en
Feedback
Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union

Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union

Open in Telegram

This is the official Channel of Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union.

Show more
4 479
Subscribers
+324 hours
-27 days
+2930 days
Posts Archive
"የሙስሊሞች ጉዳይ ያላሳሰበው ከኛ አይደለም" - ነብዩ ሙሐመድ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) https://t.me/EHEMSU

"በጁምዓ ምክንያት ጧት 5:30 የሚጀምረው የመውጫ ፈተና ወደ 7:30 ... ተቀይሯል::" የሚል ዘገባን ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ጧቱን ሰርቷል:: የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት አመሻሹን ባወጣው
+1
"በጁምዓ ምክንያት ጧት 5:30 የሚጀምረው የመውጫ ፈተና ወደ 7:30 ... ተቀይሯል::" የሚል ዘገባን ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ጧቱን ሰርቷል:: የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት አመሻሹን ባወጣው ማስታዎቂያ ደግሞ ምንም አይነት የሰዓት ለውጥ አልተደረገም ብሏል:: ፈተናውን ከየት አምጥተው ሊፈትኑት ነው? ወይንስ ባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ከሌሎች የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች የተለዬ ነው? የማይሰማ የለ! ብቻ ግን በሕግ እንደተፃፈው እና ትምህርት ሚኒስቴር እንዳፀናው ጁምዓ ቀን ከ5:30-7:30 በመንግስት መስሪያ ቤቶች ስራም ሆነ ትምህርት የለም:: ሰዓቱ የጁምዓ ነው:: https://t.me/EHEMSU

ይህ የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ይፋዊ የቴሌግራም ቻናል ነው:: በቻናሉ ከዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጋር ተያያዥነት ያላቸው ጉዳዮች እና የህብረቱ የዕለት ተዕለት ክዋኔዎች ይቀርባሉ:: በአላህ ፍቃድ እና እርዳታ ከዚያም ከሙስሊም ተማሪዎች ጋር በሚኖር መናበብና መተጋገዝ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያሉ ሙስሊም ተማሪዎች መብታቸው ተከብሮ ይማሩ ዘንድ እንተጋለን:: መረጃዎች ለሁሉም የማህበረሰብ ክፍል ይደርሱ ዘንድ ቻናሉን ለወዳጅ ዘመድዎ ያጋሩ:: @EHEMSU @EHEMSU @EHEMSU @EHEMSU @EHEMSU @EHEMSU @EHEMSU @EHEMSU @EHEMSU

የነገ Exit Exam ተፈታኝ ተማሪዎችን ሁሉ መልካም ጁምዓ እና ፈተናን ተመኘን:: አላህ ለስኬት በር ከፋች ያድርግላችሁ:: https://t.me/EHEMSU

NOTE: ስለ መውጫ ፈተናው የሰዓት መቀየር ትምህርት ሚኒስቴር መግለጫ ከማውጣቱ በፊት እንደ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ "ሰዓቱ አልተቀየረም!" እና ወሎ ዩኒቨርሲቲ "ፈተናው 7:00 ነው የሚጀምረው!" አይነት መግለጫዎች ነበሩ:: ሆኖም በዚህ ጉዳይ ያናገርናቸው የከፍተኛ ት/ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ፕሬዚዳንት ሓይሎም ስዩም በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ፈተናው 7:30 እንደሚጀምር አሳውቀዋል:: መረጃውን ላልሰሙት አሰሙ! https://t.me/EHEMSU

የExit Exam ሰዓት ለውጥ እንደተደረገ ትምህርት ሚኒስቴር በይፋ አሳውቋል:: ፍትሐዊ እና ጥራት ያለው ትምህርት ለሁሉም! https://t.me/EHEMSU
የExit Exam ሰዓት ለውጥ እንደተደረገ ትምህርት ሚኒስቴር በይፋ አሳውቋል:: ፍትሐዊ እና ጥራት ያለው ትምህርት ለሁሉም! https://t.me/EHEMSU

