en
Feedback
Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union

Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union

Open in Telegram

This is the official Channel of Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union.

Show more
4 479
Subscribers
+324 hours
-27 days
+2930 days
Posts Archive
እርስዎ በሚማሩበት ዩኒቨርሲቲ
Anonymous voting

እርስዎ በሚማሩበት ዩኒቨርሲቲ
Anonymous voting

እርስዎ በተማሩበት/በሚማሩበት 1ኛ 2ተኛ ደረጃ ት/ቤት ከሶላት ጋር ተያይዞ ያለው ሁኔታ ምን ይመስላል?
Anonymous voting

እርስዎ በሚማሩበት/በተማሩበት 1ኛ እና 2ተኛ ደረጃ ት/ቤት በአለባበስ ዙርያ ለሙስሊም ተማሪዎች ያለው ሁኔታ እንዴት ነው?
Anonymous voting

የሸዕባን ወር ትሩፋቶች... https://t.me/EHEMSU

ሒጃቧ - እምነቷ! ታምነዋለችና እንደሚጠብቃት፥ ጀነትን ደግሶ፣ ትታዘዘዋለች የጌታዋ ፍቅር፥ በልቧ ላይ ነግሶ። ልበሺው እንዳላት አላመነታችም፥ ቃሉን ስትቀበል፣ ሙስሊም መሆን ማለት ላንዱ ጌታ ትዕዛዝ፥ እጅ መስጠት አይደል?! ላፍታ ዝንፍ አትል ትዕዛዙ እምነቷ ነው፥ አትሽረው በዋዛ ድርድር እንዳትቀርብ የምድር ኃይል የለም፥ እምነት የሚገዛ። ጽናት ልቅናዋን በመ'ሸፈኗ አ'ርጎ፥ ከፍጥረት ቢመርጣት፣ አይፈቀድለትም ፍጡር ጣልቃ ገብቶ፥ ከመንገድ ሊያወጣት። https://t.me/EHEMSU

በዲላ ዩኒቨርሲቲ በኒቃባቸው ምክንያት ከትምህርት ከምግብ እና ከዶርም አገልግሎት ለ10 ቀናት የተስተጓጎሉ ሙስሊም ተማሪዎች የማካካሻ ትምህርት (ቲቶርያል) እንደሚሰጣቸውና ያለፋቸውን ፈተና ሁሉ እንደ
በዲላ ዩኒቨርሲቲ በኒቃባቸው ምክንያት ከትምህርት ከምግብ እና ከዶርም አገልግሎት ለ10 ቀናት የተስተጓጎሉ ሙስሊም ተማሪዎች የማካካሻ ትምህርት (ቲቶርያል) እንደሚሰጣቸውና ያለፋቸውን ፈተና ሁሉ እንደሚፈተኑ ADDIS STANDARD የሙስሊም ተማሪዎች ህብረት አሚርን ዋቢ አድርጎ ባወጣው ዘገባ አሳውቋል:: Well done😍 ሙሉ ዘገባውን ለማንበብ:- https://addisstandard.com/muslim-students-at-dilla-university-resume-studies-after-agreement-lifts-niqab-ban/?fbclid=IwZXh0bgNhZW0CMTEAAR1yXH0zqZrum0pQgMlDDvz2s6ejcHuvXE0ajKQgpK_CT_k_AE531Tf-vY8_aem_fUXGYoSPC9jDWZZA_4skkg&amp=1 @MohammadamminKassaw

ሒጃቧ - ታሪኳ! ታሪክ ያላውቁ ከትላንት የመጣ፥ አይሻገርም ቢሉ፣ ለብሳው ትዞራለች ቁጭት የወለደው፥ የነፍሷን ጣር ሁሉ። የመረረ ትግሏ የጽናት ትርጉሙ፥ ገጹ ላይ ያለበት፣ ሒጃቧ ድርሳን ነው የአያቶቿ ገድል፥ የሚዘከርበት። ድርሳኑ ሲገለጥ አሉ ቀደምቶቿ፥ ገዝፈው የተጠሩ፣ ስለክብሯ ብለው ሠራዊት ለማዝመት፥ ያላንገራገሩ። ድርሳኑ ሲገለጥ የአባቷ አደራ አለ፥ ሲሞት ያቀበላት፣ የዘመናት ትግሌን በዘመንሽ ሁሉ፥ "ለብሰሽ ኑሪ" ያላት። ድርሳኑ ሲገለጥ የእናቷ ቃል አለ፥ በደም የጻፈችው፣ ባልተመቸ ጊዜ ከማውለቅ በስተቀር፥ የማይቻለውን ሁሉ የቻለችው። https://t.me/EHEMSU

