en
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Open in Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Show more
2 808
Subscribers
+18124 hours
+2277 days
+23430 days
Posts Archive
7/70 ክፍለ ጦር በአጣዬ ዙሪያ ድል ሲቀናው፣ "የአርሶ አምባ አርበኞች ጦር" በአላላ ታላቅ ገድል ፈፀመ!! ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ 7/70 ክፍለ ጦር በአጣዬ እና በአላላ ከተማ በተለያዩ ሁለት አቅጣጫዎች በተፈፀመ ልዩ ኦፕሬሽን ውጤታማ ድል መቀናጀቱ ተገለፀ። በላይኛው አጣዬ ቀበሌ ምሽትን ሽፋን ተደርጎ በተካሄደው ኦፕሬሽን፣ በማታ ኬላ ዘርግተው አሽከርካሪዎችን በማስቆም ህገ-ወጥ የገንዘብ ምዝበራ ሲፈጽሙ በነበሩ የታጠቁ ሚሊሻዎች ላይ ጥቃት መፈፀሙ ተረጋገጠ። በዚህም ታዬ ገብሬ (የመንገድ ትራንስፖርት ባልደረባ)፡ በከፍተኛ ጽኑ ቆስሎ ወደ ሪፈራል ሆስፒታል ሲላክ፣ አሳልፍ አድሴና ኮማንደር የሱፍ ሙሔ፡ በጽኑ የቆሰሉ የሚሊሻ አባል መሆናቸው ተረጋግጧል። በተወሰደባቸው እርምጃ የተበሳጩት የአገዛዙ የጸጥታ አካላት፤ መረጃ ለፋኖ ሰጥተሃል በሚል ጌታዬ ሀይሉ የተባለን አንድ ወጣት በግፍ እርምጃ እደተወሰደበት ተሰምቷል። ወጣቱ ቀደም ሲል አባቱ ከብልፅግና መዋቅር ስራ እንዲወጣ ሲለምነው የነበረ ሲሆን፣ ይህንኑ ምክንያት በማድረግ መረጃ ሰጥተሃል በሚል ሰበብ በግፍ ተረሽኗል። በሌላ አቅጣጫ በአላላ ቀበሌ በተካሄደው ሁለተኛው ኦፕሬሽን ደግሞ፤ የሚሊሻ ጠርናፊ በሆነው ተሾመ ጌቶ በተባለው ግለሰብ ላይ በአላላ ከተማ እርምጃ ተወስዶ እስከወዲያኛው እንዲሸኝ ተደርጓል። 〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰ይሕ በእንዲሕ እንዳለ የአርሶ አምባ ዘንቦ ቀበሌ ሕዝብን ለመዝረፍ በሰንበቴ የሚንቀሳቀሰው የስርዓቱ አገልጋይ ሚሊሻ፡ በአርሶ አምባ አርበኞች ጦር" ቀኑን ሙሉ ሲወቃ ውሎ ከባድ ኪሳራ መከናነቡ ተገለፀ። የአርሶ አምባ ገበሬን ንብረትና ሀብት ለመዝረፍ ከኬሚሴና ሰንበቴ ሲግተለተል የመጣው ሚሊሻ፡ እንዳመጣጡ ሲያናግሩት ውለው፣ በርካታ አባላቱን ሙትና ቁስለኛ አድርገውበታል። በዚሕ አውደ ውጊያ የደረሰው የንብረትና የሰብዓዊ ኪሳራ ከባድ ሲሆን፣ በጠላት ላይ የደረሰውን ኪሳራ፣የሙትና ቁስለኛ ቁጥር ለመግለፅ በመረጃች አጣርተን፡ በቀጣይ የምንገልፅ ይሆናል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ሰበር ዜና በሳንቃ ከተማ ግንባር በአገዛዙ ሰራዊት ላይ ከባድ ጥቃት ተፈፀመ። የከማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ምኒልክ 1ኛ ዕዝ የ102ኛ ኮር የ49ኛ ክፍለጦር የሰራዊት አባላት ትናንትና ነሃሴ 29/2018ዓ/ም በጉባላፍቶ ወረዳ ከወልዲያ ከተማ በቅርብ ርቀት ሳንቃ ከተማ በአገዛዙ ሰራዊት ላይ ያልተጠበቀ መብረቃዊ ጥቃት ወሰዱ። አገዛዙ በሳንቃ ከተማ ግንባር በሌሊት ጥቃት ሊከፍት እንዳሰበ የ102ኛ ኮር ወታደራዊ አመራሮች ባገኙት መረጃ መሰረት የ49ኛ ክፍለጦር ቃኝ በሳንቃ ጌሾ በር ከምሽቱ አስራ አንድ ሰዓት ተስበው ቀድመው ቦታዎችን በመያዝ ጠላት ባልጠበቀው እና ባለአቀድው መንገድ እርምጃ ወሰዱበት። ጠላት ከምሽቱ አስራ ሁለት ሰዓት ከሳንቃ ገብርኤል ቤተክርስቲያን መነሻውን በማድረግ ወደ ጌሾ በር እና ጤና ጣቢያ ሰፈር የዘረጋ ቢሆንም በ49ኛ ክፍለጦር ነበልባሎች ከበባ ውስጥ መሆኑን ጦርነቱ እስኪጀመር ድረስ በቂ መረጃ አልነበረውም። በመሆኑም የ102ኛ ኮር ትንታጎች የ49ኛ ክፍለጦር ቃኝ በወሰዱት ድንገተኛ የፊት ለፊት የጨበጣ ማጥቃት 30 የመከላከያ ሰራዊት ሲደመሰሱ ቁጥሩ ያልታወቀ በርካታ የጠላት ሰራዊት ቆስለኛ ሆኗል። የተደመሰሱ የመከላከያ ሰራዊት አባላት በሳንቃ ከተማ ከጌሾ በር እስከ መነሐሪያ ዛሬ ነሃሴ 30/2018ዓ/ም በየ መንገዱ  አስከሬናቸው ወድቆ በአደባባይ ይታይ እንደነበር ማህብረሰቡ ገልፃል። ልማደኞቹ ዙ-23 ማራኪዎቹ ከጠላት  ስምንት ጥቁር ክላሽን ኮፍ መሳሪያ እና ስድስት ሬን ኮት እንድሁም ሶስት የወገብ ትጥቅ በሞርኮ በ49ኛ ክፍለጦር እጅ ገብቷል። ጨፍጫፊውና እብሪተኛው የብልፅግና አገዛዝ በመላው አማራ ህዝብ በደረሰበት የፖለቲካ ኪሳራ ከፍተኛ ውዝግብ ላይ መሆኑ ይታወቃል። በመሆኑም አውደ ውጊያው እስከ ምሽቱ እንድ ሰዓት ደረስ የቀጠለ ሲሆን አገዛዙ የ102ኛ ኮር የ49ኛ ክፍለጦር ቃኝ ጀግኖችን ክንድ መቋቋም ባለመቻሉ በሁሉም አቅጣጫ ሳንቃ ከተማን ሙሉ በሙሉ አሰረክቦ ወደ መጣበት ፈርጥጧል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! "ክብር ለትግሉ ሰማዕታት" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ የ102ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ነሐሴ 30/2018 ዓ.ም

በወታደራዊ ጠበብቶችና ፓለቲካዊ ልምድን ባካበቱ አርበኞች የሚመራው ጀብደኛዉ ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ከወታደራዊ ድሎች ጎን ለጎን ህዝባዊ ዉይይቶች ተጠናክረዉ ቀጥለዋል! የአናብስቶቹ ስብስብ 15ኛ ኮር 156ኛ ታቦር ተራራ ክፍለጦር ነፃ ባወጣቸው ቀጠናዎች የህዝብ አስተዳደራዊ እና መዋቅራዊ  ለውጦችን በማካሄድ ጥልቅ ሕዝባዊ ውይይት አካሄደ! የ156ኛ ታቦር ተራራ ክፍለጦር በ019 ቀበሌ የሚገኙ ማህበረሰብን በመሰብሰብ  የተለያዩ አጀንዳዎችን በማንሳት ውይይቶችን በማድረግ ከማህረሰቡ ጋር መግባባት ላይ ተደርሷል። በመድረኩ  የተለያዩ አጀንዳዎች የተነሱ ሲሆን ከነዚህም መካከል በትግሉ ሂደት ውስጥ የተፈጠሩ ችግሮችን ምን ነበሩ? ፣የፋኖና የህዝባችን የግንኙነት መስመሩ  ምን መምስል አለበት? እንዲሁም አሁናዊ የትግሉ ቁመና ምን ይመስላል?በሚሉ ሃሳቦች ላይ ሰፊ ትንተና እና ውይይት በማድረግ ከማህበረሰብ የተነሱ ጥያቄዋችን ተቀበለው ምላሽ ሰጥተዋል። ከቀበሌው ማህበረሰብ የተለያለዩ ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን በክፍለጦሩ ከፍተኛ አመራሮች ሰፊና አጥጋቢ ምላሽ  ተሰጥቷል። በመጨረሻም የ156ኛ ታቦር ተራራ የክፍለ ጦር አመራሮችም ማህበረሰቡ ላነሳቸው ጥያቄዎች ምላሹን  በመስጠት  የአምሃራ ሳይንት ቀጠና ለጠላት አስፈሪ የሆነ ኀይልን በመፍጠር የተጋረጠበትን የህልውና አደጋ በጋራ በመመከት ህዝባችን ከደጋፊነት ወደ ባለቤትነት መሽጋገር  እንዳለበት በስብሰባው የተገኘው ማህበረሰብ ጋር የጋራ መግባባት ላይ በመድረስ ውይይቱ ተጠናቋል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ነሃሴ 30/2018 ዓ.ም

3ኛ, በቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ ከዚህ ቀደም ይታዩ የነበሩ የማስ ሚዲያ አጠቃቀም ችግሮችን በተቀናጀ ሁኔታ በማረምና ድርጅታዊ የሚዲያ አጠቃቀም መርሆችን፣  መመሪያዎችንና ሕግና ደምቦችን ከምንጊዜውም በላቀ ሁኔታ አጠናክረን በመተግበር፣ በድርጅታችን፣ በዕዛችን፣ በማኀበረሰባችን፣ በሰራዊታችንና በአጠቃላይ በትግላችን ላይ ጉዳት ሲያደርሱ የቆዩ ዘ ፈቀዳዊ የሚዲያ አጠቃቀም አሰራሮችን ሸክፈን በተግባር የሚለካ ውጤት ለማምጣት እንደምንሰራ እንገልፃለን። በቀጠናችን፣ ከዕዙ ህዝብ ግንኙነት መምሪያና ከተፈቀደላቸው የሚዲያ፣ ኮሚኒኬሽንና ፕሮፖጋንዳ ክፍል ውጭ የሚደረጉ ኃላፊነት የጎደላቸው የማኀበራዊና የሳተላይት ሚዲያ ያልተገደቡ አጠቃቀሞች በትግላችን ላይ ካላቸው አሉታዊ ተፅዕኖ አኳያ ከዚህ በኋላ የማይደገሙ መሆናቸውን እያሳወቅን፣ ከመምሪያው፣ ሕግና ደንቡ ውጭ ልቅ የሆኑ የሚዲያ አጠቃቀሞች ላይ የሚገኙ የድርጅታችን አመራሮችና አባላት ላይ ተገቢውን ሕጋዊ የእርምት እርምጃ የምንዎስድ መሆኑን ተስማምተናል። 