en
Feedback
Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union

Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union

Open in Telegram

This is the official Channel of Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union.

Show more
4 474
Subscribers
-424 hours
-37 days
+2230 days
Posts Archive
ዒድ ••• በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ!‌‌ @EHEMSU
+9
ዒድ ••• በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ!‌‌ @EHEMSU

ዒድ ••• በድሬ ዳዋ ዩኒቨርሲቲ ! @EHEMSU
+2
ዒድ ••• በድሬ ዳዋ ዩኒቨርሲቲ ! @EHEMSU

ዒድ ••••• በወሎ ዩኒቨርሲቲ !
+6
ዒድ ••••• በወሎ ዩኒቨርሲቲ !

ዒድ ••• በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ! በAAU የጥቁር አንበሳ ካምፓስ ሆስፒታል ከተማሪዎቹ ባሻገር በሆስፒታሉ ካሉ ከ300 በላይ ታካሚዎች ጋር ዒድን አክብሯል! @MohammadamminKassaw
+2
ዒድ ••• በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ! በAAU የጥቁር አንበሳ ካምፓስ ሆስፒታል ከተማሪዎቹ ባሻገር በሆስፒታሉ ካሉ ከ300 በላይ ታካሚዎች ጋር ዒድን አክብሯል! @MohammadamminKassaw

Eid Mubarak! Gooftaan Hojii gaggaarii keenna nurraa haa qeebalu. Iidni iida gammachuu kan barakaa isiniif haa ta'u. firaa fi maatii keessa hunda waliin yeroo gaarii. @EHEMSU

ዒዱኩም ሙባረክ! ኢዱ ነገ መሆኑ ተረጋግጧል:: ቀሪ ዘመናችሁ እንደ ለይለተል ቀድር ሰላም እና ሰኪና የሞላበት ይሁን !" @MohammadamminKassaw
ዒዱኩም ሙባረክ! ኢዱ ነገ መሆኑ ተረጋግጧል:: ቀሪ ዘመናችሁ እንደ ለይለተል ቀድር ሰላም እና ሰኪና የሞላበት ይሁን !" @MohammadamminKassaw

የዒድ ቀንን ለመወሰን የሳዑዲ ጠቅላይ ፍ/ቤት ተሰይሟል:: ከደቂቃዎች ቡሃላ ውጤቱ የሚታወቅ ይሆናል::
የዒድ ቀንን ለመወሰን የሳዑዲ ጠቅላይ ፍ/ቤት ተሰይሟል:: ከደቂቃዎች ቡሃላ ውጤቱ የሚታወቅ ይሆናል::

ሰመራ ዩኒቨርሲቲ ለሙስሊም ተማሪዎች የኢፍጣር መርሐ- ግብር አዘጋጅቷል! መጋቢት 17/2017 ዓ.ል የሰመራ ዩኒቨርሲቲ የዩኒቨርሲቲውን ፕሬዚዳንት ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ለሙስሊም ተማሪዎች
+6
ሰመራ ዩኒቨርሲቲ ለሙስሊም ተማሪዎች የኢፍጣር መርሐ- ግብር አዘጋጅቷል! መጋቢት 17/2017 ዓ.ል የሰመራ ዩኒቨርሲቲ የዩኒቨርሲቲውን ፕሬዚዳንት ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ለሙስሊም ተማሪዎች የኢፍጣር መርሐ -ግብር አዘጋጅቷል::

ጂግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ለሙስሊም ተማሪዎች የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጅቷል! በትላንትናው እለት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር በሺር አብዱላሂ እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በጅግጂጋ ዩኒቨርሲቲ
+3
ጂግጅጋ ዩኒቨርሲቲ ለሙስሊም ተማሪዎች የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጅቷል! በትላንትናው እለት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር በሺር አብዱላሂ እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በጅግጂጋ ዩኒቨርሲቲ ልዩ የሆነ የኢፍጣር መርሐ- ግብር ተዘጋጅቷል:: ተማሪዎች ከአመራሮቹ ጋር በመሆን በምግብ አዳራሹ ውስጥ የጀመዓ ሶላትንም ከውነዋል::

