en
Feedback
Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union

Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union

Open in Telegram

This is the official Channel of Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union.

Show more
4 476
Subscribers
-424 hours
-37 days
+2230 days
Posts Archive
ፊዳከ አቢ ወኡሚ ወሩሂ ያረሱለሏህ 😍 @EHEMSU

ነፃነት በነፃ አይገኝም! @EHEMSU

መብት በትግል እንጅ በልመና አይገኝም! @EHEMSU

የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄዎች በዚህ ትውልድ ሊቋጩ የሚገቡ የትላንት አደራዎች ናቸው! https://t.me/EHEMSU

Breaking! የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ተመሰረተ! ••••••••••••••••••••••••••••••••••••• አርባምንጭ:- ረመዳን 9/9/1446 ••••••••••••••••••••••••••••••••••••• በአርባንጭ ዩኒቨርሲቲ የሚገኙ የካምፓስ አሚሮች አባያ በሚገኘው መስጂደልአንሷር ባደረጉት ጥልቅ ውይይት የአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረትን መስርተዋል:: ህብረቱ ሲመሰረት የMain campus: ኩልፎ ካምፓስ: ነጭ ሳር ካምፓስ: አባያ ካምፓስ እና ጫሞ ካምፓስ አሚሮች የተገኙ ሲሆን የህብረቱን ከፍተኛ አመራሮች መርጠዋል:: በዚህም መሠረት:- 1) ወንድም ኡሳማ አሊ ••• ፕሬዚዳንት (ከMain campus) 2) ነቢል ሙሐመድ ••• ምክትል ፕሬዚዳንት (ከነጭ ሳር ካምፓስ) 3) ኸይሩ ጀማል ••• ፀሐፊ (ከጫሞ ካምፓስ) ተደርገው ተመርጠዋል:: አላህ ለተማሪው በተሻለ ሁኔታ የሚያገለግሉበትን ብርታት ይሰጣቸው ዘንድ ዱዓችን ነው:: https://t.me/EHEMSU

ጁምዓ ሶላት ሁሉም ሙስሊም በመስጂድ ተገኝቶ ይሰግደው ዘንድ ከአላህ ግዴታ የተደረገ ነው! https://t.me/EHEMSU

ሶላት መስገድ ከአላህ በኩል የመጣ ግዴታ ነው! https://t.me/EHEMSU

ኒቃብ መልበስ ከአላህ የመጣ ትዕዛዝ ነው! https://t.me/EHEMSU

ሐረማያዎች እንዳሉት "ኒቃብ ኢትዮጵያዊ እሴት ነው!"
ሐረማያዎች እንዳሉት "ኒቃብ ኢትዮጵያዊ እሴት ነው!"

ሌላ የትግል ፍሬ ••• ከመቱ ዩኒቨርሲቲ ጀመዓዎች! መቱዎች ከጁምዓ ሶላት ጋር ተያይዞ ከ5:30 እስከ 7:30 በሕግ እንደፀናው ትምህርት እንዳይኖር በተደጋጋሚ ሲጠይቁ እንደነበር ይታወቃል:: በአላህ ፈቃድ ብሎም በተማሪዎች ትግል ከዩኒቨርሲቲው ጋር ስምምነት ተደርሶ ተግባራዊ እንደተደረገ ጀመዓው አሳውቋል:: መብት በትግል እንጅ በልመና አይገኝም! https://t.me/EHEMSU

ከሐረማያ ጀመዓዎች መግለጫ የተወሰደ:- "የጅማ ዩኒቨርሲቲ ስልጣናቸውን ተማሪን ለመጨቆን በሚገለገሉ አግላይ አመራሮቹ ላይ ጥብቅ የሆነ እርምጃ በመውሰድ: ሙስሊም ሴት ተማሪዎችን በዚህ የልሕቀት ማዕከል ውስጥ ተካታች በማድረግ: ለሕዝብ የቆመ ተቋም እንደሆነ እንዲያስመሰክር እንጠይቃለን::" እውነት ነው ••• ጥላቻው በርትቶ በሰከረ ሰዓት ተማሪን በድሎ ሲበርድለት ዝም ሊባል የሚገባ አካል ሊኖር አይገባም:: https://t.me/EHEMSU

ስለ ኒቃቢስቷ ዚክራ ሰዒድ ወርቃማ ስኬት ያልፃፈ የለም! ኒቃብን በመመሪያ ደረጃ የከለከለው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቴሌግራም ቻናል AAU መረጃ እንኳ ስኬቷን ተማሩበት ብሏል:: እናማ:- የቻናሉ ፖ
ስለ ኒቃቢስቷ ዚክራ ሰዒድ ወርቃማ ስኬት ያልፃፈ የለም! ኒቃብን በመመሪያ ደረጃ የከለከለው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቴሌግራም ቻናል AAU መረጃ እንኳ ስኬቷን ተማሩበት ብሏል:: እናማ:- የቻናሉ ፖስት "ኒቃብ የመማር ማስተማሩን ስርዓት ያስተጓጉላል!" በማለት በመመሪያ የከለከሉት የዩኒቨርሲቲው አመራሮች ያዩት ዘንድ ወደድን:: ጥላቻ ሊጋርደው ያልቻለ ስኬት !