4ኛ, ለትግል እንቅፋት የሆነ፣ ሰራዊታችንን የሚከፋፍልና ማኀበረሰባችንን ላልተገባ ወጭና እንግልት የሚዳርግ ዘፈቀዳዊ የፋይናንስ አሰባሰብ፣ ቁጥጥርና ትግበራ በተቀናጀ ሁኔታ በዕዛችን ተስተካክሎ ለቀጣይ በድርጅታችን ፋይናንስ መምሪያና ሕግ ብቻ ተፈፃሚ ሆኖ እንዲቀጥልና ጥብቅ የኦዲትና ቁጥጥር ስራዎች ከተጠያቂነት ጋራ እንዲኖሩ ዕዛችን ይሰራል። 5ኛ, የድርጅታችንን ዓላማ ከግብ ለማድረስና ሰፊው የአማራ ህዝብ በኦህዴድ ብልፅግና አገዛዝ የተጋረጠብንን ሁለንተናዊ የህልውና አደጋ ለመመከት የምናካሄደውን ፖለቲካዊ የትጥቅ ትግል ከድርጅታዊ  መርህና መመሪያ ጋራ አቀናጅተን በተዋረድ ቀጠናችንን፣ ማኀበረሰባችንንና ሰራዊታችንን በሚመጥን መልኩ እንሰራለን። ከሌሎች ዕዞችም ጋራ ከዚህ ቀደም የነበረውን ግንኙነት ወደ ከፍተኛ ሁኔታ በማሳደግ በተቀናጀ ሁኔታ እንሰራለን። 6ኛ,የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ፤ ሊቀመንበር የነበሩትን አርበኛ ዘመነ ካሴን ጨምሮ፣ በድርጅት ኃላፊነት ወደ አፋብን የሄዱ በምክተል ሊ/መንበርነትና የፖለቲካ መምሪያ ኃላፊነት፣ በምክትል ሊ/መንበርነትና ወታዳራዊ አዛዥነት እንዲሁም በየመምሪያ ኃላፊነት የቆዩ ስራ አስፈፃሚ አባላትና የትግል ጓዶቻችን በቀጠናችን በአመራርነት በነበሩበት ወቅት ላበረከቱት ከፍተኛ የትግል አስተዋፅኦ፣ የቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ አዲሱ የስራ አስፈፃሚ አባላት ከልብ አመስግነው በቀጣይ የጀመሯቸውን መልካም ስራዎች አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አሳውቀዋል። አፋብን፤ ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ፣ አዲሱ የስራ አስፈፃሚ አባላት ላለፉት ተከታታይ ቀናት በአካል በመገናኘት ባካሄድው ጥብቅ ድርጅታዊ ውይይት ከ13 በላይ አጀንዳዎችን በመለየት አቅርቧል። በሰከነና በሰለጠነ ጓዳዊ መንፈስ ውይይቱን ያካሄደው ዕዛችን፣ ከዚህ ቀደም የነበሩ ዘፈቀዳዊ አሰራሮች በማረምና በማስተካከል፣ ድርጅታዊ መርህና አሰራር ላይ ተመርኩዞ በየደረጃው የማኀበረሰባችንንና የሰራዊታችንን ሰፊ ጥያቄዎች ለመመለስ በፍፁም ጓዳዊ ዝምድና፣ በታደሰ የትግል መንፈስና ጥንካሬ ከዚህ ቀደም የነበሩ የአሰራር ክፍተቶችን በተግባር ለይቶ በማስቀረት ታጋዩንና ህዝቡን ለመካስ በከፍተኛ ወኔና ፍላጎት ላይ ይገኛል። በመሆኑም በተዋረድ የዚህን ጥልቅ ውይይት ዉሳኔ በጉጉት ስትጠባበቁ የነበራችሁ የዕዝ፣ የኮር፣ የክፍለጦርና የሻለቃ አመራሮቻችንና ማኀበረሰባችን የዚህ መልካም መንፈስ አጋር እንድትሆኑ በታላቅ አክብሮት እናሳስባለን። ነሐሴ/ 29/ 2018 ዓ.ም የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ፤ ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ፤ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!

ከአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ፤ የተሰጠ መግለጫ፦ በአገራችን ኢትዮጵያ ከተሸነፉ የቅኝ ግዛት ወራሪ ኃይሎች ፍላጎት የተቀዳው ፀረ አማራነት ትርክት፣ ላለፉት 50 ዓመታት የአማራ ህዝብን በገዛ አገሩ ለአካላዊ፣ ለስነልቦናዊ፣ ለፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ እንዲሁም ለዘርፈ ብዙ ጉዳቶች አጋልጠውት ቆይተዋል። ይህ ፀረ አማራነት ትርክት በሂደት እያደገ መጥቶ በዋናነት ከ1983 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ በነበረው አገዛዝ ሕጋዊ ቅቡልነት አግኝቷል። በሂደት ደግሞ ሕገ መንግስታዊ መዋቅራዊ ድጋፍ ተበጀቶለት፣ እስካሁን ድረስ በኢትዮጵያ በተለያዩ ክፍሎች የአማራ ህዝብን ለዘር ጭፍጨፋና ለዘር ማፅዳት ዳርጎታል። ለሁለንተናዊ የህልውና አደጋም አጋልጦታል።   በአማራ ህዝብ ጥላቻና የሀሰት ትርክት ተኮትኩቶ ያደገው የኦህዴድ ብልፅግና አለቃ አብይ አህመድ የአጤ ምኒልክ መንበርን በማደናገር ከያዘበት መጋቢት 24/ 2010 ዓ.ም ጀምሮ፣ የአማራ ህዝብ ሞት ከየ ሚዲያዎች ገፅ የማይጠፋ የየዕለት ዜና ሆኗል። ይህ የአማ፨ ህዝብ መዋቅራዊ የየዕለት ጭፍጨፋ መፍትሔ እንዲያገኝ ህዝባችን በበርካታ ሰላማዊ መንገዶች ጥያቄዎችን ለአገዛዙ ቢያቀርብም መልስ ሳያገኙ ቀርተዋል። ይባስ ብሎ፣ ይህ መንግስታዊ ድጋፍና እውቅና የተሰጠው የአማራ ህዝብ ሁለንተናዊ ጥቃት ከመጋቢ /2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ጠቅላይ ግዛቶቹ እንዲገባ ተደርጓል። የኦህዴድ በግልፅግና አገዛዝ ከአሽከሩ ብአዴን ጋር በማበር የአስቸኳይ ጊዜ አዎጅ አውጥቶ በይፋ ህዝባችንን በሩ ድረስ በመምጣት መውረሩን ተከትሎ፣ የአማራ ህዝብ ራሱን ጨርሶ ከመጥፋት ለመታደግ ሲል ልጆቹን በፋኖነት አደራጅቶ ራሱን ከጥፋት መመከት ከጀመረ 3 ዓመታት ተሻግረዋል። ላለፉት ሶስት ዓመታት፣ አገዛዙ በአየርና በምድር አለኝ የሚለውን የኃይል አማራጭ ተጠቅሞ ህዝባችንን እየጨፈጨፈ ቢሆንም፣ ጀግናው ሰራዊታችን ፋኖ ህዝቡን አስተባብሮ እያደረገ ባለው ተጋድሎ የአገዛዙን ወራሪ ኃይል እንደየ አመጣጡ በመመከት ድልን መቀዳጀት ከጀመረ በርካታ ወራት ተቆጥረዋል። ስፊ ቀጠናዎችን ከአገዛዙ መዋቅር ውጭ በማድረግና በመቆጣጠር ሕዝባዊ መንግስት አቋቁሞ ህዝቡን ማስተዳደር ከጀመረ ዓመታት ተሻግረዋል። በዋናነት መሪ ድርጅታችን የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ/ አፋብን/ በአማራ የቁርጥ ቀን ልጆች ጥረት ከተመሰረተ በኋላ የፋኖ ፖለቲካዊ የትጥቅ ትግል በአገዛዙ ወራሪ ኃይል ላይ ከሚያሳርፈው የተቀናጀ ጥቃትና ከሚያገኘው ሁለንተናዊ ድል ባሻገር ከአገር አቀፍ አልፎ ዓለም አቀፋዊ እውቅናን እያገኘ መጥቷል። ፖለቲካዊ የትጥቅ ትግላችን በዚህ ግለት እየሄደ ባለበት ወቅት የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ፣ ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ፣ ላለፉት ተከታታይ ቀናት ከአዲሱ ስራ አስፋፃሚ አባላት ጋር በአካል በመገናኘት ጥልቅ ውይይት አካሄዷል። ዕዛችን አዲሱን የስራ አስፈፃሚ አባለት አዋቅሮ ይፋ ካደረገበት ጊዜ ጀምሮ በአጭር ጊዜ ውስጥ ወሳኝ ስራዎችን አከናውኗል። የተጓደሉ የኮር አመራሮችን ማሟላት፣ የየመምሪያውን የስራ ዕቅድ ማውጣትና መገምገም፣ በስልጠና የቆዩ ፋኖዎችን አስመርቆ ማሰማራትና አልፎ አልፎ ውጊያዎችን ማድረግ እንዲሁም ህዝባዊ መድረኮችን ማድረግና የሚዲያና ፕሮፖጋንዳ ስራዎችን ማከናዎን፤ ዕዛችን በአጭር ጊዜ ያካሄዳቸው የተለመዱ ተግባራት ናቸው።   ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ፤ በዚህ ወሳኝ ሂደት በመቀጠል ላለፉት ተከታታይ ቀናት ከአዲሱ የስራ አስፈፃሚ አባላት፣  የየመምሪያ ዋናና  ምክትል ኃላፊዎች፣ ከፋይናንስ ክፍሉና ከዕዛችን ሌሎች ተጨማሪ ወታደራዊ አደረጃጀቶች ጋር ሰፊና ጥልቅ ውይይት አካሄዷል። በዕዛችን ፖለቲካ መምሪያ በኩል ለውይይት መነሻ ይሆን ዘንድ የቀጠናውን የሶስት ዓመታት ጠንካራና ደካማ ጎኖችን በመለየት አጭር ሰነድ ቀርቧል። ላለፉት ሶስት ዓመታት በጥልቀት ተፈትሸው ያልተከናወኑ ድርጅታዊ ተግባራትን በአጀንዳ በመለየትና