሊሙ ወረዳ ፊጥበቆ በመግባት ንፁኋን ላይ ጭፍጨፋ ለመፈፀም ሲገሰግስ በነበረ የጠላት ጦር ላይ ነው የደፈጣ ጥቃቱ የተፈፀመው።
የአበጀ ጥበቡ ነበልባል ክ/ጦር አርበኞች፡ ከአንገር ጉትን ከተማ በቅርብ ርቀት ልዩ ስሙ መንደር 4 ላይ የጠላት ጦርን ሁለት ሦስት ቦታ ላይ ቆርጠው በወሰዱት እርምጃ፡ አንድ ኮማደር፣ አንድ ኦፌሰር፣ አንድ መቶ አለቃ የሚኒሻ ጠርናፊን ጨምሮ ከ15 በላይ ወታደሮች ሲገደሉ፡ በርካቶች ከከባድ እስከ ቀላል ሲቆስሉ፡ ቀሪው የጠላት ኃይል ሙትና ቁስለኛውን አዝረክርኮ አርቁምቢ መንደር አንድ ተብሎ ወደሚጠራው አከባቢ መፈርጠጡን ነው ዕዙ ለመረብ ሚዲያ በላከው መረጃ ያስታወቀው።
በዚህ የፋኖ የማድረግ አቅምና ፍፁም ጀግንነት በታየበት የቆረጣ ማጥቃት፡ ከተደመሰሱ የአገዛዙ ወታደሮች በተጨማሪ፡ በርካታ የጦር መሣሪያዎችና ሌሎች ወታደራዊ ቁሳቁሶች በፋኖ ቁጥጥር ስር ውለዋል። ቀሪ የጠላት ንብረቶችም እንዲወድሙ መደረጋቸው ተረጋግጧል።
በሌላ ግንባር፡ በዕዙ ስር ከጌጤ ግርማ መብረቅ ክ/ጦርና ከታፈረ አለሙ ሳተናው ክ/ጦር የተወጣጡ አርበኞች በቅንጅት በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አቤደንጎሮ ወረዳ ቱሉጋና ከተማ በነበረ የጠላት ጦር ላይ በወሰዱት እርምጃ በርካታ ወታደሮችን ደምስሰው አመርቂ ድል አስመዝግበዋል።
አርበኞቹ በድሽቃና በብሬን ሽፋን ታግዘው የጠላት የቁም ምሽጎችን ጭምር የሰበሩ ሲሆን፡ የጠላት ጦርን አከርካሪ በመስበር በርካቶችን ደምስሰው ልዩ ልዩ የጦር መሣሪያዎችን ማርከው ታጥቀዋል።
በተመሣሣይ፡ በምስራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ ውስጥ ንፁኋንን በመጨፍጨፍ ላይ በነበረ የጠላት ኃይል ላይ በአይሻ ሰይድ ዕዝ ስር ጀብደኞቹ የአንገር ጉትን ክ/ጦር አርበኞች በወሰዱት እርምጃ፡ በርካታ ጠላትን ደምስሰው ቀጠናውን መቆጣጠራቸው ታውቋል።
በዚህ ተጋድሎ ሙትና ቁስለኛ ከተደረገው የጠላት ጦር በተጨማሪ፡ አገዛዙ የአማራን ሃብት ንብረት እየዘረፈ በተሽከርካሪ ሲጭንበት የነበረው ክሬን በፋኖ መማረኩንም አይሻ ሰይድ ዕዝ በሕዝብ ግንኙነት መምሪያው በኩል ለመረብ ሚዲያ በላከው መረጃ ገልጿል።
ለዘመናት በስርዓታዊ የዘር ማጥፋት ዘመቻ ሲማቅቅ የኖረው የወለጋ-ቢዛሞ አማራ ህዝብ በብልፅግና አገዛዝ የተጋረጠበትን የህልውና አደጋ ለመመከት ተደራጅቶ ጠላቶቹ ላይ የእሳት መዓት እያወረደ ይገኛል።
እራስን ከእልቂት የመታደግ ተፈጥሯዊ መብቱን ተጠቅሞ የተደራጀውና ብሶት የወለደው ጀግናው የአይሻ ሰይድ ዕዝ ሠራዊት ብርቱ የሆነ የፀረ ማጥቃት እርምጃ በመውሰድ የሕዝቡን ሕልውና ለማረጋገጥ የሚያደርገውን ተጋድሎ አጠናክሮ ቀጥሏል።
