Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union
Open in Telegram
This is the official Channel of Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union.
Show more4 476
Subscribers
-424 hours
-37 days
+2230 days
Posts Archive
+1
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስለ ትምህርት ስርዓቱ ጠይቁኝ ባሉት መሠረት ጥያቄዬን እንደሚታየው አቅርቤያለሁ::
ይህ የትግላችን አንዱ አካል ነው:: ፈጠን ብለን በተቀናጀ ሁኔታ በትምህርት ስርዓቱ ውስጥ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የሚደርሰውን በደል እናሰማ::
ቅሬታን ማቅረቢያው https://www.facebook.com/share/p/1LNAiWkmeA/ ነው::
ፈጠንንንንን በሉሉሉሉሉ! የላካችሁበትን @MohammadamminM ላኩልኝ::
Let us do it!
@MohammadamminKassaw
እንፍጠን ••• ቀነ ገደቡ ዛሬ ነው!
■ የጠቅላይ ሚኒስተር ጽ/ቤት በትምህርት፣ በጤና፣ በኢኮኖሚና ሌሎች አምራች ጉዳዮችም ላይ ጠይቁኝና ምላሹን በሚመለከታቸው አካላት እሰጣለሁ ብሏል። ስለሆነም በትምህርት ቤቶች ውስጥ ስላለው የሙስሊም ተማሪዎች ጥያቄ እንዲሁም ስለዚህ እኛ ፈጥነን የእህቶቻችንን የአለባበስ ጉዳይና የአየር መንገዱን ጉዳይ እንጠይቅ። ዛሬ ማክሰኞ መጋቢት 2 የመጨረሻው ቀን ነው!
መጀመሪያ በዚህ ሊንክ ወደ ፖሰቱት ጽሑፍ ግቡ።
https://www.facebook.com/share/p/1LNAiWkmeA/
ከዚያ እነዚህን ጥያቄዎች ኮመንት ላይ ጻፉና ላኩላቸው። የምትችሉ ከቀጥታ ኮፒ ፔስት ይልቅ በራሳቸው አገላለፅ ሃሳቡን ጻፉትና ጠይቁ።
ጥያቄዎቹ:-
①)
ክቡር የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት እንደገለጻችሁት ጥያቄዎችን ለመቀበል ዝግጁ መሆናችሁን ስላሳወቃችሁን እናመሰግናለን።
እኛ ሙስሊሞች በትምህርትና በመንግስት ተቋማት በተለይም ሙስሊም ሴት ተማሪዎች በሒጃብና ኒቃብ አለባበስ ምክንያት እንዲሁም በሶላት አፈጻጸም ላይ እምነት ነጻነታችን እየተገደበ መሆኑን ልናሳውቃችሁ እንወዳለን።
√ በትምህርት እና በተለያዩ የስራ መስኮች የሙስሊም ሴቶችን መብት በተመለከተ፤ በኢትዮጵያ ሕገ መንግስት አንቀፅ 27 ላይ በግልጽ እንደሰፈረው እያንዳንዱ ሰው የመረጠውን ሃይማኖት የመከተል፣ የማምለክ እና የመግለጽ መብት አለው።
ሆኖም በተጨባጭ፦
1) • በትምህርት ዘርፍ፡ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች (ለምሳሌ ጉራጌ ዞን ጉንችሬ፣ አክሱም፣ ዲላ ዩኒቨርስቲ፣ ጅማ ዩኒቨርስቲ፣ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ…) ያሉ ሙስሊም ተማሪዎች (ከቅድመ አንደኛ ደረጃ እስከ ዩኒቨርሲቲ) ኒቃብ፣ ሒጃብ እና ሌሎች ኢስላማዊ አለባበሶችን በመልበሳቸው ምክንያት፡
ከትምህርት ገበታቸው እየተባረሩ ነው። (ለምሳሌ በጉራጌ ዞን ጉንችሬ ከ3 አመት በላይ ሆኗቸዋል)
በብሔራዊ ፈተናዎች ወቅት በአለባበሳቸው ምክንያት ፈተና እንዳይፈተኑ እየተደረጉ ነው። (ለምሳሌ፦ በአክሱም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፎርም አልሞሉም፣ እስከዛሬ በበርካታ የትምህርት ተቋማት ላይ ልክ ፈተና ሲቀመጡ ኢስላማዊ ልብሳችሁን አውልቁ የሚባሉባቸው አጋጣሚዎች ነበሩ።)
ትንኮሳ እና መድልዎ እየደረሰባቸው ነው።
ከሶላት ጋር በተያያዘም የእምነት ነፃነታቸው እየተገደበ ነው።
ጥያቄያችን፡ መንግስት ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሕገ-መንግስታዊ መብታቸው ተጠብቆ፣ ያለምንም ሥጋትና መድልዎ ትምህርታቸውን እንዲከታተሉ ምን አይነት ተጨባጭ እርምጃዎችን እየወሰደ ነው? መቼስ መፍትሄ ይሰጣል?
