en
Feedback
Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union

Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union

Open in Telegram

This is the official Channel of Ethiopian Higher Education Institutions Muslim Students' Union.

Show more
4 478
Subscribers
+324 hours
-27 days
+2930 days
Posts Archive
Kaawunsilin Dargaggoota musliima Ityoophiyaa, Dillaatti argamun barattoota musliimaa yunivarsiiti diillaa wajjin mari'ateera. https://t.me/EHEMSU Bilisummaan bilisaan hin argamu!

የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል በዲላ በመገኘት ከዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጋር ተወያይቷል:: WELL DONE😍 ነፃነት በትግል እንጅ በነፃ አይገኝም! @MohammadamminKassaw
+1
የኢትዮጵያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል በዲላ በመገኘት ከዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጋር ተወያይቷል:: WELL DONE😍 ነፃነት በትግል እንጅ በነፃ አይገኝም! @MohammadamminKassaw

የፌደራል መጅሊስ ስለ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ለትምህርት ሚኒስቴር ደብዳቤ ፅፏል:: የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች በአፋጣኝ ወደ ትምህርታቸው እንዲመለሱ ብሎም ችግሩን በሀገር አቀፍ ደረ
የፌደራል መጅሊስ ስለ ዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ለትምህርት ሚኒስቴር ደብዳቤ ፅፏል:: የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች በአፋጣኝ ወደ ትምህርታቸው እንዲመለሱ ብሎም ችግሩን በሀገር አቀፍ ደረጃ በዘላቂነት እንዲፈታ ሲል አሳውቋል:: https://t.me/EHEMSU

ዲላ ዩኒቨርሲቲ የዩኒቨርሲቲው ኒቃቢስት መምህራንንም በኒቃብ መግባት እና ማስተማርን ከለከለ! •••••••••••••••••••••••••••••••••••••• በዲላ ዩኒቨርሲቲ ለአመታት እስልምናዋ የሚያዛትን ኒቃብ ለብሳ ስታስተምር የነበረች ሌክቸር ከትላንት ጀምሮ "ወይ ስራሽን ወይ ኒቃብሽን ምረጪ?" የሚል ትዕዛዝ እንደተላለፈላት ተገልፇል:: "ስራዬንም እምነቴንም ይዤ እቀጥላለሁ!" የሚል መልስ ብትሰጥም ለመጨረሻ ማስጠንቀቂያ እና ክልከላ በዛሬው እለት ጠርተዋታል:: በተማሪዎቹ ላይ እያደረሰ ያለው ግፍ አይበቃው ያለው ዲላ ዩኒቨርሲቲ ወደ እስታፍ ሰራተኞችም ተሸጋገረ:: ይህ ግልፅ የሆነ ሙስሊም ጠልነት ነው:: አዳጊ ወጣቶችን ከግቢ ውጭ ያለምግብ ያለትምህርት ያለማደሪያ የሚያሳድረው ተቋም የሀገሪቱን እናቶችንም በእምነት እየለዬ ማስለቀሱን ጀመረ:: ይህ አውሬያዊ ጭካኔ የተሞላበት ግፍ ነው! ፍትሕ ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች! ፍትሕ ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም መምህራን! ፍትሕ ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ማህበረሰብ! ፍትሕ ለኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች! ፍትሕ ለኢትዮጵያ ሙስሊሞች! https://t.me/EHEMSU

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በዲላ ዩኒቨርሲቲ እየተፈፀመ ስላለው የመብት ጥሰት ለፌደራል መጅሊስ አቤት ብሏል! ፍትሕ ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት!
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት በዲላ ዩኒቨርሲቲ እየተፈፀመ ስላለው የመብት ጥሰት ለፌደራል መጅሊስ አቤት ብሏል! ፍትሕ ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት!

