ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
Open in Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
Show more2 808
Subscribers
+18124 hours
+2277 days
+23430 days
Posts Archive
ጥቆማ!
አብይ አህመድ ሰሞኑን ነገ በ30/12/2018 ዓ.ም አብይ አህመድ የህዝብን ትኩረት ይስብልኛል : እሱ አሁንም ስራ ላይ ነው ብሎ ህዝቡ እንዲያስብ ወደ ጥንታዊቷ ጎንደር ከተማ የመገጭ ግድብን ለመጎብኘትና መገጭ ላይ ቃለ መጠየቅ በማድረግ ልማት ላይ ነን የሚል ፕሮፖጋንዳ ለመስራት አስቧል ።
ዛሬ ከተማዋ በብልፅግና ካድሬና ሚለሻ ስትጠበቅ ውላለች። ታይተው የማይታወቁ አትክልቶችና ችግኞች የከተማው አስፖልት ላይ እየተተከሉ ይገኛሉ ።
በአካባቢው የሚገኘውን የአፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝን ለመከላከል ከማክሰኝት እስከ ጠዳ እንዲሁም አዘዞ ያሉ መውጫና መግቢያ በሮች በከፍተኛ የወታደር ሀይልና በከባድ መሳርያ እየተጠበቁ ይገኛሉ ።
ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም
#ዛሬም አስመርቀናል❗152ኛ ክ/ጦር ለ7ኛ ጊዜ አስመረቀች።
☑️ አቢወቱ ላይከስም ተቀጣጥሏል።ትዉልዱ እንደ እንጉዳይ አሾትሎ ፈነዳ፣አማራ ከገዛ አፅመርስቱ ለቆ አማራ እሚባል ነገድ ነበር" እየተባለ በነገዋ ኢትዮጵያ የታሪክ ማህደር ላይ እንደተረት እንድወራ ፀረ አማራወች ለአመታት ያቀዱት እቅድ ፉርሽ ሆኖ ከራሳችን አልፈን ኢትዮጲያን በዚህ ትዉልድ እጅ የምንሰራበት የድል ዋዜማ ላይ እንገኛለን፣ኒዮፋሺስታዊ ጥጋበኞችን የሸፍጥ እብጠታቸዉን የሚያስተነፍስ ትውልድ ተፈጥሯል።
☑️በአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ አ.ፋ.ብ.ን ወሎ ቤተ- አምኃራ 1ኛ ዕዝ 15ኛ ኮር ስር የምትገኘዋ የጃማ ደጎሎዋ ቱርፋት 152ኛ ክ/ጦር ፅናትን አይበገሬነትና ታግሎ ማሸነፍን የቢጣ ጎራንና ግርግሪያት ጎራን አቀበት ቁልቁለት በመጋፈጥ ተራሮች እንደተራራ እንድገዝፉ የተፈጥሮን ፈተና ያለፉ 320(ሶስት መቶ ሀያ) የኔን ዘመን ትዉልድ አባላት ለወራት ብቃት ባላቸዉ ወታደራዊና ንቃተ ፖለቲካቸዉ በዳበረ አሰልጣኞች ማሰልጠኗ ታወቀ።
☑️የኮሩ ሰብሳቢ አርበኛ እንድሪስ ይማም በተገኙበት የምረቃን ቀናቸዉን ያከበሩት የወርቃማዉ ትዉልድ አባላትም በቅንነት በታማኝነትና በፍፁም ጀግንነት ለህዝባቸዉ መታገል እንዳለባቸዉ ከአርበኛ እንድሪስ ይማም የተሰጣቸዉ አደራ እንዳለ ሆኖ እብሪቱ ያበጠዉን አገዛዝ ለመሰልቀጥ እንደቋመጡ እፊታቸዉ ላይ የሚንቀለቀለዉ የቁጣ ትንፋጎት የአካል ምስክር ነዉ።
- የአማራ ፋኖ ብሄራዊ ንቅናቄ አ.ፋ.ብ.ን ወሎ ቤተ- አምኃራ 1ኛ ምኒሊክ ዕዝ 15ኛ ኮር ህ/ግንኙነት መምሪያ ነሀሴ 29/2018 ዓ.ም
አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ 204ኛ አስቻለው ደሴ ኮር በለሳ ታርቆ ከበደ ክፍለ ጦር በጠላት ላይ ከፍተኛ ቁሳዊና ሰባዊ ኪሳራ አደረሰ!
ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም
ከምዕራብ በለሳ አርባያ ከተማ ተነስቶ ወደ አበዬ ቀበሌ እንቅስቃሴ ያደረገው የጠላት ጥምር ኃይል በበለሳ ታርቆ ከበደ ክፍለ ጦር ብርቱ ክንድ አርፎበት ከፍተኛ ኪሳራ አስተናግዷል። ከጧቱ 12:00 ሰዓት እስከ ቀኑ 7:00 ሰዓት ድረስ ለሰባት ሰዓታት ያህል በተካሄደው በዚሁ ከፍተኛ አውደ ውጊያ፣ ክፍለ ጦሩ በጠላት ኃይል ላይ የሰውና ቁሳዊ ኪሳራ አድርሷል።
ፀረ-አንድነት ኃይሎች የተላላኪነት ሚናቸውን ወስደው ታላቁን አርበኛ ታርቆ ከበደን ያሳጡት ክፍለ ጦሩ፣ በአርበኛው ስም ራሱን እንደገና አደራጅቶ በስሙ ከሰየመ ማግስት የመጀመሪያውን ታላቅ ድል ተቀዳጅቷል።
ስለሆነም የአርበኛ ታርቆ ከበደ ዓላማ፣ ለተገፋው የአማራ ህዝብ እስከመጨረሻው ስትፋስ ድረስ መስዋት መክፈል ነውና እሱን በማሰብ ከፍተኛ ተጋድሎ ያደረገው ክፍለ ጦሩ 8 የጠላት ሰራዊት አባላት ሲደመሰሱ፣ ከ15 በላይ የሚሆኑት ደግሞ ቀላልና ከባድ አካል ጉዳት አስተናግዶ ወደመጣበት አርባያ ከተማ ለማፈግፈግ ተገዷል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
አፋብን በላይዘለቀ 3ኛ ዕዝ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ሰበር ዜና!
በዋግኽምራ ግንባር ደሀና (አዚላ ከተማ) ላይ ሰፍሮ የነበረው የአገዛዙ ኃይል ሙሉ ለሙሉ ተደም*ስሷል፣ የዞኑ ፖሊስ ኮማንደርን ጨምሮ በርካታ ኋይሉ ተማርኳል!
ምኒልክ 1ኛ ዕዝ የጀኔራል አሳምነው ፅጌ መታሰቢያ የሆነው 303ኛ አሳምነው ኮር፦ ምሽግ ደርማሾቹ 19ኛ (ተፈራ ማሞ ክፍለጦር + ዋግሹም ብርጌድ) እና መብረቆቹ 14ኛ (ኃይሉ ከበደ) ክፍለጦር በጋራ ልዩ ጀብዱ ሰርተዋል። የኮሩ አሃዶች በመሳሪያ ምርኮ ተንበሽብሸዋል።
ዝርዝሩን ከማስረጃ ጋር ይዘን የምንቀርብ ይሆናል!
+1
ሰበር ዜና!
በአፋር ኡጉጉሞ ኃይሎች በኩል የዳሉል እና የሀማድ-ዔላ ቀጠናዎች ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለጸ!
