en
Feedback
ተዋሕዶን እንወቅ።

ተዋሕዶን እንወቅ።

Open in Telegram

አቡነ ዘበሰማያት ይትቀደስ ስምከ ሥረይ ለነ ኲሎ አበሳነ ኢታብአነ ውስተ መንሱት እግዚኦ አድኅነነ እምዕለት እኪት ወባልሐነ ውስተ መንሡት። ✝በከመ ምሕረትከ አምላክነ ወአኮ በከመ አበሳነ✝ የየእለቱን ስንክሳር፥ ውዳሴ ማርያም፥ ጸሎተ አርጋኖን፥ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችን፥ የጻድቃንና የሰማዕታትን ገድል፥ የተለያዩ መንፈሳዊ ጥያቄዎችን፥ የድሮ እና አዳዲስ መዝሙራትን የሚያገኙበት ቻናል ነው። ይቀላቀሉን።

Show more
Buy Ad
2 372
Subscribers
-124 hours
-117 days
+330 days
Posts Archive
+ ስትሞት ምን የሚኾን ይመስልሃል? + የሞቴ ቀን ዛሬ ነው ብለህ በፍጹም አላሰብክም። ድንገት ግን ከሞት መልአክ ጋር ፊት ለፊት ተጋፈጥክ። ሞት ጥቁር እንግዳ አይደል? ነገ ተመለስ ብለህ አትሸኘው ነገር፥ የሚመጣው በጥብቅ ቀጠሮ ነው። እኔን እለፈኝ አትለው ነገር፥ በምንም ነገር የሚደለል አይደለም። መጥቶ ከፊትህ ቆመ። ጓዜን የለ፥ ጨርቄን የለ፥ ትንሽ ጠብቀኝ የለ፥ ዝም ብለህ ተከተልከው። ሕይወትህ አበቃ። የሌላው እጣ ለአንተም ደረሰህ። ሌላው እንደሚሞተው አንተም ሞትክ። ለነገ እየተጨነቅክ፥ ዛሬ አረፍክ። ከዚህ በኋላ ምን እንደሚኾን ታውቃለህ? የሞትህን ዜና የሰሙ ሁሉ ይደነግጣሉ። ሁሉም እየተደዋወለ ዜናውን ይቀባበለዋል። "ሰማችሁ? ሞተ እኮ! ወይኔ!" ይባባላሉ። ጎረቤቶች ሰብሰብ ብለው ለቅርብ ሰዎችህ ሞትህን ያረዳሉ። ቤተሰቦችህ ለያዥ ለገናዥ እስኪያስቸግሩ ድረስ ያለቅሱልሃል። ሶሻል ሚዲያ ላይ የሞትህ ዜና ይዘገባል፤ ሰዎች እየገቡ "RIP" እያሉ ይጽፋሉ። አንዳንዱ ፕሮፋይሉን ጥቁር ያደርግ ይሆናል። ብዙዎች ያዝናሉ። በቀብርህ ቀንም ይለቀስልሃል። መሬት ስትገባ አብሬ ካልገባሁ እስኪል ድረስ የሚያዝንልህም ላይጠፋ ይችላል። ከቀብር መልስ ሰዎች ንፍሮ እየዘገኑ ስለ አንተ ይጨዋወታሉ። ጓደኞችህ ለጥቂት ቀናት ያለቅሱልህ ይሆናል፤ ከዚያ ግን ሕይወታቸውን ይቀጥላሉ። ቤተሰቦችህ እጅግ ያዝኑ ይሆናል፤ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ግን ትዝታቸው ትሆናለህ። ቆንጆ መልክ ነበረህ? የኮራህበት መልክህ የትላትሎች ራት ይሆናል። ጥሩ ሰውነት ነበረህ? በጥንቃቄ ስትጠብቀው የነበረው ሰውነት አፈር ይበላዋል። ታታሪ ሠራተኛ ነበርህ? ታትረህ የሠራህለት መሥሪያ ቤትህ በፍጥነት ያንተን ቦታ የሚተካ ሰው ፈልጎ ይቀጥራል። ቋሚ ንብረት ነበረህ? አንድም ሳይቀር ሁሉም ለወራሾችህ ይተላለፋል። ብዙ የተማርክ ነበርህ? ዲግሪዎችህ የመዝገብ ቤት ፋይል ሆነው ይቀራሉ። አይህ... ለካ ዓለም የምትሽከረከረው በአንተ ዙሪያ አይደለም። ሁሉን ምድር ላይ ትተህ፥ ለቅርብ ሰዎችህም 'ትዝታ' ሆነህ ታልፋለህ። ሕይወትም አንዳች እንዳልተፈጠረ ሆኖ ይቀጥላል። ሁሉ በምድር ሲቀር ግን ወደ ቀጣዩ ዓለም የምትሻገረው ነፍስህ ናት። ቆንጆ መልክ መያዝ ጥሩ ሊኾን ይችላል፤ ግን ተሻጋሪ ነፍስህን ብታስውባት ይበልጣል። ጥሩ ሰውነት ማዳበር መልካም ሊኾን ይችላል፤ ግን ለነፍስህ ምግብ እያቀረብክ በእውቀት ብታዳብራት የተሻለ ነው። ለዓለማዊ ነገር መድከምህ የከፋ አይደለም፤ ግን ቢያንስ ለነፍስህ የበለጠ ድከምላት። ቋሚ ንብረት ቢኖርህ የሚጠላ ባይሆንም፤ ብል በማይበላው የሰማይ መዝገብ ቋሚ ንብረት ቢኖርህ ግን አትራፊ ትሆናለህ። ብዙ መማርህም አይከፋም፤ ትምህርትህን ግን በምግባርህ እየገለጥከው መኖሩ ዘላቂ ነው። እወቅበት! ጋጋታው ሁሉ ዘላቂ መስሎህ አትሸወድ! ✒ Fresenbet G.Y Adhanom ---------- የፌስቡክ ገጽ: https://www.facebook.com/fre.asalib ቴሌግራም: https://t.me/fresenbett ሊንክድኢን፡ https://www.linkedin.com/in/fresenbet-g-y-adhanom