ጁምዓ ሶላት ኒቃብ እና ጀመዓ ሶላት ••• በትምህርት ተቋማት! ከ5:30-7:30 በጁምዓ ቀን ትምህርት መስጠት የማይፈቀድ መሆኑ በተደጋጋሚ ቢገለፅም ከወረቀት ባሻገር ትምህርት ሚኒስቴር በተማሪዎች ጥያቄ መሠረት ለመውጫ ፈተና ያወጣውን ፕሮግራም መቀየሩ ማረጋገጫ ነው:: እንደዚህ ከሆነ ሕግን ጥሰው ለምን በጁምዓ ሰዓት ያስተምራሉ የሚል ጥያቄ ከተነሳ መልሱ እነርሱ በጥላቻ እና በእብሪት ሰክረው ለመተንኮስ እና ለመረበሽ ሲሞክሩ ዝም ስላልናቸው ይሆናል:: ኒቃብ ለብሶ መማር የሚከለከል ነገር እንዳልሆነ በተደጋጋሚ ቢገለፅም እንደ ማስረጃ ግን በዲላ ያለፈው ክስተት ጥሩ ነው:: ለምን ይከለክላሉ የሚል ጥያቄ ከተነሳ መልሱ እነርሱ ከሕግ ውጭ ሲንቀሳቀሱ በሕግ አግባብ የሚታገላቸው ሙስሊም ተማሪ ስለሌለ ይሆናል:: በትምህርት ቤት ቅጥር ግቢ ውስጥ መስገድ መብት ነው የሚል ሙግት ቢኖርም በተግባር ግን በሸይኻ ፋጢማ ትምህርት ቤት አይተናል:: ከሕግ ውጭ ሆነው ጫና ቢያሳድሩም በሕግ አግባብ በተደረገ ትግል ተማሪዎቹ የመስገጃ ቦታ ተሰጥቷቸው እየሰገዱ ይገኛል:: እነዚህ የዚህ አመት ክስተቶች መብቶቻችንን ምን እንደሆኑ ለምን ሊነጥቁን እንደሚፈልጉ እና እንዴት መውሰድ እንደምንችል አሳይተውናል:: መስገድ መብት ነው:: መልበስ መብት ነው:: በነፃነት መኖር ክብር ነው:: ለምን ይከለክላሉ የሚል ጥያቄ ከተነሳ ከነፃነት ዝቅ አድርገው ክብርን ለመግፈፍ ይሆናል መልሱ:: እንዴት ይስተካከል ከተባለም ሳይሰለቹ ሳይደክሙ ሳይታክቱ በመታገል ይሆናል መልሱ:: ነፃነት በነፃ አይገኝም! መብት በትግል እንጅ በነፃ አይገኝም! https://t.me/EHEMSU

አርብ እለት በሚሰጠው ፈተና ላይ የጁሙአ ሰላትን ምክንያት በማድረግ በትምህርት ሚኒስቴር የሰአት ማሻሻያ ተደርጓል:: " ሰመራ ዩኒቨርሲቲ" https://t.me/EHEMSU
አርብ እለት በሚሰጠው ፈተና ላይ የጁሙአ ሰላትን ምክንያት በማድረግ በትምህርት ሚኒስቴር የሰአት ማሻሻያ ተደርጓል:: " ሰመራ ዩኒቨርሲቲ" https://t.me/EHEMSU

የExit Exam የመፈተኛ ሰዓት ለጁምዓ እንደተቀየረ ድሬ ዳዋ ዩኒቨርሲቲ: ደብረ ብርሐን ዩኒቨርሲቲ እና ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ አሳውቀዋል::
+2
የExit Exam የመፈተኛ ሰዓት ለጁምዓ እንደተቀየረ ድሬ ዳዋ ዩኒቨርሲቲ: ደብረ ብርሐን ዩኒቨርሲቲ እና ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ አሳውቀዋል::

እርስዎ በሚማሩበት ትምህርት ቤት በጁምዓ ቀን
Anonymous voting

Guyyaa Jumu'a fi qormaataa bahimsaa( Exit Exim) UPDATE! •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• Ministeerri barnoota mirga barattootaa cabsun guyyaa jumu'aa qormaata bahumsaa(Exit Exam) keennu waan yaadef gamtaan keenya xalayaa komii galchuu isaa nii beekamaa. Kanumarran kan ka'ee bakaa bu'oota gamtiichaa guyyaa har'aa deebi waajjira ministeera de'taa dhaabbilee barnoota olaanoo ministeera barnootaarraa isaanitti keennamen jijjirraa sagantaa akka godhee beeksiiseera. Haaluma kanaan Qormaanni bahumsaa jumu'aa dhuufu sa'ati 7:30-10:00 akka tahuu ibseera. Kunis qaamota dhimmichi isaan ilaallatutti akka beeksiisan ibsaniru. ta'us hanga ammatti beeksiisa ifaan wanta ibsan hin jiru. Nutis haaloota jiran hordoofun sirreessuf kan hoojjannu ta'u isaa ni beeksiisnaa. Gamtaa barattoota Musliimaa dhaabbiilee olaanoo Ityophiyaa! https://t.me/EHEMSU