#Update “ በቋሚነት ይሁን ለጊዜው የተብራራ ነገር የለም፡፡ አሁን ግን ተማሪዎቹ ገብተው ትምህርታቸውን መማር ጀምረዋል ” - የዞኑ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴት ሙስሊም ተማ
+1
#Update “ በቋሚነት ይሁን ለጊዜው የተብራራ ነገር የለም፡፡ አሁን ግን ተማሪዎቹ ገብተው ትምህርታቸውን መማር ጀምረዋል ” - የዞኑ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች በአለባሳቸው ሳቢያ ግቢ እንዳይገቡ በመከልከላቸው፣ ከትምህርት፣ ከካፌና ከማደሪያ ውጪ መሆናቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታ ማቅረባቸው አይዘነጋም፡፡ ተማሪዎቹ በሰጡት ቃል፣ " 44 ሴት ተማሪዎችን ጥቁር ማስክ አድርጋችሁ 'አናስገባም' ብለው፣ ኒቃብ የለበስን 7 ሴቶችንም ከልክለውን ውጪ አደርን " ነበር ያሉት። ለቅሬታው ምላሽ የጠየቅነው ዩኒቨርሲቲው፣ እንደ ሁሉም የሀገሪቱ ዩኒቨርሲቲዎች ሁሉ በሴኩላሪዝምና ብዝሃ ሃይማኖትን ተረድቶና አክብሮ የሚሰራ ተቋም እንደሆነና ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ እንዳይለብሱ እንዳልተከለከለ ኒቃብ ደግሞ አስቀድሞም በዩኒቨርሲቲ እንደማይደረግ ገልጾ ነበር። ተማሪዎቹ ግቢ እንዲገቡ ተፈቀዳላቸው ? ወደ ግቢ ገባችሁ ወይስ አሁንም ከግቢ ውጪ ናችሁ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ ያቀረበላቸው ተማሪዎቹ፣ " ለጊዜው ከስምምንት ተደርሷል " ሲሉ መልሰዋል። " በተወካዮቻችን በኩል ኒቃብ፣ ማስክና ሂጃብ ለብሰን መግባት እንደምንችል ተነገረንና ትላንት ገብተናል " ብለዋል። በስምምነቱ መሰረት ለብሰው እንዲገቡ ከመነገራቸው ውጪ ሌላ የተባሉት ነገር እንደሌለ አስረድተው፣ " ለጊዜው ግን ግቢ ገብተናል " ነው ያሉት፡፡ በደብዳቤ ጭምር በመጠየቅ ጉዳያቸውን ሲከታተል የቆየውን የጌድኦ ዞን እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤትንም ግቢ እንደይገቡ ተከልክለው የነበሩ ተማሪዎች ወደ ግቢ ገብተዋል ? ስንል ጠይቀናል፡፡ የዞኑ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ምን አለ ? " በቋሚነት ይሁን ለጊዜው የተብራራ ነገር የለም፡፡ ግን ተማሪዎቹ ገብተው ትምህርታቸውን መማር ጀምረዋል፡፡ በዘላቂነቱ ላይ እንደ አገር የሚያዝ አቅጣጫ ይኖራል፡፡ ከዚያ ውጪ ግን ይሄ ነው ተብሎ የተገለጸ ነገር የለም፡፡ ሲጀመር ክልከለውን በተመለከተም በፅሑፍ የተገለጸ የለም፡፡ አሁን ሲፈቀድም በተመሳሳይ ነው፡፡ አገራችን የብዙ ሃይማኖቶችና ብሔሮች መገኛ ስለሆነች ስርዓቶችም ሃይማኖቶችን፣ ብሔር ብሔረሰቦችን ያማካሉ ቢሆኑ፤ ለአንዱ እድል ሰጥቶ ሌላኛውን ያላገለሉ፣ ሃይማኖት ባሉ ነገሮች ምክንያት በሌሎች ቦታዎችም ሁሉን ያማከለ ሆነው ቢወጡ የተሻለ ነው፡፡ የጥብቅ ደን/ብዙ እፅዋቶችን አንድ ላይ ነው በማልማት የሚታወቀውና እንደ አገርም ቅርስ የተያዘለት ማህበረሰብ ያለበት ዩኒቨርሲቲም ስለሆነ ነገሮች ሲከናወኑ በዚያ ቢታሰቡ እጅግ መልካም ይሆናል " ብሏል፡፡ የተደረሰውን ስምምነት በተመለከተ ማብራሪያ ለማግኘት የተደረገው ሙከራ የዩኒቨርሲቲው አካላት ስልክ ለማንሳት ፈቃደኞች ባለመሆናቸው ለጊዜው ሃሳባቸውን ማካተት አልተሳካም፡፡ #TikvahEthiopiaFamilyAA @tikvahethiopia