ዘመነ ክረምት ወደ መገባደጃው እያመራ ነው። በሦስት ንዑሳን ክፍሎች የሚከፈል ሲሆን፥ አሁን ከሁለተኛው ወደ ሦስተኛው መሸጋገሪያ ወቅት ላይ ነን። ከወር በፊት በተለቀቀችው #ድምጸ_ናብሊስ መጽሔታችን ላይ “ዘመነ ክረምት“ በሚል ዓምድ ስለ ወቅቱ በደንብ ለማወቅ የሚያግዝ ዘለግ ያለ ጽሑፍ አዘጋጅተንላችኋል። እንድታነቡት ጋበዝናችሁ።
ዘመነ ክረምት በቅድስት ቤተክርስቲያን ብዙ ምሳሌዎች ይመሰሉበታል። ከእነዚህም መካከል አንዱ ክርስትና ነው። አብዛኛዎቹ የግብርና ሥራዎች በክረምት እንደመከናወናቸው መጠን ገበሬም ብርዱንና ዝናቡን ሳይፈራ በበጋ የእጁን ፍሬ ያገኝ ዘንድ ለሥራ ይሰማራል።❞
በCanva ለማንበብ | በGoogle Drive ለማግኘት | በPDF ለማንበብ

#ከመጽሐፍ_ቅዱስ_ገጾች
#ከመጽሐፍ_ቅዱስ_ገጾች

ሰላም ለክሙ.. እነዃት ያዘጋጀዃት pdf.. ለሚያስፈልጋቸው ኹሉ share ማድረግ እንዳይረሳ!

