ru
Feedback
የወልድያ ኦርቶዶክሳዊያን ሕብረት

የወልድያ ኦርቶዶክሳዊያን ሕብረት

Открыть в Telegram
358
Подписчики
Нет данных24 часа
-27 дней
-230 дней

Загрузка данных...

Похожие каналы
Нет данных
Возникли проблемы? Пожалуйста, обновите страницу или обратитесь к нашему support-менеджеру .
Облако тегов
Нет данных
Возникли проблемы? Пожалуйста, обновите страницу или обратитесь к нашему support-менеджеру .
Входящие и исходящие упоминания
---
---
---
---
---
---
Привлечение подписчиков
февраль '25
февраль '25
+1
в 0 каналах
январь '25
+99
в 2 каналах
Get PRO
декабрь '240
в 1 каналах
Get PRO
ноябрь '240
в 0 каналах
Get PRO
октябрь '240
в 1 каналах
Get PRO
сентябрь '24
+45
в 0 каналах
Get PRO
август '24
+222
в 0 каналах
Дата
Привлечение подписчиков
Упоминания
Каналы
11 февраля0
10 февраля+1
09 февраля0
08 февраля0
07 февраля0
06 февраля0
05 февраля0
04 февраля0
03 февраля0
02 февраля0
01 февраля0
Посты канала
አስተርዮ ማርያም በዘመነ አስተርዮ የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መገለጥ የሆነበትና የአምላካችን አንድነትና ሦስትነት የተገለጠበት ብቻም ሳይሆን በጥር ፳፩ የከበረች እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም የዕረፍት ቀን በመሆኑ “አስተርዮ ማርያም” በማለት በዓልን አናደርጋለን፡፡ የአምላክ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ምድር ላይ ፷፬ ዓመታትን ከኖረች በኋላ መንፈስ ቅዱስ ባስገነዘባት መሠረት በክብር ዐርፋለች፡፡ የዚህን ዓለም መከራና ሥቃይ ለሰዎች ድኅነት የተቀበለችው ክብርት እናታችን በሥጋ ብትሞትም እንደ ልጇ ደግሞ በትንሣኤዋ ተነሥታለች፤ ይህም የሆነው በተቀደሰች ዕለት ነሐሴ ፲፮ ነው፡፡ እመ ብርሃን ከእናትና ከአባቷ ጋር ሦስት ዓመት፣ በቤተ መቅደስ ፲፪ ዓመት፣ ከተወዳጁ ልጅዋ ጋር ፴፫ ዓመት ከሦስት ወር፣ ከጌታችን ዕርገት በኋላ ከወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ጋር ፲፭ ዓመት፣ በድምሩ ፷፬ ዓመት በዚህ በኃላፊው ዓለም ኖራ ጥር ፳፩ ቀን በ፵፱ ዓመተ ምሕረት በክብር ዐርፋለች፡፡ ክርስቲያኖች በሙሉ ይህንን በዓል ልናከብር ይገባልና ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓትን ሠርታልናለች፡፡ “አስተርዮ ማርያም” በሕዝበ ክርስቲያን ዘንድ የሚከበር በዓል በመሆኑ በሀገራችን ኢትዮጵያ እና በመላው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ማኅበረሰብ ዘንድ በድምቀት ይከበራል፡፡ በዓሉን የምናከብረውም የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ከዚህ ዓለም ድካም ማረፍ በማዘከር ብቻ ሳይሆን አማላጅነቷና ተረዳኢነቷን በማሰብና ተስፋ በማድረግ ነው፡፡ ስለዚህም እመ ብዙኃን እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዐሥራት ሀገሯን ኢትዮጵያን እንድታስባት፣ ለእኛም ለሕዝቦቿ ሰላምን፣ ፍቅርንና አንድነትን ታሰጠን እንዲሁም ለነፍሳችን ድኅነትን ትለምልን ዘንድ ዕረፍቷን መዘከር ይገባል፡፡ የአምላካችን እግዚአብሔር ቸርነት፣ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነትና ተረዳኢነት አይለየን፤ አሜን!!! #ማህበረ_ጳውሎስ https://t.me/Stpoulos

2
https://youtu.be/lLNp_D4b_Xo?feature=shared
235
3
ያልተመዘገባችሁ ወልድያ የጥምቀት አስተባባሪ በመሆን ለማገልገል የምትፈልጉ ሰዎች ካላችሁ የተወሰኑ ቦታዎች አሉ በውስጥ አናግሩኝ @Abellteferaaa
449
4
ጥር 4 ማለትም ነገ እሁድ 8:30 አዳጎ ፀደይ ባንክ 4ኛ ፎቅ የብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ወርሃዊ የጽዋ እና የወንጌል ድግስ ያዘጋጀን ሲሆን እርሰዎም ወዳጅ ዘመድ ጓደኛ በመጋበዝ እንድትገኙ ጥሪ እናስተላልፋለን።
1 037
5
ሳውል የኦሪት ምሁርና ክርስቲያኖችን አሳዳጅ ነበር። ኢየሱስ ክርስቶስ ባረገ በ8ኛው ዓመት (በ42 ዓ.ም) በደማስቆ ከተማ አጠገብ እግዚአብሔር በድንቅ አጠራር ጠርቶታል። (የሐዋ. ሥራ 9፥ 1-30)። በጥላው በሽተኞችን ፈውሷል። በትምህርቱ ብዙዎችን የክርስቶስ ምርኮኛ የመንግስቱ ተካፋይ አድርጓል። በመጽሐፍ ቅዱስ 14 መልእክታትን ጽፏል። መጠሪያ ስሞቹም፦ ፩.ብርሃነ ዓለም ፪.ልሳነ ክርስቶስ ፫.ማኅቶተ ቤተክርስቲያን ፬.የአሕዛብ መምህር ፭.ሳውል ፮.ፈዋሴ ድውያን.. "መልካሙን ገድል ተጋድያለሁ ሩጫዬንም ጨርሻለሁ ሃይማኖትን ጠብቄያለሁ፤ እንግዲህስ የጽድቅ አክሊል ይቆየኛል።" 2ኛ ጢሞ 4፥7 ጥር 4 የብርሃነ ዓለም ቅዱስ ጳውሎስ ጽዋ ማኅበር ወርሃዊ የጽዋ እና የወንጌል ድግስ ያዘጋጀ ሲሆን እርሰዎም ወዳጅ፣ ዘመድ ጓደኛ በመጋበዝ እንድትገኙ ጥሪ እናስተላልፋለን። አድራሻ፦ አዳጎ ፀደይ ባንክ 4ኛ ፎቅ
1 165
6
ቴሌ ግራም WhatsApp facebook ላይ Story በማድረግ ለማስታወቂያ ሁላችሁም ተሳተፉ
ቴሌ ግራም WhatsApp facebook ላይ Story በማድረግ ለማስታወቂያ ሁላችሁም ተሳተፉ
463
7
ቴሌ ግራም WhatsApp facebook ላይ Story በማድረግ ለማስታወቂያ ሁላችሁም ተሳተፉ
ቴሌ ግራም WhatsApp facebook ላይ Story በማድረግ ለማስታወቂያ ሁላችሁም ተሳተፉ
481
8
Нет текста...