ማን ይናገር የነበረ ፥ ማን ያርዳ የቀበረ‼️
አይበገሬዋ አርበኛ አይናዲስ ዋለልኝ ከሰላማዊ የአደባባይ የህዝብ ጥያቄ እስከ አብዮታዊ የትጥቅ እንቅስቃሴ የትግል አበርክቶ በጥቂቱ ፦
ትላንት በጨለማው ዘመን የአማራን ፓለቲካዊ አጀንዳ ወደ አደባባይ ይዞ መቅረብ ይቅርና "አማራ ነኝ!" ብሎ ለመናገር አብዛኛው በሚሽኮረመምበት ወቅት ፣ከባድ ማህበራዊ ድባቴ ውስጥ በነበርንበት ወቅት ፣ብዙኅኑ ከአገዛዙ ጎን ተሰልፎ በሚያሸርግድበት ወቅት የህዝብን አጀንዳ ፣በህዝባችን ላይ እየደረሰ ያለውን በደልና ግፍ በጥቅሉ የህልውና ስጋትና አደጋ በንጉስ ተክለሃይማኖት አደባባይ ይዞ በመውጣት በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀስ ጀግና እህታችን ናት።
የአማራ ህዝብን አብዮት ለመውለድና አዲሱን ትውልድ የማንቃት፣የማሰልጠን እና በህዕቡ የማደራጀት ወቅት የሚሰጣትን አብዮታዊ ግዳጅ ወይም አደራ በብቃት የተወጣች የሴቶች ቁና ፥ ደፋር ታጋይ ፥ አታጋይ አርበኛ ናት።
በዚያም የሰልፉ ዘመን በደብረ ማርቆስ ንጉስ ተክለሃይማኖት አደባባይ በተደረጉ በርካታ መሬት አንቀጥቅጥ አትግደሉን ፣ አታፈናቅሉን ፣ ሞት በቃን ፣ መሳደድ በቃን መፈናቀል በቃን የቤተክርስቲያን መቃጠል ይቁም ፣ የካህናትና የኦርቶዶክስ አማንያን ግድያ ይቁም ወዘተ በሚሉ ተቃውሞ ሰልፎች ከጀግና የደብረ ማርቆስ ወጣቶች ጋር በመሆን የተቃውሞ ሰልፎችን በማዘጋጀት ፣ በመምራት እና የአማራ ህዝብን አጀንዳ በዓለም አቀፍ መድረክ ትኩረት ሳቢ እንዲሆን የአንበሳውን ድርሻ ከተወጡ የንጉስ ተክለሃይማኖት የመንፈስ ልጆች መካከል በግንባር ቀደምትነት የምትጠቀስ ጀግና የህዝብ ልጅ ናት።
በአብዮቱ ዋዜማ ወቅት በአብዮታዊው መሪያችንና ምልክታችን አርበኛ ዘመነ ካሴ ሃሳብ አመንጭነትና ትዕዛዝ "የእሳት ኳሶች!" ማደራጀትና ዝግጁ የማድረግ እጅግ ወሳኝ በሆነው የትግል ምዕራፍ ወቅት ፦እጅግ ውስብስብና ፈታኝ ፣ በስራ ላይ መሳሳት ፣ የመረጃ መሽሎክ ህይወትን ሊያሳጣ በሚችል ፈተና በሚያስከትለው እጅግ ከባድ የትግል ዘመን የተሰጣትን ተልኮ በመቀበል በበርካታ የጎጃም ከተሞች በመንቀሳቀስ ለአብዮቱ እርሾ የሆኑ ከሃያ እስከ ሰላሳ የሚሆኑ የእሳት ኳሶችን የማደራጀት ተግባርን ከሌሎች ወንድሞችን ጋር በመሆን በብቃት የተወጣች አይበገሬ አርበኛ ናት።የእሳት ኳሶች አደረጃጀት ለአብዮቱ መፈንዳት ያበረከተውን የላቀ አስተዋፅኦ በአደረጃጀቱ የተሳተፉ አብሪ ኮከብ ታጋዮችና የተፈፀመውን ጀብዱ ለታሪክ ተመራማሪዎች ጥናት ፥ ምርምር ልተወውና በተጨማሪ
