es
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Ir al canal en Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Mostrar más
2 923
Suscriptores
+3224 horas
+3727 días
+36630 días
Archivo de publicaciones
በመንዝ እና ግሼ አውራጃ የዕዙ ስምሪት አካላት የክላስተር አደረጃጀቶችን በመገምገም፡ በክላስተሩ የአባት አርበኞች ጦር መመስረቱ ተገለፀ!! ጳጉሜ 03/2018 ዓ.ም በመንዝ እና ግሼ አውራጃ ከአንድ ወር በፊት የተዋቀሩ ክላስተሮችንና አደረጃጀቶችን ወርሃዊ የስራ አፈጻጸም መገምገሙን የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ የስምሪት ቡድን አስታወቀ። ግምገማው በመንዝ እና ግሼ አውራጃ በሚገኙት ግራርአምባ እና ወጀድ ክላስተሮች ላይ የተካሄደ ሲሆን፣ በስራቸው የሚተዳደሩ ቀበሌዎችን ግልጽና ቀልጣፋ አሰራር በመከተል የህዝብ አገልግሎትን በማቀላጠፍ እንዲሁም የፍትህ ስርዓቱን በማሻሻል ረገድ የተከናወኑ ስራዎች ተገምግመዋል። በርካታ ቀበሌዎችን እና አባት አርበኞችን ያቀፈው "ወዠድ ክላስተር" (014፣ 015፣ 016፣ 017፣ 018 እና 019) ቀበሌዎችን በቅንጅት ገምግሞ፡ ጠንካራና ግዙፍ፣ የአርበኞች ክፍለ ጦር መመስረቱን አስታውቀዋል። የተመሠረተው የአርበኞች ክፍለ ጦሩ የአካባቢውን ሰላም ከመጠበቅ ባሻገር ለህልውና ትግሉ ስኬት ሚናውን እንደሚወጣ ተገልፆ፣ ይህ አዲስ የተመሰረተው ክፍለ ጦር በክብር በተሰዋው ታጋይ ስም " ካሳ አደፍርስ ክፍለ ጦር" ተብሎ ተሰይሟል። ይሕ ክፍለ ጦር፡ ነብሮ ሻለቃ፣ልጅ ስዩም መኮንን ሻለቃና ሙላቱ ወልደሚካኤል ሻለቃዎችን በማጣመር የተዋቀረ ሲሆን፧ ለክፍለ ጦሩ ጠንካራና ታታሪ አመራሮችን ሠይሞ ተዋቅሯል። በመጨረሻም ለክፍለ ጦሩ የተሰየሙት አመራሮች የተጣለባቸውን አደራ፡ የፍትህ እና የሰላም ማስከበር ኃላፊነት በቅንነት፣ በታማኝነትና በተጠያቂነት ለማገልገል ቃለ-መሀላ ፈጽመው ውይይቱ ተጠናቋል። "ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር ጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር አጥናፋ ብርጌድ አባላትን ለማፈን በሌሊት የተንቀሳቀሰው የአገዛዙ ሚሊሻ በደረሰበት ድንገተኛ ምት ከፍተኛ ኪሳራ ደረሰበት! ጷጉሜ 2/2018ዓ.ም ከሌሊቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ በወገራ ወረዳ  ልዩ ቦታው ብራ ታዲወስ የጠላት ኃይል አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ዳግማዊ ቴዎድሮስ 5ኛ ኮር ጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር አጥናፋ ብርጌድ አባላት ላይ አፈና ለመፈጸም እንቅስቃሴ አድርጎ የነበረውን የጠላት ኃይል የመልሶ ማጥቃት እርምጃ 3 የኃይል አባላትን ሲደመሰሱ 