en
Feedback
ጸጋ ሥላሴ || Tsegasilase

ጸጋ ሥላሴ || Tsegasilase

Open in Telegram

ከማይደርቅ እውነተኛ ምንጭ የሚቀዳ 🛑 YouTube 🛑 https://youtube.com/@tsegasilase?si=aV9bMxo_NGQBImVp ለማንኛውም ዐሳብና አስተያየት 👇👇 @TsegasilaseBot

Show more
1 020
Subscribers
-124 hours
+67 days
+2730 days

Data loading in progress...

Attracting Subscribers
September '26
September '26
+18
in 1 channels
August '26
+41
in 1 channels
Get PRO
July '26
+64
in 1 channels
Get PRO
June '26
+103
in 1 channels
Get PRO
May '26
+42
in 1 channels
Get PRO
April '26
+92
in 6 channels
Get PRO
March '26
+30
in 1 channels
Get PRO
February '26
+22
in 1 channels
Get PRO
January '26
+22
in 0 channels
Get PRO
December '25
+31
in 0 channels
Get PRO
November '25
+29
in 1 channels
Get PRO
October '25
+16
in 0 channels
Get PRO
September '25
+22
in 0 channels
Get PRO
August '25
+42
in 3 channels
Get PRO
July '25
+40
in 0 channels
Get PRO
June '25
+31
in 0 channels
Get PRO
May '25
+42
in 1 channels
Get PRO
April '25
+80
in 4 channels
Get PRO
March '25
+133
in 10 channels
Get PRO
February '25
+39
in 2 channels
Get PRO
January '25
+16
in 0 channels
Get PRO
December '24
+35
in 0 channels
Get PRO
November '24
+40
in 1 channels
Get PRO
October '24
+21
in 0 channels
Get PRO
September '24
+254
in 2 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
10 September0
09 September+1
08 September+1
07 September+2
06 September0
05 September+3
04 September+1
03 September+2
02 September+4
01 September+4
Channel Posts
ሩፋኤል አሳድገኝ!

2
ይቅርታህ ፈጥኖ ይደረግልን “የቀደመውን በደላችንን አታስብብን፥ ምሕረትህ በቶሎ ታግኘን፥ እጅግ ተቸግረናልና።” መዝሙር 79፥8
ይቅርታህ ፈጥኖ ይደረግልን “የቀደመውን በደላችንን አታስብብን፥ ምሕረትህ በቶሎ ታግኘን፥ እጅግ ተቸግረናልና።” መዝሙር 79፥8
299
3
“እኛ አገራችን በሰማይ ነውና፥ ከዚያም ደግሞ የሚመጣ መድኃኒትን እርሱንም ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን እንጠባበቃለን።” ፊልጵስዩስ 3፥20 መልካም ሰንበት
305
4
🔸የዋዘኞት ወንበር🔸 ከላይ ቀንጭቤ ያስደመጥኳችሁን ስብከት ሙሉውን ታደምጡት ዘንድ የቅዳሜ ግብዣዬ ነው። በኃጢአት ማዕበል የተናወጠች ፣ በሐዘንና በመከራ የቆሰለች ነፍሳችን ዕረፍትን ታገኝ ዘንድ ይህን የመምህር ብርሃኑ አድማስን ድንቅ ስብከት እንድታደምጡ በእግዚአብሔር ፍቅር እጋብዛችኋለሁ። ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ «በዝንጎች ምክር ያልሄደ ፣ በኃጢአተኞችም መንገድ ያልቆመ ፣ በዋዘኞችም ወንበር ያልተቀመጠ ምስጉን ነው» (መዝ. 1፥1) በማለት የተናገረውን ቃል መነሻ በማድረግ መምህራችን በዚህ ተወዳጅ ትምህርታቸው የነፍሳችንን ቁስልና የዘመናችንን ፈተና በጥልቀት ፈትሸው አሳይተውበታል። በነቢዩ ኢሳይያስ «ከእግር ጫማ እስከ ራስ ድረስ ጤና የለውም» እንደተባለው በኃጢአታችን ምክንያት የቆሰለችውን ነፍሳችንን ፣ የደረሰብንን ሰላም ማጣትና የመንፈስ መረበሽ በንስሐ እንዴት እንደምናክመው አስተምረውናል። የሰውን ልጅ ነፍስ ከእግዚአብሔር የሚለዩትና ለውድቀት የሚዳርጉት ኃጢአቶች በስፋት በስብከቱ ተተንትነዋል። ተንበርክኮ ማልቀስና ምሕረትን መለምን ፤ ባልንጀራን ማስቀደም ትሕትናን መላበስና ቅድሚያ ለሌሎች መስጠት ፤ ክፉን በክፉ አለመመለስና ስለሚያሳድዱን ሰዎች መጸለይ እንዴት መፍትሔ እንደሚኾነን ማድመጥ አትፈልጉም? ተወዳጆች ሆይ የእግዚአብሔር ቃል ለእግራችን መብራት ፣ ለመንገዳችን ብርሃን ነውና ይህንን ትምህርት በማድመጥ የቆሰለች ነፍሳችንን በጥበቡ ዘይት አክመን መንፈሳዊ ሕይወታችንንም እናድስ ዘንድ ከታች ያለውን ሊንክ ተጭነን ሙሉ ስብከቱን እናድምጥ ከስብከቱ ጋር መልካም ቀዳሚት ሰንበት 👇 👇👇 https://youtu.be/VcEb9HSdj6Y?si=sX4fMmDHqTWVDnxv https://youtu.be/VcEb9HSdj6Y?si=sX4fMmDHqTWVDnxv https://youtu.be/VcEb9HSdj6Y?si=sX4fMmDHqTWVDnxv
377
5
አይምርህም/አይምርሽም የሚለን ሰይጣን ነው ፤ ንስሓ ገብተን ደጋግመን ብንወድቅም ተስፋ አንቁረጥ!