ጁምዓ እና የመውጫ ፈተና (Exit Exam) UPDATE! •••••••••••••••••••••••••••••••••••••• የትምህርት ሚኒስቴር በጁምዓ ቀን የተማሪዎችን መብት በመጣስ ከ5:30 - 8:00 የመውጫ ፈተና ለመስጠት ማሰቡን ተከትሎ ህብረታችን ለሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የቅሬታ ደብዳቤ  ማስገባቱ ይታወቃል:: ይህንንም ተከትሎ የህብረቱ ተወካዮች በዛሬው እለት ከትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚኒስቴር ዴኤታ ፅ/ቤት በተሰጣቸው መልስ በፕሮግራሙ ላይ ማስተካከያ እንዳደረጠ አሳውቋል::  በዚህም መሠረት በመጪው ጁምዓ የሚሰጠው Exit Exam ከ7:30-10:00 እንደሚሆን ገልፇል:: ይህንንም ለሚመለከታቸው አካላት እንዳሳወቁ ገልፀውልናል:: ሆኖም ግን እስካሁኑ ሰዓት ድረስ በይፋ ማስታዎቂያ ያሳወቀው ነገር የለም:: እኛም የሚኖሩ ሁነቶችን እየተከታተልን ለማስተካከል የምንሰራ መሆናችንን እንገልፃለን:: የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት!

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተናን (Exit Exam) በመጪው አርብ በጁምዓ ሰዓት ማለትም ከ5:30-8:00 ለመስጠት ያወጣውን ፕሮግራም
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የትምህርት ሚኒስቴር የመውጫ ፈተናን (Exit Exam) በመጪው አርብ በጁምዓ ሰዓት ማለትም ከ5:30-8:00 ለመስጠት ያወጣውን ፕሮግራም እንዲቀይር ጠየቀ! ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ጥር 27 / 2017 ዓ.ል •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ህብረቱ ለትምህርት ሚኒስቴር ባስገባው ደብዳቤ ጁምዓ የሙስሊሞች ሳምንታዊ በዓል መሆኑንና ከ5:30-7:30 በሀገር ደረጃ የመንግስት መስሪያ ቤቶች እረፍት መሆናቸውን ጠቅሶ በዚህ ሰዓት የፈተና ፕሮግራም ማውጣት የሙስሊም ተማሪዎችን እሴቶችን እና መብቶችን መጋፋት እንደሆነ ገልፇል:: መሠል ጥፋቶች መደጋገማቸው ሙስሊሙን ተማሪ ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሚያራርቁ በመሆናቸውም ተመሳሳይ ችግሮች በዘላቂነት እንዳይፈጠሩ መስመር እንዲደረገም ጠይቋል:: የደብዳቤው ግልባጭ ለፌደራል እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት እና በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ገብቷል:: https://t.me/EHEMSU

በቅድመ 1966 ዓ.ል የነበሩ አባቶቻችን ስለ ጁምዓ ቀን የነበራቸው ጥያቄ ከስራ ውጭ እንዲሆን አልያም ከ5:30 - 9:00 ክፍት እንዲሆን ነበር:: የዚያኔ ባይሳካም ጥረታቸው ፍሬ አፍርቶ በ1985 ዓ.ል በሽግግር መንግስቱ ከ5:30 - 7:30 ከስራ ውጭ ይሁን የሚል ተወሰነ:: ሆኖም ግን በሕግ ፀና የተባለውን መብት ከ32 አመታት ቡሃላ ጥሶ ት/ሚኒስቴር በጁምዓው ቀን ከ5:30-8:00 ሰዓት ፈተና ካልፈተንኩ እያለ ነው:: ይህ ትውልድ መሠል ጥፋቶችን ችላ ብሎ የሚያልፍ ከሆነ በአባቶቹ ትግል ላይ አፈር ከመነስነሱም ባሻገር ሀላፊነቱን በራሱ እጅ መቅበርም ነው:: በቃ ሊባል ይገባል:: በቃን እስኪሉ ድረስ! https://t.me/EHEMSU