9 ያህሉን ደግሞ  ከቀላል እስከ ከባድ ቁስለኛ ሆነዋል። በዚህ ድንገተኛ ምት የተደናገጠው የጠላት ኃይል በርካታ ንብረቶችን  ጫማዎችን እና ትጥቆችን እያዝረከረከ ከአምባጊወርጊስ ከተማ ተጨማሪ የመከላከያ እና የአድማ ብተና ኃይል በማስገባት በብራ ታዲወስ እና ሰንበትየ ዙርያ  እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። በዚህ ድንገተኛ ምት ሽንፈት የደረሰበት ኃይል ​ተመስገን ጌታ የኋሌ የተባለ የ10 ዓመት ህፃን የተገደለ ሲሆን፣ በክረምት የግብርና እና የእንስሳት ጥበቃ ሥራ ላይ የነበሩ ከ28 በላይ ንፁሃን ዜጎች "የፋኖ ቤተሰብ ናችሁ" በሚል ሽፋን ታስረዋል። ከነዚህ መካከል እድሜ ጠገብ አዛውንቶች፣ ሴቶች እና ህፃናት እንደሚገኙበትና የአርሶ አደሩ እንስሳት ጭምር ማለትም ከብት፣ በግ፣ ፍየልና ዶሮዎችን የማረድ እና የመዝረፍ ድርጊት ዘግናኝ ችግሮችን እየተፈጸመ መሆኑን መረጃውን ያደረሰን የክፍለ ጦሩ የህዝብ ግንኙነት ነው። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! ​አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

የአጣዬ ህዝብ በረጅም የጽናትና የመከራ ታሪኩ ውስጥ፣ በየዘመናቱ አብረውት ከበሉና ከአንድ ማህፀን ከወጡ የራሱ ወገኖች ብዙ ከሃዲዎችንና ባንዳዎችን አሳልፏል፤ ዛሬም ያሳልፋል፣ ነገም በታሪክ መዝገብ ውስጥ እያሳለፋቸው ይኖራል። ነገር ግን የዚህ ግለሰብ አረመኔያዊነትና ጭካኔ የተሞላበት ተግባር ግን ከማንኛውም የበደል ታሪክ በላይ ሆኖ የጠቅላላውን የአጣዬ ህዝብ ልብ በፅኑ ሀዘን የሚያደማ፣ ለመሸከም እጅጉን የሚከብድ መራራ እውነት ሆኗል። ​ወደ ኤፍራታ ግድም ፣ ለነገ ተስፋ የነበሩ ምንም የማያውቁ ንጹሃን የአጣዬ ወጣቶችን ያሳድዳል፤ ያለ አንዳች ጥፋታቸው በእስር ቤት ውስጥ እያፈነ ያሰቃያቸዋል። በላባቸው ያፈሩትን ንብረት፣ ጥረታቸውንና መላ ጥሪታቸውን ያለ አንዳች ርህራሄ እያወደመ ይዘርፋል። በዚህ ብቻ ሳይበቃ፣ አእምሮ የሚጸየፋቸውን፣ ሰብአዊነትንና የህዝባችንን ክብር የሚያዋርዱ እጅግ አላስፈላጊና ዘጋቢ ስራዎችን ይፈጽማል። ​ከሁሉም በላይ ግን የህዝቡን አንጀት የሚያቃጥለውና እንባን የሚያስቆርጠው የሴቶቻችን ሁኔታ ነው፤ የዚህ አበሳ ደራሽ የሆነውን የአጣዬን መልካም መልካም ሴቶች "ለመከላከል" በሚል መራራና አሳዛኝ ምክንያት፣ ፍላጎታቸውንና ክብራቸውን ረግጦ ለጀነራሎች በግዳጅ አሳልፎ ይሰጣል። ይህ በህዝባችን ላይ የደረሰ ውርደትና የእናቶቻችን እንባ ሰማይን የሚያንቀጠቅጥ ሀዘን ሆኖብናል። ​እውነት ለመናገር ወንድሙ ካሳ በገዛ ወገኑና በአጣዬ ህዝብ ላይ የሚሰራው ይህ አረመኔያዊ ስራ እጅጉን ከባድ፣ ህመም የሚያበዛና የታገሱትን ድንበር ያለፈ ነው። ነገር ግን ከዚህ በላይ መከራውን ዝም ብሎ ማየት አይቻልም። ምንም ይሁን ምን ከምንም ነገር በላይ ለአማራና ለአጣዬ ህዝብ ህልውና፣ ክብርና ታሪክ የሚበልጥ የለም። ​የአጣዬ ህዝብም ይህን መራራ ሀዘንና የበደል ጽዋ እያየ ከእንግዲህ እጁን አጣጥፎ አይቀመጥም፤ እኔም የዚህ ህዝብ አካል ነኝና በቀጥታ ወደ ስራ እገባለሁ። ከዚህ በኋላ ማን እንደሆንኩኝ፣ ለወገኔና ለህዝቤ የመቆም አቅሜ ምን ያህል እንደሆነ በተግባር አሳየዋለሁ! #Dave #Amhara