322
6
መዝሙር ምስጋና ብቻ ነው? ጸሎትም ፤ ትምህርትም ፤ ምስጋናም የኾኑ በልጅነት አእምሯችን የተቀረጹ መዝሙራት አሉ። ልጅነታችንን ከማሳመር ውጪ ነገረ ሃይማኖትን በጭንቅላታችን የቀረጹ ፤ ለዘመናት የተዋሐደንን ሰላም ማስፈን የቻሉ ፤ ለንስሓ ያነቃቁ ናቸው። አኹን ላይ ልጅነታቸው ላይ መዝሙር የሚያደምጡ ካሉ የማድመጥ ዕድል የሚኖራቸው Viral የወጡ ዝማሬዎችን ይመስለኛል። ከዚያ ወደፊት የልጅነት መዝሙሬ ብለው የሚጠቅሷቸውም እነዚህኑ ዝማሬዎች ነው። ታዲያ ከላይ የጠቅስናቸውን መመዘኛዎች የትኞቹ ዝማሬዎቻችን ያሟላሉ? ምን ተሻለን? የመፍትሔ ሀሳብ አላችሁ??
373
7
+ የካም ትውልድ + ክፍል ፪ ከግብፅ ጳጳሳት ተሾመው እስኪመጡ ድረስ ከቅዱስ ማርቆስ ሐዋርያዊ መንበር ላለመውጣት በትእግሥት የጠበቀው ይህ ሕዝብ ከአንዴም ሁለቴ በስመ ግብፃዊ የጳጳስ ልብስ ለብሰው ተሾሜ መጣሁ ብለው ያጭበረበሩት የሐሰት ጳጳሳትንም ሁለት ጊዜ እውነት መስሎት ተቀብሎ ተታልሎአል፡፡ በእውነት ተሹመው ከመጡት ጳጳሳት ውስጥም ሰማዕታት እስከመሆን ደርሰው እረኝነታቸውን የተወጡ ሁለት ጳጳሳት እንደነበሩ ሁሉ የግብፅን ከሊፋዎች ፖለቲካዊ ዓላማ የሚያስፈጽሙና አንዳንዶቹም ንግድ ላይ የተሠማሩ ነበሩበት፡፡ ወደ ገጠሪቱ ክፍል ተራራ ወጥቶ ወርዶ ‘እፍ’ በማለት የሚሠጠውን የክህነት ማዕረግ ለመሥጠት ፈቃደኛ ያልነበረና ትንፋሼን በስልቻ ውስጥ ሞልቼ ልስጣችሁና ያንን እያዞራችሁ ክህነት አዳርሱ የሚል አፈር አይንካኝ ባይ አባትም ያየ ሕዝብ ነበረ፡፡ ይህን ሁሉ ክፉና ደግ እያየም የክህነት ክብር የሚገባው የኢትዮጵያ ሕዝብ አባቶቹን በትዕቢት ዓይን ለዘመናት ኖሯል፡፡ ከጥቂት ዐሠርት ዓመታት ወዲህ ግን በአባቱ ዕርቃን የሚሳለቅ የካም ትውልድ ተነሣ፡፡ የአባቱን ዕርቃን ለሴምና ለያፌት ሳይሆን ለዓለም የሚያወራና የሚሳለቅ ፣ ከቄስ እስከ ጳጳስ ፤ ከሲኖዶስ እስከ ሀገረ ስብከት በአደባባይ የሚዘልፍና የሚያንጓጥጥ ፣ ቤተ ክርስቲያንን የጋዜጣ ማድመቂያ የሚድያ ማሸብረቂያ የሚያደርግ ትውልድ ተነሣ፡፡ ‘‘እኛና መንፈስ ቅዱስ ፈቅደናል’’ ብሎ የመወሰን ሥልጣን ያለው ከሐዋርያት ጀምሮ ሲወርድ እዚህ የደረሰው ቅዱስ ሲኖዶስ የአንድ ተራ ካቢኔ ያህል እንኳን ክብር የማይሠጠው ፣ ስብሰባዎቹ በምሥጢር የማይጠበቁለት አካል መሆን ጀመረ፡፡ ሊቃነ ጳጳሳትም ካልሞቱ በስተቀር ጨርሶ ክብር እንዳይሠጣቸው የተማለ እስኪመስል ድረስ ትውልዱ ፊት ለፊት ቢያገኛቸው ቀና ብሎ ለማየት እንኳን በዕርግናቸው የሚፈራቸውን አባቶች ለቤተ ክርስቲያን በመቆርቆር ስም ማንጓጠጥ ቀስ በቀስ እየተለማመደ መጣ፡፡ በብዙዎች ምእመናን ዘንድ የተቆርቋሪነት ስሜት ለመፍጠርና መረጃ ለመሥጠት የተጀመሩ ድረ ገጾች ፍጻሜያቸው ወደ ስድብ እያደገና የአባቶችን ገመና በአደባባይ በማስጣት ሥራ ላይ በመጠመዳቸው ምክንያት ቀስ በቀስ ግርማዋ ከሩቅ የሚያስፈራውን ልዕልት ቤተ ክርስቲያን ሁሉም እየተነሣ የስድብ ምራቁን ይተፋባት ጀመር፡፡ ቤተ ክርስቲያን የምትሰኘው ሕንፃዋ ብቻ ሳትሆን ምልክቶችዋ የሆኑት ብፁዓን አበውና ካህናት መሆናቸው ተዘንግቶ በግራ በመናፍቃን ሚድያዎች በቀኝ በተቆርቋሪ ነን በሚሉ ሚድያዎች እየተላተመች የምትሰደብ ቤተ ክርስቲያን ሆና አረፈችው፡፡ ጳጳስን መሳደብ ፣ ካህንን አንተ ማለት ቀስ በቀስ እየተለመደ መጣ፡፡ ቤተ ክርስቲያን በሁለት ወገን ተጨነቀች ፤ አሰዳቢ ሥራ የሚሠሩ ልጆችዋ በአንድ ወገን ፤ ያንን እያነሡ የሚሰድቧት ደግሞ በሌላ ወገን ተሰለፉ፡፡ ሁሉም የበለጠ ተቆርቋሪነቱን አስመሰክራለሁ ሲል ቤተ ክርስቲያንዋን በልጆችዋም በውጪ አካላትም ያላትን ተቋማዊ ቅቡልነት /inistitutional acceptability/ እያጣች ሔደች፡፡ በአሰዳቢና በተሳዳቢ መካከል ቤተ ክርስቲያን ለሁለት ተቸንክራ ስትሠቃይ በመሃል ቤት ተኩላዎች በገፍ ነድተው ልጆችዋን ነጠቋት፡፡ የምትፈልገው የሚያሰድባትንም ሆነ የሚሰድባትን ሳይሆን በፈረሰው አጥርዋ በኩል ቆሞ የሚሠራላትን ነበር፡፡ በዚህ የስድብ ጎርፍ ምክንያት አቅሙ ከሚችለው በላይ መጥፎ መረጃዎችን በመስማቱ መቋቋም ተስኖት ሃይማኖቱን የጠላ ፣ ለካህን መናዘዝን የተወ ፣ በአባቶቹ ተስፋ የቆረጠ ትውልድ እየተፈጠረ መጣ፡፡ የመንግሥት አካላት እንዲሁም ከቤተ ክርስቲያን በተቃራኒ ያሉ አካላት ደግሞ በታሪክ የበላይነትዋና በመንፈሳዊነትዋ ከሩቅ ይፈሯት የነበሯትን ቤተ ክርስቲያን ወደ መናቅና የቅዱስ ሲኖዶሱንና የአባቶችን ድምፅ ከምንም ወዳለመቁጠር ደረጃ ደረሱ፡፡ ከላይ ያነሣኋቸው የአርመን ዲያቆናት ቤተ ክርስቲያን ሳትፈቅድ ቃለ መጠይቅ አንሠጥህም ሲሉኝ የከፋኝም ለዚህ ነበር፡፡ የቤተ ክርስቲያናቸውን ገጽታ በመገንባት በኩል አርኣያ የሚሆኑን ግብፃውያንም ናቸው፡፡ የግብፅ ቤተ ክርስቲያን እኛ ካየነው የከፋ ብዙ ፈተናዎችን ያሳለፈች ቢሆንም ውስጣዊ ችግሮቻቸውን አፍነው ሸሽገው በጎ በጎውን ብቻ በመጻፍ የሚታወቁ ሲሆን በዚህም ከራሳቸው ሀገር አልፈው በዓለም አቀፍ ደረጃ ቤተ ክርስቲያንዋ በጎ ስም እንዲኖራት ማድረግ በሚገባ ችለዋል፡፡ ይህንን ማድረግ የቻሉት በውስጣቸው ምግባረ ብልሹ አባቶችና አገልጋዮች ሳይኖሩ ቀርተው አይደለም፡፡ የወላጆችን መጥፎነት እየነገርህ ልጆችን ማሳደግ እንደማትችል ሁሉ የቤተ ክርስቲያንዋን የክህነት አገልግሎት ክብር አዋርደህ ምእመናንን በመንፈሳዊ ሕይወት ማሳደግም እንደማይታሰብ በመገንዘባቸው ነው፡፡ በአንድ ወቅት በደቡብ አፍሪካ ገጠራማ መንደር ውስጥ ያለችን ገዳም ለመጎብኘት ከሁለት ግብፃውያን አባቶችና ከአንድ ወዳጄ ጋር ተጉዘን ነበር፡፡ የምንጓዝበትን መኪና የሚነዱት አባ አባድር የሚባሉ መነኩሴ ሲሆኑ ከአጠገባቸው ደግሞ የኮፕቲክ ቤተ ክርስቲያን የመላው አፍሪካ ጉዳዮች ሊቀ ጳጳስ አቡነ እንጦንስ ማርቆስ ተቀምጠዋል፡፡ እኔ ከኋላ ሆኜ ብፁዕነታቸውን የባጥ የቆጡን እጠይቃቸዋለሁ፡፡ ከጠየቅሁት ጥያቄ አንደኛው ይህ ነበር ፦ ‘የእናንተ ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ጸሐፊው ኢሪስ ሀቢብ የጻፋቸውን መጻሕፍት አንብቤ ነበር...’ ፈገግ አሉና ‘ኢሪስ ሀቢብ ሴት ናት’ አሉኝ፡፡ ስኅተቴን ተቀብዬ ቀጠልሁ፦ ‘በታሪካችሁ ላይ በቤተ ክርስቲያንዋ ውስጥ ስለተነሡ አለመግባባቶች በሌላ ሀገር ሰዎች ተጽፈው የምንሰማቸውን ታሪኮች ለምሳሌ የአቡነ ቄርሎስና የአቡነ ሺኖዳን አለመግባባት ፤ የአባ ማቴዎስ አል ምስኪንና የአቡነ ሺኖዳን አለመግባባት ወዘተ ጉዳዮች በምንም ሚድያዎች አንሰማም፡፡ ይህ ለምንድን ነው?’ አልኳቸው፡፡ ብፁዕነታቸው ፈገግ ብለው ሾፌሩን አባት ተመለከቷቸውና እሳቸው እንዲመልሱ ነገሯቸው፡፡ አባ አባድር የሠጡት ረዥም መልስ በፍጥነት በሚበርረው መኪና መስኮት በሚነፍሰው ነፋስ ድምፅና አረቢኛ በጣም በተጫነው የእንግሊዝኛቸው ቃና ውስጥ ቢደበቅብኝም [ይህን ጽሑፍ ልጽፍ ስል የተቀረጸውን ሰምቼው ነበር] የማልዘነጋውና ትልቅ ትምህርት የሚሠጥ ሁለት ነገር ተናግረዋል፡- ‘በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ሥራ የሚሠራው ሁለት መንፈስ ነው፡፡ አንደኛው የእግዚአብሔር መንፈስ ነው ፤ ሁለተኛው ደግሞ የሰይጣን መንፈስ ነው፡፡ የእግዚአብሔር መንፈስ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ መልካም ነገሮችን በሰዎች አድሮ ሲሠራ የሰይጣን መንፈስ ደግሞ በሰዎች አድሮ መጥፎ ሥራ ይሠራል፡፡ እኛ በመጻሕፍቶቻችንና በሚድያዎቻችን እግዚአብሔር የሠራውን እንጂ ሰይጣን የሠራውን አንጽፍም’ ብለው አሳረፉኝ፡፡ እውነትም ሳስበው ቤተ ክርስቲያናችን ገድል ብላ ለታሪክ የምትጽፈው የቅዱሳን ተጋድሎ እንጂ የኃጥአንን ክፋት አይደለም፡፡ ዘላለም የምታስታውሰውም የቅዱሳኑን ጽድቅ እንጂ የክፉዎችን ክፋት አይደለም፡፡ አባቶች ካህናት ብዙ ክፉ ነገር ቢያደርጉ እንኳን እነሱን በአደባባይ መዝለፍ ምእመናንን ከምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ማሸሽና ቤተ ክርስቲያንን