ኡስታዝ አህመዲን አየር መንገዱ ለሚያዘጋጀው የኢፍጣር ፕሮግራም የግብዣ ጥሪ ሲቀርብላቸው እንደሚከተለው መለሱ:- "እኛ ኢፍጣርም ሆነ ተምር አልቸገረንም። የጠሩኝን ሰዎች የሙስሊም ሴቶችን መብት አክብ
ኡስታዝ አህመዲን አየር መንገዱ ለሚያዘጋጀው የኢፍጣር ፕሮግራም የግብዣ ጥሪ ሲቀርብላቸው እንደሚከተለው መለሱ:- "እኛ ኢፍጣርም ሆነ ተምር አልቸገረንም። የጠሩኝን ሰዎች የሙስሊም ሴቶችን መብት አክብሩ ያኔ የኢፍጣር ጥሪያችሁ ትርጉም ይኖረዋል በላቸው። የሙስሊም ሠራተኞችን መብት እንዲያከብሩ የቀረበላቸው አቤቱታ ምንም ምላሽ ሳይሰጡ በዝምታ አልፈው ኑና አፍጥሩ ማለት ለኔ አይዋጥልኝ::" ቆራጥነት እና ተምሳሌትነትን ያቀፈ ጥልቅ መልዕክት አለው!

መዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ጀመዓዎች መብታቸውን አስከብረዋል! ዩኒቨርሲቲው ረመዳንን አስመልክቶ ሾርባ አለማዘጋጀቱን ተከትሎ በባሌ ሮቤ ከተማ ተቃውሞ ያሰሙት የመዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተወካዮች የ ከግቢው አመራሮች ጋር በሙስሊም ተማሪዎች ጥያቄዎች ዙሪያ ለ3 ሰዓታት የዘለቀ ውይይት በዛሬው እለት አድርገው ነበር:: በውይይቱም ጠቅላላ የሆኑ ጥያቄዎች የቀረቡ ሲሆን ከዩኒቨርሲቲው ጋር በስምምነት ጨርሰዋል:: መብት በትግል እንጂ በልመና አይገኝም! https://t.me/EHEMSU

የሐረማያ ጀመዓዎች ስለኒቃብ የሚከተለውን ብለዋል:- "ኒቃብ ከአረብ ሀገራት የተወረሰ የተወረሰ ባህል አይደለም: የሐገራችን ግማሽ ማህበረሰብ የሆነው የህዝበ ሙስሊሙ ሃይማኖት አለምአቀፍ እንጅ የአረብ ብቻ አይደለምና:: ኒቃብ የአክራሪነት መገለጫ አይደለም: የመላው ኢትዮጵያዊ ሙስሊም መገለጫ እሴት ፅንፈኝነት አይሆንም::" እውነት ነው! https://t.me/EHEMSU

የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት በጅማ ዩኒቨርሲቲ ኒቃቢስት ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው የመብት ጥሰት መግለጫ አውጥቷል:: "ኒቃብ የኢትዮጵያ እሴት ነው!" - ብሏል:: አላሁ አክበር
የሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት በጅማ ዩኒቨርሲቲ ኒቃቢስት ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ስላለው የመብት ጥሰት መግለጫ አውጥቷል:: "ኒቃብ የኢትዮጵያ እሴት ነው!" - ብሏል:: አላሁ አክበርር! አላሁ አክበርርር!! አላሁ አክበርርርር!!

Let they witness it ፋና ••• EBC ••• ሌሎችም የመንግስት ሚዲያዎች ስለ እርሷ አውርተዋል ስኬቷ እንደ ፀሐይ ወጥቷልና በእጃቸው ሊጋርዱት አልቻሉም ዚክራ ሰዒድ በኒቃቧ ተውባ ክብሯን
Let they witness it ፋና ••• EBC ••• ሌሎችም የመንግስት ሚዲያዎች ስለ እርሷ አውርተዋል ስኬቷ እንደ ፀሐይ ወጥቷልና በእጃቸው ሊጋርዱት አልቻሉም ዚክራ ሰዒድ በኒቃቧ ተውባ ክብሯን አስጠብቃ ከነፃነቷ ጋር ከፊት ተሰለፈች ይህ በጥብቅነት ውስጥ የታየ ትልቅ ስኬት ነው ••• ኒቃብ መማር ማስተማርን ያስተጓጉላል ለሚሉት ሁሉ ላኩላቸውና ኒቃብ ለብሳ ከሁሉም ልቃ እንደተገኘች ይመስክሩ ••• ኒቃብ ለደህንነት ስጋት ይሆናል ለሚሉት ሁሉ ላኩላቸውና ኒቃቧን ለብሳ ከደህንነቷ ጋር በዋንጫ እንደተመረቀች ይመስክሩ Let they witness it !