"መብቴ እንዲከበር ምን ላድርግ?" ከሆነ ጥያቄህ "እስኪከበር ድረስ ጩህ!" የመጀመሪያው መልስ ነው:: ከዚያ ባሻገር ሳይሰለቹ መማር መማር መማር መማር ያስፈልጋል:: የሀገሪቱን 50% እሸፍናለሁ የሚል ህዝብን ወክሎ 20% ሳይሞላ ከትምህርት ተቋማት የሚገባ ተማሪ ሊተኛ  ሊያርፍ ሊዘናጋ አይገባም:: ውጭ ያሉ ወገኖቹንም ጭምር ደጋግሞ መማር አለበት:: እነርሱ ተጠቃለው እንዲማሩም መስራት አለበት:: እየጮኸ ••• እያነቃ ••• እየነቃ ••• እየሰራ ••• እየተጋ ••• እየተማረ ••• እያስተማረ ማለት ነው:: https://t.me/EHEMSU

በዲላ ዩኒቨርሲቲ ኒቃቢስቷ ለብሳ እየተማረች ነው! በመቱ ዩኒቨርሲቲ ኒቃቢስቷ ለብሳ እየተማረች ነው! በመዳወላቡ ዩኒቨርሲቲ ኒቃቢስቷ ለብሳ እየተማረች ነው! በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ኒቃቢስቷ ለብሳ እየተማረች ነው! በወራቤ ዩኒቨርሲቲ ኒቃቢስቷ ለብሳ እየተማረች ነው! በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ኒቃቢስቷ ለብሳ እየተማረች ነው! • • • • ግን ጂማ ዩኒቨርሲቲ ኒቃቧን ለብሳ መማሯን ከልክሏል! ግን አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኒቃቧን ለብሳ መማርን የሚከለክል መመሪያ አፅድቋል! • • • ግን ••• መብቷ ሊጠበቅ ይገባል:: መብቷን መንፈግ ኢ-ሰብዓዊነት ነው:: ከሕገ-መንግስት ውጭ ነው:: የሐይማኖት ነፃነት መብቷን ይጋፋል:: ፍትሕ ያስፈልጋታል:: ነፃነቷን ትሻለች:: እኩልነትን ትፈልጋለች:: መብቷ መጠበቁን የሚገልፅ መመሪያ ያስፈልጋል:: መብቷ ሲጣስ ከለላ የሚሆናትና አጥፊዎችን የሚቀጣ መመሪያ ያስፈልጋል:: ፍትሕ ለኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች! https://t.me/EHEMSU

በ2017 ዓ.ል በመዳ ወላቡ ጎባ ካምፓስ ላይብረሪ ውስጥ ለአመታት ተለብሶ መግባት ይከለከል የነበረው ኒቃብ በተማሪዎች ትግል ተስተካክሏል:: በመቱ ዩኒቨርሲቲ በደሌ ካምፓስ ከ2 አመታት በፊት አንድ ኒቃቢስት የተባረረችበትና ከዚያም ቡሃላ ይከለከል የነበረው ኒቃብ በተማሪዎች ትግል ተስተካክሏል:: በዲላ ዩኒቨርሲቲ ኒቃብ ተከልክሎ ከወር በላይ ቢቆይም በተማሪዎች ንቅናቄ ተስተካክሏል:: በሰላሌ ዩኒቨርሲቲ በግል ደረጃ እንኳ ሶላት መስገድ ተከልክሎ የነበረ ቢሆንም በተማሪዎች ትግል ዶርም ውስጥ መስገድ ተችሏል:: ሆኖም አሁንም ትግል ውስጥ ናቸው:: •••• እነዚህ ብዙ ልንማርባቸው የምንችልባቸው የትግል ውጤቶች ናቸው:: ተሳኩ ተብሎ መርካትና መቀመጥ ስንፍናን መውረስ ነው:: ካለፈው ልምድና ትምህርት ወስዶ ሁሉም ቦታ ከሙስሊም ጠልነት ፀድቶ የሙስሊም ተማሪዎች ሕገ-መንግስታዊ መብት እስኪከበር ድረስ መትጋት ያስፈልጋል:: መብትን አጥንቶ ማወቅ ••• ዋጋውን መረዳት ••• ለመታገል መቁረጥ እና በቁርጠኝነት ማስከበር ያስፈልጋል:: ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እስከ ጅማ ድረስ ያሉ ችግሮች ብሎም በመላ ሀገሪቱ ያሉ የመብት ጥሰቶች በዘላቂነት በመመሪያ እና በተግባር መከበር አለባቸው::