ማቃለል ነው፡፡ እግዚአብሔር እንኳን ካህን ምንም ያህል ቢያስቀይመው እንኳን በሕዝቡ ፊት አያዋርደውም፡፡ አሮንና ማርያም ሙሴን አብረው ባሙት ጊዜ ማርያም በግልፅ በለምጽ ስትነድ አሮንን በውስጥ የቀጣው የሾመውን ካህን በሕዝብ ፊት ማቃለል ስላልወደደ ነበር፡ ፡ ሐዋርያቱም አንድ ጋኔን ለዘጠኝ ማውጣት አቅቷቸው በእምነት መጉደል በሕዝብ ፊት በተዋረዱ ጊዜ ሕዝቡን ወቅሶ ካባረረ በኋላ ለብቻቸው ሲሆኑ ስለ እምነታቸው ማነስ የገሠጻቸው የሾማቸውን በሕዝብ ፊት ማዋረድ ስላልፈለገ ነበር፡፡ ወዳጄ በእኛ ቤተ ክርስቲያን እየተባባሰ ለመጣው የክብረ ክህነት መቃለል ተጠያቂው ማን ይመስልሃል? አባቶች? ቤተ ክህነት? ቤተ መንግሥት? ትውልዱ? ሁሉም ሁሉ ላይ ጣቱን ይቀስራል፡፡ የካህናት አለቃ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ዳግም ሊፈርድ ሲመጣ የሚጠይቀው ጥያቄ ግን ‘ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ውስጣዊ ችግር መስፋት ጥፋተኞቹ እነማን ናቸው?’ ብሎ አይደለም፡፡ የእርሱ ጥያቄ አንድ ነው - አንተ ምን አደረግህ? ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ እንደጻፈው መስከረም 2012 ዓ.ም የኤፍራጥስ ወንዝ ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደ
438
8
+ የካም ትውልድ + ክፍል ፩ ከዓመታት በፊት ካይሮ በሚገኘው የነገረ መለኮት ኮሌጅ ቅጽር ጊቢ ውስጥ ለጥቂት ሳምንታት ሰንብቼ ነበር፡፡ በወቅቱ ከነበረኝ የስብከተ ወንጌል አገልግሎት በተጓዳኝ የአጋፔ ቴሌቪዥን ጣቢያን ፣ የኮፕቲክ ጥናትና ምርምር ማእከል ዓይነት ተቋማትን የመጎብኘትና ለመጽሔት የሚሆኑ ሥራዎችንም የመሥራት ግዴታ ነበረብኝ፡፡ አሁን አውስትራሊያ የሚገኙት መጋቤ ምሥጢር ስንታየሁ አባተ ፣ አሁን የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ መምህር የሆኑት ግብፃውያኑ ‘መብሱት’ ብለው የሚጠሯቸው ቀሲስ ዶ/ር ደሳለኝ ዋቅጋሪ የጉዞዬን ተልዕኮ እንድፈጽም እጅግ አመቻችተውልኝ ነበር፡፡ በዚህ ጽሑፍ ላነሣው ወደፈለግሁት ጉዳይ ሳልገባ በፊት በዚያ ጉዞ ወቅት የማልዘነጋቸውን ሁለት በግብፅ የመነኮሱ ኢትዮጵያውያን መነኮሳትን ልዘክር፡- አቡነ ሐያት አንደኛው የግብፅና የኢትዮጵያን ቤተ ክርስቲያን ዕርቀ ሰላም በማመቻቸት ትልቅ ሚና የነበራቸው አቡነ ሐያት ሲሆኑ ሁለተኛው ደግሞ አቡነ ሚናስ ነበሩ፡፡ [ግብፃውያኑ ቀሳውስትንና መነኮሳትን እኛ ጳጳሳትን በምንጠራበት ስም አቡነ ብለው የሚጠሩ ሲሆን ጳጳሳትን ደግሞ ሰይድና ይላሉ] አቡነ ሐያት በግብፃውያኑ ዘንድ እጅግ የሚከበሩ ብዙ የንስሓ ልጆች የነበሯቸው አባት ሲሆኑ ተቋማቱን እንድጎበኝም ከፍተኛ ትብብር አድርገውልኝ ነበር፡፡ እርሳቸውን ሳስብ የማልረሳው ነገር በዕድሜዬ ማነስ ምክንያት ሞገስ እንዳላጣ በማሰብ ያለበሱኝ ቀሚስና መስቀል ሲሆን ሲያስተዋውቁኝም ሊቀ ዲያቆናት እያሉ መሆኑ ነበር፡፡ ከግብፃውያኑ አባቶች መካከል አንድ ሁለቱ ‘እንዴት በዚህ ዕድሜህ ሊቀ ዲያቆናት ሆንህ?’ ብለው በመጠየቅ ግራ አጋቡኝ፡፡ በኋላ አቡነ ሐያት ‘በግብፅ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ዲያቆናት መሆን ረዥም ዓመት ይፈጃል ፤ ከአናጉንስጢስ ንፍቀ ዲያቆን ፤ ከንፍቀ ዲያቆን ዲያቆን ለመድረስ በአገልግሎት ረዥም ዓመት ማሳለፍ ይጠይቃል፡፡ ሊቀ ዲያቆናት ማለት ግን በዲቁናው ረዥም ዓመታት ያገለገለና የተመሰገነ ሰው የሚያገኘው ሹመት ሲሆን ቄስ በሌለበት ሊሞት የደረሰ ሕፃን ሊጠመቅ ቢመጣ ሊቀ ዲያቆናቱ አጥምቆ ማቁረብ ይችላል፡፡ ከቀደሰ በኋላ እዚያው መቅደስ ውስጥ ቆይቶ ጳጳስ ይጠሩና ዕለቱኑ ቅስና ይሾሙታል ፤ የአንተ ሊቀ ዲያቆናት መባል ያስገረማቸው ለዚህ ነው’ ሲሉ ነገሩኝ፡፡ ይህንን ሃሳብ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ተናግሮት