በአካል በመወያየት ለቀጣይ ትግበራ የጋራ አቅጣጫ በማስቀመጥ ውሳኔዎችን አሳልፏል። በቀጠናው የሚገኘውን ህዝባችንን ከምንጊዜው በላቀ ሁለንተናዊ ደህንነቱን በመጠበቅ ተገቢውን የህዝብ አስተዳደርና ማኀበራዊ አገልግሎት እንዲያገኝ በትጋት እንደሚሰራ፤ ጊዜያዊ የሕዝብ አስተዳደሩን ጨምሮ የዕዛችንን ከፍተኛ አመራሮች በተዋረድ እስከ ሻለቃ ድረስ ከምንጊዜውም በላቀ ሁኔታ ፖለቲካዊ የትጥቅ ትግሉን በማሳለጥ የተጣለባቸውን ኃላፊነት በትጋትና በታማኝነት እንዲወጡና የሚገኘውን የፋይናንስ ማዕከላዊነት፣ አሰባሰብና ቁጥጥር እንዲከታተሉ ማድረግ፤  ከዚህ ቀደም፣ በቀጠናችን በተበታተነ ሁኔታ ሲካሄድ የቆየውን የመማር ማስተማር ሂደት በተሳለጠና በባለቤትነት ስሜት እንዲካሄድ ፅኑ ፍላጎት እንዳለውና እንደሚሰራ፤ በዕዝ ደረጃ የተጓደሉ የትግል ኃላፊነት ቦታዎች እንዲሟሉና የሰራዊታችንንና የማኀበረሰባችንን ጥያቄዎችንና ቅራኔዎች በተደራጀ ሁኔታ በመመለስና በመፍታት፣ ድርጅታችንን ከምንጊዜውም በላይ በመጠበቅ፣ ድርጅታዊ ዓላማችንን ከግብ ለማድረስ በከፍተኛ ፅናትና ትጋት ከምንጊዜውም በላቀ ሁኔታ እንደምንሰራ በውይይታችን አረጋግጠናል። እነዚህ የትግል ስራዎቻችንን በተሳለጠና በተጠና መልኩ ለማስኬድ ያስችል ዘንድ ስልታዊ ዓመታዊ እቅድ በቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ ፅ/ቤት በኩል ተዘጋጅቶ ለውይይት ቅርቧል። ስራ አስፈፃሚ አባላት ዕቅዱን በጥልቀት በመፈተሽና በማሻሻል በሙሉ ድምፅ አፅድቆታል። የአፋብን፤ ቴዎድሮስ ዕዝ ስራ አስፋፃሚ አባላት፣ በአካል በመገናኘት ለተከታታይ 10 ቀናት በተለያዩ አጀንዳዎች ዙሪያ በጥልቀት ያካሄደውን ድርጅታዊ ውይይት አስመልክቶ የሚከተሉት ነጥቦች በአስፈፃሚው በትኩረት እንዲሰራባቸው አቅጣጫ አስቀምጧል። 1ኛ, አገዛዙ በአማራ ህዝብ ላይ በከፈተው የዘር ማጥፋት ጭፍጨፋ ምክንያት ትምህርት ቤቶቻችንን ለወታደራዊ ካምፕ አገልግሎት ሲጠቀማቸው ቆይቷል። የአገዛዙ ወታደሮች የትምህርት ተቋማት መቀመጫ ወንበሮቻቸውን ጨምሮ ሌሎች ቁሳቁሶችን በመሰባበር ለምሽግነትና ለማገዶነት አገልግሎት አውሏቸዋል። እያዋላቸውም ይገኛል። ከእነዚህ እኩይ ተግባራቱ በተጨማሪ በከባድ መሳሪያዎችና በድሮን ተቋማቱን በተከታታይ በመደብደቡና በማውደሙ ምክንያት ላለፉት 3 ዓመታት የመማር ማስተማር ስራው እንዲቋረጥ ለማድረግ ሞክሯል። ይሁን እንጂ፣ ዕዛችን በዚህ ምክንያት ከትምህርት ገበታቸው ተለይተው የቆዩ ተማሪዎቻችንን በተለያዩ አማራጮች ባልተሟላ ሁኔታም ቢሆን ከፊደል ገበታ ተለይተው እንዳይቆዩ ጥረት አደርጓል። ዛሬ ደግሞ ይህ የቆዬ ጥረታችን በተሟላና በተቀናጀ ሁኔታ መስከረም ወር 2019 ዓ.ም ጀምሮ እንዲቀጥልና የትምህርት ማኀበረሰቡ፣ ሰራዊታችን፣ ህዝባችንና ሌሎች ባለ ድርሻ አካላት ከምንጊዜው በላቀ ሁኔታ ርብርብ በማድረግ  የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ስራ አስፋፃሚ በወሰነው መሰረት እንዲተገበር እንሰራለን። 2ኛ, መሪ ድርጅታችን አፋብን ያወረዳቸውንና የሚያወርዳቸውን ድርጅታዊ የአሰራር መርሆች መመሪያዎች፣ ሕግና ደንቦችን ተቀብለን የምናስፈፅምና የምንፈፅም መሆኑንን አየገለፅን፣ ዕዛችን ከዚህ ቀደም የነበሩ ደካማ አሰራሮችን በጥልቀት ገምግሞ በመለየትና ስልታዊ ዓመታዊ ዕቅድ በማውጣት ለድርጅታችን፣ ለህዝባችንና ለሰራዊታችን ከምንጊዜው በላቀ ሁኔታ ዕቅዶቻችንን በጊዜ ለክተን በመስራት የሚታይ ውጤት ለማምጣት ቁርጠኛ አቋም መያዛችንን እናሳውቃለን።

3ኛ, በቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ ከዚህ ቀደም ይታዩ የነበሩ የማስ ሚዲያ አጠቃቀም ችግሮችን በተቀናጀ ሁኔታ በማረምና ድርጅታዊ የሚዲያ አጠቃቀም መርሆችን፣  መመሪያዎችንና ሕግና ደምቦችን ከምንጊዜውም በላቀ ሁኔታ አጠናክረን በመተግበር፣ በድርጅታችን፣ በዕዛችን፣ በማኀበረሰባችን፣ በሰራዊታችንና በአጠቃላይ በትግላችን ላይ ጉዳት ሲያደርሱ የቆዩ ዘ ፈቀዳዊ የሚዲያ አጠቃቀም አሰራሮችን ሸክፈን በተግባር የሚለካ ውጤት ለማምጣት እንደምንሰራ እንገልፃለን። በቀጠናችን፣ ከዕዙ ህዝብ ግንኙነት መምሪያና ከተፈቀደላቸው የሚዲያ፣ ኮሚኒኬሽንና ፕሮፖጋንዳ ክፍል ውጭ የሚደረጉ ኃላፊነት የጎደላቸው የማኀበራዊና የሳተላይት ሚዲያ ያልተገደቡ አጠቃቀሞች በትግላችን ላይ ካላቸው አሉታዊ ተፅዕኖ አኳያ ከዚህ በኋላ የማይደገሙ መሆናቸውን እያሳወቅን፣ ከመምሪያው፣ ሕግና ደንቡ ውጭ ልቅ የሆኑ የሚዲያ አጠቃቀሞች ላይ የሚገኙ የድርጅታችን አመራሮችና አባላት ላይ ተገቢውን ሕጋዊ የእርምት እርምጃ የምንዎስድ መሆኑን ተስማምተናል። 4ኛ, ለትግል እንቅፋት የሆነ፣ ሰራዊታችንን የሚከፋፍልና ማኀበረሰባችንን ላልተገባ ወጭና እንግልት የሚዳርግ ዘፈቀዳዊ የፋይናንስ አሰባሰብ፣ ቁጥጥርና ትግበራ በተቀናጀ ሁኔታ በዕዛችን ተስተካክሎ ለቀጣይ በድርጅታችን ፋይናንስ መምሪያና ሕግ ብቻ ተፈፃሚ ሆኖ እንዲቀጥልና ጥብቅ የኦዲትና ቁጥጥር ስራዎች ከተጠያቂነት ጋራ እንዲኖሩ ዕዛችን ይሰራል። 5ኛ, የድርጅታችንን ዓላማ ከግብ ለማድረስና ሰፊው የአማራ ህዝብ በኦህዴድ ብልፅግና አገዛዝ የተጋረጠብንን ሁለንተናዊ የህልውና አደጋ ለመመከት የምናካሄደውን ፖለቲካዊ የትጥቅ ትግል ከድርጅታዊ  መርህና መመሪያ ጋራ አቀናጅተን በተዋረድ ቀጠናችንን፣ ማኀበረሰባችንንና ሰራዊታችንን በሚመጥን መልኩ እንሰራለን። ከሌሎች ዕዞችም ጋራ ከዚህ ቀደም የነበረውን ግንኙነት ወደ ከፍተኛ ሁኔታ በማሳደግ በተቀናጀ ሁኔታ እንሰራለን። 6ኛ,የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ፤ ሊቀመንበር የነበሩትን አርበኛ ዘመነ ካሴን ጨምሮ፣ በድርጅት ኃላፊነት ወደ አፋብን የሄዱ በምክተል ሊ/መንበርነትና የፖለቲካ መምሪያ ኃላፊነት፣ በምክትል ሊ/መንበርነትና ወታዳራዊ አዛዥነት እንዲሁም በየመምሪያ ኃላፊነት የቆዩ ስራ አስፈፃሚ አባላትና የትግል ጓዶቻችን በቀጠናችን በአመራርነት በነበሩበት ወቅት ላበረከቱት ከፍተኛ የትግል አስተዋፅኦ፣ የቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ አዲሱ የስራ አስፈፃሚ አባላት ከልብ አመስግነው በቀጣይ የጀመሯቸውን መልካም ስራዎች አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አሳውቀዋል። አፋብን፤ ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ፣ አዲሱ የስራ አስፈፃሚ አባላት ላለፉት ተከታታይ ቀናት በአካል በመገናኘት ባካሄድው ጥብቅ ድርጅታዊ ውይይት ከ13 በላይ አጀንዳዎችን በመለየት አቅርቧል። በሰከነና በሰለጠነ ጓዳዊ መንፈስ ውይይቱን ያካሄደው ዕዛችን፣ ከዚህ ቀደም የነበሩ ዘፈቀዳዊ አሰራሮች በማረምና በማስተካከል፣ ድርጅታዊ መርህና አሰራር ላይ ተመርኩዞ በየደረጃው የማኀበረሰባችንንና የሰራዊታችንን ሰፊ ጥያቄዎች ለመመለስ በፍፁም ጓዳዊ ዝምድና፣ በታደሰ የትግል መንፈስና ጥንካሬ ከዚህ ቀደም የነበሩ የአሰራር ክፍተቶችን በተግባር ለይቶ በማስቀረት ታጋዩንና ህዝቡን ለመካስ በከፍተኛ ወኔና ፍላጎት ላይ ይገኛል። በመሆኑም በተዋረድ የዚህን ጥልቅ ውይይት ዉሳኔ በጉጉት ስትጠባበቁ የነበራችሁ የዕዝ፣ የኮር፣ የክፍለጦርና የሻለቃ አመራሮቻችንና ማኀበረሰባችን የዚህ መልካም መንፈስ አጋር እንድትሆኑ በታላቅ አክብሮት እናሳስባለን። ነሐሴ/ 29/ 2018 ዓ.ም የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ፤ ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ፤ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!

