358
Subscribers
No data24 hours
-27 days
-230 days
Data loading in progress...
Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
February '25
February '25
+1
in 0 channels
January '25
+99
in 2 channels
Get PRO
December '240
in 1 channels
Get PRO
November '240
in 0 channels
Get PRO
October '240
in 1 channels
Get PRO
September '24
+45
in 0 channels
Get PRO
August '24
+222
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 11 February | 0 | |||
| 10 February | +1 | |||
| 09 February | 0 | |||
| 08 February | 0 | |||
| 07 February | 0 | |||
| 06 February | 0 | |||
| 05 February | 0 | |||
| 04 February | 0 | |||
| 03 February | 0 | |||
| 02 February | 0 | |||
| 01 February | 0 |
Channel Posts
አስተርዮ ማርያም
በዘመነ አስተርዮ የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መገለጥ የሆነበትና የአምላካችን አንድነትና ሦስትነት የተገለጠበት ብቻም ሳይሆን በጥር ፳፩ የከበረች እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም የዕረፍት ቀን በመሆኑ “አስተርዮ ማርያም” በማለት በዓልን አናደርጋለን፡፡
የአምላክ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ምድር ላይ ፷፬ ዓመታትን ከኖረች በኋላ መንፈስ ቅዱስ ባስገነዘባት መሠረት በክብር ዐርፋለች፡፡ የዚህን ዓለም መከራና ሥቃይ ለሰዎች ድኅነት የተቀበለችው ክብርት እናታችን በሥጋ ብትሞትም እንደ ልጇ ደግሞ በትንሣኤዋ ተነሥታለች፤ ይህም የሆነው በተቀደሰች ዕለት ነሐሴ ፲፮ ነው፡፡
እመ ብርሃን ከእናትና ከአባቷ ጋር ሦስት ዓመት፣ በቤተ መቅደስ ፲፪ ዓመት፣ ከተወዳጁ ልጅዋ ጋር ፴፫ ዓመት ከሦስት ወር፣ ከጌታችን ዕርገት በኋላ ከወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ጋር ፲፭ ዓመት፣ በድምሩ ፷፬ ዓመት በዚህ በኃላፊው ዓለም ኖራ ጥር ፳፩ ቀን በ፵፱ ዓመተ ምሕረት በክብር ዐርፋለች፡፡
ክርስቲያኖች በሙሉ ይህንን በዓል ልናከብር ይገባልና ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓትን ሠርታልናለች፡፡ “አስተርዮ ማርያም” በሕዝበ ክርስቲያን ዘንድ የሚከበር በዓል በመሆኑ በሀገራችን ኢትዮጵያ እና በመላው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ማኅበረሰብ ዘንድ በድምቀት ይከበራል፡፡ በዓሉን የምናከብረውም የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ከዚህ ዓለም ድካም ማረፍ በማዘከር ብቻ ሳይሆን አማላጅነቷና ተረዳኢነቷን በማሰብና ተስፋ በማድረግ ነው፡፡
ስለዚህም እመ ብዙኃን እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዐሥራት ሀገሯን ኢትዮጵያን እንድታስባት፣ ለእኛም ለሕዝቦቿ ሰላምን፣ ፍቅርንና አንድነትን ታሰጠን እንዲሁም ለነፍሳችን ድኅነትን ትለምልን ዘንድ ዕረፍቷን መዘከር ይገባል፡፡
የአምላካችን እግዚአብሔር ቸርነት፣ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነትና ተረዳኢነት አይለየን፤ አሜን!!!
#ማህበረ_ጳውሎስ https://t.me/Stpoulos
| 2 | https://youtu.be/lLNp_D4b_Xo?feature=shared | 235 |
| 3 | ያልተመዘገባችሁ
ወልድያ የጥምቀት አስተባባሪ በመሆን ለማገልገል የምትፈልጉ ሰዎች ካላችሁ የተወሰኑ ቦታዎች አሉ በውስጥ አናግሩኝ @Abellteferaaa | 449 |
| 4 | ጥር 4 ማለትም ነገ እሁድ 8:30 አዳጎ ፀደይ ባንክ 4ኛ ፎቅ የብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ወርሃዊ የጽዋ እና የወንጌል ድግስ ያዘጋጀን ሲሆን እርሰዎም ወዳጅ ዘመድ ጓደኛ በመጋበዝ እንድትገኙ ጥሪ እናስተላልፋለን። | 1 037 |
| 5 | ሳውል የኦሪት ምሁርና ክርስቲያኖችን አሳዳጅ ነበር። ኢየሱስ ክርስቶስ ባረገ በ8ኛው ዓመት (በ42 ዓ.ም) በደማስቆ ከተማ አጠገብ እግዚአብሔር በድንቅ አጠራር ጠርቶታል። (የሐዋ. ሥራ 9፥ 1-30)። በጥላው በሽተኞችን ፈውሷል። በትምህርቱ ብዙዎችን የክርስቶስ ምርኮኛ የመንግስቱ ተካፋይ አድርጓል። በመጽሐፍ ቅዱስ 14 መልእክታትን ጽፏል።
መጠሪያ ስሞቹም፦
፩.ብርሃነ ዓለም
፪.ልሳነ ክርስቶስ
፫.ማኅቶተ ቤተክርስቲያን
፬.የአሕዛብ መምህር
፭.ሳውል
፮.ፈዋሴ ድውያን..
"መልካሙን ገድል ተጋድያለሁ ሩጫዬንም ጨርሻለሁ ሃይማኖትን ጠብቄያለሁ፤ እንግዲህስ የጽድቅ አክሊል ይቆየኛል።" 2ኛ ጢሞ 4፥7
ጥር 4 የብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ጽዋ ማኅበር ወርሃዊ የጽዋ እና የወንጌል ድግስ ያዘጋጀ ሲሆን እርሰዎም ወዳጅ፣ ዘመድ ጓደኛ በመጋበዝ እንድትገኙ ጥሪ እናስተላልፋለን።
አድራሻ፦ አዳጎ ፀደይ ባንክ 4ኛ ፎቅ | 1 165 |
| 6 | ቴሌ ግራም WhatsApp facebook ላይ
Story በማድረግ ለማስታወቂያ ሁላችሁም ተሳተፉ | 463 |
| 7 | ቴሌ ግራም WhatsApp facebook ላይ
Story በማድረግ ለማስታወቂያ ሁላችሁም ተሳተፉ | 481 |
| 8 | No text... | 849 |
| 9 | እንኳን ለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ። መልካም በዓል ይሁንላችሁ። | 503 |
| 10 | ተወዳጆች ዛሬ መጽሐፍ ቅዱስን በተመለከተ የተወሰኑ ነጥቦችን አንስተን ሰለምንመለከት 8:45 ላይ እንዳትቀሩ። በተጨማሪም የልደት መዝሙሮች የተወሰኑት ይጠናሉ። ከጉባኤ በኋላ 11 ሰዓት ላይ ደግሞ ፈተና ይጀምራል። አዳጎ ቤተ ክህነት አዳራሽ ሰለተያዘ መድኃኒዓለም ሰ/ት/ቤት አዳራሽ እንገናኝ። | 742 |
| 11 | ወደ_ዕብራዊያን_የመግቢያ_ማብራሪያ_4.pdf | 1 015 |
| 12 | የተወደዳችሁ የዛሬው መርሐ ግብር 8:30 ይጀመራል። የሀገረ ስብከቱ አዳራሽ ሰለተያዘ አዳጎ ፀደይ ባንክ ሕንጻ ላይ ሁኗል በእግዚአብሔር ፍቅር አደራ እንዳትቀሩ። | 961 |
| 13 | የተወደዳችሁ ወንድሞች እና እህቶች በዚህ ዓመት ያሰብነውን የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ እና ጥናት እቅድ ማስተዋወቂያ መርሐ ግብር እሁድ (ታሕሳስ 6) 8:30 በአዳጎ ፀደይ ባንክ ሕንጻ ላይ ባለው አዳራሽ በልዩ ድምቀት ለማከናወን አስበናል። ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር ያለንን ትስስር ለማሳደግ ይህ መርሐ ግብር ልዩ ኦርቶዶክሳዊ ንቅናቄ እንዲሆን ታቅዷል እና በዚህ መርሐ ግብር መቅረት በፍጹም አይፈቀድም ። በሰዓቱ ከቦታው ለመገናኘት ያብቃን መልካም ቀን | 950 |
| 14 | ሠላም የተወደዳችሁ ተጓዦች" ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።"
1ኛ) የጉዞአችን መኪኖች ዛሬ ህዳር 17 ከቀኑ 9:00 ኪዳነ ምህረት ይቆማሉ ስለሆነም የሚያዘገዩ ከባባድ እቃዎቻችሁን ከወዲሁ ቀድማችሁ ዛሬ እንድትጭኑ። ጠዋት ከባድ እቃዎችን እንደማንጭን ማሳሰብ እንፈልጋለን።
2ኛ) ህዳር 18 ከሌሊቱ 10:30 አዳጎ ሀገረ ስብከታችን ህንፃ ስር በመገኘት 10:50 ለጸሎት ቆመን 11:00 እንወጣለን። 11 ሰዓት ከሞላ ማንንም እንደማንጠብቅ ከወዲሁ እናሳውቃለን።
3ኛ) ለጉዞ የሚያስፈልጉአችሁን የግል ቁሳቁሶች (እቃዎች) መያዝ ሳትዘነጉ በሰዓቱ እንድንገናኝ በትልቅ አደራ አደራ አደራ እያልን እናሳስባችኋለን። | 970 |
| 15 | ይችን ነገር ተመልከቷት እስቲ | 871 |
| 16 | No text... | 1 123 |
| 17 | ታላቅ ሀገር አቋራጭ መንፈሳዊ ጉዞ
በአይነቱ ልዩ እና በርካታ ገዳማት እና አድባራትን የምንሳለምበት ታላቅ መንፈሳዊ ጉዟ ለወልድያና አካባቢው ኦርቶዶክሳዊያን ተዘጋጅቷል። ይህ ጉዞ ሰባት ቀናትን የሚሸፍን ሲሆን መነሻውን ከወልድያ ከተማ ያደርጋል። ከወልድያ ላሊበላ እና በላስታ አካባቢ ያሉትን ገዳማትና አድባራትን አካሎ ጉዞውን ወደ ዋግ ኸምራ በማድረግ ከሰቆጣ ከተማ በቅርብ ርቀት የሚገኘውን መስቀለ ክርስቶስ ፍልፍል ቤተ ክርስቲያንን ከሰቆጣ ከተማ 51 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘውን የበርሃዋ ገነት በመባል የምትታወቀውን ባር ኪዳነ ምሕረትን ተሳልሞ ጉዞውን ወደ ትግራይ ክልል ያደርጋል።
በትግራይ ካሉ የተቀደሱ ቦታዎች መካከል ገር ዓልታ ተራራ ላይ በድንቅ መልክአ ምድር አቀማመጥ ላይ የሚገኘውን አቡነ ይምዓታ ገዳም እና ደብረ ዳሞ በተጨማሪም አብርሃ ወአጽብሃን ተመልክቶ ለህዳር 21 የንግሥ በዓል ወደ አክሱም ጽዮን ማርያም ይገሰግሳል። በክብረ በዓሉ ጽዮን ማርያምን አንግሶ ወደ ሽሬ እንደሥላሴ በማቅናት አቅጣጫውን ወደ ጎንደር ከተማ በማድረግ ታሪካዊቷ የጎንደር ከተማ አቅፋ የያዘቻቸውን ታላላቅ አድባራትን በረከት ተቀብሎ ከሊቀ ሊቃውንት የኔታ ዕዝራ እግር ስር በመቀመጥ ቃለ ምዕዳናቸውን ሰምቶ ከጎንደር ታሪካዊ የነገሥታቶቹን ቤተ መንግሥት ጎብኝቶ ወደ ጎጃሟ እመቤት ወደ ባሕር ዳር ጉዞውን ያቀናል።
በባሕር ዳር በሚኖረን ቆይታ በጣና ደሴቶችን ላይ የሚገኙትን ገዳማትን ለመሳለም ሁለት ቀን የባሕር ላይ ጉዞ ተዘጋጅቷል። በዚህ የሁለት ቀን የባሕር ጉዞ ላይ ከ17 ያላነሱ በጣና ደሴቶች ላይ የሚገኙ ገዳማትና አድባራትን ለማየት ከቦታው የሚገኘውን በረከት ለመካፈል የቅዱሳን ፈለግ ተከትሎ የጉዞ እቅዱን አውጥቷል።
መነሻ ወልድያ ከተማ ሕዳር 18
በዚህ ጉዞ ላይ ለመሳተፍ የአንድ ሰው የትኬት ዋጋ 5700 ብር ነው። 0913920421 እና 0921047323 ትኬቱን ለመቁረጥ በእዚህ ስልክ ቁጥሮች መደወል ይቻላል። ሰለጉዞው የበለጠ መረጃ ለማገኘት ደግሞ 0921954870 መደወል ይቻላል። | 1 248 |
| 18 | መንፈሳዊ ጉዞን በተመለከተ
የ7 ቀን የሚፈጀው ጉዟችን በተመለከተ ትናት እሁድ ተወያይተናል። የዋጋ ጭምሪዎች ስላሉ የ1 ሰው ትኬት 5700 ብር ሁኗል። ለመሄድ ከወሰናችሁ ወንበሩ ሳይሞላባችሁ ትኬት ቁረጡ። ትኬት ለመቁረጥ ደውሉ 👉0913920421 ፤ 0921047323 | 804 |
| 19 | ተወዳጆች እንደምን አመሻችሁ ። እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ነገ እሁድ 8:30 በኪዳነ ምሕረት ትምህርት ቤት የበጋ ኮርሳችን ይጀመራል ። መንፈሳዊ ጉዟችንን በተመለከተ ውይይት ይኖረናል እና እንዳትቀሩ። | 837 |
| 20 | በሶሪያ ኦርቶዶክስ ያዕቆባዊት ቤተክርስቲያን የሕንድ ሜትሮፖሊታን የነበሩት ብፁዕ አቡነ ሞር ባስልዮስ ቶማስ ቀዳማዊ ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸው ተዘግቧል።
ብፁዕ አቡነ ሞር ባስልዮስ ቶማስ ቀዳማዊ እ.ኤ.አ ሐምሌ 22 ቀን 1929 ዓ.ም ቡቸንክሩዝ በተባለ የሕንድ ግዛት የተወለዱ ሲሆን እ.ኤ.አ ከሐምሌ 26 ቀን 2002 ዓ.ም ጀምሮ በሶርያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሥር የምትተዳደረውን የሕንድ ቤተ ክርስቲያን ለበርካታ ዓመታት በሊቀ ጵጵስና መርተዋል።
ብፁዕነታቸው በዕድሜና በሕመም ምክንያት ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ዕረፍት በማድረግ ሕክምናቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን በዛሬው ዕለት አመሻሽ ላይ በሕንድ ኮቺ በተወለዱ በ95 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል።
ማኅበረ ቅዱሳን | 851 |