እንደነበር ከዚያ በኋላ አንብቤያለሁ፡፡ አቡነ ሚናስ በዚህ ጉዞዬ ያወቅኳቸው ሌላው አባት ደግሞ አቡነ ሚናስ ነበሩ፡፡ እኚህ አባት ደግሞ በቤተ ክርስቲያንዋ በተለያዩ ዓለማት ላሉ ምእመናን እንዲቀድሱ የሚላኩ በዐረቢኛና ኮፕቲክ የተካኑ አባት ነበሩ፡፡ ስለ እኚህ አባት የማልረሳው ደግሞ ደግነታቸውንና ወደ ምንኩስና ለመሳብ የሚያደርጉትን ውትወታ ነው፡፡ በተገናኘንበት ዕለት ብዙ ዓመት እንደሚተዋወቅ ሰው በፍቅር ብዙ ነገር ሲያወሩኝ የነበሩት እኚህ ወጣት መነኩሴ የለበሱት ከከፋይ ብቻ የተሠራ ብርዱን የሚመክት ካፖርት ላይ ዓይኔን ጥዬ ነበር፡፡ የተመረተበትን ማቴርያል ምን እንደሆነ ለማወቅ እጄን ሰድጄ እንደሚገዛ ሰው ስገምት በፈገግታ እያዩ ‘ራሺያ ያሉ ልጆቼ ናቸው ለብርድ ብለው የሠጡኝ’ አሉኝ፡፡ በእርሳቸው እርዳታ በወቅቱ የመላው አፍሪካ ሊቀ ጳጳስ ከነበሩት አባቴ ከብፁዕ አቡነ ያዕቆብ ጋር የቅዱስ ሚናስን ገዳምና የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቄርሎስን መካነ ዕረፍት በክብር አቀባበል ተሳለምን፡፡ ወደ ካይሮ ከተመለስን በኋላ የመጨረሻዋ ዕለት ሊሸኙን በአንድ መኪና ተሳፍረን ሔድን፡፡ ተሰናብተን ወደ ኤርፖርት ለመግባት ከብፁዕነታቸው ጋር ከመኪናው ወረድን፡፡ ብርዱ እጅግ ከፍተኛ ነበር፡፡ መንገድ ስንጀምር አባ ሚናስ በዚያ ብርድ ከመኪናው ወጥተው ወደ እኛ ሮጡና ዓይኔን የጣልሁባትን ያቺን ካፖርት አውልቀው አልብሰውኝ ምንም ሳይናገሩ ወደ መኪናው ሮጠው ተመለሱ፡፡ ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ አንዲት ቃል ተናገሩ ‘ይህ መነኩሴ የእውነት መናኝ ነው!’ ይህ ከሆነ ከጥቂት ዓመታት በኋላ አባ ሚናስ በድንገተኛ አደጋ አቡነ ሐያት በጽኑ ሕመም ተጋድሏቸውን ፈጽመው አርፈዋል፡፡ ፃማ ድካማቸው ይደርብን ከማለት ውጪ ምን እላለሁ? ወደ ቀደመው ነገር ልመለስ፡፡ ከዓመታት በፊት ካይሮ በሚገኘው መንፈሳዊ ኮሌጅ ማደሪያ ለጥቂት ሳምንታት ሰንብቼ ነበር - ብዬ አልነበር የጀመርሁት? አዎ በዚያ ጉብኝት ካይሮ በሚገኘው መንፈሳዊ ኮሌጅ ማደሪያ ለጥቂት ሳምንታት ሰንብቼ ነበር፡፡ በዚያ መንፈሳዊ ኮሌጅ በአንድ ፎቅ መደዳ ክፍሎች የመጀመሪያው ዳር እኔ ፣ ከዚያ ብፁዕነታቸው አቡነ ያዕቆብ ፣ መጋቤ ምሥጢር ስንታየሁ ያረፍን ሲሆን የመጨረሻው ክፍል ላይ ለዚህ ጽሑፍ ምክንያት የሆኑኝ ሁለት አርመናውያን ዲያቆናት ይኖራሉ፡፡ በኮሌጁ የዶክትሬት ዲግሪያቸውን የሚሠሩትን እነዚህን የአርመን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችን በቀሲስ ደሳለኝ በኩል ተዋወቅኳቸው፡፡ በወቅቱ የሐመር መጽሔት ከፍተኛ ሪፖርተርም ስለነበርሁ አጋጣሚውን ተጠቅሜ ስለ አርመን ቤተ ክርስቲያን ቃለ መጠይቅ ላደርጋቸው ፈልጌ ቀርቤ ጠየቅኳቸው፡፡ የሠጡኝ ምላሽ ግን ያልጠበቅሁት ዱብ ዕዳ ነበር፡፡ ‘ቃለ መጠይቅ መሥጠት የምንችለው የኢትዮጵያው ፓትርያርክ ለአርመኑ ፓትርያርክ ደብዳቤ ጽፈው የአርመን ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ ለእኛ ‘ቃለ መጠይቅ ሥጡ’ ብለው ከጻፉልን ብቻ ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያናችን ትምህርት ተማሩ ብላ እንጂ እኔን ወክላችሁ በሌላ ቤተ ክርስቲያን ለሚታተም መጽሔት ቃለ መጠይቅ ሥጡ ብላ አልላከችንም’ ብለውኝ አረፉት፡፡ ፊቴ ላይ ኀዘን ሲያነቡ ያስከፉኝ መስሏቸው የቤተ ክርስቲያኒቱን የቅዳሴ መጽሐፍና ዜማው የተቀረጸበትን ዲቪዲ ሥጦታ አድርገው ሠጡኝ፡፡ እኔ ያዘንሁት በእነርሱ አልነበረም፡፡ አንድ ዲያቆን እንኳን ቃለ መጠይቅ ለመስጠት ሊያስፈቅዳት ቀርቶ ሙሉ ሲኖዶሱን ከፍ ዝቅ አድርጎ ቢሳደብ እንደ ጀግና የሚቆጠርባት ቤተ ክርስቲያኔ ትዝ ብላኝ እርር ትክን አልኩኝ፡፡ ወደ ግብፅ የሔድሁበት ያ ወቅት ደግሞ አንድ ፍጻሜው የሚያሳዝን ሰባኪ ቅዱስ ፓትርያርኩን ‘ቁማርተኛ’ ብሎ ከፍ ዝቅ አድርጎ የሚሰድብ መጽሐፍ ጽፎ ዝና ባተረፈበትና ሀገሩ ሁሉ የእሱ ተከታይ ከሆነ አምስት ስድስት ዓመት ቢሆነው ነበር፡፡ በኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት የክህነት መዓርግ እጅግ የሚከበር ከሐዋርያት ጀምሮ በቅብብል የወረደ ትልቅ ዐምድ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ጳጳሳትን ከግብፅ ድረስ ለማስመጣት ሀብቱን ለግብፅ ከሊፋዎች በገፍ ሲገብር የኖረ ሕዝብ ነው፡፡ ከግብፅ የሚመጡትን ጳጳሳት እንደ እግዚአብሔር መልአክ ግምጃ አንጥፎ እየተቀበለ የረገጡትን መሬት የሚስም ጳጳስ ባልተሾመባቸው በርካታ ዓመታት ደግሞ ቤተ ክርስቲያኑን በዕንባ እየዞረ ምሕላ እያደረሰ አባት ፍለጋ ያለቀሰ ሕዝብ ነው፡፡ የአባ ሰላማ ግሪካዊነት ፣ የአቡነ አረጋዊ ሮማዊነት ፣ የነአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ግብፃዊነት ሳይታየው መንፈሳዊ አባት ብቻ ተርቦ የሚጠብቅ ንጹህ ሕዝብ ነበረ፡፡ ይቀጥላል . . .
384
9
"ከአንድ አፍ በረከትና መርገም ይወጣሉ። ወንድሞቼ ሆይ፥ ይህ እንዲህ ሊሆን አይገባም። ምንጭስ ከአንድ አፍ የሚጣፍጥንና የሚመርን ውኃ ያመነጫልን? ወንድሞቼ ሆይ፥ በለስ ወይራን ወይስ ወይን በለስን ልታፈራ ትችላለችን? ከጨው ውኃም ጣፋጭ ውኃ አይወጣም።" ያዕ ፫÷፲-፲፪
382
10
“እግዚአብሔርን መፍራት ዘመንን ታረዝማለች።” ምሳ ፲÷፳፯
638
11
‎📖 መማር እንሻለን - የትምህርት ቁሳቁስ ማሰባሰቢያ ዘመቻ ‎ማኅበራዊ ቀውሶች የብዙ ሕፃናትን የትምህርት ጉዞ አግድመውታል። የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት እነዚህን ሕፃናት
‎📖 መማር እንሻለን - የትምህርት ቁሳቁስ ማሰባሰቢያ ዘመቻ ‎ማኅበራዊ ቀውሶች የብዙ ሕፃናትን የትምህርት ጉዞ አግድመውታል። የማኅበረ ቅዱሳን ሙያ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ አገልግሎት እነዚህን ሕፃናት ለመደገፍ ሰፊ የንቅናቄ ዘመቻ ጀምሯል። ‎🔹 ዓላማ፦ ሕፃናቱ በትምህርት መሣሪያ እጥረት ሳይስተጓጎሉ ትምህርታቸውን እንዲቀጥሉ ማድረግ። ‎🔹 መዋጮ፦ የአንድ ተማሪ ዓመታዊ ቁሳቁስ ወጪ 3,300 ብር ቢሆንም፣ ማንኛውም ሰው የቻለውን ያህል (አንድ ደብተርም ቢሆን) ማበርከት ይችላል። ‎🏦 የባንክ መረጃዎች፦ ‎CBE: 1000309803648 ‎Ahadu: 0025393810901 ‎Abyssinia: 23375458 ‎Wegagen: 083731610101 ‎📍 የመቀበያ ቦታ፦ አምስት ኪሎ ማኅበረ ቅዱሳን ሕንፃ 1ኛ ወለል
665
12
ቅዱስ ገብርኤል ሰው እርዳ ሲሉት ደስ ይለዋል። ደስ እያለው ነው የሚመጣው ፤ እውነቴን ነው የምነግራችሁ! ደስ እያለው ይቀርባል። ደስታ ታድሎታል። ቅዱስ ገብርኤል ትልቅ ደስታ ተሸክሞ ይመጣል። ያ ትልቅ ደስታ አማኑኤል ይባላል። «እነሆ ትወልጃለሽ፤ ስሙንም አማኑኤል ትይዋለሽ» አማኑኤል የሚለውን ስም ተሸክሞ የመጣ ቅዱስ ገብርኤል ነው። ኃዘን በነበረበት ዓለም ለመጀመሪያ ጊዜ የመጀመሪያውን ደስታ ይዞ የመጣው ቅዱስ ገብርኤል ነው! ለሚያምኑትም አምላክ ደስታ ይሰጣቸዋል ፤ ቅዱስ ገብርኤል የደስታ መልአክ ነው ፤ መልአከ ሰላም ነው ቅዱስ ገብርኤል! «አትፍሩ» የሚል፣ ፍርኃትን የሚያርቅ መልአክ ነው። ዘካርያስን «አትፍራ» አለው። ፍርኃት ያርቃል ፤ የተቋጠረ ይፈታል። ርእሰ ሊቃውንት የኔታ ገብረ ኪዳን ግርማ ከስብከታቸው የተወሰደ
661
13
“በምድር ላይ የሰው ሕይወት ብርቱ ሰልፍ አይደለምን?" (ኢዮብ 7፥1) ነገር ግን ከእርሱ ጋር ከኾንን አቀበት ቁልቁለቱም ቢኾን አይበረታብንም። ማሸነፊያችን መድኃኔዓለም! መልካም ሳምንት
735
14
እንኳን ለእመቤታችን በዓለ ትንሣኤና ዕርገት በሰላም አደረሳችሁ! ከጥቂት ረፍት በኋላ ተገናኝተናል ፤ እግዚአብሔር መልካሙን እንደሚያደርግ እናምናለን። መልካም በዓል!