የአማራ ህዝባዊ ኃይል (ፋኖ) አባላትን እንዲሁም ንቁና ብቁ የአማራ ወጣቶችን በከተማ ውስጥ ለምናዋልደው አማራዊ አብዮት አንቅቶ ፥ አደራጅቶና አብቅቶ ማዘጋጀት ፤ በበርሃ ውስጥ ሄዶ ላቅ ያለ ዝግጅት የሚያደርገውን የአማራ አብዮታዊ የፋኖ ሀይል በመመልመል "በጎዛም ጭምት በርሃ ፣ በአባይ በርሃ ፣ በአብያ በርሃ ፣ በቡሬ በርሃ " ወዘተ ቦታው ድረስ በመሄድ ቦታ መረጣና ተያያዥ ተግባራትን ለአብዮቱ እጅግ ወሳኝ የሆኑ ስራዎችን የሰራች የዘመናችን ጣይቱ ፥ ሸዋረግ ገድሌ ናት።
በአዲሱ ትውልድ ፣ በአዲስ አስተሳሰብና ተስፋ ከሶስት አመታት በፊት በተቀጣጠለው አማራዊ አብዮት በፊት አውራሪ አዝማችነት የንጉስ ተክለሃይማኖትን ከተማ ደብረማርቆስን ከአገዛዙ ነፃ የማውጣት፣ የፀጥታና የፓለቲካ መዋቅሩን የማፈራረስ ወሳኝ ተግባር ላይ አብሪ በመሆን የታገለች፥ያታገለች ጀግና ፣ደፋር አብዮተኛ አርበኛ ናት።
አርበኛ አይናዲስ ዋለልኝ ላለፉት ሶስት የትጥቅ ትግል አመታት ከአማራ ህዝባዊ ኃይል (ፋኖ) እስከ የአማራ ፋኖ በጎጃም (አፋጎ) ፤ ከአፋጎ እስከ አፋብኃ ፤ ከአፋብኃ እስከ ግዙፉ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ድረስ ደጋ ወጥታ፣ቆላ ወርዳ ፤ ተራራ ዳገቱን ወጥታ፣ወንዙንና ሸንተረሩን አቋርጣ ፣በዱር ገደሉ አድራ እጅግ ፈታኝ በሆነው የትግል ምዕራፍ ውስጥ ድርጅታችን የሰጣትን አብዮታዊ ግዳጅ በብቃት፣በታማኝነት፣በቅንነት እና በሀቀኝነት ግዳጇን የምትከውን የፅናት ተምሳሌት የሆነች ጀግና መሪ ናት።
ጀግናዋ ጓዴ! አይናዲስ ዋለልኝ በአሁኑ ወቅት አንድ አማራዊ ቤታችን በሆነው የአዲሱ ትውልድ ድርጅት የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) የሴቶች ጉዳይ መመሪያ ኃላፊ በመሆን የተሰጣትን አብዮታዊ ግዳጅ ትግል አቆርቋዥ ፣ ከፋፋይ እና አውርቶ አደር የወገንን ዩኒፎርም የለበሱ የሚዲያ ሚሊሾች ጩኸትና ስም ማጥፋት ሳይበግራት ፣ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳትል የተሰጣትን ከባድ ሃላፊነት በልበ ሙሉነት እየሰራች ትገኛለች።
እህታለም ፥ ጓዴ ፥ አይናችን አንቺና መሰል ጀግና እህቶቻችን በዚህ ትግል ውስጥ በታሪክ አምድ በትውልዱ የሚዘከር ፣ የሚወደስ እና ጮክ ተብሎ የሚነገር ደማቅ ታሪክ እየሰራችሁ ነው። በርችልን ፥ በርቱልን!
ክብር ለሚገባው ክብር መስጠት ያለ ፥ የነበረ ፥ ወደ ፊት የሚኖር አገራዊም ዓለም አቀፋዊም የወል ሃቅ ነው።
መበርታት ብቻ!
ክፋት ለማንም፣በጎነት ለሁሉም!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ ፣አዲስ ተስፋ!
