Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union
Open in Telegram
This is the official Channel of Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union.
Show more4 474
Subscribers
-424 hours
-37 days
+2230 days
Posts Archive
+2
ዒድ ••• በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ!
በAAU የጥቁር አንበሳ ካምፓስ ሆስፒታል ከተማሪዎቹ ባሻገር በሆስፒታሉ ካሉ ከ300 በላይ ታካሚዎች ጋር ዒድን አክብሯል!
@MohammadamminKassaw
Eid Mubarak!
Gooftaan Hojii gaggaarii keenna nurraa haa qeebalu. Iidni iida gammachuu kan barakaa isiniif haa ta'u. firaa fi maatii keessa hunda waliin yeroo gaarii.
@EHEMSU
ዒዱኩም ሙባረክ!
ኢዱ ነገ መሆኑ ተረጋግጧል::
ቀሪ ዘመናችሁ እንደ ለይለተል ቀድር ሰላም እና ሰኪና የሞላበት ይሁን !"
@MohammadamminKassaw
የዒድ ቀንን ለመወሰን የሳዑዲ ጠቅላይ ፍ/ቤት ተሰይሟል:: ከደቂቃዎች ቡሃላ ውጤቱ የሚታወቅ ይሆናል::
+6
ሰመራ ዩኒቨርሲቲ ለሙስሊም ተማሪዎች የኢፍጣር መርሐ- ግብር አዘጋጅቷል!
መጋቢት 17/2017 ዓ.ል የሰመራ ዩኒቨርሲቲ የዩኒቨርሲቲውን ፕሬዚዳንት ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ለሙስሊም ተማሪዎች የኢፍጣር መርሐ -ግብር አዘጋጅቷል::
+3
ጂግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ለሙስሊም ተማሪዎች የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጅቷል!
በትላንትናው እለት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር በሺር አብዱላሂ እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በጅግጂጋ ዩኒቨርሲቲ ልዩ የሆነ የኢፍጣር መርሐ- ግብር ተዘጋጅቷል:: ተማሪዎች ከአመራሮቹ ጋር በመሆን በምግብ አዳራሹ ውስጥ የጀመዓ ሶላትንም ከውነዋል::
+2
በድሬ ዳዋ ዩኒቨርሲቲ የነበረ የኢፍጣር መርሐ- ግብር:: ተማሪዎች ከዩኒቨርሲቲው አመራሮች ጋር በጋራ አፍጥረው ነበር::
+5
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ለሙስሊም ተማሪዎች ልዩ የሆነ የኢፍጣር መርሐ- ግብር አሳውቋል!
በመጋቢት 17/2017 ዓ.ል የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ለዩኒቨርሲቲው ሙስሊም ተማሪዎች ልዩ የሆነ የኢፍጣር መርሐ- ግብር አዘጋጅቷል:: በዝግጅቱ የዩዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ፋሲል ደሊልን ጨምሮ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ ባለስልጣናት ተሳትፈዋል:: ተማሪዎችም መሠል ፕሮግራሞች ዩኒቨርሲቲው ከተማሪዎቹ ጋር የሚኖረውን ግንኙነት እንደሚያግለብት ገልፀዋል::
+6
የወራቤ ዩኒቨርሲቲ ለወራቤ ማህበረሰብ እና ለወራቤ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች የኢፍጣር መርሐ- ግብር አዘጋጅቷል!
በመጋቢት 18/2017 ዓ.ል የወራቤ ዩኒቨርሲቲ የኢፍጣር መርሐ-ግብር ያዘጋጀ ሲሆን በመርሐ-ግብሩ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ኢንጅነር ተውፊቅ ጀማልንና የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካን ጨምሮ የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች ታድመዋል::
+4
ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ እና ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲም ለሙስሊም ተማሪዎች የኢፍጣር መርሐ- ግብር ማዘጋጀታቸውን ገልፀዋል::
በኢፍጣር ፕሮግራሙ ላይ ተማሪዎች ከዩኒቨርሲቲዎቹ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በአብሮነት የተሰባሰቡ ሲሆን የጀመዓ ሶላትንም ከውነዋል!