751
15
እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! መልካም በዓል https://youtu.be/1sUF5BiP6Ag?si=IlLJhsAmHFGp9zPe
669
16
በቤተ መቅደሱ መሠዊያ ፊት ቆመው ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለምእመናን የሚያቀብሉት ቀሲስ ሥልጣኑ ፣ ከቤተ መቅደስ መውጫ በስተጀርባ እጅግ ከባድ የኾነ የሕይወት መስቀል ተሸክመዋል። እርሳቸው ለቤተ ክርስቲያን አባቶችና ምእመናን መንፈሳዊ አገልግሎት የሚሰጡ ፣ ለአምላካቸው ታማኝ አገልጋይ ቢኾኑም ፤ በውስጣዊ ሕይወታቸው ግን በከባድ ሕመም እና በድህነት እሳት ውስጥ ያልፋሉ። የመጀመሪያ ልጃቸው የኾነችው ሕፃን ዓለም ሥልጣኑ በከባድ የአእምሮና የአካል ሕመም ምክንያት መናገር ፣ መራመድ ፣ ሰዎችን መስማትም ሆነ ምግብ በራሷ መመገብ አትችልም። ዳይፐር የመግዛት አቅም ስለሌላቸው ሕፃኗ ለብርድና ለእንግልት ትዳረጋለች። የሕፃኗን ሁኔታ የሚያዩ አከራዮች «ልጃችሁን ይዛችሁ ውጡልን» እያሉ በየሳምንቱ ስለሚያባርሯቸው ፣ አባታችን ልጃቸውን አዝለው በየደጁ ለማልቀስና ቤት ለመቀየር ተገደዋል። ቀሲስ ሥልጣኑ በቤተ መቅደሱ ከመቀደስ አልፈው ፣ የቀን ደሞዛቸው ለልጃቸው ዳይፐርና ምግብ እንኳ ስለማይበቃ በየመንገዱ ሎተሪ ፣ ሽቶና ካልሲ እያዞሩ ይሸጣሉ። ከዚህ ሁሉ ልፋትና እንግልት የተነሣ እርሳቸውም ደም እየተፉ አገልግሎታቸውን ይቀጥላሉ። ቀሲስ ሥልጣኑ ከዚህ ሁሉ ሥቃይ ጋር ልጃቸውን እንደ ዓይናቸው ብሌን ይንከባከቧታል። በቅኔያቸውም እንደ ኢዮብ ይሄን ከባድ ፈተና ለመልካም እንዳመጣባቸው ገልጸው ፣ የልጃቸውን ሕመም በራሳቸው ላይ እንደደረሰ አድርገው ይገልጡታል። ዛሬ እኚህ አገልጋይ አባት የሚያስፈልጋቸው ነገር ቢኖር የሕፃኗን ሕክምና ማድረግ ፣ የተረጋጋ የመጠለያ ቦታ ማግኘት እና የዕለት ምግባቸውን ማሟላት ነው። «እነሆ በኢየሩሳሌም እና በኢያሪኮ መካከል ወድቀው ደም የሚተፉ የተጎዱ አባታችንን የምናይበት ጊዜ አሁን ነው!» እግዚአብሔር አምላክ ለሁላችንም ከሰጠን በረከትና ሀብት ላይ ጥቂት አካፍለን ፣ የእኚህን የእግዚአብሔር አገልጋይና የሕፃኗን ዕንባ እንድንጠርግ ፤ «እንደ ደጉ ሳምራዊ በመንገዳቸው አልፈን» የእርዳታ እጃችንን እንድንዘረጋላቸው የዛሬ ጥሪዬ ነው። እገዛ ለማድረግ👇 1000252386215 ቀሲስ ሥልጣኑ ዋስይኹን 0929244662 የዛሬ የፊልም ዳሰሳችንን በዚህ ተክተነዋል። በቀጣይ ሳምንት በሰላም ያድርሰንና Man of God የሚለውን ፊልም እንዳስሳለን። በማኅበረ ቅዱሳን ቲቪ የተለቀቀውን ከላይ የጻፍኩትን ሀሳብ በሙሉ ቪዲዮ ለመመልከት ከታች የተያያዘውን Link ተጫኑ። https://youtu.be/ZGFOdAeTeqI?si=prb0LrAzxW0tzv0L
531
17
"ገንዘብ እንፈልጋለን ፤ የገንዘብን ባለቤት ግን ትተነዋል። ጤና እንፈልጋለን ፤ የጤናን ባለቤት እግዚአብሔርን ትተነዋል። ሰላም እንፈልጋለን ፤ የሰላምን ባለቤት ርቀነዋል። ከእሱ ርቀን ምንስ ሊገኝ ይችላል? እግዚአብሔር ባለበት ግን ሁሉ አለ። እግዚአብሔር ያለበት ሁሉ ገንዘብም ነው ፣ ሰላምም ነው። እግዚአብሔር የሌለበት ደግሞ፦ 🔸ምቾት እንኳን ቢሆን . . . ስቃይ ነው! 🔹ነፃነት ቢሆን እንኳን . . . እስራት ነው! 🔸ክብር ቢሆን እንኳን . . . ውርደት ነው! 🔹ባለጸግነት እንኳን ቢሆን . . . ድህነት ነው!" ርእሰ ሊቃውንት የኔታ አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