#ዘቀዳሚት 🔸 ተቀበል 🔸 ከ14ቱ የሱባዔ ቀናት መካከል በአንዱ እንደተለመደው ለሰዓታት ጸሎት ለእኩለ ሌሊት አቅራቢያ ደወሉ ተደውሎ ኹሉም በቤተ መቅደስ ተሰባስቧል። ጸሎቱም "አአትብ" ብሎ ተጀምሮ
#ዘቀዳሚት 🔸 ተቀበል 🔸 ከ14ቱ የሱባዔ ቀናት መካከል በአንዱ እንደተለመደው ለሰዓታት ጸሎት ለእኩለ ሌሊት አቅራቢያ ደወሉ ተደውሎ ኹሉም በቤተ መቅደስ ተሰባስቧል። ጸሎቱም "አአትብ" ብሎ ተጀምሮ "ንዒ" ላይ ደርሷል። በዚህ የጸሎት ክፍል እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን "ከልጅሽ ጋር ወደኔ ነዪ" ከሚለው ጀምሮ አዳምንና አቤልን ጨምሮ ሌሎች ደጋጎችን ጠርተን ፤ ከይሁዳና ከሰማርያ ነቢያት ሁሉ ጋር ነይ ብለን አባቶቿን እየጠቀስን እንለምናለን። በሰዓታት ጸሎት ውስጥ ከተካተቱ ጸሎቶች መካከል እጅግ ታላቅ ክብር የሚሰጠውና የሚወደድ ጸሎት ነው። "ወዳጄ ሆይ ነዪ ፤ ርግቤ ሆይ ነዪ ፤ ሙሽራይቱ ሆይ ነዪ ፤ ከተወዳጅ ልጅሽ ጋር ነዪ ፤ ልጅሽን ታቅፈሽ ነዪ ፤ ከሚካኤልና ከገብርኤል ጋር ነዪ ፤ መልካሚቱ ሆይ ነዪ" እያሉ ካመሠገኗት ቅዱሳን አባቶቿ ጋር ኾነን ዛሬም እኛ በኅብረት "ንዒ ኀቤየ ኦ ድንግል" ድንግል ሆይ ወደ እኔ ነዪ እንላታለን። ታዲያ ጸሎቱ እንዳበቃና ማሳረጊያ "አቡነ ዘበሰማያት" እንደተደገመ ከአገልጋዮች መካከል አንድ ወዳጃችን የሰዓታት ጸሎቱን ጨርሶ መውጣት አልቻለም ነበር። በሌሊት ሥራ መግባት ስለነበረበት "ንዒ" ተብሎ እንዳበቃ ከመውጣቱ በፊት እጅግ ከምናከብራቸው አረጋዊ አባት እጅ ቡራኬ ለመቀበልና መስቀል ለመሳለም ወደ እርሳቸው ዘንድ ሄደ። አባታችንም በቀልድ መልክ " 'ንዒ' ብለህ ጠርተሃት እርሷ ስትመጣ አንተ ትወጣለህ?" በማለት ፈገግ አስብለውት ከባረኩት በኋላ ረፍት ለማድረግ ይወጣል። የአባታችን ንግግር በቀልድ መልክ የተነገረ ቢኾንም ነገሩ ወደራሳችን ሕይወት የሚመለስና እጅግ ጥሩ ትምህርት የሚገኝበት ነው። በብዙ የሕይወታችን ውጣውረድ ውስጥ እርሷን ያልተማጸንበት ጊዜ የለም ፤ ነገር ግን ጠርተናት እርሷ ስትመጣ የምታገኘን ቦታ የተቀመጥንባቸው ጊዜያት ስንት ናቸው? "ከልጅሽ ከወዳጅሽ" ብለን እንድታማልደን እግሯ ሥር ተደፍተን ያለቀስንባቸው እልፍ ጉዳዮች እንዲፈቱልን ከጠየቅናት ቦታ ጸንተን የጠበቅን ስንቶቻችን ነን? በምሕረት ና ያልከው ጌታ ሲመጣ አንተ ወዴት ትሄዳለህ? ለኃጢአትህ ሥርየትን ለምኚልኝ እያልክ ስታለቅስባት የነበረች እመቤት ስትቀርብህ ወዴት ትሸሻለህ? ጸሎታቸው በዐይን ጥቅሻ ፍጥነት የተሰማላቸው እንደነበሩ ኹሉ ለዘመናት እንቆቅልሾቻቸው ያልተፈቱላቸው ሰዎች ታሪክን ከመጽሐፍ ቅዱስ አላነበብህም? ጾሙን ታግሰህ ፤ ከኃጢአት ርቀህ ፤ በሱባዔ ተወስነህ "ንዒ" በማለት በዕንባ ስትማጸናት የነበረች አዛኝቷ እመቤት ራርታልህ ከልጇ ጋር ብትመጣ አንተን ከጾሙ በፊት ወድቀህ የነበርክበት ቦታ ልታይህ አትወድም! "ነይ" እያልን ስንለምናት የከረምን ልጆቿን ጾሙ ተፈታ ብለን በኃጢአት ስንጨቀይ ማየትን አትሻም! ንጽሕና የባሕርዩ የኾነ ቅዱስ አምላክን በንጽሕና የወለደች ቅድስት እናታችንን በንጽሕና መቀበል እንችል ዘንድ ከሚያቆሽሸን ነገር እስከመጨረሻው እንራቅ። "ንዒ" ያልናትን ጸሎት የምትሰማ እናት እንዳለን እናምናለን አይደል? ካመንን እንደምትመጣም እናምናለን! ስለዚህ እርሷ ስትመጣ የማንሳቀቅበት ቦታ ላይ እንጠብቃት። የከበሩ ሰዎችን እንኳ ከቦታ መርጠን የከበረ ቦታ አይደል የምንቀጥራቸው? ከፍጡራን ኹሉ በላይ የከበረች እመቤታችንን ከልጇ ጋር ነይ ካልናት የት መጠበቅ እንዳለብን አይጠፋንም! የከበረ ቦታ ብቻ!!! በሰዓታቱ ጸሎት "ንዒ ኀቤየ" ያልካትን እመቤት ወደ አንተ ትመጣለችና ና ቀራንዮ ከመስቀሉ ሥር ኾነህ ተቀበል! ና ከዮሐንስ ጋር የምታገኛት እዚህ ከልጇ መስቀል ሥር ነውና ተቀበል! የጸሎትህ መልስ መምጫው ቅርብ ነውና ከቦታህ ሳትጠፋ መልስህን ተቀበል! @Tsegasilase ከቀናት በአንዷ ቅዳሜ ነሐሴ ፲፯/፳፻፲፯ የምሕረት ዓመት #ዘቀዳሚት_challenge https://t.me/Tsegasilase ለአስተያየትዎ 👉 @Tsegasilasebot