በድሬ ዳዋ ዩኒቨርሲቲ የነበረ የኢፍጣር መርሐ- ግብር:: ተማሪዎች ከዩኒቨርሲቲው አመራሮች ጋር በጋራ አፍጥረው ነበር::
+2
በድሬ ዳዋ ዩኒቨርሲቲ የነበረ የኢፍጣር መርሐ- ግብር:: ተማሪዎች ከዩኒቨርሲቲው አመራሮች ጋር በጋራ አፍጥረው ነበር::

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ለሙስሊም ተማሪዎች ልዩ የሆነ የኢፍጣር መርሐ- ግብር አሳውቋል! በመጋቢት 17/2017 ዓ.ል የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ለዩኒቨርሲቲው ሙስሊም ተማሪዎች ልዩ የሆነ የኢፍጣር መርሐ- ግብ
+5
የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ለሙስሊም ተማሪዎች ልዩ የሆነ የኢፍጣር መርሐ- ግብር አሳውቋል! በመጋቢት 17/2017 ዓ.ል የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ለዩኒቨርሲቲው ሙስሊም ተማሪዎች ልዩ የሆነ የኢፍጣር መርሐ- ግብር አዘጋጅቷል:: በዝግጅቱ የዩዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶክተር ፋሲል ደሊልን ጨምሮ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ ባለስልጣናት ተሳትፈዋል:: ተማሪዎችም መሠል ፕሮግራሞች ዩኒቨርሲቲው ከተማሪዎቹ ጋር የሚኖረውን ግንኙነት እንደሚያግለብት ገልፀዋል::

የወራቤ ዩኒቨርሲቲ ለወራቤ ማህበረሰብ እና ለወራቤ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች የኢፍጣር መርሐ- ግብር አዘጋጅቷል! በመጋቢት 18/2017 ዓ.ል የወራቤ ዩኒቨርሲቲ የኢፍጣር መርሐ-ግብር ያዘጋጀ ሲሆን
+6
የወራቤ ዩኒቨርሲቲ ለወራቤ ማህበረሰብ እና ለወራቤ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች የኢፍጣር መርሐ- ግብር አዘጋጅቷል! በመጋቢት 18/2017 ዓ.ል የወራቤ ዩኒቨርሲቲ የኢፍጣር መርሐ-ግብር ያዘጋጀ ሲሆን በመርሐ-ግብሩ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ኢንጅነር ተውፊቅ ጀማልንና የስልጤ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘይኔ ቢልካን ጨምሮ የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች ታድመዋል::

ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ እና ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲም ለሙስሊም ተማሪዎች የኢፍጣር መርሐ- ግብር ማዘጋጀታቸውን ገልፀዋል:: በኢፍጣር ፕሮግራሙ ላይ ተማሪዎች ከዩኒቨርሲቲዎቹ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በአብሮነ
+4
ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ እና ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲም ለሙስሊም ተማሪዎች የኢፍጣር መርሐ- ግብር ማዘጋጀታቸውን ገልፀዋል:: በኢፍጣር ፕሮግራሙ ላይ ተማሪዎች ከዩኒቨርሲቲዎቹ ከፍተኛ አመራሮች ጋር በአብሮነት የተሰባሰቡ ሲሆን የጀመዓ ሶላትንም ከውነዋል! @MohammadamminKassaw

መቀሌ ዩኒቨርሲቲ የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጀ! መቀሌ ዩኒቨርሲቲ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ የሚገኙ 200 ተማሪዎችን እና ከማህበረሰቡ ውስጥ የተውጣጡ የሐይማኖት አባቶችን ያሳተፈ የኢፍጣር ፕሮግራም እንዳዘጋ
+4
መቀሌ ዩኒቨርሲቲ የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጀ! መቀሌ ዩኒቨርሲቲ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ የሚገኙ 200 ተማሪዎችን እና ከማህበረሰቡ ውስጥ የተውጣጡ የሐይማኖት አባቶችን ያሳተፈ የኢፍጣር ፕሮግራም እንዳዘጋጀ አሳውቋል:: ከኢፍጣር ቡሃላ ተማሪዎች የጀመዓ ሶላት የሰገዱ ሲሆን በፕሮግራሙ ላይ የተገኙ የዩኒቨርሲቲው አመራሮችም መልዕክቶችን አስተላልፈዋል::