በፈቃዱ በላይ ክፍለ ጦር በወታደራዊ ብልሃትና ህዝባዊ ወገንተኝነት፡ አገዛዙ በግዳጅ ለጥይት ማብረጃ ያሰለፋቸውን ንጹሐን ዜጎች ሕይወት ታደገ!! ጳጉሜ 02/2018 ዓ.ም በሸዋ ጠቅላይ ግዛት፣ መራቤቴ አውራጃ ደራ ወረዳ በሚገኘው ቱቲ ገብሮ (01 ቀበሌ) ሠቀዮ ጎጥ፣ ጨቋኙ የአበይ አህመድ አገዛዝ ወንበር አስጠባቂ የሚሊሻ ኃይል በህዝቡ ላይ የደቀነውን የግዳጅ ሰንሰለትና የጥይት ማብረጃ ሴራ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ፣ አፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር፣ በፈቃዱ በላይ ክፍለ ጦር አናብስቶች በላቀ ወታደራዊ ብልሃትና ጥበብ ማክሸፋቸውን የኮሩ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አስታወቀ። ገዥውን ስርዓት እያገለገሉ የሚገኘው ሚሊሻ፣ ትናንት ምሽት በ01 ቀበሌ የሚሊሻ ጠርናፊ ሻለቃ መሪ አቶ ደረጀ ተምትም ጥሩምባ በማስነፋት፣ ህዝቡ ማለዳ ላይ ወደ ማሳ ወጥቶ አረም እንዲያርምለት ትዕዛዝ አውርደው፤ ይሕንን የግዳጅ ትዕዛዝ በማይቀበሉ አካላት ላይ የ2,000 (ሁለት ሺህ) ብር የገንዘብ ቅጣት እንደሚጣልበት በመግለፅ ከፍተኛ ማስፈራሪያና ማስጠንቀቂያ አስተላልፎ ነበር። መረጃው በአግባቡ የደረሳቸው የበፈቃዱ በላይ ክፍለ ጦር የተሸረበውን ሴራ አስቀድሞ በመረዳት፣ ከከተማው ወጣ ብሎ በሚገኘው የአቶ ደረጀ ተምትም ማሳ አካባቢ ቀድሞ ስልታዊ ቦታ በመያዝ ደፈጣ አዘጋጅተው፤ ከተጣለበት የገንዘብ ቅጣት ለማምለጥ ማለዳ በልጁ ወደ ማሳው የተገደደውን ሕዝብ ያለምን ተኩስ ለመታደግ ተችሏል። ጥበቃ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቅ የነበረው ሚሊሻ ህዝቡን አሳልፎ ወደ ማሳ በመላክ አፋፍ ተኩስ እዲከፈትባቸው ያደረገ ቢሆንም በተሳካ የመረጃ ክትትል ሕዝቡን ሰብሰቦ ግንዛቤ በመስጠት የጠላትን እቅድ ሳይሳካ እዲመለሱ ተደርጓል።መታደግ ተችሏል። መረጃን ተጠቅማችሁ ላደረጋችሁት ወታደራዊና ፖለቲካዊ ጥበብ እጅግ እያደነቅን፣ እዲሕ አይነቱን የሴራ ፖለቲካ ግንዛቤውም ይሁን ጠላትን የመተባበር ፍላጎቱ ሳይኖረን በግዳጅና በቅጣት ማስፈራሪያ ተደርጎብን ነው ከዚሕ የተገኘንው ሲሉ ሃሳባቸውን ገልፀዋል። " ክብር ለትግሉ ሰማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