የዚህ ዓለም ነገር ኹሉ #አይመጥናትምና የሚመጥናትን ምን ዓይነት ምስጋና እናቅርብላት? ቅዱስ ጳውሎስ ስለ ቅዱሳን ሲናገር ‛ዓለም አልተገባቸውም’ ካላቸው ከከዋክብት በላይ ኾና እንደምታበራው ፀሐይ ለኾነችው ለአምላክ እናትማ ምን ልንል እንችል ይኾን? ...” (ቅዱስ ባስልዮስ) እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም የዕርገት በዓል በሰላም አደረሳችሁ።

“... በእሳት ሰረገላ ላይ የተሳፈረው ኤልያስ፥ ወደ እሳታዊው ክርስቶስ ደረት የተጠጋውን፥ ዮሐንስን አየው። የታቦር ተራራ የቤተ ክርስቲያን ምሳሌ ሆነ፤ ክርስቶስም ሁለቱን ኪዳናት አዋሐዳቸው!” (ቅዱስ ኤፍሬም) እንኳን ለበዓለ ደብረ ታቦር አደረሳችሁ!

Repost from Theo-Sophia
ሰላም እንዴት አረፈዳችሁ! ዛሬ ማታ 3:00 ሰዓት ላይ ከወንድማችን ኪዳን ጋር ነገረ እግዚአብሔር በብሉይ ኪዳን ላይ ትምህርት ይኖረናል። እንዳትቀሩ! @Theo_Sophia_apology
ሰላም እንዴት አረፈዳችሁ! ዛሬ ማታ 3:00 ሰዓት ላይ ከወንድማችን ኪዳን ጋር ነገረ እግዚአብሔር በብሉይ ኪዳን ላይ ትምህርት ይኖረናል። እንዳትቀሩ! @Theo_Sophia_apology

ከሰኞ ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ ጥቂቱን እነሆ... ❝ርዕየ ኢሳይያስ ነቢይ በመንፈሰ ትንቢት ምስጢሮ ለአማኑኤል... ❞
ነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት በሚገልጽ መንፈስ ቅዱስ የአማኑኤልን ምሥጢር አየና አሰምቶ ተናገረ። አማኑኤል ማለት ሰው የኾነ አምላክ ማለት ነውና “ሕጻን ተወለደልን፤ ወልድ ለሕማም ለሞት ተሰጠልን። አንድም ወልድ ለኩነተ ሥጋ ተሰጠልን፤ ሕጻንም ኾኖ ተወለደልን” ብሎም ጮኸ (ኢሳ. ፱፥፮)። አትናቴዎስ ሐዋርያዊም “ስለ ድኅነተ ሰብእ የአዳምን ባሕርይ ገንዘብ አደረገ፤ ካሣ ይከፍልልን ዘንድ ቃል ሥጋ ኾነ” ይላል (Ep. 61:3.)። ወልድ ዘበላዕሉ ሕፃን ዘበታሕቱ ከሚባል ልጅሽ እመቤታችን ጽንዕት በድንግልና ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን።