Hailemichael Bayeh
+2
በከባድ መሳሪያ በሞርተር ደብረ ማርያም ቀበሌ ሸማት ጎጥ የአራት (4) የንፁሀን አርሶ አደሮች ቤት ከጥቅም ውጭ አድርገዋል።
$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$$
.......ሰኔ 15/2018 ዓ.ም
የፋኖን ክንድ ብትር መቋቋም ያቃተው የብልፅግናው ወንበር አስጠባቂው በሞርተር ደብረ ማርያም ቀበሌ ሸማት ጎጥ የአራት የንፁሀንን አርሶአደር ቤታቸው የፈረሰባቸው አርሶ አደሮች።
1ኛ.ፍቃዴ መልኬ
2ኛ.ባወቀ ተሹ
3ኛ ልገረው አይቸህ
4ኛ.ጌትነት ፈንታሁን ሲሆኑ ፊት ለፊት ለመግጠም ሞራል የሌለው የብልፅግና አገልጋይ በዛሬው እለትም የተለመደውን የበቀል ጥሙን የአርሶ አደሮችን ቤት አፈርሷል።
በዚህ ሊቆም እና ሊሸማቀቅ የሚችል አንድም አማራ እንደሌለ ይኸን ስርአት ከስሩ ነቅለን ለመጣል አስፈላጊውን መስዋት ለመክፈል ዝግጅ መሆናቸውን አርሶ አደሮች ተናግረዋል።
የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክፍለ ጦር የ2/ጁ እነሴ ወረዳ ሚዲያና ግንኙነት መረጃውን አጋርቶናል።
+1
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 101ኛ ኮር 35ኛ ክፍለጦር ከስርዓቱ ጨፍጫፊ ጦር በመክዳት ፉኖን የተቀላቀሉትን የሰራዊት አባል የአማራ ፉኖ የትግል አላማን በተመለከተ የፖለቲካ ግንባታ በመስጠት ወደ አማራ ትግል በፍላጎታቸዉ እንድቀላቀሉ ተደርጓል።
ከሰኔ 10 -13 ድረስ ከአብይ አህመድ ዙፉን ጠባቂነት ወደ ፉኖ ሙሉ ትጥቃችውን ከነፍስ ወከፍ እስከ ቡድን መሳሪያ በመያዝ የተቀላቀሉትን 16 የስራዊት አባላትን ትላንት ሰኔ 14/2018 ዓ.ም የአማራ ፉኖ ብሄራዊ ንቅንቄ ምክትል ህግ መምሪያ ሀላፊ አርበኛ መሀመድ ሞገስ ፡ የአማራ ፉኖን ወቅታዊ የትግል ሁኔታ :ትግሉ የደረሰበትን ደረጃ፣የአማራ ፉኖ በደም እና አጥንቱ ስለመሰረተው መሪ ድርጂት /አፉብን/ የትግል አቋም:የምርኮኛ አያያዝ እና የድርጂታችን የድፕሎማሲ ቅቡልነት እንድሁ ውጊያውን እንዳሸነፍን የሚያመለክቱ ማሳያዎችን እና ጦርነቱንም ያለ ጥርጥር በስኬትና በድል እንደምናሸንፍ ያሉትን መልካም አጋጠሚዎችን እና መሰል ጉዳዮችን ከስራዐቱ ከድተው ፉኖን የተቀላቀሉ የሰራዊት አባላትን ከላይ በተዘረዘሩት ጉዳዮች የፖለቲካ ግንባታ ሰጥተው ወደ ክፍለጦሩ መደበኛ ሰራዊት እንድቀላቀሉ ተደርገዋል ሲል የ 35ኛ ክፍለ ጦር ህዝብ ግንኙነት መረጃዉን አድርሷል።
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!!
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!!
አፋብን ወሎ ቤተ- አማራ ምኒልክ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!!
ሰኔ 15/2018 ዓ.ም
በሶስቱም አቅጣጫ የአብይ ሰራዊት በየሄደበት ሰብአዊ እና ቁሳዊ ኪሳራ እያስተናገደ ይገኛል።
=============================
.....ሰኔ 15/2018 ዓ.ም
በዛሬው እለት መነሻውን በተለያዩ ሶስት አቅጣጫ ከአዴት ከጎንጂ እና ከሞጣ የአማራን አርሶአደር ትጥቅ አስፈታለሁ በማለት የተንቀሳቀሰው የጠላት ሀይል በንስሮች የ201ኛ ኮር 54ኛ ክፍለ ጦር ሻለቃ 3 እና የ102ኛ ኮር 33ኛ ክ/ጦር 5ኛ ሻለቃ የጋራ ጥምረት በመፍጠር ወለቆይ ላይ ጠላት እንደ እባብ ሲቀጠቀጥ አርፍዶ ሙት እና ቁስለኛውን በመያዝ ወደ መጣበት ቀጠና እየተዘረከረከ እንዲመለስ አድርገውታል።
በሌላኛው ግንባር ከሞጣ ከተማ በመነሳት በዙ=23 የተደገፈ የማጥቃት ሙከራ ቢያደረግም አይበገሬወች የ54ኛ ክ/ጦር ሻለቃ ሁለት አጋም ውሀ ላይ በተለያዩ አቅጣጫ ገዥ ቦታወችን በመያዝ ጥቃት በመክፈት ዙ=23ቱን በመጣበት እግሩ ተመልሶ ወደ ሞጣ እንዲገባ በማድረግ አንገት አስደፍተው ቁስለኛውን ሸክፎ እንዲመለስ አድርገውታል።
አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስተስፋ
የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
+7
በ2እጅ እነሴ ወረዳ ወብ ቀንጫሪት ቀበሌ ላይ በወቅታዊ ጉዳዮች ከህዝቡ ጋር ውይይት ተካሄደ።
=============================
ሰኔ15/2018 ዓ.ም
የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር በ2እጁ እነሴ ወረዳ ወብ ቀንጫሪት ቀበሌ ህዝብ ጋር ሰኔ 14/2018 ዓ.ም የጋራ ውይይት ተደርጓል።
➺ በፍትህ አሰጣጥ እና የመልካም አስ/ር ➺በፀጥታ ዙሪያ ያሉ ችግሮችን በመለየት
➺የአፋብን ትግል ከየት ወደየት የደረሰበት ሁኔታ እና ህዝባዊ አስተዳደርን ጨምሮ የተገመገመና የወደፊት አቅጣጫ የተቀመጠበት ሲሆን ትግላችን አሁን ላይ የደረሰበትን ሁኔታ አጭር ማብራሪያ በኮሩ እና በክፍለ ጦር አመራሮች የማስረዳት ስራ ተሰርቷል።
እናደራጃለን ! እንመክራለን! እንፈፅማለን!!