(ነሐሴ 29 ቀን 2018 ዓ.ም — ኢትዮ 251 ሚዲያ)
በአፋር ቀጠና የሚንቀሳቀሰው የአፋር ኡጉጉሞ ነጻነት ኃይል በወሰደው የተቀናጀ ወታደራዊ እርምጃ የዳሉል ሁለቱን ባዳን ጨምሮ እስከ ሀማድ-ዔላ ያሉ ስትራቴጂካዊ ቦታዎችን ሙሉ በሙሉ በቁጥጣራቸው ስር ማዋላቸው ተጋልጿል።
ለሚዲያችን የደረሱ መረጃዎች እንደሚያመላክቱት፣ በአካባቢው የተካሄደውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ ተከትሎ የአፋር ኡጉጉሞ ኃይሎች የቀጠናውን የበላይነት በመጨበጥ ጠላትን በማስወጣት ቦታዎቹን መቆጣጠር ችለዋል። ይኸው የድል እንቅስቃሴ በአሁኑ ወቅት አቅጣጫውን ወደ በራህሌ በማድረግ ወደ ፊት ግስጋሴውን አጠናክሮ ቀጥሏል ተብሏል።
እንደተገኘው መረጃ፣ የአፋሩ ኡጉጉሞ ወታደራዊ እንቅስቃሴ በስትራቴጂካዊ ዕቅድ መሠረት እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን፣ በሚቀጥሉት ቀናትም በዞኑ የሚገኙ ተጨማሪ አካባቢዎችን ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር ለማዋል ጥቃቱ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ታውቋል።
+1
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ፣የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ምዝገባና ትምህርት ማስጀመሪያ መመሪያ
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ፣የ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ምዝገባና ትምህርት ማስጀመሪያ መመሪያ
አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሥር የሚገኙ ሁለት ክፍለ ጦሮች በተለያዩ ግንባሮች በተደረጉ ውጊያዎች፤ በአገዛዙ ሰራዊት ላይ ከፍተኛ ድል መቀዳጀታቸው ተገለፀ!!
ነሐሴ 29/2018 ዓ.ም
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ)ዕዝ፡ መሀመድ ቢሆነኝ ኮር፡ አስቴጎማ ተራራ ክፍለ ጦርና እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር በተለያዩ ግንባሮች በጠላት ላይ ድል መቀዳጀታቸውን የኮሩ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ኃላፊ አስታወቀ።
የአገዛዙ ኃይል፤ ከመኮይ ከተማና ከኬሚሴ ከተማ ተጨማሪ ኃይል ወደ ሴራር ጉር ቀበሌ አዳሩን በማንቀሳቀስ፡ አስቴ ጎማ ተራራ ክፍለ ጦር 4ኛ ሻለቃን ለማፈንና ለመደምሰስ ሲደናበር አይበገሬዎቹ በመልሶ ማጥቃት እርምጃ የጠላትን እቅድ ሙሉ ለሙሉ ማክሸፋቸውን ገልጿል።
በሌሊት የተደናበረው ጠላት ተሸንፎ በመሸሽ ላይ እያለ፡ የክፍለ ጦሩ ሌሎች ሻለቆች ማለትም ሸጌ ሻለቃና አያሌው መክት ሻለቃ የጠላትን ኃይል እስከ መኮይ ከተማ ድረስ በመከተል ተጨማሪ ኪሳራ ሲደርሱበት ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሙትና ቁስለኛ እዳስተናገደ ተረጋግጧል።
ወደ ካምፓቸው ድረስ ለመደምሰስ የተጓዘው የአገዛዙ ጠባቂ፡ በፋኖ ፈጣን የመልስ ምት ክፉኛ ተመቶ ወደ መጣበት ሲፈረጥጥ፡ እራሱን ለማትረፍ ከባድ መሳሪያን ወደተራራ ሲተኩስ በንፁሐን ሃብት ንብረት ላይ ውድመት ፈፅሟል ብሏል።
〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰〰
በሌላ በኩል የመሀመድ ቢሆነኝ ኮር እቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር በአንኮበር ቀጠና አመርቂ ድል መቀዳጀቱን አክሎ ገልጿል።
