Natural and Social Science Department G-12ABC
Open in Telegram
🎯AIM 🎯 💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫💫 ➥To create a modern and online study community . . . ➥Description box ➽Home and Assignment Reminder ➽Motivational Speech's ➽Exam and Study Tips ➽YouTube video's ➽Announcement's
Show more360
Subscribers
No data24 hours
-17 days
-230 days
Posts Archive
Dear all natural science students tomorrow come early in the morning at 7:00am .we'll leave the school at 7:30am in the morning. Don't be late.
መቼም የማህበራዊ ድረ ገፆችን ውዥንብር እና የሰዎችን ተንኮል ለናንተ መናገር ለድመት አበሩላት ነው ሚሆንብኝ።
አሰላሙአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ።
ውድ ተማሪዎቼ ወንድም እና እህቶቼ እንዴት ናችሁ? ዛሬ አዲስ ነገር ሰማሁ እና ይሄንን መልዕክት ለመላክ ተገደድኩ።
👉ፈተና ወጥቷል የሚል¿ ለዚህ ምንም አይነት ማረጋገጫ የሌለ በመሆኑ ባጭሩ በደንብ ተረጋጉ እባካችሁ ይሄ ነገር ከሆነ መንግስት ይወጣው። በተዘጋጃችሁት ልክ ሳይኮሎጂያችሁን ጠብቃችሁ ወደ ግቢያችሁ ሄዳችሁ ከድሮውም በበለጠ ተረጋግታችሁ የሚሆነውን ነገር መጠባበቅ እና በአላህ መወከላችሁን እንዳትዘናጉ።
Scholastic Aptitude 2016 social (maths part ) solution.pdf
Repost from Entrance prep E-learning
ዛሬ ሶሻሎች እስከ ቀኑ 5:00 የተፈተኑት የ SAT ፈተና
🔹 የጥያቄ ብዛት: 60
Join us👇👇👇👇
@Entranceprepare
@Entranceprepare
Repost from Advanced Freshman
የፈተና ሳይኮሎጂ💡
#reposted🔨 የ 4 ዓመት ልፋትህን የሚወስነው የ 2 ሰዓት ፈተና ነው። ፈተና ክፍል ስትሆን የምታደርገው ነገር የማትሪክ ውጤትህን ይወስነዋል። 🔻ፈተና ክፍል ከደነገጥክ የምታቀው ሁሉ ይጠፋብሀል፤ ቀላል ጥያቄ ሳይቀር መመለስ አትችልም፤ የብዙ ተማሪዎች ችግር ነው። 💻ፈተና ክፍል ስትሆን ራስህን ካረጋጋህ ግን በConfidence የምትችለውን ሁሉ ትሰራለህ፣ ከዛ ጥሩ ውጤት ታመጣለህ፤ አየህ ፈተና የሳይኮሎጂ ጨዋታ ነው። መልካም ዕድል ❤️ JOIN: @ETHIO_ENTRANCEG12⭐️
If there is any difficulties about this 2016 social science exam you can come and contact me tomorrow
Repost from Entrance prep E-learning
ዛሬ social የተፈተኑት ፈተና🥳🥳🥳🥳
Subject : maths
Credit : grade 12 students channel
join us👇👇👇👇
@Entranceprepare
@Entranceprepare
Any teacher or supervisor can inform us any updates becuase the university that we are going to is written as one of the online examination places?
-Any response please
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
+1
#AddisAbaba #NationalExam
“ በሙከራ ላይ እኛ ያጠፍናቸው ጣቢያዎች አሉ እንጂ ፈተና ይቀራል ብለን የሰጠነው መግለጫ የለም ” - ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከተማሪ ወላጆችና ከተማሪዎች ግልጽ የሆነ ማብራሪያ ስለተጠየቀበት የበየነ መረብ (ኦንላይን) የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተናን በተመለከተ የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዘላለም ሙላቱን ጠይቋል።
ዶ/ር ዘላለም ሙላቱ ምን አሉ ?