ት/ሚኒስቴር Exit Examን በጁምዓው ከ5:30 - 8:00 ለመስጠት እንደወጠነ ነው:: እዚህጋ ጥያቄ አለን ••• የሚፈተን ሙስሊም ተማሪ የላቸውም? ወይንስ ጁምዓ ለሙስሊም ምን ማለት እንደሆነ አያ
ት/ሚኒስቴር Exit Examን በጁምዓው ከ5:30 - 8:00 ለመስጠት እንደወጠነ ነው:: እዚህጋ ጥያቄ አለን ••• የሚፈተን ሙስሊም ተማሪ የላቸውም? ወይንስ ጁምዓ ለሙስሊም ምን ማለት እንደሆነ አያውቁም? ወይንስ በጁምዓ ቀን ከ5:30 - 7:30 የመንግስት ስራ ዝግ እንደሆነ አያውቁም? ወይንስ ምንም ቢፃፍ ምንም ቢሆን ሙስሊሙ ተማሪ ከትምህርቱ እና ከጁምዓው መምረጥ አለበት? ዘላቂ መፍትሔ ያሻል ••• ይህ የመጀሪያ ስህተታቸው አይደለም ••• የሪሜዲያል ተማሪዎችን ፈተና ከዒድ ጋር አድርገው ብዙ ተማሪ ላይ ተፅዕኖ መፍጠራቸው የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ነው:: https://t.me/EHEMSU

የትምህርት ሚኒስቴር Exit Examን በጁምዓ ሰዓት አድርጓል! ጁምዓ ቀን በመንግስት መስሪያ ቤቶች ደረጃ ከ5:30 - 7:30 ለስግደት በሚል ዝግ እንደሆነ ይታወቃል:: የፌደራል መጅሊስ በቅርቡ በሰ
የትምህርት ሚኒስቴር Exit Examን በጁምዓ ሰዓት አድርጓል! ጁምዓ ቀን በመንግስት መስሪያ ቤቶች ደረጃ ከ5:30 - 7:30 ለስግደት በሚል ዝግ እንደሆነ ይታወቃል:: የፌደራል መጅሊስ በቅርቡ በሰጠው ፈታዋም የጁምዓ ሶላት የደረሰበት ማንኛውም ሙስሊም ወደ መስጂድ ሄዶ መስገድ ግዴታው እንደሆነ አሳውቋል:: ሆኖም የትምህርት ሚኒስቴር የመውጪያ ፈተናን በመጪው ጁምዓ ከ5:30 - 8:00 ለመስጠት ፕሮግራም አውጥቶ ሙስሊም ተማሪዎችን ከጁምዓ ሶላትና ከፈተናቸው እንዲመርጡ የሚያስገድድ ሁኔታ ፈጥሯል:: ይህ ሀገራችንን የምትመራበትን መመሪያ መጣስ ብሎም የሙስሊም ተማሪዎችን መብት መዳፈር ነው:: በትምህርትም ሆነ በፈተና ፕሮግራም ከትምህርት ሚኒስቴርም ሆነ ከዩኒቨርሲቲዎች ወይንም ከበታች ትምህርት ቤቶች በተደጋጋሚ የሚፈፀሙ የመብት ጥሰቶች በዘላቂነት ሊፈቱ ይገባል:: ካላንደር ከሌላቸው ወይንም ስለሙስሊሙ መሠረታዊ መብቶች እውቀቱ ከሌላቸው እንዲያውቁ ይደረጉ:: እየረሱ ወይንም ሆን ብለው እያበላሹ ከሆነ ደግሞ መንግስት ብዙም የማይረሳና የማያበላሽ ሰው በቦታው ላይ ያስቀምጥ:: @MohammadamminKassaw