ኒቃቢስቷ ዛኪራ ሰዒድ በወርቅ ተመርቃለች! በወሎ ዩኒቨርሲቲ የሳይኮሎጂ ተማሪ የነበረችው ዛኪራ ሰዒድ 3.99 በማምጣት በሁለት ዋንጫ እና የወርቅ ሜዳልያ ተመርቃለች:: Congratulations 🎉�
ኒቃቢስቷ ዛኪራ ሰዒድ በወርቅ ተመርቃለች! በወሎ ዩኒቨርሲቲ የሳይኮሎጂ ተማሪ የነበረችው ዛኪራ ሰዒድ 3.99 በማምጣት በሁለት ዋንጫ እና የወርቅ ሜዳልያ ተመርቃለች:: Congratulations 🎉🎉🎉 Our sister! Once again ኒቃብ ከመማር ከመመረቅ ከመሸለም አያግድም:: ተምራለች: ተመርቃለች: ተሸልማለች:: ትለብሳለች ትማራለች! Congratulations 🎉🎉🎉🎉

"ጅማ ዩኒቨርሲቲ ኒቃብ ከለከለ!" - የሚለው ዜና surprising የሆነባቸው ብዙ ሰዎች አሉ:: "መዳ ወላቡ ለረመዳን ሾርባ አላዘጋጅም አለ!" የሚለውም ግርምትን የፈጠረባቸው ብዙሐን ናቸው:: እዚህጋ አትሳሳቱ ••• በዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ያለውን የመብት መገፋት ጠለቅ ብለን ካየነው ጥልቀቱ የትየሌለ ነው:: ሆኖም ዋነኛው ችግር ከእኛ ነው:: እስካሁን ድረስ በእኛ ላይ ምን እየተካሄደ እንዳለ እንኳ አናውቅም:: ስለ መብቶቻችን አምርረን አንጠይቅም:: ጅማ ኒቃብ ጀለብያ እና መሠል የሙስሊም መብቶችን ካፈነ አምስት አመታት ተቆጥሯል:: አሁን ለመብቱ የሚታትር ትውልድ ሲፈጠር ነው በጓዷ የነበረው ወደ አደባባይ የወጣው:: መዳ ወላቡ በታሪኩ በረመዳን ሾርባ አዘጋጅቶ አያውቅም:: የሾርባውን በጀት ወደየት እንደሚያስገቡት አላህ ይወቅ:: አሁን ግልፅ የሆነው ተማሪው እምቢኝ ብሎ ሲነሳ ነው:: አሁንም ቢሆን ••• ምን ውስጥ ነው እየኖርን ያለነው ብሎ መጠየቅ ያሻል:: ምንድን ነው የነጠቁን ብሎ ማሰላሰል ያስፈልጋል:: ከዚያም ቡሃላ መጠየቅ መጠየቅ መታገል መታገል ማለት ነው:: እነርሱ ሳያፍሩ ሳይፈሩ ሕግን ተላልፈው የከለከሉንን እኛ ተሽኮርምመን ዝም ማለት የለብንም:: እየተማርን ያለን ሙስሊም ነንና:: ካልጠየቅን ግን ተምረንም አንጠቅም! https://t.me/EHEMSU

መዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ለረመዳን ሾርባ አላዘጋጅም ማለቱን ተከትሎ ተማሪዎች በሰላማዊ ሁኔታ ጥያቄያቸውን አቅርበዋል! ለረመዳን ሾርባ በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች በሚባል ደረጃ ይዘጋጀል:: የሚዘጋጀው በአዲስ በጀት ሳይሆን የቁርሱን ምግብ ወደ ሾርባ በመቀየር ነው:: ዩኒቨርሲቲው ባለፉት አመታትም የማያዘጋጅ ሲሆን በዘንድሮው አመት ተማሪዎች ረመዳን ከመግባቱ በፊት ጀምረው ጠይቀው እሺ ቢባሉም ሳያዘጋጅ ቀርቷል:: ለማድረግ ቀላል ለተማሪው ለእሴቱና ለዩኒቨርሲቲው ከበባቢ ትልቅ ትርጉም ያላቸውን ጉዳዮች ባያወሳስቡ ለሁሉም በጎ ነው:: ትምህርት ሚኒስቴርም በመሠል ጉዳዮች ላይ ወጥ የሆነ ስርዓት ሊዘረጋ ይገባል:: አለዚያ ሙስሊም ጠል የሆኑ አመራሮች አጀንዳ መፍጠር በፈለጉ ቁጥር የሚያነዱት እሳት ሁሉንም ዋጋ ያስፈልጋል:: ፍትሕ ለኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች!