en
Feedback
Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union

Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union

Open in Telegram

This is the official Channel of Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union.

Show more
4 476
Subscribers
-424 hours
-37 days
+2230 days
Posts Archive
የታሰሩትን እንድትፈቷቸዉ ስለመጠየቅ ከኢፍጣር መልስ ከተለያዩ አከባቢዎች የታሰሩ እህት ወንድሞቻችንን እንድትፈቷቸዉ ስለመጠየቅ! በአዲስ አበባና በዙሪያዋ የሚገኙ ነዋሪዎች መጋቢት 7 በኢድ/አብዮት አደባባይ በተካሄደዉ ታላቅ ዝግጅት ላይ በሰላም ተሳትፈዉ ሲመለሱ የነበሩ እህት ወንድሞቻችን በመንገዶች ላይ በተነሱ ጥቃቅን አለመግባባቶች ምክንያት እናጠራለን በሚል የፀጥታ አካል በርካቶችን በእስር እንዲያሳልፉ አድርጓል። ከእሁድ ጀምሮ እስከዛሬ ባሉት ተከታታይ ቀናት ቡኅላም በዛሬው እለት ፍርድ ቤት ቀርበዉ ዋስትና ቢፈቀድላቸዉም የፖሊስ አባላት ለመፍታት አልፈቀዱም። የዋስ መብት ሀገራችን ባፀደቀቻቸው አለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ሰነዶች እንዲሁም በኢ.ፌ.ድ.ሪ ህገ-መንግስት የህግ ጥበቃ ከተሰጣቸው ሰብአዊ መብቶች መካከል አንዱ ነው፡፡ በአለም አቀፉ ሲቪል እና የፖለቲካ መብቶች ኮንቬንሽን አንቀጽ 9(3)፣ በኢ.ፌ.ድ.ሪ ህገ-መንግስት አንቀጽ 19(6) እንዲሁም በወንጀል ሥነ -ሥርአት ህግ ቁጥር 59 መሰረት የተያዙ ሰዎች የዋስ መብት እንዳላቸው በግልጽ ተደንግጎ ይገኛል፡፡ በድንጋጌዎቹ መሰረት የተያዙ ሰዎች በ48 ሰአት ውስጥ ፍርድ ቤት መቅረብ እና የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው የመጠየቅ መብት ያላቸው ሲሆን ፍርድ ቤትም የዋስ መብትን የማስከበር ወይም በህግ የተደነገጉ ልዩ ሁኔታዎች በተገኙ ጊዜ ደግሞ ዋስትና ሊነፍግ እንደሚችልም ያመለክታል፡፡ በመሆኑም የዋስ መብት የመርህ ና የህገ መንግስት እንዲሁም የመብት ጉዳይ እንጂ አንድ የፀጥታ አካል ሲሞቀዉና ሲበርደዉ የሚሰጠዉና የሚያስቀረዉ ጉዳይ አይደለም። ለምሳሌ ያህል በቁጥር 51 የሚሆኑ ፆመኛ ወንድሞቻችን ጀሞሚካኤል ፖሊስ ጣቢያ ታስረዉ የነበረ ሲሆን በዛሬው እለት ፍርድ ቤት ቀርበዉ ሁሉም የዋስትና መብታቸዉ ቢረጋገጥም ፖሊስ ከሕገ መንግስቱ በተቀራኒ ቆሞ መፍታትን አሻፈረኝ ብሏል። ወላጆች የዋስትና ገንዘብ ከፍለው በፖሊስ ጣቢያ ሰነድ ገቢ በማድረግ መፈታታቸዉን ቢጠባበቁም ከበላይ አካል ፈቃድ አላገኘንም በሚል በእስር እንዲቆዩ ምክንያት ሆኗል። ጊዜዉ የፆም ወቅት በመሆኑና በርካቶቹም ተማሪና በተለያዩ መልኩ ቤተሰብ የሚያስተዳድሩ ወጣቶች በመሆናቸዉ ይህን ከግምት ዉስጥ በማስገባት ትፈቷቸዉ ዘንድ በአክብሮት እንጠይቃለን። ምናልባትም በጊዜዉ አላስፈላጊ ሁከቶች ተፈጥረዉ ከሆነም በፕሮግራሙ አዘጋጆችና በተቋማችን በኩል የሚመከሩና የሚታረሙ ይሆናል። ከላይ ከተገለጸዉ ፖሊስ ጣቢያ ውጪ በአምስተኛ ፖሊስ ጣቢያ፣ ቄራ ፔፕሲ ፖሊስ ጣቢያ...በበርካታ ፖሊስ ጣቢያዎች በእስር ላይ እንደሚገኙ ይታወቃል።

መታገል ••• ከ5ቱ የመ ሕጎች 3ኛው! አስቦ እና አቅዶ በቀመር መብት የነጠቀን አካል "መብቴን ስጠኝ!" ስላልነው ብቻ ይሰጠናል ማለት አይደለም:: በእኩልነት ሳያምን ነፃነታችንን የገፈፈን አካል "በነፃነታችን አትምጣ!" ስላልነው ከሕገ- ወጥ ስራው ይቆጠባል ማለት አይደለም:: አስቦበት ነውና የነጠቀን አስበን ልንታገለው ይገባል:: በቀመር ነውና የሚጨቁነን በቀመር ልንታገለው ይገባል:: "መብት በትግል እንጅ በልመና አይገኝም!" የሚባለውም ለዚህ አይደል? ነፃነት በነፃ አይገኝም የሚባለውስ ለዚህ አይደል? እናስ? እናማ ••• መብትን ከተረዱ ቡሃላ መጠየቅ ••• ከጠየቁ ቡሃላ እስኪመለስ እና እስኪስተካከል ድረስ ያለመታከት በቅንጅት እና በጥበብ መታገል ያስፈልጋል:: የዚያኔ ሁሉም ይስተካከላል:: የዚያኔ ነፃነት ይመጣል:: የዚያኔ መብት ይከበራል:: የዚያኔ እኩልነት ይፀድቃል:: @EHEMSU

መጠየቅ ••• ከ5ቱ የመ ሕጎች ሁለተኛው! ስለ መብት መጣስ እና መውሰድ: ስለ ነፃነት መገፈፍ እና መጎናፀፍ: ስለ እኩልነት መሸርሸር እና መሙላት: ስለ ክብር መደፈር እና መጠበቅ መረዳትን መያዝ የመጀመሪያው የትግል መስመር ቢሆንም ማወቁ ብቻ መፍትሔ ያመጣል ማለት አይደለም:: የቀሙንን ለመውሰድ: የገፈፉንን ለመጎናፀፍ: የሸረሸሩትን ለመሙላት: የደፈሩትን ለማስጠበቅ መጠየቅ ያስፈልጋል:: በጫንቃችን ላይ ያሸከሙንን የጭቆና ቀንበር አንሱት ብሎ መጠየቅ ያስፈልጋል:: በጨዋ ደንብ ትክክል አይደለም ብሎ በማስረዳት ከስራቸው እንዲታቀቡ ብሎም የሌላን አካል ነፃነት እኩልነት ክብር እና ሰብዓዊነት ከመዳፈር ይታቀቡ ዘንድ መጠየቅ ያስፈልጋል:: ምናልባት እኛ በአዕምሯችን የዝሆን ያክል አግዝፈን ያየነው ችግር ከአይጥ ያነሰ ሊሆን ይችላልና መጠኑን አውቆ የሚያስፈልገውን ለመፈለግ መጠየቅ ያስፈልጋል:: ምናልባት የተራራን ያክል ገዝፎብን በሀሳብ ስንዋልልበት የነበረው መከራ እግራችን ስራ ያለ ደረጃ ያክል ሊሆን ይችላልና ከፍታውን ለማወቅ እና የሚጠበቀውን ለማሟላት መጠየቅ ያስፈልጋል:: ካልጠየቅን ግን ••• ሳይጠይቁ መልስ የለምና ምላሽ አናገኝም:: ሳንጠይቅ ችግሮቻችንን ሊፈቱልን አይችሉምና ከጀርባችን የተበተነው ትቢያ የተራራን ያክል ከብዶን እንቀጥላለን:: ሳንጠይቅ የችግሮቻችንን ክብደት እና ግዝፈት ልናውቅ አንችልምና ለመታገል የሚያስፈልገንን ስንቅ ለመሸመት ሳንታጠቅ ለቀጣዩም ትውልድ የጥያቄ ካዝናን አስረክበን እናልፋለን:: እናስ? እናማ ••• መብታችን ሆኖ የተነጠቅነውን "ለምን ነጠቃችሁን? ለምን አትመልሱም?" ብለን እንጠይቅ ••• ነፃነታችን ሆኖ የገፈፉንን "ለምን በነፃነታችን መጣችሁ? መጎናፀፊያችንን አትንኩ!" ብለን እንጠይኩ ••• ክብራችንን የተዳፈሩን "ለምን በክብራችን መጣችሁ? ክብራችንን አትንኩ!" ብለን እንጠይቅ ••• የዚያኔ ••• በአላህ ፈቃድ መንገዱ ይበራል! @EHEMSU

የጁምዓ ቀን የትምህርት ሰዓት ከ2:30 - 5:30 እንደሆነና ከሰዓት 7:30 እንደሚጀምር አዋጅ ቁጥር 43/1985 አንቀፅ 3 ቁጥር 1 ላይ ይናገራል:: እንዲህም ይላል:- "የመንግስት መስሪያ ቤቶች
+1
የጁምዓ ቀን የትምህርት ሰዓት ከ2:30 - 5:30 እንደሆነና ከሰዓት 7:30 እንደሚጀምር አዋጅ ቁጥር 43/1985 አንቀፅ 3 ቁጥር 1 ላይ ይናገራል:: እንዲህም ይላል:- "የመንግስት መስሪያ ቤቶች የስራ ቀንና ሰዓት እንደሚከተለው ይሆናል:: ለ) ዓርብ:- ከጠዋቱ 2:30-5:30 ከቀኑ 7:30 - 11:30 ጁምዓ ከ5:30 - 7:30 ባለው ትምህርትም ፈተናም ሆነ ሌላ ነገር ሊኖር አይገባም ማለት ነው:: በአዋጁ መሠረት ይህንን የሚያደርግ ወንጀለኛ ነው:: @EHEMSU

ይህ ስልት ነቢያችንን (ሰዐወ) የተሳደበውንና የጥላቻ ንግግር የሠነዘረውን ግለሰብ “ሙስሊሞች ሊገድሉት ነው” በሚል የሐሰት ትርክት የእምነት ወገኖቹ ለእሱ እንዲከላከሉ ማነሳሳት ነው። የጉዳዩን አደገኛነት እያወቁ የግለሰቡን ስም በማንሳት፣ “እኛም እገሌ ነን” የሚሉ ጥቂት ታዋቂ ግለሰቦችን ወደሚዲያ በማውጣት ተርታው ሕበረተሰብ የእነሱን ፈለግ እንዲከተል አነሳስተዋል። “ጉዳዩ የቤተ ክርስቲያኒቱ ጉዳይ ነው” የሚል ምስል በመፍጠር ወንጀለኛውን ግለሰብ ለአስነዋሪ ተግባሩ እንዲቀጣ ከማድረግ ይልቅ እንደጀግና እንዲታይ ለማድረግ ጥረዋል። ባለጌን በመጠየፍ፥ ስድ አደግነትን በመኮነን እና ጋጠወጥነትን በማውገዝ “ሌላው ቢቀር ለአብሮነታችን ሲባል እንኳ ከእውነት ጎን እንቁም” ማለት በተገባቸው ነበር። ሆኖም የእነርሱ ምርጫ ከተሳዳቢው ቆን መቆም ነበር። በዚህም ይህን ትርክትና አካሄዱን የሚቃወሙ ሙስሊሞችን መልሶ ተከሳሽ፥ ተወቃሽና በዳይ አድርጎ ማቅረብ ሽተዋል። ይህንኑ ዓላማ ለማሳካትም በተለያዩ ሚዲያዎች “ችግር ፈጣሪዎቹ ሙስሊሞች ናቸው” የሚል ምስልና ግንዛቤ ለመፍጠር ጥረዋል። 13/ መንታ ምላስ መንታ ሚዛን[Double Standard] 🚻🚻🚻🚻🚻🚻🚻🚻🚻🚻🚻🚻🚻🚻🚻 “የሀገር ሚዲያ ነን” ሲሉ፣ ሚዛናዊ መስለው ለመቅረብ ሲጥሩ የኖሩ አካላት በሰሞኑ ክስተት ጫፍ ደርሶ የነበር ጭንብላቸው ሙሉ ለሙሉ ተገልጧል። መስፈሪያቸው ለራሳቸው ሲሆን በዚህ፥ ለሌላው ሲሆን በዚያ መሆኑን አሳይተውናል። ሌሎችን መስደብ የጥላቻ ንግግር ሆኖ ሳለ ነቢዩ ሙሐመድን (ሰዐወ) መስደብ እንዴት የሃይማኖት ንጽጽርና የመናገር ነጻነት ሊሆን ይችላል? መሳደብ ወንጀል ካልሆነስ ስለምን የጥላቻ ንግግር አዋጆች ማውጣት አስፈለገ?  በሃይማኖት ቀርቶ በኢትዮጵያ ታሪክ ልዩነቶች ላይ እንኳ የማይቀበሉትን ትርክትና አቀራረብ በማስረጃ ከመሞገት ይልቅ “የሐስት ትርክት”፣ “ሕዝብ ለሕዝብ ለማባላት ያለመ”፣ “በሕግ ሊታገድ የሚገባው”፣ “አንድ የማያደርግ አቀራረብ” ወዘተ እያሉ ከእነሱ የሚለየውን እይታና አቀራረብ ለመድፈቅ ሲጥሩ የኖሩ አካላት በነቢዩ (ሰዐወ) መሰደብ ጉዳይ ለታሪክ እንኳ ሲያነሱ የኖሩትን የመምቻ መሳሪያ ተቃርነው መንታ ምላስና መንታ ሚዛን እንዳላቸው አሳይተውናል። ያጠለቁት ሽፋን ወልቆ እርቃናቸውን ቀርተዋል። 14/ ሐሰተኛ ንጽጽር (False Analogy) 📺📺📺📺📺📺📺📺📺📺📺📺 ይህ ስልትም በሁለቱ የማይገናኙና የማይነጻጸሩ ጉዳዮች መካካል አሳሳች ንጽጽሮሽ በመፍጠር ተመሳሳይ የማድረግ ጥረት ነው። በሚዲያ በቀጥታ በነቢዩ ሙሐመድ (ሰዐወ) ላይ የተደረገው የጥላቻ፥ የማነወርና የመሳደብ ተግባር አቻ መስሎ የሚታይ ነገር ፍለጋ ሰነድ ማገላበጥ ያዙ። ከዓመታት በፊት ተሰርተው በዝምታ ያለፏቸውን የሃይማኖት ንጽጽር መጽሐፍቶች፥ ቪዲዮዎች ወዘተ ዳግም በማንሳት "የእነዚህ ባለቤቶችም አብረው ይጠየቁልን" የሚል ቅኝትና ትርክት ለመፍጠር መታገል ጀመሩ። ለዚህ ጥሩ ምሳሌ መስሎ ከታያቸው አንዱ ከ16 ዓመታት በፊት ጥር 2001 የታተመው "ክርስቶስ ማነው? 303 ወሳኝ ጥያቄዎች" የሚለው የኔን መጽሐፍ ነው።  እግረ መንገዴን ግን እውነታውን መረዳት የፈለገ ሰው "ክርስቶስ ማነው? 303 ወሳኝ ጥያቄዎች" ስለሚለው መጽሐፌ የሰዎቹን ፕሮፓጋንዳ ሳይሆን ራሱን መጽሐፉን ከኦንላይን አውርዶ እንዲያነብ፥ ማህበረ ቅዱሳን ከ15 ዓመታት ቆይታ በኋላ አምና የሰጠውን ምላሽ መጽሐፍ እንዲያነብ እጋብዛለሁ። በዚህ መልኩ መጽሐፉን ዳግም የትኩረት ማዕከል በማድረጋቸው እያመሰገንኩ ከሕትመት ርቆ በመቆየቱና ዳግም ለማሳተም እንኳ ሶፍት ኮፒው ስለሌለኝ ማንበብ የምትሹ ፒዲኤፍ ፎርማቱ ኢንተርኔት ላይ ስለማይጠፋ ፈልጋችሁ እንድታነቡት እጋብዛለሁ። መጽሐፉ አንዳችም ስድብ፥ የጥላቻ ንግግርም ሆነ ማንቋሸሽ የሌለው መሆኑን፣ የሚያስጠይቅ ይዘት ካለበትም በሕግ ፊት ለመከራከር ዝግጁ መሆኔን ለማሳወቅ እወዳለሁ። የሚገርመው ደግሞ የሃይማኖት ንጽጽር በእነሱም በኩል ካሪኩለም ተቀርፆ በኮሌጅ ደረጃ፥ በመጽሐፍትና በቤተ እምነት ውስጥ እየተሰጠ ሳለ በማስረጃ፥ በምክንያታዊነት፥ እንዲሁም በተጠይቃዊ ስነ-ምግባር የቀረበውን የሃይማኖት ንጽጽር ከጥላቻ፥ ከስድብና ከንቀት ጋር አቻ አድርገው ለማቅረብ መጣራቸው ነው። የዚህ ድርጊታቸው ዓላማ በግለሰቡ የተተገበረው የጥላቻ ንግግር፥ ስድብና ማንቋቋሸሽ "ለሙስሊሞች ጥያቄ፣ አልያም ለሃይማኖት ንጽጽር ትምህርታቸው ምላሽ ነው" የሚል የሐሰት ንጽጽር (False Analogy) በመፍጠር ሙስሊሙን ከሳሽ ሳይሆን ተከሳሽ፥ ወቃሽ ሳይሆን ተወቃሽ አድርጎ በመሳል ወቀሳውን መልሶ በሙስሊሞች ላይ ማዞር (shifting blame) ነው። ከላይ የተብራሩት ስልቶች በሙስሊሞችና በእምነታቸው ላይ የሚደርሰውን የፖለቲካ፣ የስነ-ልቦና እና የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ እንደሚያሳይ ግልጽ ነው። ስልቶቹም በተደጋጋሚና በተጨባጭ በተግባር ላይ መዋላቸውን ተመልክተናል። እነዚህ ስልቶች የሃይማኖትን ክብርና ጥበቃን ለመሸርሸር፥ የህብረተሰባችንን አንድነት ለመሸርሸር፣ ከራስ ወገን የሚሰነዘሩ የጥላቻ ንግግሮችና ተናጋሪዎችን ለመከላከል ለጊዜው ብቻ ያግዙ ካልሆነ በቀር ለዘለቄታው አብሮነታችን ግን አደጋ መሆናቸው እሙን ነው። በተለይ ደግሞ የሚዲያ ፕላትፎርም ያላችሁ፣ ራሳችሁም ተጽዕኖ ፈጣሪ የሆናችሁ አክቲቪስቶች በህግ፣ በስነ-ምግባር እና በእውነታ ላይ የተመሠረተ መከባበር የተሞላበት ውይይት ለሀገራችን እጅግ ወሳኝ መሆኑን ትረዳላችሁ ብዬ አስባለሁ። ይህ ሲሆን ውይይቶቻችን ትክክለኛ ብለን የምናምነውን መረዎችንና ማስረጃዎችን መለዋወጥ፥ መግባባትን ማጎልበት፥ መተማመን ባንችል እንኳ ከእነ ልዩነቶቻችን በመከባበር መኖር የምርጫ ጉዳይ ሳይሆን የግድ ይሆናል። ቸር ያሰማን!

የሚዲያ የአቀራረብ ቅኝት (Media framing) ስልቶችን በመጠቀም የህብረተሰቡን ትኩረት ከዋናው ጉዳይ የማራቅ፣ አልያም የክርክር ጭብጡን ወይም አጀንዳውን የመለወጥ ጥረትም ተደርጓል። ለምሳሌ የሰሞኑ አጀንዳ በግልጽና በአደባባይ የአላህ መልዕክተኛ (ሰዐወ) በሚዲያ መሰደብ መሆኑ ግልጽ ነው። ሆኖም ግን ጉዳዩ ላይ የሚጽፉ፥ የሚናገሩ፥ ወንጀለኛው ግለሰብ ተይዞ ለህግ እንዲቀርብ የሚጠይቁ፣ አልያም ከዚህ ጋር የተያያዘ አንዳች ሚና ይኖራቸዋል ብለው የሚያስቡዋቸውን ሙስሊሞች የተለያዩ ንግግሮች፥ ጽሁፎችና ቪድዮዎች ቆራርጠውና ቀጣጥለው አውዱን ከነበረው ወደሚፈልጉት እንዲለወጥ ለማድረግ ጥረዋል። እነዚያን ግለሰቦችም በጥርጣሬ የሚታዩ፥ አስጊ፥ አደገኛ፥ የውጭ ተላላኪ፥ ብሄርተኛ፥ ጠላት ወዘተ አስመስለው በማቅረብ የቀደመው ጉዳይ ደብዝቦ አልያም አጀንዳው ተቀይሮ ህብረተሰቡ ስለነዚህ ግለሰቦች እንዲያስብ፥ እነሱም ጉዳዩን ትተው ራሳቸውን እንዲከላከሉ ለማድረግ ሞክረዋል። ወይም ደግሞ አጀንዳውን የነቢዩ ሙሐመድ (ሰዐወ) መሰደብ ከመሆን ጭብጥ አውጥቶ ሙስሊሞችም ተመሳሳይ ነገር እያደረጉ ነው ወደሚል ጭብጥ ማዞር ነው። 7/ ሐሳብን በነጸነት መግለጽን በሽፋንነት መጠቀም (Free Speech Rhetoric) ☀☀☀☀☀☀☀☀☀☀☀☀☀☀☀☀ የአላህን መልዕክተኛን (ሰዐወ) ክብረ ነክ በሆነ መንገድ መስደብና ማነወር ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ አካል እንደሆነ አድርጎ ማቅረብ ሌላው የተከተሉት ስልት ነው። “የሀሳብ ነጻነት ሊከበር ይገባል” በሚል ስልት የጥላቻ ንግግሩና ስድቡ ዝም እንዲባል ለማድረግ ጥረዋል። ይህ ደግሞ ብዙውን ጊዜ በሙስሊሞች ላይ ከሚተገበሩ የተለመዱ ስልቶች አንዱ ነው። የአላህ መልዕክተኛ ነቢዩ ሙሐመድ (ሰዐወ) ሲሰደቡና ሲንቋሸሹ ጉዳዩ ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ይሆናል። አንዳንድ ሙስሊሞች ስሜት የተሞላበት ምላሽ ሲሰጡ ግን ጽንፈኝነት ይደረጋል።  ይህ አካሄድ ሁለት ግቦችን ለማሳካት ያለመ ነው። የመጀመሪያው ምንም ይፈጠር ምን በሁሉም ሁኔታ በሕብረተሰቡ ዘንድ ሙስሊሞች ሁሌም ጽንፈኞች፥ የመቻቻል አደጋዎች፥ የሀገር ስጋቶችና የውጭ አካላት ወኪሎች ተደርገው እንዲታዩ ማድረግ ሲሆን ሁለተኛው ዓላማ ደግሞ ሙስሊሞች ትንኮሳውን ዝም ብለው እንዲያሳልፉ በማስገደድ በእስልምና ላይ የሚፈጸም የጥላቻ ንግግር እንዲለመድ ማድረግ ነው።  8/ ከአክራሪዎች ጋር ማያያዝ (Association with Extremists) 🌎🌎🌎🌎🌎🌎🌎🌎🌎🌍🌍🌎🌍🌍🌍🌍 ይህ ስልት “የእስልምና ክብር መጠበቅ አለበት” የሚሉ ሙስሊሞችን አክራሪ ተብለው ከተፈረጁ አካላት ጋር ግንኙነት እንዳላቸው አድርጎ በማቅረብ በዚህ ጉዳይ ላይ የሚንቀሳቀሱ፥ የሚናገሩና የሚጽፉ ሙስሊሞችን ማሳቀቅ ነው። ይህ ሲሆን የእነዚህን ሙስሊሞች ፈለግ ተከትሎ ለሃይማኖት መብት መቆም አስፈሪ ይሆናል። ይህም በየሰበብ አስባቡ ሁለቱን አካላት ግንኙነት እንዳላቸው አስመስሎ በማቅረብ ግለሰቦቹ ተሸማቀው ጉዳዩን እንዲተዉት፣ አልያም አጀንዳውን ጥለው ራሳቸውን ወደ መከላከል እንዲገቡ ለማድረግ ታስቦ የሚደረግ ስልት ነው። 9/ የመረጣ ገለልተኝነት (Selective Neutrality) 🌐🌐🌐🌐🌐🌐🌐🌐🌐🌐🌐🌐🌐🌐🌐 ይህ ስልት በተለያዩ ዘዴዎች ሲተገበር ታይቷል። በአንድ በኩል ሚዲያዎች ተጠቂ የሆኑትን ሙስሊሞችና በሀሰት “ተጠቂ” መስሎ እንዲቀርብ የተደረገውን ግለሰብ በማቅረብ እነርሱ ገለልተኛ ሆነው የሚዲያ ሥራቸውን እየሰሩ ያሉ መስለው ለመታየት ይሞክራሉ። እንደ ግለሰብም ሆነ እንደሚዲያ በሌሎች ጉዳዮች ገለልተኝነት ሳይመርጡ አቋም ይዘው ዘገባ ሲሰሩ፥ መግለጫ የሚመስል ነገር በራሳቸው ሲያወጡና የዚያን ወገን ሰፊ ጊዜ ሰጥተው የመናገሪያ መድረክ ለብቻው ሲሰጡ ቆይተው አሁን በዚህ ጉዳይ ግን ደርሶ “ገለልተኛ ነኝ” የሚል ጨዋታ ይጫወታሉ። ጠያቂ ከመጣ “እኛ ሁለቱንም አመለካከቶች አቅርበናል” በማለት ይመልሳሉ። ሌሎች ደግሞ “ገለልተኛ ነኝ” በሚል መዘገብ በማይፈልጓቸው ርዕሰ ጉዳዮች ላይ እየመረጡ ገለልተኛ ሆነው ለመታየት ይሞክራሉ። አንዳንድ ሚዲያዎች ደግሞ “እኔም ከእናንተ ጋር ሳይሆን ከተሳዳቢው ግለሰብ ጋር ነኝ” የሚል በሚመስል መልኩ የመግለጫውን ጥሪ ባለመቀበል ከስፍራው አልተገኙም። 10/ በሌሎች ጉዳዮች ማዘናጋት (Distraction with Other Issues) ❌❌❌❌❌❌❌❌❌❌❌❌❌❌❌❌ ይህ ስልት ሌሎች ከጉዳዩ ጋር የማይገናኙ ሙስሊም ነክ ሁኔታዎችን፥ ሀገራዊ ችግሮችን ወይም ሌሎች ነገሮችን በማንሳት ጉዳዩን የማቃለል ስልት ነው። “እነኚህን የመሳሰሉ ከባባድ፥ አንገብጋቢ እና ፈታኝ ሁኔታዎች እያሉ የግለሰቡን ድርጊት ይህን ያክል አጋኖ ማቅረብ ተገቢ አይደለም፤ ድርጊቱ አግባብ አለመሆኑን እኛም ገልጸናል፤ ሆኖም በዚህ ደረጃ መለጠጥ ወይም ይህን ያክል የጎላ ትኩረት መስጠት ተገቢ አይደለም” የሚል አቀራረብን በመከተል ጉዳዩ ተገቢውን ቦታ እንዳያገኝ ወይም እንዲዘነጋ ለማድረግ የመሞከር ስልት ነው። 11/ "የእነ እገሌ ሥራስ?" (whataboutism)  ⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽⚽ ይህኛው ስልት “የሃይማኖታችሁ መነካት በእናንተ አልተጀመረም። እኛም ሰንትና ስንት መከራ አሳልፈናል። ተሰድበናል፤ ተሳደናል። እንለጥጠው ካልን እናንተም ክርስቲያኖች ያ ሁሉ መከራ ሲደርስባቸው ዝም ማለት አልነበረባችሁም” ወዘተ የሚሉ ሀሳቦችን በማንሳት ጉዳዩን ማሳነስ አልያም ማስጣል ነው። ነቢዩ ሙሐመድን (ሰዐወ) የተሳደበውን ግለሰብ የጥላቻ ንግግር ሳያወግዙ፥ በአጀንዳውም ሚዛናዊ ዘገባ ሳይሰሩ ባላቸው የሚዲያ ፕላትፎርም ትይዩነት ለመፍጠር የሃይማኖት ንጽጽርን ተጠቅመዋል። “በእኛ ሃይማኖት ምን አገባቸው” በሚል ቅኝት የሃይማኖት ንጽጽር የሚሰሩ ሙስሊሞች የትኩረት ማዕከል እንዲሆኑ ጥረዋል። “የእነ እገሌ ሥራስ?” ዓይነት ተጠይቅ (whataboutism) በመተግበር ሊያስቀይሱ ሞክረዋል። የሙስሊሞችን ድምጽ በማፈን የእነሱ ወገን ድምጽ እንዲስተጋባ በሚዲያ ፕላትፎርሞቻቸው ታግለዋል። ጥቂት ሚዲያዎችም መጅሊስና የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ያወጡትን መግለጫ ወደዚህ ቅኝት ለማስገባትና “በሁለቱም ዘንድ ያላችሁ ጥፋተኞች እረፉ” ዓይነት ቅኝት ለመፍጠር ሲታትሩ ታይተዋል። 12/ የበዳይና የተበዳይን ሚና ማቀያየር (Reversing the Victim & Aggressor Roles) 🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁

አቻነት ፍለጋ የ16 ዓመት ጉዞ ❇❇❇❇❇❇❇❇❇ በአሕመዲን ጀበል 🕜🕝🕝🕝🕝 ይህችን አምስት ገጽ አንብቦ መጨረስ ካቃተህማ ጉድ ነው! መልክቱ ለሁሉም እንዲደርስ በሁሉም መንገድ ያሰራጩ። ❌❌❌❌❌❌❌❌❌❌❌❌❌❌❌❌ ሰሞኑን አጀንዳ የሆነው ሙስሊሞችን በማስቆጣት ቀድሞ የታቀደ በሚመስል መልኩ የሆነ ዓላማን ለማሳካት  የአላህን መልዕክተኛ (ሰዐወ) በማህበራዊ ሚዲያ የማንቋሸሽ፥ የማነወር እና የማዋረድ ተግባር ሁሉንም ሙስሊሞችን አስቆጥቷል። የድርጊቱ ፈጻሚ ግለሰብም በአስቸኳይ ለሕግ ቀርቦ ተገቢውን ቅጥት ማግኘት ይገባዋል። በፕሮፓጋንዳ፥ በፖለቲካና በስነ-ልቦና ጦርነት ስልቶች ላይ የህብረተሰቡን ግንዛቤ በመቆጣጠር የራስን ወገን ወንጀል ለመደበቅ፥ ሌላውን ተከሳሽ አድርጎ ለማቅረብ፥ ተጠቂ በደሉን እንዳያቀርብ ለማፈን፥ አልያም የምላሹን መጠንና የሙቀት ደረጃን ለመለካት ሲባል ሁለት የማይገናኙ ወይም የማይዛመዱ ነገሮችን አሳሳች በሆነ መልኩ ትይዩ አድርጎ አመሳስሎ ለማቅረብ የተለየያዩ ስልቶችና ጥረቶች ይተገበራሉ። በሰሞኑ የአላህ መልዕክተኛ (ሰዐወ) ክብረ ነክ ስድብ፥ የጥላቻ ንግግርና ማንቋሸሽ ጉዳይ ላይ አንዳንድ ግለሰቦች፥ አክቲቪስቶችና ሚዲያዎች ጉዳዩ ላይ የተከተሏቸውን ስልቶች፥ ጉዳዩን የዳሰሱበትን መንገድና ተያያዥ ነገሮችን ከፕሮፓጋንዳ፥ ከስነልቦና ጦርነትና ከፖለቲካ ስትራቴጂ አንጻር ያስተዋለ ሰው የተገበሯቸውን በርካታ ስልቶች በቀላሉ ይረዳል። በማስከተል የሚከተሉትን ጥቂት ቁልፍ ስልቶቻቸውን እንመልከት። 1/ የሐሰት አቻነት መፍጠር (False Equivalence) 🚼🚼🚼🚼🚼🚼🚼🚼🚼🚼🚼🚼🚼🚼🚼 ይህ ስልት ታዋቂ ግለሰቦች፥ አክቲቪስቶችና ሚዲያዎች በሰሞኑ እንደታየው የነቢዩ ሙሐመድን (ሰዐወ) ክብር ነክ በሆነ ሁኔታ መሰደብን ከሃይማኖት ንጽጽር ጋር አቻ አድርጎ በማቅረብ ሁኔታ የታየ ነው። በዚህ ሂደት “ነቢዩ ሙሐመድን መስደብ የሃይማኖት ንጽጽር ነው” የሚል አቻነት የመፍጠር ጥረት ተደርጓል። ይህን ያደረጉበት ዓላማም በሃይማኖት ንጽጽር እና በጥላቻ ንግግር፥ በስድብና በሹፈት መካካል ያለው ልዩነት እንዲደበዝዝ በማድረግ የግለሰቡ ተግባር በኖርማልነት እንዲታይ ለማድረግ ነው። በተጨማሪም አንዳንድ ወገኖች ደግሞ ከዚሁ የሐሰት አቻነት ፈጠራ ጋር በተያያዘ ማህበራዊ ሚዲያ ላይ እንደታየው ከጥላቻ ንግግር ባለቤትና ተሳዳቢው ግለሰብ ጋር አብረው እንደሆኑ በመግለጽና ቤተ እምነታቸው እንደ መጅሊስ መግለጫ እንዲያወጣ ጥሪ ያደረጉ ሲሆን ከፊሎቹ ደግሞ “የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ እኛንም እነሱንም በእኩል ዓይን ማየት ሲገባውና ዋና ጸሐፊው ቀሲስ ታጋይ የእኛን ሃይማኖት እየተከተለ ስለምን በእኛ ላይ መግለጫ ያወጣል?” በማለት የግለሰቡን እምነት ጥያቄ ዉስጥ ለመክተት ሲታትሩ አይተናል። 2/ ታሪክን ዋቢ በማድረግ ትክክለኛነትን ማሳየት (Historical Justification) ✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅✅ ይህ ስልት ከዚህ ከአሁኑ የነቢዩ (ሰዐወ) ክብረ ነክ ስድብ ጋር የማይገናኙ የተለያዩ ታሪካዊ ማስረጃዎችን በመለቃቀም ታሪክን አጣቅሶ የአሁን ነውረኛ ድርጊትን ትክክለኛነት ለማሳየት መሞከር ነው። “ክርስቶስ ማነው?” መጽሐፍና ሌሎችም ከዚህ የተነሳ ነው ለዋቢነት ተፈላልገው ዳግም መቅረብ የያዙት። ነቢዩ ሙሐመድን (ሰዐወ) መስደብ፥ ማንቋሸሽና ማነወርን ዓላማ ያደረገውን የጥላቻ ንግግር ሁሉም ሃይማኖቶች ከሚተገብሩት የሃይማኖት ንጽጽር (comparative religion) መካከል የሙስሊሞችን ብቻ ነጥሎ ከስድቡ ጋር በአቻነት እንዲታይ የሚያደርግ የሚዲያ ቅኝት ተጠቅመዋል። የሃይማኖት ንጽጽር የሚደረገው እውነትን ለማወቅ በሚደረግ ማስረጃን መሠረት ያደረገ ጨዋ ትንታኔ መሆኑን እያወቁ ሆነ ብለው ከግላዊ ጥላቻ፥ ስድብና ሹፈት ጋር አመሳስለው ለማቅረብ ጥረዋል። 3/ የሞራል እኩሌታ መፍጠር (Moral Equivalence) 🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀🏀 የግለሰቡን ክብረ ነክ ድርጊት አንዳንድ በድርጊቱ የተናደዱ ሙስሊሞች ስሜታዊ ሆነው ከሚሰጡት ግብረ መልስ ጋር በማነጻጸር ግለሰቡን ለመጉዳት የዛቱ ጥቂት ሙስሊሞችን ድርጊት በማጉላት “ሰላማችን አደጋ ውስጥ ወድቋል” የሚሉ አቀራረብ ያላቸውን መልዕክቶችን አሠራጭተዋል። እጅግ አደገኛ የሆነውን የጥላቻ ንግግርን፥ ስድብን እና ማንቋሸሽን ከሃይማኖት ንጽጽር ጋር አመሳስለው በማቅረብ የሃይማኖት ንጽጽርን ልክ እንደ ጥላቻ ንግግር ቆጥረዋል። የዚህ ሂደት አስኳል “እናንተ እገሌ የተናገረውን እንደ ጥላቻ፥ ስድብና ማንቋሸሽ ከቆጠራችሁ እኛም የእናንተ ድርጊት ተመሳሳይ ነው የሚል እንድምታ እንፈጥራለን” የሚል ነው። መቋጫውም “ያ ጥፋት ከሆነ ይህም ጥፋት ነው” የሚል ግንዛቤ መፍጠር ነው። 4/ ቅኝቱን በመቆጣጠር ድርጊቱ በተናጠል እንዳይወገዝ መከላከል (Controlling the Discourse to Avoid Isolation) 📥📥📥📥📥📥📥📥📥📥📥📥📥📥📥📥 ይህ ስልት በገለጽነው መልኩም ሆነ በማንኛውም መንገድ ለወንጀሉ አቻ የሚመስል ነገር በመፍጠር በሚዲያ፥ በሕብረተሰቡ ዘንድ፥ በአጀንዳነት ብሎም በውግዘት ጉዳዩ ለብቻው እንዳይወገዝ መታገል ነው። ይህም እውን እንዲሆን የህብረተሰቡን ስሜት፥ እምነትና ስስ ጎኑን ነካክቶ በዚያ መስመር ውስጥ እንዲፈስ በማድረግ ሀሳቡን በስሜት እንዲገልጽ በማድረግ በመሰል ጉዳዮች ላይ ባለድርሻ የሆኑት የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ፥ የመንግስት አካላት፥ ሚዲያዎችና ሌሎች አካላት የእነሱን ትርክት ተቀብለው ጥፋተኛውን ግለሰብ፣ ወይም ደጋፊዎቹን በተናጠል ከመተቸት እንዲርቁ በማድረግ በሁሉም መንገድ መታገል ነው። ይህ ሲሆን የሙስሊምና የክርስትና ሃይማኖት አባቶች በጋራ ወጥተው “ጥፋተኞች ሁላችንም ዘንድ አሉ” የሚል አቀራረብ ያለው ትርክትን እንዲቀበሉ ጫና ይፈጥርላቸዋል። መንግስትም በዚህ ትርክት ጫና ዉስጥ ገብቶ በሚዲያዎቹ በኩልም ሆነ በባለስልጣናቱ በኩል ደረጃው ምንም ይሁን ምን ጉዳዩ ሁለቱንም ወገን እንደሚመለከት የሚያንጸባርቅ ቅኝት ያለው ዘገባ ወይም ንግግር ወደማድረግ ይዘነበላል። 5/ ተበዳይን ማዞር (Victim Reversal) ↖️↖️↖️↖️↖️↖️↗️↗️↘️↘️↖️↗️ ይህ ስልት ተጠቂ የሆኑትን አካላት መልሶ አጥቂ አስመስሎ ማቅረብ ነው። ለምሳሌ በሕግ አግባብ ቅጣቱን ማግኘት የሚገባውን ወንጀለኛ ተግባር ችላ በማለት በንዴት ዛቻ መሰል ይዘት ያለው ንግግር ያደረጉ ሙስሊሞችን ንግግር ደጋግሞና በብዛት ተቀባብሎ በማቅረብ “ሙስሊሞቹ ሊገድሉት ስለሆነ ህይወቱ አደጋ ውስጥ ነው” በማለት ግለሰቡን አጥቂ ሳይሆን ተጠቂ አድርጎ የማቅረብ ስልት ተከትለዋል። ህብረተሰቡን “ጀግናችሁን ተከላከሉ” በሚል አቀራረብ  በዙሪያቸው ኃይል ለማሰባሰብ ስሜት ኮርኳሪ ይሆናሉ ብለው ያሰቧቸውን ዘገባዎች በቆርጦ-ቀጥል ስልት በመጠቀም እውነታውን ለማዞር ሲዳከሩ ታይተዋል። 6/ አጀንዳ ማስለወጥ (Agenda Shifting) 💧💧💧💧💧💧💧💧💧💧💧💧💧