2)• በመንግስት ተቋማት (ለምሳሌ በኢትዮጵያ አየር መንገድ)፡
ሙስሊም ወንዶች እምነታቸው ስለሚያዛቸው ፂማቸውን በማስረዘማቸው እና ሱሪያቸውን በማሳጠራቸው ምክንያት የመቀጠር እድል እየተነፈጋቸው ነው።
ሒጃብ የሚለብሱ ሙስሊም ሴቶች የመስራት መብታቸው እየተገደበ ነው።
ጥያቄያችን፡ እነዚህ ተቋማት ከሕገ መንግስቱ ጋር የሚቃረኑ አሰራሮችን እንዲያስተካክሉ እና ኃይማኖታዊ ነፃነትን እንዲያከብሩ መንግስት ምን አይነት ቁጥጥር እና የማስተካከያ እርምጃዎችን እየወሰደ ነው? ለዚህ አንገብጋቢ ጉዳይ በዝርዝር እንድታብራሩልን እና ተገቢውን ትኩረት በመስጠት አፋጣኝ እና ዘላቂ መፍትሄ እንዲሰጡን በአክብሮት እንጠይቃለን::
@EHEMSU
በመጨረሻም ሁላችንም የሃይማኖት ተቋሞቻችንንና የአስተምህሯችንን ክብር፣ ልዕልናና ቅድስና እንጠበቅ በማለት ጉባኤያችን የአደራ መልዕክቱንና ጥሪውን ያቀርባል፡፡
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ - ለሰላም፣ ለመተባበር እና ለአብሮነት
ፈጣሪ ኢትዮጵያን ይባርክ
መጋቢት 2 ቀን 2017
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
በወቅታዊው በማኅበራዊ ሚዲያ እየተካሄደ ያለውን ሃይማኖትን ሽፋን ስላደረገው ክብረ-ነክ፣ የትንኮሳ፣ የጥላቻና ጸብ ቀስቃሽ ዘመቻዎችን አስመልክቶ
በኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የተሠጠ መግለጫ
🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴🔴
“የሃይማኖት ንጽጽር - በከፍተኛ የሃይማኖት ሊቃውንቶች መካከል በሕግ፣ በሥርዓት እና በጥብቅ ዲሲፕሊን የሚመራ በዶግማዊ ጉዳዮች ላይ የሚደረግ የሰከነ ውይይት ነው፤ በአማኞች መካከል የሚደረግ ሥርዓት የለሽ እና አንዱ ሌላውን የሚያውገዝ፣ የሚያጠልሸ እና ክብረ-ነክ መሆን ወንጅል ነው፤” ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የማኅበራዊ ሚዲያውን እድገትና ተደራሽነት መስፋትን ተከትሎ በተለያዩ ርዕሠ ጉዳዮች ላይ የሚያተኩሩ አጀንዳዎች ላይ በአወንታዊነት እና በአሉታዊነት የሚፈረጅ ይዘት ያላቸው ሥራዎች ተሠርተው አየር ላይ ሲውሉ እናያለን፤
አንዳንዶች ደግሞ የራሳቸውን የማኅበራዊ ሚዲያ መድረክ በመክፈት የተለያዩ ግለሰቦችን ወደመድረካቸው በመጋበዝ በተለያዩ አጀንዳዎች ላይ በደጋፊነት እና በነቃፊነት ላይ ተሰልፈው የጦፈ ክርክር ሲደርጉም እንመለከታለን፡፡