"ጀብደኛው 14ኛክ/ጦር በአንድ ወር ውስጥ የአገዛዙን ዙፋን አስጠባቂ ሰራዊት በማፈራረስ በውጊያ በመማርክና ስቦበማስከዳት በርካታ መሳሪያ እና ተተኳሺ ማግኘት ችሏል":- የጠላትን ሀይል በማፈራረስ ያለምንም ተኩስና ምሷትነት ስቦ በማስከዳት ወደተቋም መቀላቀል ከድልም በላይ ታላቅ ስኬት ነው:: =============================== ከንሃሴ01/12/2018 - 30/12/2018ዓ,ም የአብይ አህመድን ስርዓት በመቃወም 14ኛ ክ/ጦር የተቀላቀሉ የሰራዊት አባላት ዝርዝር:- 1ኛ:ወ/ር በላቸው ካሴ=ፓራኩማዶጋታመሪ ከደ/ኤልያስ 2ኛ:ወ/ር ዳዊት ይሁኔ==ፓራኩማዶቲም መሪከደ/ኤልያ 3ኛ:ወ/ር እሱባለው ወድሙ==ፓራኩማዶከደ/ኤልያስ 4ኛ:ወ/ር ሰለሞን አለነ===ፓራኩማዶ ከደ/ኤልያስ 5ኛ:ወ/ር አስጨንቅ አደርው==ፓራኩማዶከደ/ኤልያስ 6ኛ:ወ/ር ታደሰ ባሴ===ፓራኩማዶ ከደ/ኤልያስ 7ኛ:ም/ሳጅን ደጉገ/ይኋንስ==አድማበትን ከሊባኖስ 8ኛ:ወ/ር ምግባር ቆያቸው==ፓራ ኩማዶ ከፈደቃ 9ኛ:ወ/ር ይኋንስ ሞሴ====አድማብተና ከቸርተከል 10ኛ:ወ/ር ታረቀኝ ሉሌ===ፓራ ኩማዶ ከፈደቃ 11ኛ:ወ/ር አብርሀም ይሁኔ==አድማበትን ከባሶሊበን የላምገጅ 12ኛ:ወ/ር አቢዩት ካሴ====ፓራኩማዶ ከደ/ኤልያስ 13ኛ:ወ/ር ሙሉሰው እድሚለም==ፓራኩማዶ ከደ/ኤልያስ 14ኛ:አስር/አለቃ እሸቴ መርሻ==መከላከያ ጋታመሪ ከቸርተከል 15ኛ:ወ/ር ሀብታሙ ጊዜ===ፓራኩማዶ ከደ/ኤልያስ 16ኛ:ወ/ርነብዩ ስታየሁ===ፓራ ኩማዶ ከደ/ኤልያስ 17ኛ:ወ/ር ጌታቸው ገደፈው===መከላከያ ከቸርተከል 18ኛ:ወ/ር አበባው ዳኝ====መከላከያ ከቸርተከል 19ኛ:ወ/ር አየነው ከበደ===መከላከያ ቲም መሪ ከቸርተከል 20ኛ:መቶ/አለቃ ውድነህ አጅጉ==መከላከያ ሬጅመት አዛዥ ከደ/ኤልያስ 21ኛ:ወ/ር ያሲን ሙሀመድ===መከላከያ ከደ/ኤልያስ 22ኛ:******=መከላከያ 01ብሬን ከነሸሸሉናአንድ ኮፍ ክላሺ በመያዝ ከደ/ኤልያስ 23ኛ:******=መከላከያ 01ስናፓርና ሁለት እግር ክላሺ በመያዝ ከደ/ኤልያስ **#በምርኮየተገኝ:- 👉በቀን 13/12/2018ዓ,ም ስናን ደብርዘይት በንጉስተክለሃይማናኖት ሻለቃና በስናን አባጅሜ ሻለቃ እንዲሁም በ14ኛክ/ጦር ቃኝናምሃዲስ ጥምርት በተካሄደውጊያ የተገኝ ድል 👉ክላሺ=====56ክላሺ 👉ምርኮኛ=====20 👉ብሬን=====02 👉የተደመሰሰ====አንድ ሬጅመት 👉አብራረው=====አራትት 👉ኤስኪየስመሳሪያ===02 👉ከላሺ ተተኳሺ====9500 👉ድሺቃ ተተኳሺ====400 👉ብሬንተተኳሺ=====2000 *## በቀን 21/12/2018ዓ,ም በረኸኛው ጅበላሙተራ ሻለቃ በደ/ኤልያስ ወረዳ አበሺም በተሰራው አስደናቂ ኦፕሬሺን የተገኝ ድል:- 👉በቁጥር ያልታወቀ የጥላት ሀይል ሙትና ቁስለኛ 👉በእጅ የተማረከ=አንድ ሰላም አስከባሪ ሚሊሻ 👉ክላሺ=====አንድ 👉ሲሶ ክላሺ===አንድ 👉በርካታ ወታደራዊ ሚሊተሪናሻጣ ተገኝቷል ✍️14ኛክ/ጦር የጠላት የራስ ምታት፤ ✍️የወገን ኩራት ፤ምንግዜም አንድ እርምጃ ወደፊት! አዲስትውልድ!አዲስ አስተሳስብ !አዲስ ተስፋ!!! ከፋት ለማንም !በጎነት ለሁሉም!! ነጻነታችን በተባበረ ክዳችን!💪💪 የአፋብን፤ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 206ኛ ኮር የ14ኛ ክ/ጦር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሀላፊ ፋኖ ላቃቸው በላይ

64ኛ ክ/ጦር ከጠላት ነፃ በወጡ ቀጠናዎች ህዝባዊ ውይይት አካሄዶል። ነሀሴ 29/2018 ዓ.ም ~~~ አፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር እና የእነማይ ወረዳ ጊ/መንግስት አመራሮች በእነማይ ወረዳ ደብረፅሞና ቀበሌ ከሚገኙ ማህበረሰብ ክፍል ጋር ነሀሴ 29/2018 ዓ.ም ሰፊ ውይይት አካሂደዋል። በውይይት መድረኩ የተገኙት የማህበረሰብ ክፍል የአገዛዙ ብልፅግና ሰራዊት በእነማይ ወረዳ ዲማ ጊዮረጊስና ደብረፅሞ ቀበሌዎች የጤና ተቋም ውድመት፣ የንፁሃን ግድያ፣ የንፁሀን ሀብት ንብረት ውድመትና ዝርፊያ የፈፀማቸው ግፎች በተመለከተ በስብሰባ መድርኩ ለተገኙ የማህበረሰብ ክፍል አገዛዙ ለህዝባችን ዕርህራሄ የሌለው መሆኑን ግንዛቤ ተሰጥቷል። ትምህርትን በተመለከተ የብልፅግና አገዛዝ በዚህ ሶስት ዓመት ትምህርትን እንደ ትልቅ የፖለቲካ ፍጆታ በመጠቀም የፕሮፓጋንዳ መሳሪያ በማድረግ ሲጠቀምበት መቆየቱን ግንዛቤ በመስጠት ትምህርት ለሰው ልጆች አስፈላጊ መሆኑን ግንዛቤ በመስጠት በ2019 ዓ.