849
9
እንኳን ለጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ። መልካም በዓል ይሁንላችሁ።
503
10
ተወዳጆች ዛሬ መጽሐፍ ቅዱስን በተመለከተ የተወሰኑ ነጥቦችን አንስተን ሰለምንመለከት 8:45 ላይ እንዳትቀሩ። በተጨማሪም የልደት መዝሙሮች የተወሰኑት ይጠናሉ። ከጉባኤ በኋላ 11 ሰዓት ላይ ደግሞ ፈተና ይጀምራል። አዳጎ ቤተ ክህነት አዳራሽ ሰለተያዘ መድኃኒዓለም ሰ/ት/ቤት አዳራሽ እንገናኝ።
742
11
ወደ_ዕብራዊያን_የመግቢያ_ማብራሪያ_4.pdf
1 015
12
የተወደዳችሁ የዛሬው መርሐ ግብር 8:30 ይጀመራል። የሀገረ ስብከቱ አዳራሽ ሰለተያዘ አዳጎ ፀደይ ባንክ ሕንጻ ላይ ሁኗል በእግዚአብሔር ፍቅር አደራ እንዳትቀሩ።
961
13
የተወደዳችሁ ወንድሞች እና እህቶች በዚህ ዓመት ያሰብነውን የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ እና ጥናት እቅድ ማስተዋወቂያ መርሐ ግብር እሁድ (ታሕሳስ 6) 8:30 በአዳጎ ፀደይ ባንክ ሕንጻ ላይ ባለው አዳራሽ በልዩ ድምቀት ለማከናወን አስበናል። ከመጽሐፍ ቅዱስ ጋር ያለንን ትስስር ለማሳደግ ይህ መርሐ ግብር ልዩ ኦርቶዶክሳዊ ንቅናቄ እንዲሆን ታቅዷል እና በዚህ መርሐ ግብር መቅረት በፍጹም አይፈቀድም ። በሰዓቱ ከቦታው ለመገናኘት ያብቃን መልካም ቀን
950
14
ሠላም የተወደዳችሁ ተጓዦች" ከእግዚአብሔር ከአባታችን ከጌታም ከኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋና ሰላም ለእናንተ ይሁን።" 1ኛ) የጉዞአችን መኪኖች ዛሬ ህዳር 17 ከቀኑ 9:00 ኪዳነ ምህረት ይቆማሉ ስለሆነም የሚያዘገዩ ከባባድ እቃዎቻችሁን ከወዲሁ ቀድማችሁ ዛሬ እንድትጭኑ። ጠዋት ከባድ እቃዎችን እንደማንጭን ማሳሰብ እንፈልጋለን። 2ኛ) ህዳር 18 ከሌሊቱ 10:30 አዳጎ ሀገረ ስብከታችን ህንፃ ስር በመገኘት 10:50 ለጸሎት ቆመን 11:00 እንወጣለን። 11 ሰዓት ከሞላ ማንንም እንደማንጠብቅ ከወዲሁ እናሳውቃለን። 3ኛ) ለጉዞ የሚያስፈልጉአችሁን የግል ቁሳቁሶች (እቃዎች) መያዝ ሳትዘነጉ በሰዓቱ እንድንገናኝ በትልቅ አደራ አደራ አደራ እያልን እናሳስባችኋለን።
970
15
ይችን ነገር ተመልከቷት እስቲ
ይችን ነገር ተመልከቷት እስቲ
871
16
Нет текста...
1 123
17
ታላቅ ሀገር አቋራጭ መንፈሳዊ ጉዞ በአይነቱ ልዩ እና በርካታ ገዳማት እና አድባራትን የምንሳለምበት ታላቅ መንፈሳዊ ጉዟ ለወልድያና አካባቢው ኦርቶዶክሳዊያን ተዘጋጅቷል። ይህ ጉዞ ሰባት ቀናትን የሚሸፍን ሲሆን መነሻውን ከወልድያ ከተማ ያደርጋል። ከወልድያ ላሊበላ እና በላስታ አካባቢ ያሉትን ገዳማትና አድባራትን አካሎ ጉዞውን ወደ ዋግ ኸምራ በማድረግ ከሰቆጣ ከተማ በቅርብ ርቀት የሚገኘውን መስቀለ ክርስቶስ ፍልፍል ቤተ ክርስቲያንን ከሰቆጣ ከተማ 51 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኘውን የበርሃዋ ገነት በመባል የምትታወቀውን ባር ኪዳነ ምሕረትን ተሳልሞ ጉዞውን ወደ ትግራይ ክልል ያደርጋል። በትግራይ ካሉ የተቀደሱ ቦታዎች መካከል ገር ዓልታ ተራራ ላይ በድንቅ መልክአ ምድር አቀማመጥ ላይ የሚገኘውን አቡነ ይምዓታ ገዳም እና ደብረ ዳሞ በተጨማሪም