ዘርፉና የመገናኛ መድረኩ የራሱ የሆነ የአጠቃቀም መመሪያ ያለውና በጥብቅ ዲሲፕሊን እንዲመራ የሚጠበቅ ቢሆንም አንዳንድ ግለሰቦችና ቡድኖች መድረኩን ከዓላማው ውጪ ለሆነና ለግልና ቡድናዊ ፍላጎታቸው መጠቀሚያ በማድረግ በተለያዩ ሃይማኖት/እምነት ተከታዮች መካከል መተማመኑ እና መከባበሩን የሚሸረሽሩ ይዘቶችን፣ ክብረ ነካዊ በሆነ አቀራረብ ግልፅ ጥላቻን የመስበኩ ልምምድ ከጊዜ ወደጊዜ እየተባባሰ ይገኛል፡፡
ይህ ዓይነቱ አቀራረብና ልምምድ አልፎ አልፎ በአንዳንድ የሃይማኖት ተቋማት ውስጥ በመደበኛ የአምልኮ መርሀ ግብር ላይ በፊት ለፊት መድረኮች ሲቀርብ አይተናል፡፡ ልምምዱና አቀራረቡ ከወዲሁ ሊታረምና በሕግና ሥርዓት ሊከናውን እንደሚገበው ጉባኤያችን በጽኑ ያምናል፡፡ ከዚህ አንፃር ከሰሞኑ የሁለቱ ታላላቅ ሃይማኖቶች የተቀደሰ የጾም፣ የጸሎትና በከፍተኛ ደረጃ የመንፈሳዊ እነፃ ላይ በሚገኙበት ጊዜ ከመንፈሳዊነትና ከሃይማኖቶች መሠረታዊ ዕሴት ጋር የሚቃረን ተግባር በማኅበራዊ ሚዲው በስፋት እየተሠራጨ ይገኛል፡፡
በተለይም አንዳንድ የኦርቶዶክስ ክርስትና አማኝ ነን የሚሉ ግለሰቦች፣ የእስልምና ሃይማኖት ነቢይ በሆኑት በነቢዩ መሐመድ (የአላህ እዝነትና ሰላም በእሳቸው ላይ ይሁንና) ላይ ድፍረት የተሞላበት ክብረ ነክና ጽያፍ ንግግር ሲያደርጉ ታየረተዋል፡፡ ይህም ሙስሊሙን ወገን ብቻ ሳይሆን ሰላም ወዳዱን ወገን ሁሉ አሳዝኗል፡፡
ጉባኤችንም ይህ ዓይነቱ ኢ-ሥነምግባራዊ እና ሕገ ወጥ ተግባር የትኛውንም የሃይማኖት ተቋም የማይወክል፣ ይልቁንም የሚወገዝ ተግባር መሆኑን ለመግለጽ ይወዳል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘም አንዳንድ የኦርቶዶክስ አማኝ ነን የሚሉ ወንድሞችና እህቶች የግለሰቡን ሕገ-ወጥ ተግባር ተቋማዊ ለማድረግ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ እንዲያጤኑና ግለሰብንና ተቋምን እንዲለዩ እንመክራለን፡፡
በአንፃሩ አንዳንድ ሙስሊም ነን የሚሉ ግለሰቦች ተደፈርን በሚል ስሜት የክርስትና አስተምህሮንና የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር የሚነቅፍና የሚያጠለሽ፣ መላውን ክርስቲያን በሚያዋርድ መልኩ ምላሽ ሲሠጡ እና ድርጊቱን በፈፀመው ግለሰብ ላይ የደቦ ፍርድ ሲያስተላልፉ ይታያሉ፡፡
ይህም ሕገ-ወጥነትን ከማስፋፋት ባለፈ ጥፋትን በሌላ ጥፋት ማረም ፈጽሞ የማይቻል መሆኑን ተገንዝበው ከድርጊታቸው በመታረም የሕግ የበላይነትን እንዲስቀድሙ ጉባኤያችን በአጽንኦት ይመክራል፡፡ በየትኛውም አካል የተፈፀሙትና የሚፈፀሙት ይህን መሠል ሕገ-ወጥ ተግባራት በሁሉም ሃይማኖቶች አስተምህሮ ተቀባይነት
የሌላቸው ብቻ ሳይሆን የሚወገዙ ተግባራት መሆናቸውን ጉባኤያችን እያስገነዘበ ድርጊቱ በወንጀል የሚስጠይቅ ስለመሆኑም ለማስታወስ ይወዳል፡፡
