Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union
Open in Telegram
This is the official Channel of Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union.
Show more4 479
Subscribers
+224 hours
-77 days
+2930 days
Posts Archive
ጅንስ ሱሪን የዩኒቨርሲቲ ልብስ ያደረገው ማን ነው? ሱፍ ኮትን የዩኒቨርሲቲ የክት ልብስ ያደረገው ማን ነው? ሱሪ በኮትን የሴኩላር አለባበስ ያደረገው ማን ነው? ሲጀመር እነዚህ አለባበሶች ከየት የመጡ አለባበስ ናቸው? ይህንንስ የለበሰ አካል ጀለብያን/ሙደወርን አትልበሱ ብሎ የሚከለክለው በምን አግባብ ነው?
ይህ መሐይምነት የወለደው የጥላቻ በትር እንጅ ሌላ አይደለም:: ጅንስ ሱሪም ሆነ ሱፍ ከምዕራብም መጣ ከሰሜን ቢለብሱ ባይለብሱ ጉዳያችን አይደለም:: ይበጀናል ካሉ ይልበሱት:: ግን ለጀለብያ/ሙደወር ሌላ ስም ሰጥተው እንዲከለክሉ አንፈቅድም:: እነርሱ የመረጡትን መልበስ እንደቻሉት ሁሉ እኛም የመረጥነውን የመልበስ መብት አለን:: የእኛን ልበሱ አንልም ••• አትልበሱ እንዲሉን ግን አንፈቅድም:: ይሰመርበት!
https://t.me/EHEMSU
ጁምዓ ነው ••• በዚያ ላይ ረመዳን ••• በጅማ ዩኒቨርሲቲ ላሉ ሙስሊም እህት ወንድሞቻችንም ሆነ በመላው ኢትዮጵያ መብታቸው እየተገፋ ላሉ ሙስሊም ተማሪዎች ሁሉ ዱዓ እናድርግ:: አላህ መፍትሔውን ያቅርብ!
https://t.me/EHEMSU
"We are in the community!" ••• ይላል በጅማ ዩኒቨርሲቲ አርማ ላይ በደማቁ የሰፈረው መለያ ቃል:: ትርጉሙ "እኛ በማህበረሰቡ ውስጥ ነን!" እንደማለት ነው::
•••••••••••••••••••••••
እዚህጋ ጥያቄ አለን!
••••••••••••••••••••••••
በየትኛው ማህበረሰብ ውስጥ ናቸው? በጅማ ማህበረሰብ ውስጥ? በኦሮምያ ማህበረሰብ ውስጥ? በኢትዮጵያ ማህበረሰብ ውስጥ? በጅማ ውስጥ ከሆኑ የጅማ ማህበረሰብ መገለጫ የሆነውን ባህላዊ አለባበስ ስለምን ይከለክላሉ? በኦሮምያ ውስጥ ከሆኑ ከኦሮምያ ክልል ብዙሐን የሆነውን ሙስሊም መብት ስለምን ይገፋሉ? ከኢትዮጵያ ከሆነ የኢትዮጵያ ግማሽ ሕዝብ የሆነውን ሙስሊም በማንነቱ ስለምን መጨቆን ይፈልጋሉ?
ወይንስ ባህር ተሻግረው ማህበረሰብነትን ከፈረንሳይ መውሰድ ፈለጉ:: እንደ ፈረንሳይ ሙስሊሞችን በአለባበስ መጨቆን ፈለጉ::
የፈለጉትን ይፈልጉ:: ግን ከረሱት ያስታውሱ ዘንድ ጅማ ዩኒቨርሲቲ የሚገኘው በአባ ጅፋሯ ጅማ ውስጥ ነው:: በአባ ጅፋር ሐገር ደግሞ የአባ ጅፋር ልጆች ባዕድ አይሆኑም:: መብታቸው ይከበራል:: ነፃነታቸው ይጠበቃል::
ጅማ ዩኒቨርሲቲ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ ሲሰራ የነበረው ግፍ ጎንደርን ያስንቃል:: ጎንደር ኒቃብ አይከለከልም:: ላለፉት አምስት አመታት ሙስሊም ተማሪዎች ጥያቄያቸውን ሲያቀርቡ ፀጥ እረጭ ማለቱ ደግሞ በየትኛውም አካባቢ ታይቶ የማይታወቅ ንቀት ነው::
አሁን ትግሉ ተጀምሯል ••• የጀመረውን ሳይጨርስ የማያርፍ ትውልድም ተፈጥሯል ••• ለሙስሊም ተማሪዎች ጥያቄ ይፋዊ እና ሕጋዊ ምላሽ እስኪሰጥም ትግሉ ይቀጥላል::
መብት በትግል እንጅ በልመና አይገኝም!