ለቅምሻ ያህል ከነገው ትርጓሜ... የተቀረውን ነገ አዳምጡት። ❝አንቲ ውእቱ ተቅዋም ዘወርቅ እንተ ጾርኪ ማኅቶተ ጸዳል... ❞
ብርሃንነት ያለውን ፋና የተሸከምሽ የወርቅ ተቅዋም (መቅረዝ) አንቺ ነሽ (ዘጸ. 25፥31-40)። ይኸውም ፋና ለሰው ኹሉ ዕውቀትን የሚገልጽ ብርሃን ነው። ጥንት ከሌለው ከብርሃን የተገኘ ብርሃን ነው። ከባሕርይ አምላክ የተገኘ የባሕርይ አምላክ ነው። ሳይለወጥ ካንቺ ሰው የኾነው ነው። ሰውም በመኾኑም በድንቁርና በቀቢጸ ተስፋ ለምንኖር ለኛ አበራልን (ዕውቀትን ገልጸልን)። በጥበቡ ባደረገው ሥጋዌ እግረ ልቡናችንን ወደ ሕገ ወንጌል ጎዳና አቀናልን (ኢሳ. 9፥1-2፥ ማቴ. 4፥14-16)። ታላቁ የዜማ አባት ሊቁ ቅዱስ ያሬድም፡- “አንቲ ውእቱ ተቅዋም ዘወርቅ ዘኢገብራ እደ ኬንያ ዘሰብእ… - የብልሐተኛ እጅ ያልሠራት በውስጧም መብራት የሚያበሩባት የወርቅ መቅረዝ አንቺ ነሽ፤ ራሱ የአብ ብርሃን ያበራባታል እንጂ። ከብርሃን የተገኘ ብርሃን ወደ አንቺ መጥቶ አደረ። አምላክነቱም በዓለም ኹሉ አበራ። ጨለማን ከሰዎች ላይ አራቀ። እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ፤ በብርሃኔ እመኑ፤ ብርሃን ሳለላችሁ ተመላለሱ ብሎ በሚያድን ቃሉ አዳነን” ብሏል /ቁ. 8፤ ዮሐ. 12፥35፤ 1ኛ ዮሐ. 1፥5/። በጥበቡ ባደረገው ሥጋዌ እግረ ልቡናችንን ወደ ሕገ ወንጌል ጎዳና ከአቀናልን ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን።

ቅዳሜ ከሚተረጎመው የውዳሴ ማርያም ትርጓሜ ቅምሻ (ሙሉውን የዕለቱን ውዳሴ ማርያም ትርጓሜ ሔዳችሁ አዳምጡት።) ❝ተፈሥሒ ኦ ምልእተ ጸጋ ድንግል ዘእንበለ ርኵስ... ❞
አደፍ ጉድፍ የሌለብሽ ድንግል ምልዕተ ክብር ሆይ! ደስ ይበልሽ፡፡ ከእናትሽ ማኅፀን ጀምሮ መንፈስ ቅዱስ ጠብቆሻልና የዓለም ኹሉ መክበሪያ ንጽሕት ጽዋዕ ነሽ (ከሥላሴ ለምንጠጣው ክብር ምክንያት አንቺ ነሽ)፡፡ ኤንደ ደብተራ ኦሪቷ ማለትም ሙሴና አሮን በቀዳማይ ሰዓተ ሌሊት አብርተው በቀዳማይ ሰዓተ መዓልት እንደሚያጠፏት ፋና ያይደለሽ የማትጠፊ ፋና ነሽ (ዘጸ. 25፥31-40)። እንደ ቀደመችው የኦሪት ቤተ መቅደስ ያይደለሽ የማትፈርሺ መቅደስ ነሽ (1ኛ ነገ. 7፥48-50)። ሊቁ አባ ጊዮርጊሥ ዘጋሥጫም፡- “አንቲ ውእቱ መቅደስ ዘሐነጸ ሰሎሞን ወአስቀጸላ በሜላትሮን ወለበጠ ዳቤራ በውሳጥያተ መቅደስ፤ … - ሰሎሞን ያሠራት እንደ ዝናር እንደ ዐምድ ባለ ወርቅ የጠፈሯን ዙርያ ያስጌጣት፤ በመቅደስ ውስጥ ያለቺውን ቅድስተ ቅዱሳንዋን ዐውደ ምሕረቷን ግድግዳዋን በጥሩ ወርቅ ያስጌጣት፤ ቁመቱ ሃያ ክንድ፤ ክንፉ ዐሥራ አምስት ክንድ የሚኾን ኪሩብን በውስጧ ያሣለባት ቤተ መቅደስ አንቺ ነሽ” በማለት በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች እመቤታችን ሰሎሞን ባሠራት የወርቅ ቤተ መቅደስ መስሎ ኹለንተናዋ በንጽሕና በቅድስና ያጌጠች የተዋበች መኾኗን አስተምሯል (አርጋኖን ዘዐርብ) ዳሩ ግን እመቤታችን በንጽሕናዋ በቅድስናዋ በሰሎሞን ቤተ መቅደስ ብትመሰልም ሊቁ (ኤፍሬም) እንዳለው ክብሯ የላቀ ነው፤ የሕያው እግዚአብሔር ቤተ መቅደስ ናትና የማትፈርስ መቅደስ ናት (መዝ. 86፥1-5)። የማትለወጥ የቅዱሳን ሃይማኖታቸው (ቅዱሳን የሚያምኑበት ክርስቶስን የወለድሽላቸው አንቺ) ነሽ፡፡ ድንግል ሆይ! በውስጥ በአፍአ በነፍስ በሥጋ ይቅር ይለን ዘንድ፣ ኃጢአታችንን ያስተሠርይልን ዘንድ ከልጅሽ ዘንድ አማልጅን፡፡ ኃጢአታችንን ከሚያስተሠርይልን ልጅሽ ፅንዕት በድንግልና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳይነሣን ለምኚልን።