መረዳት ••• ከ5ቱ የመ ሕጎች የመጀመሪያው! መብትን ከተነጠቁበት ቦታ መልሶ ለመውሰድ የመጀመሪያው እርምጃ መረዳት ነው:: አንድ ሰው እንደ ዜጋ በሀገሩ ውስጥ ያለውን መብት መረዳት ማለት ነው:: አንድ ሰው እንደ ሰብዓዊ ፍጡር ያለውን መብቱን መረዳት ማለት ነው:: የመብቱን ዋጋ መረዳት ማለት ነው:: ለነፃነቱ ••• ለእኩልነቱ ••• ለመብቱ እና ለክብሩ ሊከፍል የሚገባውን ዋጋ መረዳት ማለት ነው:: የነፃነቱን የእኩልነቱን የመብቱን እና የክብሩን ዋጋ መረዳት ማለት ነው:: ካልተረዳና ካልገባው ግን ••• እየተጨቆነ እንኳ በነፃነት የኖረ ያክል ይሰማዋል:: መጨቆኑን አውቆ እንኳን የነፃነትን ዋጋ አሳንሶ ይመለከታል:: የነፃነቱን ዋጋ ተረድቶ እንኳን ሊከፍል የሚገባውን መስዋዕትነት ይዘነጋል::: እናስ? እናማ ••• ስለ መብቶቻችን ሁሉን አቀፍ መረዳት ሊኖረን ይገባል:: ልናስረዳም ግድ ይለናል:: @EHEMSU