“ ፈተና በሁለት አይነት መልኩ (በኦንላይንና በወረቀት) ይሰጣል።
በኦን ላይን የሚሰጠው ዩኒቨርሲቲ ላይ ተመድበው የነበሩ አብርሆት ላይብረሪና ሁለት አዳሪ ትምህርት ቤቶች ብቻ ይሆናሉ።
የተቀሩት ግን በሁሉም በግልም በመንግስም መፈተኛ ጣቢያ ተመድበው የነበሩ ት/ቤቶች ሆኖ በተመደቡበት (ድልድል የወጣላቸው ት/ቤቶች ያውቃሉ) መሠረት ፈተናውን በወረቀት ይወስዳሉ።
በኦንላይን ፈተና የሚወስዱት፦
- በኮተቤ ዩኒቨርሲቲ
- በሲቪል ሰርቪስ
- በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
- በአዲስ አበባ ሳይንሰና ቴክኖሎጂ
- በጳውሎስ ሚሊኒየም የተመደቡ በዚያ ይወስዳሉ።
እንዲሁም፣ በአብርሆት ላይብረሪ ላይ የተመደቡ ተማሪዎች፣ የሁለቱ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪዎች በኦንላይን ይወስዳሉ።
የቀሩት ግን በሌላ መፈተኛ ጣቢያ ተመድበው የነበሩት ስለታጠፈ በወረቀት ይወስዳሉ።
በወረቀት የሚወስዱት ዩኒቨርሲቲ ነው የሚገኙት በባለፉት ሁለት አመታት እንደተሰጠው ማደሪያቸውም፣ መዋያቸውም፣ መፈተኛቸውም እዛው ይሆናል። አድረው ሲጨርሱ ነው የሚወጡት።
በኦንላይን የተመደቡት ግን ውሎ ገብ ነው። ተፈትነው ወደ ቤታቸው ሂደው አድረው ተመልሰው በጠዋት መጥተው ይፈተናሉ። ” ብለዋል።
የተፈጠረው ውዝግብ ምንድን ነው ? ተብሎ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄ በሰጡት ምላሽ ፥ “ የተፈጠረ ነገር የለም። በድብልቅ መንገድ እንደምንጥ ታሳቦ ነበረ። እሱን ነበር ስንለማመድ የነበረው ” ነው ያሉት።
“ አሁን More እርግጠኛ በተኮነበት መፈተኛ ጣቢያ (ከላይ በተገለጹት) ብቻ ይሰጣል። ” ሲሉ አክለዋል።
ትምህርት ቤቶች “ ቀርቷል ” ሲሉ ተስተውለዋል፤ ታዲያ መረጃውን ከየት አግኝተውት ነው ? ቢሮው ትዕዛዝ አውርዶ ነበር ? ስንል ኃላፊውን ጠይቀናል።
ዶ/ር ዘላለም ፥ “ በዩኒቨርሲቲዎችና በሌሎች ጣቢያቸዎች እንደሚሰጥ ነገር ግን ሌሎች ጣቢያዎች የነበሩት፣ በእነርሱ ላይ ካልሆነ በስተቀር ' ቀርቷል ' ተብሎ የተሰጠ መግለጫ አልነበረም ” ብለዋል።
አክለው፣ “ ለሙከራ ስንሞክርባቸው የነበሩ እርግጠኛ ያልሆንባቸውን ተማሪዎችና ቤተሰብ ላይ እንግልት እንዳይሆን እርግጠኛ ያልሆንባቸውን ቀንሰናል ” ያሉት ኃላፊው፣ “ በእርግጠኝነት ሊፈጸሙባቸው ተብሎ ከትምህርት ሚኒስቴር ጋር በጋራ የተወሰኑት ላይ ግን ተወስኗል ” ብለዋል።
ትምህርት ሚኒስቴር የበየነ መረብ (ኦንላይን) ፈተናው እንደቀረ ያስተላለፈው መልዕክት ነበር ? ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ ደግሞ፣ “ ትምህርት ሚኒስቴር እኮ በገጹ ላይ አስታውቋል እንዳልቀረ ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
“ በሙከራ ላይ እኛ ያጠፍናቸው ጣቢያዎች አሉ እንጂ ፈተና ይቀራል ብለን የሰጠነው መግለጫ የለም። በግልና በመንግስት ትምህርት ቤቶች ተይዘው የነበሩት በተለያዩ ምክንያቶች ተቀንሰዋል ” ብለዋል።
ቢሮዎ ለትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት፣ ለትምህርት ሚኒስቴር ጻፈው ተብሎ ሲሰራጭ የነበረው ደብዳቤ (ከላይ ተያይዟል) የቢሮ ነው ? ለሚለው ጥያቄ ፥ “አዎ። ትክክል ነው !! ” ብለዋል።
“ አሁን ባልናቸው ጣቢያዎች ማለት ነው። በፊት በ153 ጣቢያዎች ብለን ነበር ይዘን የነበረው አሁን ግን በእርግጠኝነት ይሳካል የተባለበት ቦታ ከላይ የተጠቀሱት ጣቢያዎች ብቻ ናቸው ” ሲሉ ተናግረዋል።
በመሆኑም በተቀመጠው መርሀ ግብር መሠረት ተማሪዎች ከምንም አይነት ውዢምብር ራሳቸውን ጠብቀው ከቢሮውና ከትምህርት ሚኒስቴር በሚወርዱ መመሪያዎች ብቻ ተረጋግተው እንዲፈተኑ አሳስበዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