ሀገራችን ኢትዮጵያ የብዝሀ ሀይማኖት መገኛና መኖሪያ ከመሆኗ አንፃር የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የትኛውንም ዓይነት የሃይማኖት ተቋማትን፣ አስተምህሯቸውንና መገለጫዎቻቸውን የሚያንቋሽሹና የሚያዋርዱ ንግግሮችንም ሆነ ተግባራትን በጽኑ ያወግዛል። እንዲህ ያሉት ክብረ-ነክ የሆኑ ተግባራትና አስተያየቶች ሁሉ ድርጊቱ ለተፈፀመባቸው እምነት ተከታዮችን በእጅጉ የሚያስቆጡ ብቻ ሳይሆኑ መላ ኢትዮጵያዊያንን በእጅጉ የሚያስቆጡ ናቸው፡፡ የመከባበርና የአብሮነት እሴቱን በመሸርሸር በሀገራችን የሰላምና የሰላማዊ ማህበረሰብ ግንባታ ሂደቱንና ጥረቱን እንዳይያሳካ ያደርጋሉ፡፡
ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት አንዱ የሌላውን እምነት ለመስደብ ወይም ለማዋረድ በፍፁም ጥቅም ላይ መዋል የለበትም። የእምነት ነፃነት እና የማምለክ መብት ለሁሉም ማህበረሰቦች የተጠበቀ ሲሆን ይህ መብት የሌሎች አማኞችን መብት በመጋፋና ስሜት በመንካት ለጠብ ማነሳሽነት ሲውል በዝምታ ሊታለፍ አይገባውም፡፡
ይህንን ከባድ ጥፋት በዘላቂነት እንዲታረም የሚመለከታቸው አካላት አግባብነት ባላቸው ሕጎች መሰረት ይህንንና ተመሳሳይ ተግባር በፈፀሙና በሚፈጽሙ አካላት ላይ አፋጣኝ ሕጋዊ እርምጃ እንዲወስዱ እንጠይቃለን። ለእንደዚህ አይነት ወንጀሎች ተጠያቂነትን ማረጋገጥ ለወደፊቱ የሃይማኖትን ስም ማጥፋት ለመከላከልና የሁሉም እምነት ተከታዮች ክብርን ለመጠበቅና
ለማስጠበቅ በእጅጉ ይረዳል።
በተጨማሪም የሃይማኖት መሪዎች፣ የሃይማኖት ምሁራን እና መላ ሕብረተሰቡ በሃይማኖቶች መካከል መከባበር፣ መግባባትና መረዳዳት ይበልጥ ሊያጠናክሩ በሚያስችሉ የጋራና የተመረጡ አጀንዳዎች ላይ በሕግ፣ በሥርዓትና በጥብቅ ዲሲፕሊን የሚመሩና ግልጽ ዓላማና ግብ የተቀመጠላቸው ውይይቶችና ምክክሮች በተጠናከረ መልኩ በማከናውን በሃይማኖቶች መካከል ትብብራቸውንና አጋርነታቸውን እንደ ሚያጠናክሩ ይጠበቃል፡፡
በቅርቡ ጉባኤያችን ወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታዎችን በመዳሰስና በመተንተን ሀገራዊ ዓውዱንና ተግዳሮቶች ታሳቢ በማድረግ፣ እንዲሁም ተቋሙ ብቁና ተወዳዳሪ እንዲሆን ለማስቻል የመተዳደሪያ ደንቡን አሻሽሏል፡፡ የተሻሻለው ደንብም በተቋማት መካከል አለመከባበርን፣ አለመቻቻልን የሚሰብኩ፣ ጥላቻን የሚቀሰቅሱና ግጭትን የሚያባብሱ ተንኳሽና ክብረ-ነክ ንግግሮችንና ተግባራትን የሚፈፅሙ ግለሰቦችና ቡድኖች በራሳቸው ተቋም ተጠያቂ የሚያደርግ ሥርዓት እንዲኖር የሚያደርግ ድንጋጌ በደንቡ ላይ እንዲካተት ተደርጓል፡፡