መነሻውን ከአንኮበር አድርጎ ወደ ጎረቤላ ቀበሌ ቤት ለቤት በመግባት ወጣቶችን ለማፈስ ሲንቀሳቀስ በነበረው የአድማ ብተና ኃይል ላይ የእቴጌ ጣይቱ ክፍለ ጦር 2ኛ ሻለቃ ፈጣን እርምጃ ወስዷል።
በልዩ ቦታው "ጠምቄ" በተባለ ቦታ በቀን 28/12/2018 ዓ.ም ከቀኑ 11:00 ሰዓት ላይ መረጃው የደረሰው የወገን ጦር ፈጣን የደፈጣ ውጊያ በመክፈት ወታደራዊ የበላይነትን በማሳየት፡ ጠላት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሲያደርሱበት፥ በዚህ አውደ ውጊያ 5 የጠላት አባላት ሲደመሰሱ፣ ቁጥራቸው ያልታወቀ በርካቶች መቁሰላቸውን መረጃዎቼ አረጋግጠዋል ሲል ኮሩ አስታውቋል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው (5ኛ) ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
በጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ ወረዳ ከሚገኙ መምህራን ጋር በትምህርት ጉዳይ ወቅቱን ያማካለ ስብሰባ ተካሔደ።
~~~~~~~~
ነሐሴ 28 /2018 ዓ.ም
ድርጅታችን አፋብን በአወረደው መመሪያ መሠረት በጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ የሚገኙ መምህራን፣ ዕርሰ መምህራንና ሱፕር ቫይዘሮች ጋር ነሀሴ 28/12/2018 ዓ.ም በጎንቻ ወረዳ ባርጃኖ ከተማ ጥልቅ ውይይት አካሂዶል።
የብልፅግና አገዛዝ በዚህ ሶስት ዓመት ትምህርትን እንደ ትልቅ የፖለቲካ ፍጆታ በመጠቀም የፕሮፓጋንዳ መሳሪያ በማድረግ ሲጠቀምበት ቆይቷል። አገዛዙ በጊዚያዊነት በተቆጣጠረባቸው ቦታዎች ሳይቀር ማህበረሰቡን በመሰብሰብ ጽንፈኛው ልጆቻችሁ ትምህርት እንዳይማሩ ከልክሏል እኛ ግን ትምህርት እናስጀምራለን የሚሉ የሐሰት አጀንዳዎችን በመንዛት ማህበረሰቡን ከፋኖ ለመነጠል ከፍተኛ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል።
መድረኩን የመሩት የ74ኛ ክ/ጦር እና የጎንቻ ወረዳ ጊ/መንግስት አመራሮች ጠላት በትምህርት ጉዳይ ሲያሰራጨው የነበረው የሐሰት መረጃ መሆኑን ግንዛቤ በመስጠት አፋብን በሚያስተዳድረው የትኛውም ቀጠና ትምህርት እንዲጀመር የፈቀደ መሆኑን ለመድረኩ ተሳታፊ መምህራን ሰፊ ግንዛቤ በመስጠት በጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ ፋኖ በተቆጣጠራቸው ነፃ ቀጠናዎች የትምህርት ተቋማት ከየትኛው የፀጥታ አካላት ነፃ እንደሚያደረግና ህዝባችን ልጆቻቸውን ወደ ት/ት ተቋማት እንዲልኩና ትምህርት እንዲጀምሩ ጥሪ አስተላልፏል።
በውይይት መድረኩ ከተገኙት መምህራን ጋር በተካሄደው ቅድመ አቅጣጫ መተግበር ያለባቸው ጉዳዩች ውስጥ ትምህርት ቤቶች ከማነኛም ወታደራዊ አካል ነፃ ማድረግ፣ በት/ቤቶች የትምህርት ቁሳቁስን እንዲሟሉ ማድረግ፣ የተሰባበሩ ወንበሮችን መጠገንና በአገዛዙ የወደሙ ት/ቤቶች ጥገናና እድሳት በማድረግ በ2019 ዓ.ም በሁሉም የጎንቻ ቀጠና ትምህርት እንዲጀመር አቅጣጫ ሰጥቷል።
አፋብን ቴዎድሮ ፪ኛ ዕዝ 201ኛኮር 74ኛ ክ/ጦር ህ/ግንኙነት
መረጃ ምንጭ ፦ የጎ/ ሲ /እነሴ ወ/ጊ/መ/ አስተዳደር ሚዲያ አና ኮምኒኬሽን
"ክፋት ለማንም በጎነት ለሁሉም"
ሰበር አሁን ከመሸ‼️
እጅግ በርካታ ህፃናት በአስገዳጅ ወታደራዊ አፈሳ ታፍሶ ከአዲስ አበበ ወደ አማራ ክልል ደጀኝ ከተማ የደረሱ ህፃናት ኢትዮጵያዊን🤔
በመርሐቤቴ አውራጃ በአገዛዙ ሆድ አደር ሚሊሻዎች ላይ የማያዳግም እርምጃ ተወሰደ!!
ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም
በሸዋ ጠቅላይ ግዛት መርሐቤቴ አውራጃ ታች ቤት ጊደብ ወረጎ ቀበሌ፣ በአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ አፄ ዘርያዕቆብ ፩ኛ ኮር ናደው ክፍለ ጦር የአገዛዙ ሆድ አደር ሚሊሻዎች ላይ አመርቂ እርምጃ መወሰዱን የኮሩ ህዝብ ግንኙነት አስታወቀ።
ዛሬ ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:30 ላይ የአገዛዙ ጥምር ጦር ከአለም ከተማ በመነሳት፣ «የሰላም አስከባሪ» ሲል የሚጠራቸውን ሚሊሻዎች ሰብል ለማረም በሚል ወደ ታች ቤት ጊደብ ወረጎ ቀበሌ አሰማርቶ ነበር።
አገዛዙን የሚያገለግለው ይህ ኃይል የጭቁኑን ህዝብ በአስገዳጅነት ሰብል ሊያሳርም በሚንቀሳቀስበት ወቅት የተካሄደ ልዩ ፈጣን እርምጃ ነው። በጊደብ ወረጎ ቀበሌ ሸንኮራ ጎጥ በተሰማራው የዚሁ ሚሊሻ ኃይል በየናደው ክፍለ ጦር ቀኝ አዝማች ለማ ጠጁ 3ኛ ሻለቃ ቃኝዎች በበቂ ወታደራዊ ስልት ፈጣን ደፈጣ በማካሄድ የማያዳግም ምት አድርሰውበታል።
በነበረው አውደ ውጊያ በፋኖ ፈጣንና የተቀናጀ የማጥቃት ስልት ግራ የተጋባው የአገዛዙ ሚሊሻ ኃይል ግራ ተጋብቶ መበታተኑ ሲገለፅ፤ ከ6 በላይ የሚሊሻ አባላት ከባድና ቀላል ቁስለኛ ሆነዋል።
አቶ አይደንፉ ብልጭ የተባሉ አንድ ቀንደኛ የአገዛዙ ተላላኪ ሚሊሻ ላይ የማያዳግም እርምጃ ሲወሰድበት፦1 ክላሽንኮቭ (AK-47) ጠመንጃ በምርኮ መያዙ ተረጋግጧል።
" ክብር ለትግሉ ሠማዕታት!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!
የአፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
የአደረጃጀት ዜና!
አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ 14ኛ ኮር 142ኛክ/ጦር ለተከታታይ ቀናት ሲያደርግ የቆየውን ጥልቅ ግምገማ በስኬት በማጠናቀቅ፣ ድርጅታዊና ወታደራዊ ተልኮን ለማስፈፀም ብቁ የሆኑ አመራሮች የተመደቡ ሲሆን በግምገማውም የኮሩና የክ/ጦር አመራሮች በንቃት ተሳትፈዋል።
ይህ አደረጃጀት በየደረጃው ያሉ አርበኞችን አፈፃፀምና ብቃት መሠረት በማድረግ የተከናወነ ሲሆን፣ የክ/ጦሩን የወደፊት ድርጅታዊና ወታደራዊ ተልዕኮዎች በተሻለ ቁመና ለማስፈጸም ያለመ ነው።
በዚህም የግምገማ ፕሮግራም የምኒልክ 1ኛዕዝ ሰብሳቢ ፊታውራሪ ድርሳን ብርሀኔ እና የ14ኛ ኮር አመራሮች በመገኘት ጥልቅ ግምገማ በማድረግ የስራ ልምድና የስራ አፈፃፀም ጥንካሬን እንድሁም የአመራር ጥበብና ብቃትን ከግምት ውስጥ በማስገባት የክ/ጦሩን አመራር አደረጃጀት ሰርተዋል።
ወደ ክ/ጦሩ የተመደቡ አመራሮችም ትግሉን የማስቀጠል ታሪካዊ አደራ ከትግሉ ሰምዓት ስላለብን የህዝባችን መከራ ለማሳጠር ቆርጠን ለመታገልና ለማታገል ቃለ-መሀላ በመፈፀም አጠናቀዋል።
📌
አዲስ የተመደቡ የ142 ክ/ጦር አመራሮች ዝርዝር
1, አርበኛ እንድሪስ ጉደሌ.... ወታደራዊ አዛዥ
2, አርበኛ ቃሪው ጌቶ..ም/ታደራዊ አዛዥ
3, አርበኛ ጌታቸው ሰጠ.....አስተዳደር
4,አርበኛ ገዛህኝ ካሳ....ሎጀስቲክ
5 አርበኛ ደምሌ መኮነን..ፓለቲካዘርፍ ሀላፊ
6, አርበኛ ይማም አህመድ .....ፀሀፊ
7,አርበኛ በረከት ተገኘ ...ኦድትና ቁጥጥር
8,አርበኛ ሰይድ እንድሪስ....ኢንስፔክሽን
9, አርበኛ እሸቱ ወርቁ....ዘመቻ
10, አርበኛ ሁሴን ሷሊህ....ም/ዘመቻ
11, አርበኛ ሻለቃ ክንዱ....ስልጠና ዘርፍ
12, አርበኛ ተስፋዬ አበራ....መገናኛ
13, አርበኛ __መረጃ
14, አርበኛ __ም/መረጃ
15, አርበኛ ይማም ሀይሌ.....ም/አስተዳደር
16, አርበኛ ............ቃኝ መሪ
17, አርበኛ ሙጃይል ሽመልስ ....የሰው ሀይል
18, አርበኛ አብዱ ሀሰን ....ፋይናስ
19,ህግ አገልግሎት
1ኛ አርበኛ ሰይድ የሱፍ
2ኛ አርበኛ ተመስገን አሰፋ
3ኛ አርበኛ ከድር ይማም
20, አርበኛ ግዛው ሰለሞን.....ግዥ
21, አርበኛ ጀማል ሙሳ ......ም/ሎጀስቲክ
22, አርበኛ አወል ተገኝ .......ኦርድናስ
23, አርበኛ በለጠ ተፈራ ......ስቶር
24, አርበኛ ፍቅሩ ጌታሁን.....ስንቅና እደላ
25, ዶ/ር ከድር ሁሴን ....ህክምና
26, ዶ/ር መልካሙ ተገኘ......ም/ህክምና
27, አርበኛ ሙሀመድ አያሌው......ነዘቅ
28,አርበኛ ጀማል ሙሀመድ.....ትራንስፖርት
29, አርበኛ አብዱ ዳውድ.......ኢንዶክትሪኔሽን/ስርፀት/
30, አርበኛ ዮወናስ አሉላ....የክፍለ ጦሩ ቃል አቀባይ በማድረግ አደረጃጀቱ በተሳካ ሁኔታ ተከናዉኗል!!
መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል።
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !!
አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን መምሪያ!