መብትን ለማስመለስ የሚረዱ 5ቱ የመ ሕጎች! • መረዳት • መጠየቅ • መታገል • መታገል • መታገል https://t.me/EHEMSU

Yunivarsiiti jiimmaatti rakkoon Niiqaaba wajjin wal qabate Uumamee turee hiikamuu isaa jama'aa barattoota Musliima yunivarsiiti jiimmaa beeksiiseera. Allaahu Akbar!!!!!!! https://t.me/EHEMSU

Once again መብት በትግል እንጅ በልመና አይገኝም! https://t.me/EHEMSU

በጅማ ዩኒቨርሲቲ ከኒቃብ ጋር ተያይዞ ተፈጥሮ የነበረው ችግር እንደተፈታ የጅማ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ አሳውቋል:: አላሁሁ አክበርርርር ! https://t.me/EHEMSU

Jamaa'a barattoota yunivarsiiti walloo Yunivarsiitichi Baruumsa, Qormaata fi Sagantaawwan Guyyaa jumu'aa sa'ati 5:00-7:30tti keennaman irratti sirreeffama akka taasiisu gaafate! Jamaa'aan yunivarsiitichaa waajjira prezdaantii itti aanaa dhiimma aakkaadami yunivarsiitichaatti akka beeksiseetti Sagantaawwan guyyaa jumu'aa Sa'ati 5:00-7:00tti keennamaa jiran barattoota musliimaa Salaata ykn Baruumsa Akkasumas Baruumsa ykn kaaffe keessaa tookko akka filatan isaan dirqiisisaa Baruumsa isaan irratti dhiibba hin barbaachiisnee geessaa jiraa. Guyyaa jumu'aa manneen Hojii mootummaa kamu Sa'ati 5:00-7:30 Hojii ala ta'u isaani seeraan kan murtaa'ee akka ta'ee ibsun sirreffama hatattamaa akka taasifamu gaafateera. https://t.me/EHEMSU

የወሎ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ ዩኒቨርሲቲው በጁምዓ ቀን ከ5:30 እስከ 7:30 ባለው የጊዜ ልዩነት የሚሰጣቸው የትምህርት የፈተና እና መሠል ፕሮግራሞች ላይ ማስተካከያ እንዲያደርግ ጠየቀ!
የወሎ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ ዩኒቨርሲቲው በጁምዓ ቀን ከ5:30 እስከ 7:30 ባለው የጊዜ ልዩነት የሚሰጣቸው የትምህርት የፈተና እና መሠል ፕሮግራሞች ላይ ማስተካከያ እንዲያደርግ ጠየቀ! ጀመዓው ለዩኒቨርሲቲው አካዳሚክ ጉዳዮም ምክትል ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ላይ እንደገለፀው በጁምዓ ቀን ከ5:30 ቡሃላ እና ከ7:30 በፊት እየተሰጡ ያሉ ፕሮግራሞች ሙስሊም ተማሪዎችን በጁምዓ ሶላት እና በትምህርታቸው ብሎም በካፌ አግልግሎት መካከል እንዲመርጡ እያስገደደ በትምህርታቸው ላይ አሉታዊ የሆነ ተፅዕኖ በመፍጠር ላይ ይገኛል:: ጁምዓ ቀን በሁሉም የመንግስት መስሪያ ቤቶች እና በአንዳንድ መስሪያ ቤቶች በሕግ እንደፀናው ከ5:30 እስከ 7:30 ከስራ ውጭ መሆኑን ጠቅሶም አስቸኳይ የሆነ ማስተካከያ እንዲደረግ አሳስቧል:: https://t.me/EHEMSU

“ummata kiyyarraa anaaf jaalala cimaa kan qaban ka ana boodaan  dhufantu jira. Tokkoon isaanii maatii isaatii fi qabeenya isaa  naaf wareegama godhee na arguu jaalata.” Ergamaa Rabbii (ﷺ) https://t.me/EHEMSU