የችግሩ ስፋትና ጥልቀት እየጨመረ ከመምጣቱ ጋር ተያይዞም ችግሮን በዘላቂነት ለመፍታትም ከአባል የሃይማኖት ተቋማት የሚወከሉ የሕግና አግባብነት ያላቸው ባለሙያዎች የሚካተቱበት የተከላካይ ግብር-ኃይል አደረጃጀት በጊዜያዊነትና በቋሚነት በማደራጀት የቅደመ መከላከል ሥራዎች ለመስራት ተዘጋጅቷል፡፡
ግብር-ኃይሉም ችግሮችንና የችግር አዝማሚያዎችን በማሰባሰብ፣ በመተንተንና የመፍትሔ ሀሳቦችን በመስጠት ሙያዊ እገዛ በማድረግ ሕግና ሕጋዊነትን የማስጠበቅ ሥራ በመስራት የሀገር ሰላምንና የሃይማኖት ተቋማትን ክብርና ልዕልና የማስጠበቅ ኃላፊነቱን ይወጣል፡፡
የሁለቱም እምነት ተከታዮች እና አማኞች በማኅበራዊ ሚዲያው ባለው አሉታዊ ዘመቻና በተፈጠረው ወቅታዊ ችግር ሳይረበሹ የጾም፣ ጸሎትና የንስሀና ተግባሮቻቸው ላይ እንዲያተኩሩ ጉባኤያችን ይመክራል፡፡
የሕግ አስከባሪ አካሉም፣ በአማኞች መካከል ያለው ሰላምና መከባበር የሚያውኩ፣ ሕገ-ወጥ ግለሰቦችና ቡድኖች ከድርጊታቸው እንዲታረሙ በማድረግ ሕግና ሥርዓት የማስጠበቅ የተለመደ ሕጋዊ ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጉባኤያችን ጥሪውን ያቀርባል፡:
ሸሐዳ እንኳ ያለ ነቢ ስም አይሞላም!
••• ወአሽሀዱ አን-ነ-ሙሐመደን ረሱለላህ!
@EHEMSU
We love Prophet Muhammad (صلى الله عليه و سلم) more than ourselves!
@EHEMSU
Muhammad (صلى الله عليه و سلم) !
@EHEMSU
May our parents and soul sacrificed for Allah's Messenger ﷺ !
@EHEMSU
Our greatest dream is to be the neighbor of Prophet Muhammad (صلى الله عليه و سلم) in Jennah !
@EHEMSU
We are the nation of Prophet Muhammad (صلى الله عليه و سلم) !
@EHEMSU
Our leader is Prophet Muhammad (صلى الله عليه و سلم) !
@EHEMSU
Our way is the way of Prophet Muhammad (صلى الله عليه و سلم) !
@EHEMSU
Prophet Mohammad (صلى الله عليه و سلم) is our great teacher!
@EHEMSU
ከወሎ ዩኒቨርሲቲ በዋንጫ የተሸለመችውን ዚክራ በሐሩን ሚዲያ እያየሁ ነበር:-
ጠያቂ:- ኒቃብ እንደሚሉት አዕምሮሽን ጋርዷል? በትምህርትሽ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ አሳድሯል?
ዚክራ:- በፍፁም! በፍፁም! እንደውም አግዞኛል:: ኒቃብ ፊቴን ልሸፍንበት እንጂ አዕምሮዬን ሊጋርድ አልተቀመጠም::
Congrats again 🎉🎉🎉
@MohammadamminKassaw
አንዱ የሌላውን መብት ማክበሩ ግዴታው ነው!
@EHEMSU
+1
ከኦዳ ቡልቱም ጀመዓዎች ትንሽ ብንማር!
ባለፈው አመት ሚያዚያ ወር ላይ ነበር አብርሐም የተባለ የሪሜዲያል ተማሪ በቲክቶክ ብቅ ብሎ የቁርዓን ክብርን የሚነካ ለ4 ደቂቃ የዘለቀ ንግግር ያደረገው:: ሆኖም በመቅፀብት ጀመዓው በግቢም በከተማም ባሉ ተቋማት ዘንድ ከሰሰ:: ክሱንም ሳይሰለቹ ተከታተሉ:: በመጨረሻም ተማሪው በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሎ ለ2 አመታት ያክል ከትምህርት እንዲታገድ ሆነ::
አሁንስ የነቢ ክብርን ለማስመለስ እኔ ብሎ ሀላፊነት የሚወስደውና መሬት ላይ ያለውን ትግል የሚመራው ማን ነው?
@MohammadamminKassaw
+1
በ1998 ዓ.ል በአዲስ አበባ: ከሚሴ እና ሐዋሳ የነቢ ክብርን ለመንካት የሞከሩ አካላትንና የቁርዓን ክብርን የተዳፈሩ አካላትን አስመልክቶ በወቅቱ የነበሩ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ጥያቄያቸውን ለጠቅላይ ሚኒስቴር መለስ ዜናዊ ያደረሱበት ደብዳቤ ነው::
አሁንስ የነቢን ክብር መነካት አስመልክቶ የሙስሊሙ መሪ ተቋም የሙስሊሙን ጥያቄ ለማን አቀረበ?!
@MohammadamminKassaw
"ኒቃብ መልበሴ አጠነከረኝ እንጅ አዕምሮዬን አልሸፈነውም!" - የዋንጫ ባለቤቷ ዚክራ ሰዒድ
ከወሎ ዩኒቨርሲቲ በ2 ዋንጫ እና የወርቅ ሜዳሌያ የተመረቀችው ታታሪዋ ዚክራ ሰዒድ ከሐሩን ሚዲያ ጋር በነበራት ቆይታ "ኒቃብ መልበሴ ለትምህርት አግዞኛል እንጅ አዕምሮዬን አልሸፈነውም!" ብላለች::
📌ሙሉ ፕሮግራሙ በሀሩን ሚዲያ ልዩ ዝግጅት በኢፍጣር ሰዓት ይለቀቃል!
+9
"በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የራስ ገዝነት ጉዞ ዙሪያ ጥያቄ አለዎት?" በሚል መነሻ የማህበረሰቡን ቅሬታ ለዩኒቨርሲቲው ለማድረስ ሐሳብ እያሰባሰበ መሆኑን የገለፀው ቲክቫህ Magazine ካወጣው ማስታዎቂያ ቡሃላ ህብረታችንን ጨምሮ ብዙ ሙስሊም ተማሪዎች እና የሰብዓዊ መብት ተቆርቋርዎች ዩኒቨርሲቲው ባወጣው ጨቋኝ መመሪያ ዙሪያ ቅሬታቸውን ልከዋል::
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
እንደሚታወቀው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከሕግም ከሞራልም ውጭ ሆኖ ኒቃብ እና የጀመዓ ሶላትን የሚከለክል መመሪያ አውጥቷል!
••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ለምን እንዳወጣ ጥያቄ አለንና ጥያቄያችንን ሁላችሁም ልታቀርቡ ይገባል:: የጥያቄ ሳምፕል ከላይ ተያይዟል:: ጥያቄዎችን ለማቅረብ @tikvahmagbot ይጠቀሙ።
የላካችሁበትን Screenshot አድርጉና @Aaumuslimstudentsunion1 ላኩልን::
መብት በትግል እንጅ በልመና አይገኝም!
ነፃነት በነፃ አይገኝም!
የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ የዚህ ትውልድ አደራ ነው!
@aaumsu