አዲስ ትውለድ፣አዲስ አስተሳሰብ፣አዲስ ተስፋ!!
አፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት
#የአማራ_ፋኖ_ብሄራዊ_ንቅናቄ(አፋብን) በላይ ዘለቀ ዕዝ #ዘመቻ_መቶ_አለቃ_ያለው_አዱኛ እና የመብረቅ ክፍለ-ጦር አመራሮች በጋራ በመሆን ወደተለያዩ የበላሳ አካባቢዎች በመንቀሳቀስ ለተከታታይ 3ቀናት
ከማህበረሰቡ እና በተለያዩ ምክንያት ከአደረጃጀት ውጭ ሲንቀሳቀሱ ከነቀሩ ሃይሎች ጋር ውይይት ተደረገ ።
በተለያየ ምክንያት ከአደረጃጀት ከውጭ ከሆኑ ሃይሎች ጋር ውይይት የተደረገ ሲሆን በውይይቱ የተለያዩ ጥያቄዎች ተነስተው በዋናነት የዕዝና የኮር አመራሮች ላይ ችግሮች እንዳሉ ጠቅሰው ችግሮቹ እንዲስተካከሉና ቀጣይ እንዳይደገሙ በቁርጠኝነት መስራት ያስፈልጋል ያሉ ሲሆን ጥያቄያቸውን ተቀብለው ውስጣዊ ችግሮቻቸውን በመፍታት በመቅራዊ አደረጃጀቱ እንዲገቡ በማድረግና አንደነትን በማጠንከር ተቋማዊ አሰራርን ተከትለው ህዝባቸውን በቅንነት በታማኝነት እንዲያገለግሉ ተቋማቸውን እንዲጠብቁና ለማይቀረው ድላችን እንዲዘጋጁ ማድረግ ተችሏል።
ከማህበረሰቡ ጋር በተደረገ ውይይት የተለያዩ ችግሮችና ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን በዋናነት ድም መመላለስ የሚባል አጉል ባህል በማህበራዊ ሂወታቸው ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰባቸው እንደሆነ ገልፀዋል ።
አመራሩም ጥያቄዎችንና ችግሮችን መነሻ በማድረግ ችግሮች በዘላቂነት እልባት አግኝተው ማህበረሰቡ በጋራ እንዲኖር በጋራ እንዲያለማ እርስበርስ መተማመን እንዲፈጠር ለማድረግ ውስጣዊ ችግሮቻችን በዘላቂነት ይፈታልናል ያሉትን የተለያዩ ህጎችን ከማህበረሰቡ ጋር ያወጡ ሲሆን የገደለ እንዲክስና እንዲታረቁ በማድረግ ድጋሜ መገዳደል እንዳይኖር የሚያደርጉ ህጎችንም በማውጣት በማህበረሰቡ ውስጥ ያሉ አጉል ባህሎችን በዘላቂነት ለመፍታት ይረዳዘንድ ማህበረሰቡ ከህግ አካላት ጋር በመሆን ህግ ለማስከበር ዝግጁ እንዲሆን የጋራ ውሳኔ ላይ ተደርሷል ።
ክብር ምስጋና ለትግሉ ሰማዕታት 🙏
ህሊናችን በተባበረ ክንዳችን 💪
አማራ በጀግና ልጆቹ ያሸንፋል!!
መብረቅ ክፍለ-ጦር ህ/ግንኙነት ክፍል
Alazar Dagmawi Tedros