ም አፋብን ትምህርት መፈቀዱን ለቀበሌው ኗሪዎች በማሳወቅ ልጆቻቸውን ወደ ት/ቤት በመላክ ምዝገባ እንዲያካሂዱና ትምህርት እንዲጀመሩ አቅጣጫ ተሰጥቷል። በስብሰባ መድርኩ የተገኙት የማህበረሰብ ክፍል ደስተኛ መሆናቸውን አረጋግጠናል። አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!                ነሀሴ 29/2018 ዓ.ም አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 2ኛ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት

ሰበር ዜና! በ303ኛ አሳምነው ኮር ፋኖዎች ድሐና ወረዳ አዚላ ከተማ መሽጎ የነበረውን የብልፅግና ጦር ሙሉ በሙሉ ተደመሰሰ! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ምኒልክ 1ኛ ዕዝ 303ኛ አሳምነው ኮር አካል ከሆኑት 14ኛ ኃይሉ ከበደ ክፍለ ጦር፣ 19ኛ ተፈራ ማሞ ክፍለ ጦር እና ከዋግሹም ብርጌድ በተውጣጡ ፋኖዎችና የኮሩ ከፍተኛ ወታደራዊ አመራሮች በተሳተፉበት አውደ ውጊያ ዋግኸምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ድሃና ወረዳ 020 ቀበሌ አዚላ ከተማ መሽጎ የነበረው የብልፅግና ሰራዊት ሙሉ በሙሉ የተደመሰሰ ሲሆን የተረፈው ሃይል ደግሞ ራሳቸውን ለማዳን ለፋኖ እጅ ሰጥተዋል። ነሃሴ 29 ቀን 2018 ዓ/ም ከጧቱ 1:30 ሰዓት ላይ ውጊያው ተጀምሮ ከረፋዱ 3:30 ሰዓት ላይ ሙሉ በሙሉ ፋኖዎች ከተማዋን የተቆጣጠሩ ሲሆን የዋግኸምራ ዞን የምርመራ ኃላፊው ኮማንደር ሀብታሙን ጨምሮ ሰባ አንድ (71) ሚሊሻና ፖሊስ፣ አንድ(01) ድሽቃ፣ አንድ(01) ብሬን፣ አንድ(01) ኢምፎርቲ፣ 80 Ak-47 ክላሽንኮቭ፣ ሁለት ሳጥን የብሬን ተተኳሽ፣ አምስት የብሬን ሸንሸል፣ አንድ ሸንሸልና አንድ ሳጥን የድሺቃ ተተኳሽ መማረክ ተችሏል ሲል የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ምኒልክ 1ኛ ዕዝ 303ኛ አሳምነው ኮር ቃል አቀባይ መረጃውን አድርሷል። ተጨማሪ የቁስ ምርኮ መረጃዎችን ነገ የምናደርስ ይሆናል! መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ነሃሴ 29/2018 ዓ.ም

ለታላቁ የአማራ ሕዝብ ሕልውና መከበር ጀግኖች ታላላቅ ገድል ፈፅመው አልፈዋል! የጀግናው ፋኖ ደምሌ ይመር ተጋድሎ እና እስከ መስዋዕትነት የዘለቀ ለሕዝብ መታመን! ለታላቁ የአማራ ሕዝብ ሕልውና መከበርና ፍትሕ ርትዕ ለማስፈን በሚደረገው ተጋድሎ ውስጥ ታላቅ ገድል የፈፀመው፡ የቀድሞው ምስራቅ አማራ ፋኖ ካፈራቸው እንቁ ጀግኖች መካከል አንዱ የሆነው ፋኖ ደምሌ ይመር (የብሬኑ ንጉስ) ለዓመታት ስለ አማራ ሕዝብ ሲል በዱር በገደሉ ሲዋደቅ ቆይቶ  በጀግንነት እንደተዋጋ በመጨረሻም ክቡር መስዋዕትነትን ከተቀበለ እንሆ ድፍን አንድ ዓመትን አስቆጥሯል። እምቢ ለሕዝቤ፤ እምቢኝ ለነፃነቴ በሚል ገና በጧት ዱር ቤቴ ያለው ይህ ጀግና፡ በዞብል፣ በቀዩ ጋሪያ እና በበላጎ ትውልድ የሚኮራባቸውና ታሪክ በወርቅ ቀለሙ የከተባቸው አስደናቂ ጀብዶችን ፈፅሟል። በተጨማሪም፡ የአምባሰል ተራሮች፣ የወልዲያ፣ የጊራና፣ የውርጌሳ፣ የቃሊም፣ የተኩለሽ፣ የካራኤላ፣ የጠዘጠዛ፣ የኮቡ ጋሪያ፣ የአዲስቅኝ፣ የሮቢት፣ የመንጀሎ፣ የአዋስ፣ የሳንቃ፣ የሙጃና ሌሎች በርካታ ስፍራዎች ስለ አርበኛ ደምሌ ይመር (የብሬኑ ንጉስ) ጀግንነትና ተጋድሎ አፍ አውጥተው ይመሰክራሉ። ፋኖ ደምሌ ይመር በወሎ ቤተ አማራ ቀጠና ወግዲ ወረዳ ልዩ ስሙ አብየ ጉርባ በተባለ አከባቢ ነሐሴ 29/ 2017 ዓ/ም በተደረገ ተጋድሎ በርካታ የጠላት አባላትም ደምስሶ ስለ ታላቁ አማራ ሕልውና ሲል ክቡር መስዋዕትነትን ተቀብሏል። የጀግናው ደምሌ ይመር ህያው ታሪክና የጀግንነት አሻራ በትግል አጋሮቹና በህዝቡ ልብ ውስጥ ዘላለም ሲታወስ ይኖራል። የጀግና ሞቱ እረፍቱ ነው፣ ጀግኖች የወደቁበት ትግል በድል ይቀጥላል! ክብርና ዘላለማዊ ሞገስ ለሕልውና ትግሉ ሰማዕታት!!