ወድቆ መማር እንዴት ደስ ይላል መሰለህ ወንድሜ ... የምር የሚያስተምርህ እሱ ነው ... ክርስቶስ ከዚህ በኋላ በሱ ላይ ብቻ እንድትመካ ነው በሃጢአት እንድትወድቅ  የተወህ .... ከዛ በራስ መተማመንህ ይወጣልሀል ... የሆነ ሰአት ከሃጢአት ስትርቅ በራስህ ጉብዝና ይመስልህና እና መኮፈስ ትጀምራለህ .... እግዚአብሄር ደግሞ እንደ ትዕቢት የሚጠላው ነገር ስለሌለ ጸጋውን ያርቅብህና እና ድጋሚ እንድትወድቅ ይተውሀል ...እንደዚ እያደረገ  ብዙ አመት ያስተምርሀል .... ከዛ በራስህ መሳቅ ትጀምራለህ...በራስ መተማመን ምን አይነት ትዕቢት እንደሆነ ትረዳለህ ....ፈፅሞ ራስህን ማመን ታቆማለህ .... ከሱ ጸጋ ውጪ በራስህ ምንም ማድረግ እንደማልችል ስትረዳ ትዕቢትህ ይተነፍሳል ..... የፈለገ ከሃጢአት ብትርቅ ያንኑ ቀን ወይም ሚቀጥለው ቀን የምትወድቅ በጣም ደካማ ፍጥረት መሆንህን ትረዳለህ .... ድካምህን አምነህ ሀይሌም ብርታቴም አንተ ነህ ማለት ስትጀምር በሰላም መኖር ትጀምራለህ.... ያለሱ ምንም አቅም እንደሌለህ ውድቀቶችህ ያስተምሩሀል .... እግዚአብሄር እንድትወድቅ እየተወህ ያለው ትዕቢትን ነቅሎ ሊጥልልህ ነው .... አሁን ደካማነትህን አምነህ ወደሱ ተመለስ ... በራስህ የተማመንክባቸውን ዘመኖች እያሰብክ በራስህ ላይ ሳቅበት በራስህ የተመካህ  ምኑ ከንቱ ነህ በለው.... እም እኁከ ኃጥእ @amlake_birhan