አብርሃ ወአጽብሃን ተመልክቶ ለህዳር 21 የንግሥ በዓል ወደ አክሱም ጽዮን ማርያም ይገሰግሳል። በክብረ በዓሉ ጽዮን ማርያምን አንግሶ ወደ ሽሬ እንደሥላሴ በማቅናት አቅጣጫውን ወደ ጎንደር ከተማ በማድረግ ታሪካዊቷ የጎንደር ከተማ አቅፋ የያዘቻቸውን ታላላቅ አድባራትን በረከት ተቀብሎ ከሊቀ ሊቃውንት የኔታ ዕዝራ እግር ስር በመቀመጥ ቃለ ምዕዳናቸውን ሰምቶ ከጎንደር ታሪካዊ የነገሥታቶቹን ቤተ መንግሥት ጎብኝቶ ወደ ጎጃሟ እመቤት ወደ ባሕር ዳር ጉዞውን ያቀናል። በባሕር ዳር በሚኖረን ቆይታ በጣና ደሴቶችን ላይ የሚገኙትን ገዳማትን ለመሳለም ሁለት ቀን የባሕር ላይ ጉዞ ተዘጋጅቷል። በዚህ የሁለት ቀን የባሕር ጉዞ ላይ ከ17 ያላነሱ በጣና ደሴቶች ላይ የሚገኙ ገዳማትና አድባራትን ለማየት ከቦታው የሚገኘውን በረከት ለመካፈል የቅዱሳን ፈለግ ተከትሎ የጉዞ እቅዱን አውጥቷል። መነሻ ወልድያ ከተማ ሕዳር 18 በዚህ ጉዞ ላይ ለመሳተፍ የአንድ ሰው የትኬት ዋጋ 5700 ብር ነው።  0913920421 እና 0921047323 ትኬቱን ለመቁረጥ በእዚህ ስልክ ቁጥሮች መደወል ይቻላል። ሰለጉዞው የበለጠ መረጃ ለማገኘት ደግሞ 0921954870 መደወል ይቻላል።
1 248
18
መንፈሳዊ ጉዞን በተመለከተ የ7 ቀን የሚፈጀው ጉዟችን በተመለከተ ትናት እሁድ ተወያይተናል። የዋጋ ጭምሪዎች ስላሉ የ1 ሰው ትኬት 5700 ብር ሁኗል። ለመሄድ ከወሰናችሁ ወንበሩ ሳይሞላባችሁ ትኬት ቁረጡ። ትኬት ለመቁረጥ ደውሉ 👉0913920421 ፤ 0921047323
804
19
ተወዳጆች እንደምን አመሻችሁ ። እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ነገ እሁድ 8:30 በኪዳነ ምሕረት ትምህርት ቤት የበጋ ኮርሳችን ይጀመራል ። መንፈሳዊ ጉዟችንን በተመለከተ ውይይት ይኖረናል እና እንዳትቀሩ።
837
20
በሶሪያ ኦርቶዶክስ ያዕቆባዊት ቤተክርስቲያን የሕንድ ሜትሮፖሊታን የነበሩት ብፁዕ አቡነ ሞር ባስልዮስ ቶማስ ቀዳማዊ ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸው ተዘግቧል። ብፁዕ አቡነ ሞር ባስልዮስ ቶማስ ቀዳማዊ እ
በሶሪያ ኦርቶዶክስ  ያዕቆባዊት ቤተክርስቲያን የሕንድ ሜትሮፖሊታን የነበሩት ብፁዕ አቡነ ሞር ባስልዮስ ቶማስ ቀዳማዊ ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸው ተዘግቧል። ብፁዕ አቡነ ሞር ባስልዮስ ቶማስ ቀዳማዊ እ.ኤ.አ ሐምሌ 22 ቀን 1929 ዓ.ም ቡቸንክሩዝ በተባለ የሕንድ ግዛት የተወለዱ ሲሆን እ.ኤ.አ ከሐምሌ 26 ቀን 2002 ዓ.ም ጀምሮ በሶርያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሥር የምትተዳደረውን የሕንድ ቤተ ክርስቲያን ለበርካታ ዓመታት በሊቀ ጵጵስና መርተዋል። ብፁዕነታቸው በዕድሜና በሕመም ምክንያት ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ዕረፍት በማድረግ ሕክምናቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን በዛሬው ዕለት አመሻሽ ላይ በሕንድ ኮቺ በተወለዱ በ95 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል። ማኅበረ ቅዱሳን
851