ነሀሴ :- 28/2018 ዓ.ም
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ዕዞች የ2019 ዓ/ም የትምህርት ዘመን መደበኛ የመማር ማስተማር ሥራ በይፋ እንዲጀመር ጥሪ አቅርበዋል!!
ነሐሴ 27/2018 ዓ.ም።
ትምህርት ለአንድ ሀገር ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ እድገት ወሳኝ መሠረት መሆኑ በውል የሚታወቅ ሲሆን፤ ሀገራችን ከገጠማት ውስብስብ ችግር እና የጸጥታ ስጋት አንጻርም ጭምር የትምህርትን አስፈላጊነት ከግምት ውስጥ በማስገባት የ2019 ዓ/ም የትምህርት ዘመን በወቅቱ እና በአግባቡ እንዲጀመር የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ዕዞች ጥሪ አስተላልፈዋል።
የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ባስቀመጠው አጠቃላይ አቅጣጫ መሠረት፦
፩. አፋብን አሳምነው 5ኛ ዕዝ (በማኅበራዊ ጉዳዮች መምሪያ ኃላፊ አርበኛ አስታወሰኝ ላቀ በኩል) እንደገለጸው፤ ትምህርት ሰላም እና መረጋጋት ቢፈልግም፣ ከሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ አኳያ በስጋት ውስጥ ሆነንም ቢሆን የ2019 ዓ/ም የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሥራ በወቅቱ እንዲጀመር አቅጣጫ ተቀምጧል። በመሆኑም በየደረጃው ያሉ የፋኖ አመራሮች፣ ወላጆች፣ መምህራን፣ ርዕሰ መምህራን እና የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ ቀርቧል።
፪. አፋብን ቴዎድሮስ 2ኛ ዕዝ ለሁሉም ኮሮች ባስተላለፈው ጥሪ፣ ድርጅታችን ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት መደበኛ ትምህርት እንዲጀመር አሳስቧል። ለዚህም ስኬት አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት እንዲደረግ አሳስቦ፣ ሁሉም ኮሮች ትምህርት እንዲጀምሩ ጥሪ አቅርበዋል።
፫. አፋብን በላይ ዘለቀ 3ኛ ዕዝ (በማኅበራዊ ጉዳይ መመሪያ ኃላፊ አርበኛ ብዙአየሁ ወንድምነው አማካኝነት) በሰጠው መግለጫ፣ ድርጅቱ ያስቀመጠውን አቅጣጫ መሠረት በማድረግ በዕዙ ሥር የሚገኙ ሁሉም ኮሮች አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት አድርገው ትምህርት እንዲያስጀምሩ አሳስቧል። ሙሉው ሕዝብ፣ መምህራን፣ የተማሪ ወላጆች እና ባለድርሻ አካላት አስፈላጊውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ ተላልፏል።
፬. አፋብን ምኒልክ 1ኛ ዕዝ በሰጠው ማሳሰቢያ፣ የ2019 ዓ/ም የትምህርት መርሐ ግብር እውን እንዲሆን በቁጥጥራቸው ሥር በሚገኙ አካባቢዎች የሚገኙ ትምህርት ቤቶች ወደ ሥራ እንዲገቡና የምዝገባ ሥራዎች እንዲጀመሩ አሳስቧል፤ ለዚህም አስፈላጊው ትብብር እንዲደረግ ጥሪ አቅርቧል።
በአጠቃላይ የአፋብን ዕዞች ባስተላለፏቸው መልእክቶች፤ ትውልድን ለማዳን፣ አስተሳሰብን ለመገንባት እና ትናንትን በአዲስ ተስፋ ለመተካት ትምህርት ቤቶች መደበኛ አገልግሎታቸውን እንዲጀምሩና መላው የህብረተሰብ ክፍል አስፈላጊውን እገዛና ትብብር እንዲያደርግ አጽንኦት ተሰጥቷል።
— የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ(አፋብን) ወታደራዊ ቃል አቀባይ