ይህ ነገ ከሚተረጎመው የረቡዕ ውዳሴ ማርያም የተወሰደ ነው፤ ሙሉውን ነገ በደብራችሁ ሔዳችሁ አዳምጡ። ❝አንቲ ዘበአማን ደመና እንተ አስተርአይኪ ለነ ማየ ዝናም...❞
“እንተ በአማን ንጹሕ ዝናም” የተባለ፣ የነፍሳትን ጥም ያበረደ የሕይወት ዝናም፣ የሕይወት ጠል፣ የሕይወት ውሃ ክርስቶስን ቋጥረሽ (በድንግልና ፀንሰሽ፣ በድንግልና ወልደሽ) የታየሽልን እውነተኛ ደመና አንቺ ነሽ፡፡ ኢትዮጵያዊው ቄርሎስ አባ ጊዮርጊሥ ዘጋሥጫም፡- “ንዑ እንከ ከመ ናልዕላ ለዛቲ ደመና ብርሃን እንተ ጾረቶ ለማየ ዝናም ንጹሕ- ንጹሑን የዝናም ውሃ የተሸከመችውን የብርሃን ደመና ኑ ከፍ ከፍ እናድርጋት” ብሎ ጋብዞናል /አርጋኖን ዘሠሉስ ፮፡፪/፡፡ ስትወልጂው ማኅተመ ድንግልናሽ አለመለወጡ፤ አካላዊ ቃል ሰው ሲኾን አምላክነቱ ላለመለወጡ፣ ድንግል ወእም (ድንግልም እናትም) ስትባዪ መኖርሽም ልጅሽ  አምላክ ወሰብእ (ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው) ሲባል ለመኖሩ ምሳሌ ነውና አብ የልጁ ምልክት አደረገሽ፡፡ መንፈስ ቅዱስ ቢያድርብሽ፣ ኀይለ ልዑል ወልድም ሥጋሽን ቢለብስ፤ አንድም መንፈስ ቅዱስ ከሦስቱ ግብራት (ማለትም ከሩካቤ፣ ከዘር፣ ድንግልናን ከመለወጥ) ቢከለክልሽ፣ ኀይለ ልዑል ወልድም ከሦስቱ ግብራት ቢከልልሽ ለዘላለሙ የሚኖር አካላዊ ቃልን ወለድሽልን /ሃይ.አበ.፻፲፡፳፱/፡፡ እርሱም ሰው ኾኖ ከኃጢአት አንድም ከኃጢአታችን ፍዳ አዳነን፡፡ ደስ ያለህ ባለ ምሥራች ገብርኤል ሆይ! ወደኛ የመጣ የጌታን ልደት ነግረኸናልና ላንተ የተሰጠ ክብር ፍጹም ነው፡፡ አንድም “ወነዋ ተወልደ ፍስሐ ዘይከውን ለክሙ ወለኩሉ ዓለም - እነሆ ለሕዝቡ ኹሉ የሚኾን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁ” ብለህ (ሉቃ. ፪፡፲) የጌታን ልደት ለኖሎት (ለእረኞች) ነገርኻቸዋልና ለአንተ የተሰጠ ክብር ፍጹም ነው፡፡ “እግዚአብሔር ከሥጋሽ ሥጋ ከነፍስሽ ነፍስ ነሥቶ ካንቺ ጋራ አንድ ይሆናልና ደስ ይበልሽ” ብለህ (ሉቃ. ፩፡፴) ለእመቤታችን ነግረኻታልና ለአንተ የተሰጠ ክብር ፍጹም ነው፡፡ እንዲህ ካለ ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳነሣን ለምኚልን፡፡