በረመዳን ውስጥ እንደ ዩኒቨርሲቲ መቅረብ ያለባቸው አገልግሎቶች:- ■ረመዳን ሲደርስ ሙስሊም የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መደበኛው አገልግሎት ከወሩ ጋር እንዲገጥም ተደርጎ ሊቀርብላቸው ይገባል:: ይህ በሀገራችንም ሆነ በሌላው አለም በሚገኙ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚቀርብ ቢሆንም ሀገራችን ውስጥ የሚገኙ አንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች ሲያጓድሉ ይስተዋላል:: ለመሆኑ በረመዳን ወር ምን አይነት ዝግጅት ሊኖር ይገባል? እንደ ሞዴል በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ያለውን አስቀምጠን እንይ:- • የምግብ ሰዓት:- የረመዳን ፆም የሚታሰረው ከሌሊቱ 9:30 ጀምሮ እስከ 11:00 በመሆኑ የግቢው ካፌ በዚያ ሰዓት ተከፍቶ ለተማሪዎች አገልግሎት ይሰጣል:: በመቀጠልም ለኢፍጣር ሰዓት ከ12:00 ጀምሮ እስከ ምሽቱ 1:30 ድረስ ክፍት ይሆናል:: • የምግብ አቅርቦት:- በተለምዶው ይቀርብ ከነበረው ሶስት የምግብ ፕሮግራም አንድኛው ተቀንሶ ሁለት ስለሚሆን እንዲሁም ጧት ላይ ለቁርስ የሚቀርበው ሻይ ስለማይኖር በአፍጥር ሰዓት ሾርባ ጭማሬ ሆኖ ይቀርባል:: አንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች ደግሞ ቴምር ጭምር ያቀርባሉ:: • የግቢ በር:- በመጀመሪያዎቹ 20 ቀናት ለተራዊህ ሶላት የግቢ በር እስከ 4:30 የሚከፈት ሲሆን በመጨረሻዎቹ 10 ቀናት ለተሐጁድ ሶላት ከ8:00 ጀምሮ ክፍት ይሆናል:: ■ ይህ አገልግሎት በብዙሐኑ የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች የሚሰጥ ቢሆንም አንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች ግን ስሁር የማያቀርቡ ወይንም ለስሁር ተማሪዎች እንዲያበስሉ የሚያደርጉ እንዲሁም የግቢ በር ሌሊት የማይከፍቱ አሉ:: ይህ እምነቱን ጠብቀው ሊያገለግሉት እና ሊያስተምሩት የተቀበሉትን ሙስሊም ተማሪ መብት መጣስ ሲሆን ሊስተካከል የሚገባ ነው:: ረመዳንም አንድ ወር እና ጥቂት ቀናት ብቻ የቀሩት ሲሆን ከአሁኑ ጊዜ ጀምሮ እንዲስተካከል መሠራት አለበት:: አላህ በሰላም ደርሰው ከሚፆሙት እና ከሚጠቀሙበት ያድርገን! https://t.me/EHEMSU

"መሠል ጥፋቶች በሙስሊም ተማሪዎች ላይ ዳግም እንዳይፈጠሩ ሙስሊም ተማሪዎች ጅልባብንም ጠቅሶ ሙሉ ሰውነታቸውንና ፀጉራቸውን የሚሸፍን ልብስ መልበስ ይችላሉ የሚል አንቀፅ ምክር ቤታችን ማውጣት የለበትም ወይ?" - ዶ/ር ኤሊያስ ለፓርላማ ያቀረቡት ጥያቄ ••• የትምህርት ሚኒስቴር በሚያወጣቸው መመሪያዎች ላይ እንደሚያይበት ከፓርላማው መልስ ተሰጥቷል:: ትምህርት ሚኒስቴር የሚያወጣውን መመሪያ ደግሞ የምናይ ይሆናል:: https://t.me/EHEMSU

"ኒቃብ ነው ወይንስ ሒጃብ የተከለከለው?" ብለው በመጠየቅ ኒቃብ እና ሒጃብን በመለያየት ጀምረው ኒቃብ ከሆነ የተከለከለው ሱና ስለሆነ ችግር የለውም ወደሚል መስመር መግባት የሚፈልጉ የእኛው ሰፈር ሰዎች ብዙሐን ናቸው። ልብ ሊባል የሚገባው ኒቃብ ሱናም ሆነ ዋጂብ ሊሆን ይችላል። እንደ ትምህርት ተቋም ስናወራ ግን that is not our ajenda.  እዚህጋ ሊሰመርበት የሚገባው ይሆነኛል ብላ የለበሰችው የትኛውም አለባበስ መብቷ ነው የሚለው ላይ ነው። ሙስሊምነትን አስታኮ ለሚመጣ የመብት ጥያቄ ደግሞ ከጀሰዲን ዋሂድ ሆኖ ሁሉም መቆም አለበት። ኒቃብ ለባሿም ሆነች የማትለብሰዋ: ሴቷም ሆነች ወንዱ ጥያቄው የመብት ነውና በአንድነት ሊሰለፍ ይገባል። https://t.me/EHEMSU