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠይቁ ባሉት መሠረት ተማሪው በትምህርት ስርዓቱ ውስጥ ያለውን ጥያቄ እያቀረበ ነው! አሁንም ገና ነው ጥያቄዎቻችንን እናስገባ! ቅሬታ ማቅረቢያው https://www.facebook.co
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠይቁ ባሉት መሠረት ተማሪው በትምህርት ስርዓቱ ውስጥ ያለውን ጥያቄ እያቀረበ ነው! አሁንም ገና ነው ጥያቄዎቻችንን እናስገባ! ቅሬታ ማቅረቢያው https://www.facebook.com/share/p/1LNAiWkmeA/ ነው:: መብት በትግል እንጅ በልመና አይገኝም! https://t.me/EHEMSU

# Waajjiri Mummee ministeraa gaaffiiwwan keessan barumsaan , fayyaadhaan , ikonomii fi wantoota bu'ura ta'an kaanin walqabatan gaafadhaa. Qaamni dhimmichi ilaallatu deebii ni kenna jedhe jira. Kanaafuu nuti gaaffiwwan barattootni muslimaa mana barumsaa kessatti qabnu fi akkasumas gaaffiwwan uffata obboleettiwwan keenya hijabaa fi niqaaba ilaalchisee akkasumas dhimma karaa qilleensaan ( airportin) walqabatee jiru dafnee ha gaafannu . Jalqaba linki kanaan gara postichaa seenaa . https://www.facebook.com/share/p/1LNAiWkmeA/ San booda gaaffiwwan armaan gadi koomanti irratti barressaa ergaafi. Warri dandeessan copy paste gochurra yaaduma keessanin barressa. Kabajamoo mummicha ministera akkuma ibsitanitti gaafilee qeebaluuf qophii tahu keessaniif galatooma. Nuti muslimoonni barnootaafi dhabbata mootummaa keessatti keessattu dubartiin muslimaa sababa hijaabaa fi niqaabaan akkasumas akkata raawwii solaataan walqabate bilisummaan amanti keenyaa sarbamu jiraachu isaa sin beeksisu barbaadna . # barnootaa fi hojiiwwaan kan irratis ta'e mirga dubartoota muslimaa ilaalchisee heera itoophiyaa keewwata 27 irrati ifaan akkuma ibsametti namni kamu amantaa filate hordofuu, gabbaru fi ibsachu mirga qaba. Haa ta'u malee qabatamaan : 2ffa damee barnootaan : naannoowwan garagaraa ( fknf godina guraagee aanaa gunchireetti , aksuum , yuniivarsitii dillaatti ,yuniivarsitii jimmaatti , yuniivarsitii addis abaabaafi kkf....) Niqaaba ,Hijaaba fi uffata amantaa islaamaa mulli'isan kan sababa uffachuu isaanitiin barnoota isaani irra arihamaa jiru. ( fkf gunchireetti bara 3 isaan guute jira . ) Yeroo qormaata biyyoolessaa sababa uffannaa isaanitiin akka qormaata hin fudhanne godhamaa jiru.(fkf barattootni muslimaa aksuumitti formi hin guunne, hanga harra yeroo qormaata irra taa'an uffata keessan baasa kan jedhaman jiru ) sarbamu fi dhiibamun mirgaa irraan gahamaa jira. solaataan walqabatees mirgi isaani daangeffamaa jira . Gaaffiin keenya : mootummaan dubartoonni muslimaa mirgi isaani eeggameefi sodaa tokko malee barumsa isaani akka hordofan tarkaanfiin qabatamaan fudhatamaa jiru maali ?? furmaannis yoom kennama ?? 4ffaa Dhaabbata mootummaa ( fknf karaa qilleensaa keessatti ) Dhiirri muslimaa areeda isaanii fi akka amantaan isaani ajajutti uffatani akka hin qacaramne ugguramaa jiru . Dubartootni hijaaba uffatanis akkasuma akka hin hojjanne dhorkamaa jiru. gaafin keenya mootummaan dhaabbanni heeraa fi seeraan ala mirga amantii namaa dhiiban akka waan kana sirreessan tarkaanfiin fudhatamaa jiru maali ?? Gaaffi yaachiisaa kana deebii fi ibsa ballaa hatattamaan akka nu kennitan fi furmaata akka nuuf kennitan kabajaan isin gaafanna . https://t.me/EHEMSU

ይህ የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች ጥያቄ ነው ••• ለኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶክተር አብይ አህመድ! ጠይቁን ብለዋልን ጥያቄዎቻችንን በጨዋ ደንብ አሰናድተን እንጠይቅ:: መልስ እንሰጣለን ብለዋልና
+2
ይህ የኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች ጥያቄ ነው ••• ለኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስቴር ዶክተር አብይ አህመድ! ጠይቁን ብለዋልን ጥያቄዎቻችንን በጨዋ ደንብ አሰናድተን እንጠይቅ:: መልስ እንሰጣለን ብለዋልና መልሳቸውን እናውቅ ዘንድ ጥያቄዎቻችንን እናቅርብ:: ሁላችንም እንጠይቅ ••• ለጥያቄያችን ትኩረት እስኪሰጡ ድረስ ••• ድምፃችንን ሰምተው መልስ እስኪሰጡ ድረስ! ቅሬታ ማቅረቢያው https://www.facebook.com/share/p/1LNAiWkmeA/ ነው:: መብት በትግል እንጅ በልመና አይገኝም! @EHEMSU

በሚጠየቁ ጥያቄዎች ዙሪያ የሚመለከታቸው የሥራ ሀላፊዎች ተገኝተው ማብራሪያ እንደሚሰጡ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፅ/ቤት አሳውቋል:: የተደገሰልን ምን እንደሆነ እናውቅ ዘንድ እንጠይቅ ••• ስለ መብቱ የቆመ
በሚጠየቁ ጥያቄዎች ዙሪያ የሚመለከታቸው የሥራ ሀላፊዎች ተገኝተው ማብራሪያ እንደሚሰጡ የጠቅላይ ሚኒስትሩ ፅ/ቤት አሳውቋል:: የተደገሰልን ምን እንደሆነ እናውቅ ዘንድ እንጠይቅ ••• ስለ መብቱ የቆመ ትውልድ እንዳለ ያውቁ ዘንድ እንጠይቅ ••• መብቱን ለመውሰድ የተዘጋጀ ትውልድ እንዳለ ይረዱ ዘንድ እንጠይቅ! ቅሬታ ማቅረቢያው https://www.facebook.com/share/p/1LNAiWkmeA/ ነው:: መብት በትግል እንጅ በልመና አይገኝም!

ይህንን ሀላፊነት መወጣት ቀላል ቢሆንም እያደረግን ላለው ሁሉን አቀፍ ትግል ግን ትልቅ ሚና ይጫወታል:: መብታችንን ለማስመለስ በምናደርገው ትግል ጥቂት ነው ብለን የምንተወው ሚና የለም:: ዛሬ የምንወረውራት ጠጠር ተደምራ ተራራን ትሰራለች ••• ኢንሻ አላህ!