ይህ ነገ ከሚተረጎመው የረቡዕ ውዳሴ ማርያም የተወሰደ ነው፤ ሙሉውን ነገ በደብራችሁ ሔዳችሁ አዳምጡ። ❝አንቲ ዘበአማን ደመና እንተ አስተርአይኪ ለነ ማየ ዝናም...❞
“እንተ በአማን ንጹሕ ዝናም” የተባለ፣ የነፍሳትን ጥም ያበረደ የሕይወት ዝናም፣ የሕይወት ጠል፣ የሕይወት ውሃ ክርስቶስን ቋጥረሽ (በድንግልና ፀንሰሽ፣ በድንግልና ወልደሽ) የታየሽልን እውነተኛ ደመና አንቺ ነሽ፡፡ ኢትዮጵያዊው ቄርሎስ አባ ጊዮርጊሥ ዘጋሥጫም፡- “ንዑ እንከ ከመ ናልዕላ ለዛቲ ደመና ብርሃን እንተ ጾረቶ ለማየ ዝናም ንጹሕ- ንጹሑን የዝናም ውሃ የተሸከመችውን የብርሃን ደመና ኑ ከፍ ከፍ እናድርጋት” ብሎ ጋብዞናል /አርጋኖን ዘሠሉስ ፮፡፪/፡፡ ስትወልጂው ማኅተመ ድንግልናሽ አለመለወጡ፤ አካላዊ ቃል ሰው ሲኾን አምላክነቱ ላለመለወጡ፣ ድንግል ወእም (ድንግልም እናትም) ስትባዪ መኖርሽም ልጅሽ  አምላክ ወሰብእ (ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው) ሲባል ለመኖሩ ምሳሌ ነውና አብ የልጁ ምልክት አደረገሽ፡፡ መንፈስ ቅዱስ ቢያድርብሽ፣ ኀይለ ልዑል ወልድም ሥጋሽን ቢለብስ፤ አንድም መንፈስ ቅዱስ ከሦስቱ ግብራት (ማለትም ከሩካቤ፣ ከዘር፣ ድንግልናን ከመለወጥ) ቢከለክልሽ፣ ኀይለ ልዑል ወልድም ከሦስቱ ግብራት ቢከልልሽ ለዘላለሙ የሚኖር አካላዊ ቃልን ወለድሽልን /ሃይ.አበ.፻፲፡፳፱/፡፡ እርሱም ሰው ኾኖ ከኃጢአት አንድም ከኃጢአታችን ፍዳ አዳነን፡፡ ደስ ያለህ ባለ ምሥራች ገብርኤል ሆይ! ወደኛ የመጣ የጌታን ልደት ነግረኸናልና ላንተ የተሰጠ ክብር ፍጹም ነው፡፡ አንድም “ወነዋ ተወልደ ፍስሐ ዘይከውን ለክሙ ወለኩሉ ዓለም - እነሆ ለሕዝቡ ኹሉ የሚኾን ታላቅ ደስታ የምሥራች እነግራችኋለሁ” ብለህ (ሉቃ. ፪፡፲) የጌታን ልደት ለኖሎት (ለእረኞች) ነገርኻቸዋልና ለአንተ የተሰጠ ክብር ፍጹም ነው፡፡ “እግዚአብሔር ከሥጋሽ ሥጋ ከነፍስሽ ነፍስ ነሥቶ ካንቺ ጋራ አንድ ይሆናልና ደስ ይበልሽ” ብለህ (ሉቃ. ፩፡፴) ለእመቤታችን ነግረኻታልና ለአንተ የተሰጠ ክብር ፍጹም ነው፡፡ እንዲህ ካለ ልጅሽ ጽንዕት በድንግልና ሥርጉት በቅድስና እመቤታችን ጸጋውን ክብሩን እንዳነሣን ለምኚልን፡፡

ወደ እግዚአብሔር የምንፈልስበት ጾም ያድርግልን።

ጥያቄዎቻችሁን በcomment አስቀምጡልን ወይም @SSC_gibe_gubae_qa_bot ጠይቁን። ረቡዕ ማታ ሁለት ሰዓት ከሃያ እንገናኝ።
ጥያቄዎቻችሁን በcomment አስቀምጡልን ወይም @SSC_gibe_gubae_qa_bot ጠይቁን። ረቡዕ ማታ ሁለት ሰዓት ከሃያ እንገናኝ።

ተስፋውን በሰው ወይም በፍጥረት የሚያደርግ ከንቱ ነው። ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍቅር ለሌሎች መገዛት በዚህ ዓለም ድኃ ሆኖ መታየት አያሳፍርህ። ተስፋህን በእግዚአብሔር አድርግ እንጂ በራስህ አ
ተስፋውን በሰው ወይም በፍጥረት የሚያደርግ ከንቱ ነው። ስለ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፍቅር ለሌሎች መገዛት በዚህ ዓለም ድኃ ሆኖ መታየት አያሳፍርህ። ተስፋህን በእግዚአብሔር አድርግ እንጂ በራስህ አትቁምየሚቻልህን አድርግ መልካም ፈቃድህንም እግዚአብሔር ያግዘዋል። ትዕቢተኞችን በሚያዋርድ ትሑታንን በሚረዳ በእግዚአብሔር ጸጋ ታመን እንጂ በእውቀትህ ወይ በማንም ሰው ብልሐት አትታመን። ኹሉን በሚሰጥ ራሱንም ከኹሉ በላይ ሊሰጥ በሚፈልግ በእግዚአብሔር ተመካ እንጂ ቻዮች ናቸው ብለህ በወዳጆችህ፣ ባለጸግነትም ቢኖርህ በባለጸግነትህ አትመካ። በተፈጥሮህ ያለህ መልካም ነገር ኹሉ ገንዘቡ የእግዚአብሔር ነውና በእውቀትህና በብልሐትህ ደስ አይበልህ። በሰው ያለውን በሚያውቅ በእግዚአብሔር ፊት እንዳትነቀፍ ከሌሎች እሻላለሁ አትበል።