ኒቃብ በጉንችሬ ተከልክሏል ኒቃብ በAAU ተከልክሏል ኒቃብ በአክሱም ተከልክሏል ኒቃብ በሰላሌ ተከልክሏል ኒቃብ በጂማ ተከልክሏል ኒቃብ በዲላ እየተከለከለ ነው • • • • • ዝምታችን በዚህ ከቀጠለም በሁሉም ቦታ ይከለከላል:: በዚሁ ከቀጠሉም ከትምህርት ቤት ባሻገር በመኖሪያ ቤትም መከልከላቸው አይቀርም:: ዝምታ ይብቃ ! ፍትሕ ለኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች! https://t.me/EHEMSU

Kun Ityophiyaatti magaala diilla keessatti... Hammana garaa waljabaanne jirraa? Ilaalaa...Hunduu akka beekus Share goodhaa! Mutaniqqibootaa dukkana keessaa yeroo isaan deebisan mul'ata. Galu hin dandeessani jeechun mooraa hanga har'aatti seenani itti barachaa turan irraa isaan deebisan. Eessatti haa buulan? Eessatti haa baratan? Kan illee hin yaadani? Namuummaan hin jiru? Hanga kana bineensa ta'aniru. Yunivarsiiti diillaa keessatti Islaamaa fi muslimootaaf jibiinaa hangana gahuu tulamee jiraa! Haqa barattoota yunivarsiiti dillaaf Haqa barattoota musliimaa yunivarsiiti Ityoophiyaaf

Gamtaan barattoota musliima dhaabbilee Olaanoo Ityophiyaa Midiyaa Harun walin Marii taasiise! Kaleessa Amajji 13/2017 A.L.I Hogantoonni Gamtaa barattoota musliimaa dhaabbilee barnoota Olaanoo Ityophiyaa, muslimoota ilaalchisee Hojii gaggeessaa Midiyaa Harun jan ta'an Bahru Abbaas waliin  marii bal'aa taasiisaniiru. Sarbiinsa miirga fi qabsoo barattoota musliima ilaalchiise marii kan goodhamee yoo ta'uu jijjirama fiduf shoorri midiyaachi qabus ka'ee jiira. Midiyaan Harun qabsoo barattoonni musliima  cunqursaan isanirratti gahaa jiruu yeroo dhumaaf fala akka argatu taasiisaa jiran bukkee dhaabbachun itti gaafatamuummaa inni bahaacha jiruf kabaja guddaa qabnaa. Cunqursii barattoota musliima irratti gahaa jiru Mormu fi fala barbaadu irratti, Nammoonni bebbekamoo, dhabbattotaa fi hoggantoonni gahee isaani akka bahaatan waammicha keenyaa in dhiyeessiinaa. Gamtaa barattoota Musliima dhaabbilee Ol'aanoo Ityophiyaa. https://t.me/EHEMSU

ሌላው ይቅር ••• ሴት ልጅ ፀንሳ አልወለደቻቸውም? ሴት ልጅስ የላቸውም? ነገ በእኔ ብለው አያስቡም? እንዴት ቢጨከን ነው ሴት ልጅ ክብሬን ልልበስ ገላዬ ይሸፈን ስላለች ብቻ ልትኖርበት ልትማርበት
+1
ሌላው ይቅር ••• ሴት ልጅ ፀንሳ አልወለደቻቸውም? ሴት ልጅስ የላቸውም? ነገ በእኔ ብለው አያስቡም? እንዴት ቢጨከን ነው ሴት ልጅ ክብሬን ልልበስ ገላዬ ይሸፈን ስላለች ብቻ ልትኖርበት ልትማርበት ከገባችበት ዩኒቨርሲቲ በምሽት 3:00 አትገቢም ተብላ የምትመለሰው? ይህ ሁሉንም ይመለከታል ••• ዜጎቹን በፍትሕ ሊያስተዳድር ቃለ-መሐላ ገብቶ ከወንበር የተቀመጠውን መንግስት ይመለከታል:: የሙስሊሞችን መብት እና ጥቅም ሊያስከብር የተቋቋመውን መጅሊስ ይመለከታል:: ስለሙስሊሞች እንጨነቃለን ብለው የሚያስቡትን ሁሉ ይመለከታል:: ሙስሊሙን ማህበረሰብ ሁሉ ይመለከታል:: ሰብዓዊ ፍጡርን ሁሉ ይመለከታል:: ••• የኢትዮጵያ ልጆችን ሊያስምር በኢትዮጵያ ህዝብ የተገነባው ዲላ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ ልጆችን ሙስሊም ሆነው ሒጃብ ስለለበሱ ብቻ በምሽት ከበር እየመለሰ ነው:: ይህ ለመላው ኢትዮጵያ ውርደት ነው ••• በራስ እጅ መነከስ ያማል! ፍትሕ ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች! ፍትሕ ለኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች!! @MohammadamminKassaw

ይህ ኢትዮጵያ ውስጥ በዲላ ከተማ ነው ••• የዚህን ያክል ተጨካክነናል? ተመልከቱት ••• ሁሉም ያውቀው ዘንድም Share አድርጉት! ኒቃቢስቶቹን በጨለማ ያለምንም ርህራሄ ሲመልሷቸው ይታያል:: አትገቡም ብለው ••• እስከዛሬ ገብተው ሲማሩበት ሲኖሩበት ከነበረው ግቢ መለሷቸው:: የት ይደሩ? የት ይማሩ? ይህንን እንኳን አያስቡም? ሰብዓዊነት የለም? የዚህን ያክል አውሬ ሆነዋል:: ለእስልምና እና ለሙስሊሞች በዲላ ዩኒቨርሲቲ ከባድ የጥላቻ ክምር ተቆልሏል:: ፍትሕ ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች! ፍትሕ ለኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች! @MohammadamminKassaw

ዲላ ዩንቨርስቲ "ኒቃብ" የደህንነት ስጋት ነው በሚል ሙስሊም ተማሪዎችን ከትምህርት ገበታ ካገደ አምስት ቀናት መቆጠሩ ተገለፀ! - ከትምህርት የታገዱ ሙስሊም ተማሪዎችም የሚመለከተው አካል አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል። ሀሩን ሚድያ፥ ጥር 14/2017፣ ደቡብ ስቱድዮ በደቡብ ኢትዮጲያ ክልል ጌድኦ ዞን ውስጥ የሚገኘው ዲላ ዩንቨርስቲ ኒቃብ የደህንነት ስጋት ነው በሚል ሙስሊም ተማሪዎችን ከትምህርት ገበታ ውጪ ካደረገ አምስት ቀናት መቆጠሩን ተማሪዎቹ ለሀሩን ሚድያ ተናግረዋል። በዲላ ዩኒቨርሲቲ የሚማሩ ሙስሊም ተማሪዎች በተጣለው የኒቃብ ክልከላ የሚማሩበትን ግቢ ለቀው የወጡት ቅዳሜ ጥር 10/2017 መሆኑ የተገለፀ ሲሆን ክልከላውን የጣሉት የዩኒቨርሲቲው ሁለት ካምፓሶች ናቸው፡፡ ካምፓሶቹም ነባሩ ግቢ እና ኦዳያ የተሰኙት መሆናቸው ተገልጿል፡፡ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታትም ሰኞ ጥቅምት 12/2017 ዓ.ል ከሙስሊም ተማሪዎች ተወካዮች ጋር ውይይት ያደረገው የዲላ ዩኒቨርሲቲ አስተዳደር "ኒቃብ ለደህንነት ስጋት ስለሆነ በግቢ ውስጥ ለብሶ መግባትም ሆነ መንቀሳቀስ አይቻልም" የሚል መልስ እንደሰጣቸው ተማሪዎቹ አሳውቀዋል። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የጌድኦ ዞን እስልምና ጉዳች ምክር ቤት ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ጽሕፈት ቤት ጥር 5/2017 በጻፈው ደብዳቤ፤ የተጣለው ክልከላ ተገቢ እንዳልሆነ በማሳወቅ ተቃውሞውን አቅርቧል፡፡ ምክር ቤቱ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የዑለማ ጉባዔ ባለፈው ታኅሣሥ ወር በሰጠው ፈትዋ (ብይን) “ማንኛውም አካል ወይም ግለሰብ” የፈጣሪ ትዕዛዝ የሆነውን አለባበስ “መከልከልም ሆነ ማደናቀፍ” እንደሌለበት ማሳሰቢያ መስጠቱን በማስታወስ ተማሪዎች የተወጡት ኢስላማዊ ግዴታ መሆኑን ጠቁሟል። በተጨማሪም የከፍተኛ ተማሪዎች የዲሲፕሊን መመሪያ፤ በዩኒቨርሲቲ ቅጽር ግቢ የተከለከሉ ተግባራትን በሚዘረዝርበት ጊዜ “ፖለቲካዊ እና ሃይማኖታዊ መልዕክት ያላቸውን አልባሳት፣ ቅርጻ ቅርጽ፣ ጌጣጌጥ፣ የተለያዩ ቦርሳዎችና መያዣዎችን መጠቀም” የሚለውን ከማንኛውም ሃይማኖታዊ አለባበስ ጋር ማያያዝ፤ “የብሔር ወይም የሃይማኖት ማንነትን ሳያወልቁ የትምህርት ቅጥር ግቢ ውስጥ መግባት አይቻልም እንደማለት” መሆኑንም አብራርቷል፡፡ አያይዞም የተከለከሉ አለባበሶች ዝርዝር ውስጥም ቢሆን የሙስሊም ሴቶች ኢስላማዊ አለባበስ እንደሌለ የመመሪያውን አንቀጽ 7 ቁጥር 17.2ን በመጥቀስ አፋጣኝ መፍትሄ እንዲሰጣቸው ጠይቋል። ▣ ሀሩን ሚድያ በዲላ ዩንቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ዙሪያ ተጨማሪ መረጃዎችን እንደምናደርስ ለመግለፅ እንወዳለን። © ሀሩን ሚድያ https://t.me/EHEMSU

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ከከሀሩን ሚዲያ ጋር ተወያየ! •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ትላንት ማለትም ጥር 13/2017 ዓ.ል
የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ከከሀሩን ሚዲያ ጋር ተወያየ! •••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ትላንት ማለትም ጥር 13/2017 ዓ.ል የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ከፍተኛ አመራሮች በሙስሊሙ ማህበረሰብ ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ ዙሪያ ከሚንቀሳቀሰው ሀሩን ሚዲያ ዋና ማናጀር አቶ ባህሩ አባስ ጋር ሰፊ ውይይት አድርገዋል:: በውይይቱም ስለ ሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጭቆና እና ትግል ዙሪያ ዳሰሳ የተደረገ ሲሆን አዎንታዊ ለውጥ በማምጣት ረገድ ሚዲያው ሊኖረው ስለሚችለው አስተዋፅዖም ተነስቷል:: ሀሩን ሚዲያ ሙስሊሙ ተማሪ እየደረሰበት ያለውን ግፍ ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ለመቋጨት እያደረገ ያለውን ትግል ከጎን ሆኖ በማገዝ እያደረገ ለሚገኘው ታረካዊ ሀላፊነት አክብሮታችንን እንገልፃለን:: በሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍ በመቃወም እና መፍትሔ በመፈለግ ረገድ ታዋቂ ግለሰቦች: ተቋማት እና አመራሮችም የበኩላቸውን አስተዋፅዖ በማበርከት በሀላፊነታቸውን ይወጡ ዘንድ ጥሪያችንን እናቀርባለን:: የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት! https://t.me/EHEMSU

ድላ ዩኒቨርሲቲ ታስሮ የነበረው ወንድማችን ጧት ላይ ተፈትሏል:: አልሐምዱሊላህ ••• ትግል ይቀጥላል:: ፍትሕ ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች! ፍትሕ ለኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች! https://t.me/EHEMSU

ይደንቃል ••• ቁራጭ ልብስ ጣል አድርጎ መንቀሳቀስ ከነፃነት ተቆጥሮ ሰውነቴን ልሸፍን በሚል ሰልፍ ይወጣል:: ጥያቄ ይጠየቃል:: ትግል ይደረጋል:: ግን ሀገራችንን የሚመሩ ሰዎች እሳቤ ምን ያክል ቢያጥር ነው የዚህን ያክል ከሕግ እና ከጤና ያፈነገጠ ጭቆና የነገሰው? ያም ሆነ ይህ ግን አጥፊዎች ሳይፈሩ ሳያፍሩ እያጠፋ እኛ ለሐቅ እና ለነፃነት ማፈር እና መፍራት አይጠበቅብንም:: ነፃነት በነፃ አይገኝምና! https://t.me/EHEMSU

ዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎችን ማሠር ጀምሯል! ላለፉት አመታት በነፃነት ሲለበስ የነበረውን ኒቃብ ከልክሎ ሙስሊም ተማሪዎችን ማንገላታት የጀመረው ዲላ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ወደማስፈራራት እና ማሳሰር እንደተሸጋገረ ተገልፇል:: እስካሁንም ከኦዳያ ካምፓስ አንድ ሙስሊም ተማሪ ታስሯል:: ኒቃብ ለባሽ እህቶች ግቢ መግባት አትችሉም ከተባሉ ከዛሬ ጋር 4ተኛ ቀናቸውን የያዙም ሲሆን መስጂድ ውስጥ ከተማሪዎች እና ከትምህርት ርቀው እንደሚውሉና እንደሚያድሩም ታውቋል::   የነፃነት እና እኩልነት ጥያቄን በማስፈራራት እና በማሰር ማቆም አይቻልም:: ፍትሕ ለዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች! ፍትሕ ለኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች! https://t.me/EHEMSU

Cunqursa adda baasani beekun ka'uumsa qabsooti... Cunqursa irratti duuluf karaa jalqabun immo xumuura qabsiichaaf isa jalqabaati... Jaallewwan keenya kan tigraay keessa jiran kan nutti himanis, kan nutti agarsiisanis kanuma. Cunqursi yeroo dheraaf isaniitti fe'ame ture diiduu isaani ifattii agarsiisaniru.. Gabruummaa wajjin wal jaalachun itti fuufu akka hin nandeenye ifaan ibsaniru. Biliisummaa barbaadu fi ta'ani ilaalun walitti deemu akka hin dandeenyes agarsiisaniru. Raayyaan yeroo mu'tasim billaah Hijaabaaf jeedhe dulee nu yaadachiisaniru. Aarsaawwan hijaabaaf kaffalamu danda'an haalaan ibsaniiru. Uummaan nabii har'as haafura baasaa jiraa...Dhaalmaan najaashi isa sirri har'as ilmoole ilma isaa harka jiraa...Ashaaraan bilaal har'as ni jiraa!

ሒጃቤ መልኬ ነው!" - ከመቋለ የተሰማ የሚነዝር መፈክር ••• እውነት ነው ••• መልክ ደግሞ አይገፈፍም! @MohammadamminKassaw

መበደልን ማወቅ የትግል መነሻው ነው ••• በደልን ለመዋጋት መንገድ መጀመር ደግሞ ለትግሉ መጨረሻ መጀመሪያው ነው ••• ትግራዋይ ወዳጆቿችን ያሳዩን የነገሩን ይህንኑ ነው ••• ለዘመናት ተጭኗቸው የ
መበደልን ማወቅ የትግል መነሻው ነው ••• በደልን ለመዋጋት መንገድ መጀመር ደግሞ ለትግሉ መጨረሻ መጀመሪያው ነው ••• ትግራዋይ ወዳጆቿችን ያሳዩን የነገሩን ይህንኑ ነው ••• ለዘመናት ተጭኗቸው የነበረውን የጭቆና ክምር እምቢ ብሎ ከልቦናቸው ተፍተዋል ••• ከባርነት ጋር ተዋደው መቀጠል እንደማይችሉ በግልፅ ተናግረዋል ••• ነፃነትን መፈለግ እና ቁጭ ብሎ መመልከት አብረው ሊሄድ የሚችሉ ጉዳዮች እንዳልሆኑ ገልፀዋል ••• ለሒጃብ ሲባል ሙዕተሲም ቢላህ ያዘመተውን ሰራዊት አስታውሰውናል ••• ለሒጃብ ሲባል ሊከፍሉ የሚችሉትን መስዋዕትነት በቁጭት እና ወኔ ገልጠዋል:: የነቢ ኡማ ዛሬም እየተነፈሰ ነው ••• ትክክለኛው የነጃሺ ውርስ በልጅ ልጆቹ እጅ ዛሬም አለ ••• የቢላል አሻራ ዛሬም አልከሰመም! @MohammadamminKassaw

የትግራይ መጅሊስ ስለሒጃብ እየተደረገ ያለውን ትግል መቋለ ላይ ባካሄደው 3KM የሚረዝም ሰልፍ አቀጣጥሎታል:: አክሱም ላይ ላለው ችግር መፍትሔ የሚያፈላልጉ 11 ሰዎችን እንዳስቀመጠም አሳውቋል:: ይህ ለሴት ልጅ ክብር ሲባል የሚከፈል ትንሹ መስዋዕትነት ነው ••• ትግራዋይ ሙስሊሞች ትልቅ ሆነው ያስተማሩን ••• ብዙ ትምህርት ሰጥተውናል ••• ውድድድ😍 ፍትሕ ለአክሱም ሙስሊም ተማሪዎች! ፍትሕ ለኢትዮጵያ ሙስሊም ተማሪዎች!! @MohammadamminKassaw