ወሎ ኮምቦልቻ 2ተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በኒቃብ ምክንያት ከፈተና የታገዱ ተማሪዎች ወደ ፈተና እንደተመለሱ ሰምተናል:: ሆኖም ግን ከት/ቤቱ አመራሮች ሕገ-ወጥ የሆኑ ዘለፋዎች እየደረሱባቸው ነው:: ከአሁን ቡሃላ ባለው ችግሩ በዘላቂነት እንዲፈታ በየትኛውም አካባቢ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የመብት ጥሰት የሚፈፅሙ አካላት አስተዳደራዊ እርምጃ እስኪወሰድባቸውና በሕግ አግባብ እስኪጠየቁ ድረስ መትጋት ያስፈልጋል:: አለዚያ እነርሱ በሰከሩ ቁጥር የስካራቸው ማስታገሻ ማድረጋቸው አይቀርም:: ከአቅል ርቀው ለመበደል ወደሗላ ያላሉትን በሐቅ ላይ ሆነን ፍትሕ እንዲሰፍን ማድረግ አለመቻል ታሪካዊ ክስረት ነው:: መብቶቻችንን በየቦታው እንጠይቅ ••• ለመብቶቻችን እንታገል ••• እስከ ፍትሕ ••• እስከ ነፃነት ••• እስከ መከባበር! https://t.me/EHEMSU

Mana barumsa sadarkaa 2ffaa kombolchaa barattoota mutanaqqiiba Qormaata irraa dhorkee! ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• Walloo kombolchaatti kan argamu manni barumsa sadarkaa 2ffaa kombolchaa niqaaba kanaan duraa biliisaan uuffatamaa turee yeroo qormaata eegun dhorkeera. Guyyaa har'aa barattoonni qormaata waligalaa yeroo fudhatan "Niqaaba ykn qormaata" filadhaa jeechun, qormaatarraa ala akka ta'an godhamaniiru. barattoonni cunqursaa fi reebamu irra deeddibin isaanirratti gahaa jiru majliisa dablatee qaamni dhimmicha ilaallatu dhimmicha furmaata akka argatuu akka goodhu gaafataniru. https://t.me/EHEMSU

ከሒጃቡ ጀርባ ••• በየዘመኑ ላይ ድንገት የሚያገረሽ፥ ይህ ነው ያልተባለ፣ እስከዛሬ ድረስ ስሙን ያላወቅነው፥ አንዳች ልክፍት አለ። አንዳች ልክፍት አለ በተማረች ቁጥር፥ ዓይኑን የሚያቀላው ያላለቀ ትርክት ያልተቋጨ ቂሙ፥ ውስጡን የሚበላው። አንዳች ዓመል አለ ለክፋት የታጨ፥ በስውር ጥላቻ፣ የሚያንገበግበው መማርን አስባ፥ መገኘቷ ብቻ። ሠላም ያልፈለገ የመበጥበጥ ሱሱ፥ አቅሉን ያናወዘው፣ ወገኑን ገፍቶ ነው የሀገሩን ዕድገት፥ የኋሊት ያስጓዘው። ታሪክ ያልመከረው በጨርቁ ነው ቢልም፥ ስጋቴ ያየለ ሒጃቡ ሲገለጥ ሒጃብ ያልሸፈነው ብርቱ ጥላቻ አለ። https://t.me/EHEMSU

የወሎ ኮምቦልቻ 2ተኛ ደረጃ ት/ቤት ኒቃብ ለባሽ ተማሪዎችን ከማጠቃለያ ፈተና አግዷል! ••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• በወሎ ኮምቦልቻ የሚገኘው የኮምቦልቻ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከዚህ በፊት በነፃነት ሲለበስ የነበረውን ኒቃብ የፈተና ወቅት ጠብቆ ከልክሏል:: በዛሬው እለትም የማጠቃለያ ፈተና እየወሰዱ የነበሩ ኒቃቢስት ተማሪዎችን "ወይ ከኒቃብ ወይ ከፈተና!" በሚል ማስፈራሪያ ከፈተና ውጭ እንዲሆኑ አድርጓል:: ተማሪዎቹ እየደረሰባቸው ያለው ትንኮሳ እና ግፍ ተደጋጋሚነት ያለው መሆኑን ገልፀው እየደረሰባቸው ያለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት በዘላቂነት እንዲፈታ መጅሊስን ጨምሮ የሚመለከተው አካል ሁሉ እንዲረባረብ ጠይቀዋል::