መጥፎ ሰዎች እና እባብ የመመሳሰል ችግር የለባቸውም የማይለወጥ አንድ አይነት ባህሪያቸው በማይክሮ ሰከንድ መርዘው በደቂቃወች ውስጥ የመግደል አደገኛነት መለያቸው ነው። ውድ የሰራዊታችን አባላትና አመራር ውስጠ ማንነታቸው በማይታወቅ የሰው እባቦች  ተነድፎ ላለመውደቅ ዋነኛው መፍትሄ አስተውሎ በመራመድ ለጉዞአችን ልዩ ትኩረት በመስጠት ብቻ ነው። "እባብ ለመደ ተብሎ በኪስ አይያዝም" ገላጭ አባባል ነው። ክፉ ሰዎች አዘናግተው ክፉ ተግባራቸውን ከመፈፀም ላይመለሱ መራራትም ልክ አይሆንም። መጥፎ ሰውና እባብ ተፈጥሯቸው ሁለቱም በጸጥታ ይሳባሉ፡ ጥቃታቸውም ድንገተኛና መርዝ ያዘለ ነው። ​የመጥፎ ሰው እና የእባብ ተመሳሳይ ባህሪያት • ​እባብ በሳርና በድንጋይ መካከል ተሸሽጎ እንደሚድበሰብስ ሁሉ፡ መጥፎ ሰውም የእውነተኛ ማንነቱን (ክፋት) በውሸት ፈገግታና በለሰለሰ አንደበት ደብቆ ይንቀሳቀሳል። •  እባብ አደኑን ለመያዝ በጸጥታ እንደሚከታተልና አመቺ ጊዜ እንደሚጠብቅ፡ መጥፎ ሰውም የሰውን ድክመትና ምስጢር በጥንቃቄ ያጠናል። የቀረበህና የወደደህ የሚመስለው ጥቅም ለማግኘትና ጊዜውን ጠብቆ ለመውጋት ነው። •  የእባብ ዋነኛ መሳሪያው መርዙ እንደሆነ ሁሉ፡ የመጥፎ ሰው መርዝ ደግሞ ምላሱ ነው። ያመነከውና የተጠጋኸው መስሎህ ሳለ፡ ሳታስበው ከጀርባህ በሃሜት፡ በሴራና በክፋት ይወጋሃል። •  እባብን ያሞቀውና የተንከባከበው ሰው ቢኖር እንኳን ተፈጥሮውን ቀይሮ ከመንደፍ እንደማይመለስ ሁሉ፡ መጥፎ ሰውም የተደረገለትን መልካም ነገር አያውቅም። ፍቅርና ደግነት ቢሰጡትም ክፋቱን ከመተግበር አይቆጠብም። ​በአጠቃላይ፡ ከመርዛማ እባብ አጠገብ መቆም እንደሚያጋልጥ ሁሉ፡ ከመጥፎ ሰው ጋር የሚደረግ ቅርበትም ውሎ አድሮ ድርጅታዊ አላማን፣ የአንተን ህይወትንና ሰላምን መመረዙ አይቀርም። ይህ ፅሁፍ በራሳቸው ሰው ለተከዱ እና ከጀርባቸው ለተወጉ ለሁሉም  አርበኞች  ይሁን። 👉ከቅርቡ ያለውን ጓዱን ያልጠበቀ ትግል ከሩቅ ያለውን የተበተነ አማራ እንዴት ሊታደገው ይችላል!!!??? መልካም ግዳጅ በያላችሁበት!! #አርበኛ #ዝናቡ #ልንገረው

መጥፎ ሰዎች እና እባብ የመመሳሰል ችግር የለባቸውም የማይለወጥ አንድ አይነት ባህሪያቸው በማይክሮ ሰከንድ መርዘው በደቂቃወች ውስጥ የመግደል አደገኛነት መለያቸው ነው። ውድ የሰራዊታችን አባላትና አመራር ውስጠ ማንነታቸው በማይታወቅ የሰው እባቦች ተነድፎ ላለመውደቅ ዋነኛው መፍትሄ አስተውሎ በመራመድ ለጉዞአችን ልዩ ትኩረት በመስጠት ብቻ ነው። "እባብ ለመደ ተብሎ በኪስ አይያዝም" ገላጭ አባባል ነው። ክፉ ሰዎች አዘናግተው ክፉ ተግባራቸውን ከመፈፀም ላይመለሱ መራራትም ልክ አይሆንም። መጥፎ ሰውና እባብ ተፈጥሯቸው ሁለቱም በጸጥታ ይሳባሉ፡ ጥቃታቸውም ድንገተኛና መርዝ ያዘለ ነው። ​የመጥፎ ሰው እና የእባብ ተመሳሳይ ባህሪያት • ​እባብ በሳርና በድንጋይ መካከል ተሸሽጎ እንደሚድበሰብስ ሁሉ፡ መጥፎ ሰውም የእውነተኛ ማንነቱን (ክፋት) በውሸት ፈገግታና በለሰለሰ አንደበት ደብቆ ይንቀሳቀሳል። • እባብ አደኑን ለመያዝ በጸጥታ እንደሚከታተልና አመቺ ጊዜ እንደሚጠብቅ፡ መጥፎ ሰውም የሰውን ድክመትና ምስጢር በጥንቃቄ ያጠናል። የቀረበህና የወደደህ የሚመስለው ጥቅም ለማግኘትና ጊዜውን ጠብቆ ለመውጋት ነው። • የእባብ ዋነኛ መሳሪያው መርዙ እንደሆነ ሁሉ፡ የመጥፎ ሰው መርዝ ደግሞ ምላሱ ነው። ያመነከውና የተጠጋኸው መስሎህ ሳለ፡ ሳታስበው ከጀርባህ በሃሜት፡ በሴራና በክፋት ይወጋሃል። • እባብን ያሞቀውና የተንከባከበው ሰው ቢኖር እንኳን ተፈጥሮውን ቀይሮ ከመንደፍ እንደማይመለስ ሁሉ፡ መጥፎ ሰውም የተደረገለትን መልካም ነገር አያውቅም። ፍቅርና ደግነት ቢሰጡትም ክፋቱን ከመተግበር አይቆጠብም። ​በአጠቃላይ፡ ከመርዛማ እባብ አጠገብ መቆም እንደሚያጋልጥ ሁሉ፡ ከመጥፎ ሰው ጋር የሚደረግ ቅርበትም ውሎ አድሮ ድርጅታዊ አላማን፣ የአንተን ህይወትንና ሰላምን መመረዙ አይቀርም። ይህ ፅሁፍ በራሳቸው ሰው ለተከዱ እና ከጀርባቸው ለተወጉ ለሁሉም አርበኞች ይሁን። 👉ከቅርቡ ያለውን ጓዱን ያልጠበቀ ትግል ከሩቅ ያለውን የተበተነ አማራ እንዴት ሊታደገው ይችላል!!!??? መልካም ግዳጅ በያላችሁበት!! አርበኛ ዝናቡ ልንገረው

64ኛ ክ/ጦር በሽበል በረንታ ወረዳ በረንታ ቀጠና ከሚገኙ ርዕሰ መምህራን፣ ሱፐር ቫይዘርና፣ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ መ/ራንና ህዝባችን ጋር ጥልቅ ውይይት አካሄደ። 64ኛ ክ/ጦር ጶጉሜ 02/2018 ዓ.ም ~~~~~~~~~ ድርጅታችን አፋብን ለ2019 ዓ.ም በሁሉም ቀጠና ት/ት እንዲጀመር መግለጫ መስጠቱን ተከትሎ የአፋብን ቴወድሮስ 2ኛ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦና የወረዳ ጊ/መንግስት አመራሮች በሸበል በረንታ በረንታና አካባቢው ከሚገኙ መምህራን፣ ርዕሰ መምህራን፣ ሱፐር ቫይዘሮች፣ በቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ከሚገኙ መ/ራንና ህዝባችን ጋር ሰፊ ውይይት ተካሂዶል። በውይይቱ መድረኩ ትምህርትን በተመለከተ በርካታ ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን በተነሱ ጥያቄዎች መልስ በመስጠት ለቅድመ ትምህርት ስራ መሰራት ያለባቸው ጉዳዩች በመድረኩ ተለይተዋል። በዚህም መሰረት በአገዛዙ ኃይሎች የፈራረሱ ክላሶችን፣ የተሰበሩ፣ ጠረንጼዛዎች፣ መንበሮች፣ ብላክ ቦርድና የመሳሰሉት የት/ት ቁሳቁሶች ተሟልተው በአጭር ግዜ አገልግሎት እንዲሰጡ ግንዛቤ ተሰጥቷል። መድረኩን የመሩት የክ/ጦርና የወረዳ ጊ/መንግስት አመራሮች እንደተናገሩት ት/ቤቶች ከፖለቲካ ጣልቃ ገብነት ነጻ ማድረግ፣ የተማሪዎች ቅስቀሳ፣ ምዝገባ፣ መ/ራን ከቀበሌ ጊ/አስተዳደሮች ማገናኘት፣ ማህበረሰቡን ግንዛቤ መስጠት፣ አፋብን የሚያወርዳቸው የትምህርት መመሪያዎችና ደንቦችን በጠበቀ መልኩ መ/ራን ተጠሪነታቸው ለወረዳ ጊ/መንግስት መሆኑን፣ ተማሪዎች በአጭር ግዜ ወደ ት/ት ተቋማት እንዲገቡና በሸበል በረንታ ወረዳ ፋኖ በተቆጣጠረባቸው ነፃ ቀጠናዎች የሚገኙ ት/ቤቶች የመማር ማስተማር ሂደቱ በአስቸኳይ እንዲጀምሩ ትዛዝ ተላልፎል።                 ጳጉሜ 02/2018 ዓ.ም አፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት

በቡልጋ በተደረገ ውጊያ ቡልጋ ክፍለ ጦር፡ በሪፐብሊካን ጋርድ ኃይል ላይ ከፍተኛ ኪሳራ ማድረሱ ተገለፀ!! ጳጉሜ 02/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (፭ኛ) ዕዝ፣ ከሰም ፪ኛ ኮር ቡልጋ ክፍለ ጦር ለከበባ በተንቀሳቀሰው የሪፐብሊካን ጋርድ ኃይል ላይ ከፍተኛ ድል መቀዳጀቱን የኮሩ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አስታወቀ። የአገዛዙ ስልጣን ጠባቂ የተባለው ሪፐብሊክ ኃይል ከምንጃር አረርቲ ከተማ በመነሳት ወደ በረኸት ወረዳ መተህብላ ከተማ የወረዳው አመራሮችንና የስንቅ አቅርቦት (ሬሽን) ለማድረስ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ሳለ፣ በቡልጋ ክፍለ ጦር አባላት ባልተጠበቀ ጥቃት ከፍተኛ ኪሳራ አስተናግዷል። ከምንጃር የተነሳው የአገዛዙ ኃይል ሜጢ በተባለው ልዩ ቦታ ላይ ሲደርስ ከባድ ኪሳራ አስተናግዷል። በተመሳሳይ ሰዓት ከመተህብላ ከተማ በመውጣት የመጣውን ኃይል ለመቀበል ተሬ በተባለ ቦታ በተደረገው የጨበጣ ውጊያ፣ ያልጠበቀው ጥቃት ስለደረሰበት ወደ ኋላ ለማፈግፈግ ተገዷል። ከ10 ሰዓታት በላይ በፈጀው በዚህ ውጊያ በመንግሥት ኃይል በኩል ከተራ ወታደር እስከ መስመራዊ መኮንኖች ድረስ ሙትና ቁስለኛ መሆናቸው ተገልጿል። በዚሕም አንድ (01) ጥርጥር ክላሽንኮቭ ጠመንጃ ከነ ሙሉ ተተኳሹ መማረኩ ታውቋል። በዚሕ አውደ ውጊያ ፋኖ በከፍተኛ የስነ-ልቦና የበላይነትና በላቀ ብቃት መጠናቀቁ ተጠቅሷል። እንደ ኮሩ ሕዝብ ግንኙነት ገለፃ፡ የተገኘው ድል በቀጣይ ዘመቻዎች ከፍተኛ የሞራል የበላይነት የሚሰጥ መሆኑን አክሎ ገልጾታል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (፭ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ትምህርት የማስጀመር ውይይቶች ተጠናክረው ቀጥለዋል!! =================== .ቀን 2 /13/2018 ዓ/ም አፋብን ድርጅታችን በ2019 ዓ.ም ትምህርት እንዲጀመር ባወጣው መመሪያ መሰረት የቴዎድሮስ 2ኛዕዝ 201ኛ ኮር74ኛ ክ/ጦር ስር የሚገኙትን የእናርጅ እናዉጋ ወረዳ መምህራንን ገደብ ቀበሌ ቀጥረን ሰፊ ውይይት ተደርጓል። በዋናነት የመወያያ አጀንዳ ያደረግናቸዉ 1, የመማር ማስተማሩ ጉዳይ በተመለከተ ቅድመ ዝግጅትና ምዝገባን በተመለከተ 2,የመምህራንን ደንነት ከመጠበቅ አንፃር 3, የድርጅቱን ህጎች ከመፈፀምና ከማስፈፀም አንፃር ምን መሆን እዳለበት 4,የትምህርት ቤት ንብረቶችን በተመለከተ ከመሬት ጀምሮ ሌሎችንም ንብረቶች ማንን እደሚመስሉ 5,ትምህርት ቤቶች ያሉበትን አሁናዊ ሁኔታ ምን ላይ እዳሉና ምን መሆን እዳለባቸዉ በስፋት ተወያይተናል _ በመምህራን በኩል ትምህር በመጀመሩ የአፋብንድርጅቱን አመስግነዉ እና በዚህም በጣም ደስተኛ መሆናቸዉን ገልፀዉልናል በቀጣይ የትኛዉንም ጫና ተቆቁመን እናስተምራለን የፋኖ ድርጅት የሚያወጣቸዉን ህጎችም እንቀበላለን አብረናቹህ እንሰራለንእንተጋገዛለን ብለዉ ስብሰባዉ ቀጣይም ይቀጥል በሚል ሀሳብ ሰጥተዉናል። መረጃው ፦የእናርጅ እናውጋ ጊ/መንግስት ሚዲያ እና ኮሚዩኒኬሽን ነው አፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ 201ኛ ኮር 74ኛ ክ/ጦር ህ/ግንኙነት

#አጋልጥ ሸር #ሸር !! ይሔ ሁሉ ፋኖን እና አማራን ሲራገም እና ሲራገጥ የሚውል "አራት እግር አሳማ" ነው ። መሬት ላይ በወታደራዊ ኃይል የተሸነፈው ብልፅግና በማህበራዊ ሚዲያ የፋኖ አመራር ስም ማጥፋት እና አጀንዳ መስጠት ላይ ያሰማራቸው እነዚህ የፌስቡክ ገፆች ናቸው ። የፌስቡክ አካውንቶች ዝርዝር፦ 1. Ethio Mereja 2. ስንቅ 3. ሁሴን ገዳ ከኦሮሚያ 3. Lula Kebede 4. ሀገሬን 5. Sebona Eliyas Tofik 6. Ethio Daily Media 7. ፍቅርተ ይበልጣል 8. Edu Lala 9. Yene Ethiopia 10. Ethio Intercept 11. Ardi Info 12. Meron Tadesse 13. Asmera Press 14. ዲጅታል ኢትዮጵያ 15. Addis Zemen 15. Selam mulugeta 16. ጥቁር አንበሶች 17. Ethio Press 18. Addis view አድስ እይታ 19. Nardos Page 20. Gohe tv ጎህ ቲቪ 21. ወደ ፍቅር ጉዞ ተያይዞ 22. ጎንደር ፋሲለደስ 23. hagere zena 24. የፍቅር መንገድ 25. Fast Mereja ፈጣን መረጃ 26. Solomon Gumba 27. Ethiopiya Adane 28. Sheger press 29. የሰላም ዘብ 30. Melat Bekele 31. Beti Tesfaye 32. Eden Hagose 33. Liya Eshetu 34. Eden Tamerat 35. አማኑኤል አወቀ 36. O U R Raya 37. One Ethiopia 38. Kelemu Taddele 39. ኢትዮፒድያ ዜና 40. Obbo Chidessa Odda 41. Sis Press 42. Betty Gullele 43. የበለፀገች ኢትዮጵያ 44. Ethiopia voice 45. Gullale post 46. Lucy media 47. Maski Bekele 48. Saroon 49. Dz Ethio 50. የኛ info 51. Meri konjoooo 52. Zemed Mekonnen 53. ጧፈኛ 54. Gondar Times 55. ብሌን ሰለሞን 56. Msgei 57. ጉና ክምር ድንጋይ 58. ሰላም ለሃገሬ 59. አቦል መረጃ 60. ሰላም ለኢትዮጵያ 61. Helen Sisay 62. Nafkot Tesema 63. Thomas Jejaw 64. Abiti Ankober 65. ሮዛ ፍቅር 66. Melat Bekele 67. እውነተኛ ፋኖ 68. Wollo Gerado 69. መልህቅ የመረጃ ምንጭ 70. Yordanos Tekeste 71. Ethiopian Insight 72. Hibist Kefyalew 73. Sonan Press 74. Bole Times 75. Assab Ethiopia 76. በጌምድር-ጎንደር 77. Hiwot A Feleke 78. Meles Bisrat 79. Ethio Intercept 80. ብላቴናው