670
18
🎬 “አሁን ሰዓቱ ስንት ነው?” የቅዱሱ አባት የአባ ዮስጦስ (ዝምተኛው መነኩሴ) አስደናቂ ታሪክ “እግዚአብሔር አባ ዮስጦስን በ20ኛው ክፍለ ዘመን ያመጣቸው፣ በ4ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበሩ ቅዱሳንን የቅድስና ሕይወት በዓይናችን እንድናይ ለማድረግ ነው” ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ ከእግዚአብሔር ውጪ ለዚህ ምድር ነገር ሁሉ ጀርባቸውን የሰጡት ፣ በጸሎትና በታላቅ ተጋድሎ የኖሩትና “ዝምተኛው መነኩሴ” እየተባሉ የሚጠሩት የጻድቁ አባ ዮስጦስ ታሪክ በሁለት ክፍሎች ተከፍሎ በመንፈሳዊ ፊልም መልክ ቀርቧል። 📌 ክፍል አንድ፦ ከተደነቀው ዝምታ በስተጀርባ . . . ታሪኩ የሚጀምረው በታላቁ የግብፅ ገዳም (በአባ እንጦንስ ገዳም) ውስጥ ነው ፤ አባ ዮስጦስ በገዳሙ ውስጥ ለብዙ ዘመናት ፍጹም ዝምታን መርጠው በታላቅ መንፈሳዊ ተጋድሎ ኖረዋል። ከተደነቀውና ድንበር ከሌለው ዝምታቸው ባሻገር ግን ፣ በገዳሙ መነኮሳትንና ሰዎችን በድንገት ሲያገኙ የሚጠይቋት አንዲት እንግዳ ጥያቄ ነበረቻቸው፦ 👉 “አሁን ሰዓቱ ስንት ነው?” ይህችን ጥያቄ ለምን ይጠይቃሉ? ከዚህስ ጥያቄ ጀርባ ምን ዓይነት ጥልቅ መንፈሳዊ ምስጢር ተሸሽጓል? ይህ በክፍል አንድ ላይ በስፋት ይተረካል . . . 👉 [ ክፍል 1ን እዚህ ይጫኑና ይመልከቱ ] 📌 ክፍል ሁለት፦ የመጨረሻው ሰዓትና የተገለጠው ተአምር! በሁለተኛው ክፍል የጻድቁ አባት የአባ ዮስጦስ የመጨረሻ የዕረፍት ጊዜ (ሞት) ሲቃረብ የሚታዩትን እጅግ ልብ የሚነኩ መንፈሳዊ ክስተቶች ይመለከታሉ። ሁልጊዜ “አሁን ሰዓቱ ስንት ነው?” እያሉ የሚጠይቁበትን የሰዓቱን እውነተኛ ምስጢር ፤ ማለትም ሰው ወደ ዘላለማዊ ቤት ከመሄዱ በፊት ቀሪው ሰዓት ምን ያህል አጭር እንደሆነ ለእኛ ማስተማሪያ መሆኑን እንረዳለን። ጻድቁ አባ ዮስጦስ ሲያርፉ (ሲሞቱ) መላው ገዳምና ሰማይ በምን ዓይነት ሰማያዊ ምስጋናና ደስታ እንደተሞላ ፣ ያሳዩትስ የመጨረሻው አስገራሚ ተአምር ምን እንደነበረ ክፍል ሁለት ላይ ይመለከታሉ። ይህ ፊልም ልብን የሚነካ ፣ ከምድራዊ ኑዛዜ በላይ ሰውን ወደ ንስሐና ወደ መንፈሳዊ ሕይወት የሚጠራ እውነተኛ ታሪክ ነው። 👉 [ ክፍል 2ን እዚህ ይጫኑና ይመልከቱ ] ለዓለማዊ ሩጫችን ማቆሚያ መስታወት ነው! አባ ዮስጦስ “አሁን ሰዓቱ ስንት ነው?” እያሉ የጠየቁት እኛንም የንስሓ ጊዜያች ሳያልፍብን ነቅተን እንድንጠብቅ ያደርገናል። ለዘመናችን ቅርብ በኾነው በ20ኛው ክፍለ ዘመን በግብፅ በረሃ የነበረውን እውነተኛ ተጋድሎ በዓይናችን እንድንመለከት የሚያደርገንን ይህንን መንፈሳዊ ፊልም ያልተመለከታችሁ እንድትመለከቱት ግብዣችን ነው። በሳምንት አንድ መንፈሳዊ ፊልም እየተመለከትንንና እየተማማርንበት እንቀጥላለን። የቅዱሳን አምላክ እግዚአብሔር በረድኤት አይለየን። @Tsegasilase ሐምሌ ፯/፳፻፲፰ የምሕረት ዓመት
693
19
ዛሬ ማክሰኞ አይደል? ቀጠሮ አለን ፊልሞቹን ተመልክተናል በሚል ተስፋ እንቀጥላለን
524
20
እንኳን ለብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ በዓለ ዕረፍት በሰላም አደረሳችኹ! የሐዋርያቱን በረከት ያሳድርብን! መልካም በዓል!!!
637