Gamtaan barattoota musliima Yunivarsiiti diillaa barattoota sababa niqaaba isaanitin barumsa, nyaata fi bakka ittin bulan dhorkamaa turan Akkuma niqaaba isaani uuffataniitti gara barumsa isaani akka deebi'an yunivarsiiticha waliin waligalee! Gamtaan barattoota musliimaa Yunivarsiiti diillaa  ji'oota darbanif dhibamuu fi cunqursaa barattoota dubara musliimaa yunivarsiiticha irratti gahaa turee karaa nagaatin hiikuf yaalaa akka turee ibseera. Qabsoo nagayaa fi marii hoggansa yunivarsiiticha waliin taasifameen guyyaa har'aa barattoota guyyoota kurnan darbanif barumsa, nyaata fi bakka ittin bulan dhorkamaa kan turan  niqaaba isaani uuffatani gara barnoota isaanitti akka deebi'an waligalameera. Barattoota yunivarsiiticha Kun akka ta'uf qabsa'aniifi qaamoonni miirga namooma akka kabajamu tumsa isaani agarsiisan guutu  galeetaffachun, cunqursii mirgaa, barattoota musliimaa yunivarsiiticha irratti qaqqabu kamu fala akka argatuufi mirgii isaani akka kabajamu ciime akka hoojjatu ibseera. https://t.me/EHEMSU

ዲላ ላይ ያሉ ሙስሊም ተማሪዎች መብታቸው መከልከሉ ቆመ ማለት የቤት ስራችን ተጠናቀቀ ማለት አይደለም:: በዲላውም ሆነ በሌሎች ጉዳዮች በሚቀጥሉት ጊዜ ለመብቶቻችን መከበር አስተማማኝ ዋስትና ሊሰጠን የሚችለው የእኛ ጥንካሬ እና ህብረት ነው:: መብቶቻችንን በሌሎች እዝነት ላይ የምናስቀምጠው ከሆነ ሲከፉ ይነጥቁናል:: በሕግ አግባብ እስከ መጨረሻው ለመታገል ከቆረጥን ግን ከአሁኑ ባሻገር ከጅማ: ከጂንካ: በሰላሌ እየደረሱ ያሉ የመብት መገፋቶችን ማስቆም: የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ያወጣውን ኒቃብ የሚከለክል መመሪያ ማስቀየር: ከአጥናፍ እስከ አጥናፍ ከመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ጀምሮ እስከ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚደርሱ በደሎችን ታሪክ ማድረግ ብሎም የትምህርት ሚኒስቴር ለመብታችን እውቅና የሚሰጥ እንዲሁም መብቶቻችን ሲጣሱ የሚጥሱ አካላትን ተጠያቂ የሚያደርግ መመሪያ እንዲያወጣ ማድረግ እንችላለን:: በአላህ ፈቃድ ይህ ትውልድ በትምህርት ቤቶች የሚደርሱትን የመብት መገፋቶች ታሪክ ያደርጋል:: Once again መብት በትግል እንጅ በልመና አይገኝም:: Once again መብት በነፃ አይገኝም:: @EHEMSU   @EHEMSU  @EHEMSU @EHEMSU   @EHEMSU @EHEMSU @EHEMSU    @EHEMSU @EHEMSU

NOTE: ከሒጃብ ከኒቃብም ሆነ ከየትኛውም የሙስሊም ተማሪዎች መብት ጋር ተያይዞ "ተፈቀደ!" የሚልን ቃል አንጠቀም:: መብቶቻችን እንደ እስልምና ግዴታ የተደረጉ እና እንደ ሕገ-መንግስት ደግሞ እውቅና የተቸራቸው ናቸው:: ማንም አካል የመፍቀድ ስልጣን የለውም:: ግን ከሕግ ውጭ ሆኖ ሊከለክል ይችላል:: SO ተፈቀደ በማለት ፋንታ "መከልከሉን አቆመ! ወደ ሕግ ተመለሰ!" የሚሉትን ቃላት እንጠቀመ:: ሁሉም እሳቤ እና ጉዞ ከእሳቤ እና ከቃላት ይጀምራልና:: @EHEMSU