en
Feedback
Abg kality 2018G3

Abg kality 2018G3

Open in Telegram
293
Subscribers
+124 hours
+27 days
+1330 days
Posts Archive
ውድ ወላጆች እንደምን ቆያችሁ? ሰሞኑን ልጆቻችንን በክርምቱ መውጫ ከነሐሴ 28  እስከ መስከረም 3 የተዘጋጀ ዓውደ ርዕይ ላይ እንዲታደሙ በሐመረ ብርሃን ግብዣ ቀርቦላቸው እንደነበር ይታወሳል። ልጆቻችን የአቡነ ጎርጎርዮስ ተማሪዎች በመሆናቸው የመግቢያ ቲኬቱ ከ500 ብር ታላቅ ቅናሽ ተደርጎ 300 ብር እንደተደረገላቸው ያሳወቅናችሁ ሲሆን ይህ የሚሆነው ዓውደ ርዕዩን በጋራ ሂደን ስንታደም ብቻ ነውና ሁላችሁም ወላጆች ልጆቹ የዚህ ታሪካዊ ዓውደ ርዕይ ተካፋይ መሆን አለባቸው ብላችሁ ካሰባችሁ ከታች ባሉት ስልኮች ደውላችሁ ክፍያ በመፈጸም ቦታ ማስያዝ እንደምትችሉ እናሳውቃለን።  ከሁሉም የአቡነ ጎርጎርዮስ ቅርንጫፎች የሚነሱ መኪናዎች ስላሉ በመረጣችሁት ቅርጫፍ መኪና መሳፈር ትችላላችሁ፤ ውድ ወላጆች ቦታ ለማስያዝ ስትደውሉ የመረጣችሁትን ቅርንጫፍ እንድታሳውቁን እንጠይቃለን። ቅናሹ የሚሠራው በጋራ በመኪና በተያዘው ቀን ለሚመጡ ተማሪዎች ብቻ እንጂ በግል ጉዞውን ለሚመጡ ቤተሰቦች ስላልሆነ እስከ ቅዳሜ ነሐሴ 29 ድረስ ብቻ ደውሎ በማስመዝገብ ይህን እድል እንድትጠቀሙ እንጠይቃለን። ☎️ 0913332445 ማርታ ዓለሙ / ወይራ ቅርንጫፍ/ ☎️ 0988470647 ሳባ ዓለም / መሪ እና ሰሚት ቅርንጫፍ/ ☎️ 0911921383 ሰለሞን ዘለቀ / ለቡ ቅርንጫፍ ☎️ 0912635036 ዐይን አበባ /ቃሊቲ ቅርንጫፍ/ ☎️ 0911660911 ሐይማኖት ቃኘው / አዋሬ እና እግዚአብሔር አብ ቅርንጫፍ/ ☎️ 0943172425 ሶስና ተስፋው / 22 እና ሰንሻይን ቅርንጫፍ/

photo content
+1

photo content

Video from Alemu Woldie

photo content

photo content

photo content

Book Distribution.pdf1.11 MB

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content

ለውድ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት ነባር የተማሪ ወላጆች በሙሉ። ከሁሉ አስቀድመን የከበረ ሰላምታችን በያላችሁበት ይድረስ። የ2019 ዓ.ም. የነባር ተማሪዎች ምዝገባ ከሐምሌ 6 እስከ 10 ቀን 2018 ዓ.ም. እንዲካሄድ ታቅዶ ቢጀምርም ያልተመዘገቡ ተማሪዎች በመኖራቸው እና ለወላጆች ተጨማሪ ዕድል ለመስጠት ሲባል የምዝገባው ጊዜ ለተጨማሪ ቀናት ተራዝሞ ቆይቷል። በአሁኑ ወቅት ለ2019 ዓ.ም. አዲስ ተማሪዎችን የመቀበል ሂደት እየተካሄደ በመሆኑ ያሉትን ክፍት ቦታዎች በትክክል ለመለየት የነባር ተማሪዎች ምዝገባን በአፋጣኝ ማጠናቀቅ አስፈላጊ ሆኗል። ስለሆነም የሁሉም ቅርንጫፎች የነባር ተማሪዎች የመጨረሻ ምዝገባ እስከ ሐምሌ 20 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ የተራዘመ መሆኑን እናሳውቃለን። እባክዎ ልጅዎን እስከ ሰኞ ሐምሌ 20 ቀን 2018ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ብቻ በሚማርበት ቅርንጫፍ ትምህርት ቤት በመቅረብ ምዝገባውን እንዲያጠናቅቁ በአክብሮት እንጠይቃለን። ከተጠቀሰው የመጨረሻ ቀንና ሰዓት በኋላ ያልተመዘገቡ ነባር ተማሪዎች በፈቃዳቸው እንደለቀቁ በመቆጠር በክፍት ቦታው አዲስ አመልካች ተማሪዎችን የምንቀበልበት መሆኑን በጥብቅ እናሳውቃለን። ስለ ትብብርዎ እናመሰግናለን። የዋናው መሥሪያ ቤት የተማሪዎች ምዝገባና ቅበላ ኮሚቴ

photo content

photo content

photo content

photo content