@MohammadamminKassaw
+4
መቀሌ ዩኒቨርሲቲ የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጀ!
መቀሌ ዩኒቨርሲቲ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ የሚገኙ 200 ተማሪዎችን እና ከማህበረሰቡ ውስጥ የተውጣጡ የሐይማኖት አባቶችን ያሳተፈ የኢፍጣር ፕሮግራም እንዳዘጋጀ አሳውቋል:: ከኢፍጣር ቡሃላ ተማሪዎች የጀመዓ ሶላት የሰገዱ ሲሆን በፕሮግራሙ ላይ የተገኙ የዩኒቨርሲቲው አመራሮችም መልዕክቶችን አስተላልፈዋል::
+8
አምቦ ዩኒቨርሲቲ ለሙስሊም ተማሪዎች የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጀ!
በዛሬው እለት ማለትም መጋቢት 19/2017 ዓ.ል አምቦ ዩኒቨርሲቲ ለሙስሊም ተማሪዎች በዋናው ግቢ ታላቅ የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጅቷል:: በዝግጅቱ ወቅት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት እና ምክትል ፕሬዚዳንትን ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮች የተገኙ ሲሆን ፕሮግራሙ የተዘጋጀው በሐይማኖት እሴቶች መካከል መከባበር እንዲኖር ለማድረግ እንደሆነ ተወስቷል:: ከዚህም በተጨማሪ የተማሪዎች ህብረት አመራሮች እና የሌላ እምነት ተከታይ ተወካዮች ተገኝተው የፕሮግራሙ ተሳታፊ ሆነዋል::
+4
ተምሳሌታዊ ተግባር ••• ከደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ!
የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ለሙስሊም ተማሪዎች ደማቅ የሆነ የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጅቷል:: በፕሮግራሙ ላይ በአካባቢው የሚገኙ ኡስታዞች እና መሻይኾች የተገኙ ሲሆን ከተማሪዎች ጋር አብረው አፍጥረው ሰግደዋል:: የተለያዩ መልዕክቶችም ተላልፈዋል::
+4
ተምሳሌታዊ ተግባር ••• ከአርሲ ዩኒቨርሲቲ!
በዘንድሮው ረመዳን የአርሲ ዩኒቨርሲቲ ለሙስሊም ተማሪዎች የአካባቢው ኡስታዞች እና ሽማግሌዎች በተገኙበት የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጅቷል:: በፕሮግራሙ ላይ ሙስሊም ተማሪዎች በአብሮነት አፍጥረው በጀመዓ የሰገዱ ሲሆን የተለያዩ መልዕክቶችም ተላልፈዋል::
+3
የመዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ከዩኒቨርሲቲው ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ ጋር በመተባበር ታላቅ የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጀ!
እለተ እሁድ መጋቢት 14/2017 ዓ.ል የመዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ውስጥ ከዩኒቨርሲቲው ሙስሊም ተማሪዎች ጋር በመተባበር ታላቅ የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጅቷል:: በፕሮግራሙ ላይ የባሌ ሮቤ ከተማ ከንቲባ: የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አቶ አህመድ ኸሊል: የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ም/ፕሬዚዳንት ዶክተር በዛብህ: የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት ኢሳ (ረዳት ፕሮፌሰር): የተማሪዎች መስጂድ ኢማም የሆኑት ሸይኽ ጧሐ እና ኡስታዝ አብዱልወሐብ እንዲሁም ሌሎች የዩኒቨርሲቲውና የከተማው ከፍተኛ አመራሮች የተገኙ ሲሆን ለተማሪዎች መልዕክት አስተላልፈዋል:: መሠል ፕሮግራሞችና ትስስሮች አዎንታዊ የትምህርት ከባቢን በመፍጠር ረገድ የጎላ ሚና እንደሚኖራቸውም ተወስቷል::