ፍትሕ ለጅማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች!
https://t.me/EHEMSU
የጅማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ ዩኒቨርሲቲው በሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጉዳይ ያለውን አቋም እስከ የካቲት 29/2017 ከቀኑ 10:00 እንዲያሳውቅ አሳሰበ:: ጀመዓው በተለይም በሴት ሙስሊም ተማሪዎች ላይ ተደጋጋሚ የሆነ የመብት ጥሰት እየደረሰ መሆኑን ገልፆ ዩኒቨርሲቲው ምላሽ የማይሰጥ ከሆነ ከተማሪዎቹ ጋር በመሆን ወደ ቀጣይ ሰላማዊ ትግል እንደሚሸጋገር ገልፇል::
መብት በትግል እንጅ በልመና አይገኝም!
በሚከተለው መልኩም ጥያቄያችሁን አቅርቡ
"የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ ከሆነ ቡሃላ ባወጣው መመሪያ የሚከተሉት አንቀፆች ይገኛሉ:-
• አንቀፅ 6:- "ከደህንነት ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ማንነትን ለመለየት ሲባልና ከፀጥታ ጋር በተገናኘ ምክንያት አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቅጥር ግቢ ውስጥ ፊትን በመሸፈን ማንነትን ለመለየት አዳጋች የሚያደርጉ አለባበሶችን መልበስ አይፈቀድም::"
ይህ በግልፅ ሙስሊም ተማሪዎች ሐይማኖታቸው አዟቸውና ሕገ መንግስታቸው ፈቅዶላቸው የሚለብሱትን ኒቃብ የሚከለክል ድንጋጌ ነው:: በየትኛው አግባብ ነው በአንድ ሐይማኖት ጣልቃ ገብቶ አለባበስ ለመምረጥ መመሪያ ያወጣው? ኒቃብ መልበስ እንደ ሐይማኖት ትዕዛዝ ነው:: እንደ ሕገ መንግስት መብት ነው:: ከሐገራችንም ባሻገር የሌሎች ሀገራት ዩኒቨርሲቲዎች ልምድ ይህንን ያፀናል:: ሆኖም ግን ዩኒቨርሲቲያችን ባልታወቀ ምክንያት ይህንን ድንጋጌ አውጥቷል:: ከዚህ በመቀጠልም ተማሪዎች ጥያቄ ቢያቀርቡም መጀመሪያ አከባቢ ለማወያየት ቢሞክርም ቡሃላ ግን ከአንድ የልሕቀት ማዕከል በማይጠበቅ መልኩ የሙስሊም ተማሪዎችን ተወካዮች አናወያይም ብሎ በር ዘግቷል:: ለምን ብላችሁ እንድትጠይቁልን እንፈልጋለን::
@aaumsu
ለመላው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች እንዲሁም ለሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪዎች!
ቲክቫህ ኢትዮጵያ "በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝነት ጉዞ ዙሪያ ጥያቄ አለዎት?" በሚል ርዕስ ከዩኒቨርሲቲው ጋር በመነጋገር ተማሪዎች፣ የግቢው ማህበረሰብ እንዲሁም አጠቃላይ ህዝቡ በዩኒቨርሲቲው የራስ ገዝነት ዙሪያ ያላቸውን ጥያቄዎች ለማቅረብ ዝግጅት ላይ እንደሆነ አሳውቋል።
ስለሆነም እንደ ሙስሊም ተማሪ ዩኒቨርሲቲያችን ራስ ገዝ ከሆነ ቡሃላ ሐይማኖታዊና ሰብዓዊ መብታችንን የሚረግጥ መመሪያ ለምን እንዳወጣ እንዲጠየቅልን እንፈልጋለን። ስለሆነም ሁሉም ተማሪ የሚከተለውን ቅሬታ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለዩኒቨርሲቲው እንዲያደርስልን ልንጠይቅ ይገባል።
"አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስ ገዝ መሆኑን ተከትሎ በ2017 ዓ.ል ባወጣው መመሪያ የሙስሊም ተማሪዎችን ሐይማኖታዊ ሰብዓዊ እና ሕገ-መንግስታዊ መብት የሚያፍን መመሪያ አውጥቷል:: በመመሪያው ኒቃብ የሙስሊም ተማሪዎች ልብስ ሆኖ ሳለ "መልበስ አይቻልም!" የሚልን ድንጋጌ አውጥቷል:: ይህ ደግሞ በሐይማኖታችን ጣልቃ መግባት ነው:: ሙስሊሞች ሶላት መስገድ እንዳለባቸው የሚታወቅ ሆኖ ብሎም ባደጉት ሀገራት ዩኒቨርሲቲዎች የመስገጃ ቦታ ተመቻችቶላቸው እየሰገዱ ሳሉ ዩኒቨርሲቲያችን ግን ከሕግም ከልምድም ውጭ ሆኖ ሶላት በሕብረት መስገድ ይከለከላል የሚል መመሪያ አውጥቷል:: የሙስሊም ተማሪዎች ተወካዮች ለዩኒቨርሲቲው አመራሮች ቅሬታውን ቢያቀርቡም ዩኒቨርሲቲው ለማወያየት ፈቃደኛ ሳይሆን ቀርቷል:: ይህ ደግሞ ከአንድ የልሕቀት ማዕከል የማይጠበቅ የውይይት ባህላችንን የጣሰ ተግባር ነው:: ስለሆነም ይህንን ለምን እንዳደረገ ማብራሪያ እንሻለንና ጠይቁልን::"
ጥያቄዎችን ለማቅረብ @tikvahmagbot ይጠቀሙ።
@MohammadamminKassaw
Warri Yunivarsitii jimmaa ajandaa haaraa muslimootaaf uumuu dhaabaa. Mirga barattootaa muslimaa kabajaa!
Gali Ababor
@MohammadamminKassaw
ከጅማም ሆነ ከሌሎች የመብት ጥያቄዎች የምንረዳው አንድ ሐቅ ቢኖር:- መብት በትግል እንጅ በልመና አይገኝም!" የሚለውን ነው:: ለአመታት እሽሩሩ ሲባሉ የነበሩ አካላት በ3 ቀናት ትግል ከቦታቸው ተቀምጠዋል:: አሁንም ቢሆን ግን ትግሉ ሊቀጥል ይገባል ••• መብት በትግል እንጅ በልመና አይገኝምና:: ቅንጣት ታክል መብት እስካትሸረፍ ድረስ ትግል ያሻል!
https://t.me/EHEMSU
በጅማ ያሉ እህቶች ዛሬም ከክብራቸው ጋር ገብተዋል!
ትግሉ ይቀጥላል!
https://t.me/EHEMSU
ትምህርት ሚኒስቴር በጅማ ዩኒቨርሲቲ እየተፈፀመ ያለውን ነገር አልሰማ ይሆን? ወይንስ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱም ከተቋቋመለት አላማ ውጭ እየተንቀሳቀሰ ነው?
ጥያቄ አለን!
ከኒቃብ ባሻገር የአባ ጅፋሯ ጅማ ውስጥ የሚገኘው ዩኒቨርሲቲ ጀለብያ: አማኢማ እና መሠል የሙስሊሞችን አልባሳት ይከለክላል!" አሉ::
ይህ በአባ ጅፋር ሀገር ያጠላው የአባ ኮስኳሴ እሳቤ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ሊወገድ ይገባል::
https://t.me/EHEMSU
እስልምና ከዩኒቨርሲቲ ደጅ ተወልቆ የሚገባ ልብስ አይደለም!
https://t.me/EHEMSU
ክብር ከበር ተጥሎ አይገባም!
ትለብሳለችም
ትማራለችም !!
ፍትሕ ለጅማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች!
@MohammadamminKassaw
በደረቀ ሌሊት አፍነው የወሰዱትን ልጅ በደረቀ ሌሊት መልሰዋል!
ፍትሕ እስኪመጣ ትግሉ ይቀጥላል!
ፍትሕ ለጅማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች!
መብቱን በሰላማዊ መንገድ የጠየቀን ተማሪ አፍኖ መውሰድ ከአንድ የልሕቀት ማዕከል አይጠበቅም:: ጅማ ዩኒቨርሲቲ ሌላው ቢቀር ዩኒቨርሲቲ የሚለውን ማዕረግ ሊያከብር ይገባል:: ትምህርት ሚኒስቴር በስሩ ያሉ ተቋማት በተማሪዎቻቸው ላይ እየፈፀሙት ስላለው የመብት ጥሰት ሊገመግም ይገባል:: ስለ ሴት ልጅ መብት የሚሞግት ሁሉ ዩኒቨርሲቲዎች በሙስሊም ሴቶች ላይ እየፈፀሙት ስላለው ነገር አቤት ሊሉ ይገባል:: መጅሊስ የሙስሊሞች ተቋም እስከሆነ ድረስ ይህንን የህልውና ጥያቄ ለማስከበር እስከ ጥግ ድረስ መሄድ አለበት::
ጥያቄያችን ሙስሊም ሆነን እንማር ነው ••• ሙስሊም ተማሪዎች ነንና:: ይህ ደግሞ በጅማ ተለይቶ የሚፈፀም ሳይሆን ከዲላ እስከ አዲስ አበባ ••• ከሐረማያ እስከ ባህር ዳር ••• ከመቱ እስከ ድሬ ዳዋ ያሉ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ የሚፈፀም ነው:: ወይንስ ጅማ ከሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ይለያል?
ፍትሕ ለጅማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች!
https://t.me/EHEMSU
Justice for Jimma university Muslim Students!
🛑Oduu yaachisaa ta'e kan amma nu qaqqabe.
Gaaffii barttoonni muslimaa niqaabni akka nuuf hayyamamu gaafatan hoggansi yuunivarsitichaa gurra isaa cufatee akka hin dhageenyee fi akka hin argine gochuudhaan amiirota jama'aa ukkaamsuudhaan fuudhuu eegalee jira.
Amiira jama'aa kaampaasii Agrii kan ta’e Abdulkariim kormaa namoota eenyummaan isaanii hin beekkamneen patrooliidhaan qabamee deemameenii jira.
Gocha seeraan alaa Yuunivarsiitichaa kanaan wol qabatee jama'aan keenya ejjannoo inni fudhatu dhiheenyatti kan isin beeksifnu ta’a.
Jama'aa muslimaa Yuunivarsiitii jimmaa.
https://t.me/EHEMSU
ጅማ ዩኒቨርሲቲ
የሙስሊም ተማሪዎችን የኒቃብ ይፈቀድልን ጥያቄ እንዳላየና እንዳልሰማ ጆሮ ዳባ ልበስ ያለው የዩኒቨርስቲ አስተዳደር የጀመዓውን አሚሮች አፍኖ መውሰድ ጀምሯል።
የአግሪ ኮምፓስ የተማሪዎች አሚር የሆነው አብዱልከሪም ኮርማ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች በፓትሮል መኪና ተይዞ ተወስዷል።
ይህንን የዩኒቨርስቲውን ህገወጥ ስራ አስመልክቶ ጀመዓችን የሚሰጠውን ውሳኔ በቅርቡ የምናሳውቅ ይሆናል
••• የጅማ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ
https://t.me/EHEMSU
ይህ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው:: በቻናሉ ከዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጋር ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮች እና የህብረቱ የዕለት ተዕለት ክዋኔዎች ይቀርባሉ::
በአላህ ፍቃድ እና እርዳታ ከዚያም ከሙስሊም ተማሪዎች ጋር በሚኖር መናበብና መተጋገዝ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያሉ ሙስሊም ተማሪዎች መብታቸው ተከብሮ ይማሩ ዘንድ እንተጋለን::
መረጃዎች ለሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ይደርሱ ዘንድ ቻናሉን ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ::
@EHEMSU @EHEMSU @EHEMSU
@EHEMSU @EHEMSU @EHEMSU
@EHEMSU @EHEMSU @EHEMSU