ንጉስ 81. Helen Getachew 82. Tesfayehun Seme 83. Amhara Post 84. Beza Kebede 85. Bilen Mesfin 86. ጯሂት ጎርጎራ 87. Selam Alemu 88. ዲጂታል ኢትዮጵያ 89. Sonan press press 90. Pro peace press 91. Eden Nigussie 92. የሸገር ልጆች 93. የመደመር ትውል 94. አርጎባ ወሎ ጀበርቲ 95. ጀበርቲ አርጎባ አገር 96. Meron Tsegaye 97. Selam Adan 98. Medener 99. Mekides Melaku 100. Meri Konjoo 101. Geda Moti 102. ዝምተኛው ንጉስ መደመር 103. Amihara Fano 104. Wubit Seyoum Gashaw 105. አንድ አምሓራ 106. Semira Jamal 107. Tizta Melaku 108. Miser Dagne 109.አገው ነኝ 110. Lasta Agew 111. Kidist Nega 11. የውብዳር አረጋ 112. Shebelaw Getachew 113 .ዲጂታል ጦቢያ 114. Helen Tesfa 115. ቡሬ ዳሞት ፋኖ 116. Tigist Kefale 117. Tg Love Andebt B Ali 118. እውነታ ሚድያ 119. Ethio press 120. ቀይ ባህር 121. ተዋበች ጎንደር 122. Nigat Nigat 123. አፍሮ ሚድያ 124. Selam Fentie 125. Zemed Mekonen 126. ድጅታል ፋኖ-digital fano 127. ፈጣን መረጃ 128. Dibora Mekonen Atinafu 129. Burie Damot Fano 130. Addis View አድስ እይታ 131. ጎጃሜዋ መቅደስ 132. ብሌን 133. Helina Alebachew 134 .ፀረ ሌባ ፀረ ሌባ 135.GoJam GoJam 136.Dered Der 137.ጣዝማ ማር 138. ኢትዮጵያMekete 139.Endalamawealama 140.Quarite Press 141.Nile Bluile 142.Bekalu Yehuala 143.Yehuala Yehu 144.Mihret Abewa 145.አብዱሮህማን ኢብራሂም 146.ስዩም ይዘንጋው ድንቁ 147.Indo Amhara 148.Amha Mulat 149.Addis Fikrte 150.AlemuTigist 151.Zelalem Sisay 152.Baynesagn Fentie 153.ሀሴት አየለ 154.አባይ ሚዲያ 155.ራያ ራዩማ 156.ወልቃይት ጠገዴ አማራ 157.ጦሳ ሚዲያ 158. Ghone Forces 159.Raya prayss 160.ጎጃም አማራ.....ይቀጥላል ከብልፅግና ገንዘብ የሚከፈላቸው ናቸው ። ሌሎችን ለቅሞ ማጋለጡ ተጠናክሮ ይቀጥላል ። ድል ለጀግናው አማራ ድል ለጀግናው ፋኖ ፍኖተ-አማራ ሚዲያ ወቅታዊና ትኩስ የፋኖ እንቅስቃሴን መረጃን ከግንባር ሁነን በአራቱም ማዕዘን እየሰራን እንገኛለን። ለሁሉም አማራ ተደራሽ እንሆን ዘንድ እየሰራን እንገኛለን የበኩሉዎን አስተዎፆ የቴሌግራም ቻናላችን ጆይን ሸር አድርጉ አድራሻችን👇👇👇👇 ‼️ https://t.me/httpsuYkZrGfSZrNjNjFk