አምቦ ዩኒቨርሲቲ ለሙስሊም ተማሪዎች የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጀ! በዛሬው እለት ማለትም መጋቢት 19/2017 ዓ.ል አምቦ ዩኒቨርሲቲ ለሙስሊም ተማሪዎች በዋናው ግቢ ታላቅ የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጅቷል
+8
አምቦ ዩኒቨርሲቲ ለሙስሊም ተማሪዎች የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጀ! በዛሬው እለት ማለትም መጋቢት 19/2017 ዓ.ል አምቦ ዩኒቨርሲቲ ለሙስሊም ተማሪዎች በዋናው ግቢ ታላቅ የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጅቷል:: በዝግጅቱ ወቅት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት እና ምክትል ፕሬዚዳንትን ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮች የተገኙ ሲሆን ፕሮግራሙ የተዘጋጀው በሐይማኖት እሴቶች መካከል መከባበር እንዲኖር ለማድረግ እንደሆነ ተወስቷል:: ከዚህም በተጨማሪ የተማሪዎች ህብረት አመራሮች እና የሌላ እምነት ተከታይ ተወካዮች ተገኝተው የፕሮግራሙ ተሳታፊ ሆነዋል::

ተምሳሌታዊ ተግባር ••• ከደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ! የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ለሙስሊም ተማሪዎች ደማቅ የሆነ የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጅቷል:: በፕሮግራሙ ላይ በአካባቢው የሚገኙ ኡስታዞች እና መሻይኾች
+4
ተምሳሌታዊ ተግባር ••• ከደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ! የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ለሙስሊም ተማሪዎች ደማቅ የሆነ የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጅቷል:: በፕሮግራሙ ላይ በአካባቢው የሚገኙ ኡስታዞች እና መሻይኾች የተገኙ ሲሆን ከተማሪዎች ጋር አብረው አፍጥረው ሰግደዋል:: የተለያዩ መልዕክቶችም ተላልፈዋል::

ተምሳሌታዊ ተግባር ••• ከአርሲ ዩኒቨርሲቲ! በዘንድሮው ረመዳን የአርሲ ዩኒቨርሲቲ ለሙስሊም ተማሪዎች የአካባቢው ኡስታዞች እና ሽማግሌዎች በተገኙበት የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጅቷል:: በፕሮግራሙ ላይ
+4
ተምሳሌታዊ ተግባር ••• ከአርሲ ዩኒቨርሲቲ! በዘንድሮው ረመዳን የአርሲ ዩኒቨርሲቲ ለሙስሊም ተማሪዎች የአካባቢው ኡስታዞች እና ሽማግሌዎች በተገኙበት የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጅቷል:: በፕሮግራሙ ላይ ሙስሊም ተማሪዎች በአብሮነት አፍጥረው በጀመዓ የሰገዱ ሲሆን የተለያዩ መልዕክቶችም ተላልፈዋል::

ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች መንቃት አለብን !!!

የመዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ከዩኒቨርሲቲው ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ ጋር በመተባበር ታላቅ የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጀ! እለተ እሁድ መጋቢት 14/2017 ዓ.ል የመዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግ
+3
የመዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ከዩኒቨርሲቲው ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ ጋር በመተባበር ታላቅ የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጀ! እለተ እሁድ መጋቢት 14/2017 ዓ.ል የመዳ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢ ውስጥ ከዩኒቨርሲቲው ሙስሊም ተማሪዎች ጋር በመተባበር ታላቅ የኢፍጣር ፕሮግራም አዘጋጅቷል:: በፕሮግራሙ ላይ የባሌ ሮቤ ከተማ ከንቲባ: የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት አቶ አህመድ ኸሊል: የዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ም/ፕሬዚዳንት ዶክተር በዛብህ: የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር ጉዳዮች ም/ፕሬዚዳንት ኢሳ (ረዳት ፕሮፌሰር): የተማሪዎች መስጂድ ኢማም የሆኑት ሸይኽ ጧሐ እና ኡስታዝ አብዱልወሐብ እንዲሁም ሌሎች የዩኒቨርሲቲውና የከተማው ከፍተኛ አመራሮች የተገኙ ሲሆን ለተማሪዎች መልዕክት አስተላልፈዋል:: መሠል ፕሮግራሞችና ትስስሮች አዎንታዊ የትምህርት ከባቢን በመፍጠር ረገድ የጎላ ሚና እንደሚኖራቸውም ተወስቷል::