en
Feedback
እምየ ተዋሕዶ ሚዲያ - Emye Tewahedo Media

እምየ ተዋሕዶ ሚዲያ - Emye Tewahedo Media

Open in Telegram

እሔ የቴሌግራም መንፈሳዊ ቻናላችን ስለ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሀይማኖታችን ምንማማርበት መንፈሳዊ መድረክ ነው። ለሌሎች ያጋሩ፣ አዳዲሶችም ተቀላቀሉ(join) አድርጉ።

Show more
2 247
Subscribers
-124 hours
-47 days
+530 days
Posts Archive
♦የኢትዮጵያ ውስብስብ ፖለቲካ አንዱ ማሳያ . . . በኪነ-ጥበብ ሙያቸውና በፅኑ የፖለቲካ ትግላቸው ከወጣትነታቸው ጀምሮ የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ንቁ አባል የነበሩት አንጋፋዋ አርቲስት እልፍነሽ ቀኖ፣ በሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ ከበሬታን አትርፈው በዛሬው ዕለት በአምቦ ከተማ ሥርዓተ ቀብራቸው ተፈፅሟል። ፈጣሪ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለአድናቂዎቻቸውና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን ይስጥ፤ ለሟችም ነፍስ ምህረትን ይስጥልን ። ሆኖም ግን፣ የእኚህ አንጋፋ አርቲስትና ታጋይ ሥርዓተ ቀብር በተፈጸመበት መድረክ ላይ የታየው የሰንደቅ ዓላማዎች ክምችት፣ ከሽኝት ውበትና ከክብር ይልቅ ጥልቅ የሆነ ፖለቲካዊና ታሪካዊ ቅራኔን አጉልቶ አውጥቷል። በአስክሬናቸው ሳጥን ላይ ሦስት እርስ በእርስ የማይታረቁ የፖለቲካ መስመሮችን የሚወክሉ ሰንደቅ ዓላማዎች በአንድነት ተከናንበው ታይተዋል፦ የኦነግ ሰንደቅ ዓላማ፦ አርቲስቷ እድሜያቸውን በሙሉ ሲታገሉለት የነበረውን፣ የኦሮሞን ህዝብ የራስን እድል በራስ የመወሰን መብት እስከ መገንጠል የሚያራምደውን የታሪካዊ ትግል መስመር የሚወክል ነው ፤ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ ፦ ምንም እንኳን አርማው ላይ ባለው መደብ የተለያየ ፍላጎት ቢኖርም ኦነግ ሲታገለውና ሲቃወመው የነበረውን ሀገረ-መንግሥታዊ ህልውናና መዋቅር የሚያንጸባርቅ ነው ፤ የኦሮሚያ ክልላዊ መንግሥት ሰንደቅ ዓላማ ፦ በታሪክ ሂደት ውስጥ ከኦነግ ጋር በፅንሰ-ሀሳብም ሆነ በትግል መስመር ተቃራኒ ሆኖ የቆየውን የኦህዴድ ድርጅትና የመንግሥት ውክለናን የሚያሳይ ነው ። ይህ ክስተት ተራ የሥነ-ሥርዓት ስህተት ሳይሆን፣ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፈተና ምን ያህል ጥልቅና ውዥንብር የሞላበት ደረጃ ላይ እንደደረሰ በግልጽ ማሳያ ነው። የጣሊያንን ወራሪ ጦር በጀግንነት በመዋጋት የሀገር ፍቅር ምሳሌ የሆኑት እንደ ኮሎኔል አብዲሳ አጋ፣ “የበጋው መብረቅ” በሚል ቅፅል ስማቸው የሚታወቁት ሌተና ጀነራል ጃገማ ኬሎ፣ እንዲሁም ስፍር ቁጥር የሌላቸው ከኦሮሞ አብራክ የተገኙ የኢትዮጵያ ጀግኖች የታገሉላትና ደማቸውን ያፈሰሱላት ሀገር ዛሬ ያለችበትን የፖለቲካ የፅንሰ-ሀሳብ ውዥንብርና የማንነት ውዝግብ ቢመለከቱ ምን ይሉ ይሆን ?! ይህ በሽኝት መድረክ ላይ የታየው ሁኔታ፣ የሀገራችን ኢትየጵያ የወደፊት የጋራ ጉዞ መመርመር እንዳለባት የሚያስጠነቅቅ ትልቅ መስታወት ነው ! ይድነቃቸው ከበደ

መንግስታዊ ኃይማኖት (State Religion):- ፕሮቴስታንት (ቆስጤ) መንግስታዊ ባህል (State Culture):- የኦሮሞ ባህል ርዮተ አለም:- የስበት ህግ (law of attraction) እንዲህ ያለ ውጥንቅጥ ነው የገጠመን፣ ይህን ስርዓር "የኦሮቴስታንት ስርዓት" ብዬ የምጠራው በምክንያት ነው ካሊጉላ አህመድና ሽመልስ አብዲሳ በአስር ሺህዎች የሚቆጠሩ ስራ-አጥ የኦሮሞ ወጣቶችን አበል ከፍለው፣ ልብስ አልብሰው፣ የአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ አፍስሰው ሲያበቁ በድሮን ቀረጸው እያሳዩን ነው፣ በአንድ ሳምንት ውስጥ ይህ ለሁለተኛ ጊዜ መደረጉ ነው፣ በቀደም የኦሮሞ አሽንዳ ተከበሮ ነበር፣ ጎቤ፣ ሽኖዬ ቅብርጥሴ እየተባለ ቀጥሏል፣ ራሱን ወደ ፌስቲቫልነት ቀይሮ ለቀናት መከበር የጀመረው የዋቄ ፈታ የፋሲካ በዓል (ኢሬቻም) እየደረሰ ነው፣ በአል የሚከበረው የበዓሉ ባለቤት ህዝቡ ወዳለበት ተሂዶ እንጂ ከህዝቡ ወጥቶ አይደለም፣ ጎቤና ሸጎዬ አዲስ አበበ ጎዳናዋች ላይ ምን ይሰራል? ኢሬቻ በታሪኩ ለመጀመሪያ ጊዜ ደረቅ መሬት ላይ የተከበረው አዲስ አበባ ውስጥ በዚህ የበሰበሰ ስርዓት ወቅት ነው፣ ***ሊያስተላልፉት የፈለጉት political statement ጠፍቶኝ ግን አይደለም፣ Don't get me wrong! I am entirely open to and respectful of the celebration of all cultural holidays. ግን በልኩ መሆን አለበት፣ ከፍተኛ በጀት ተመድቦለት፣ መንገድ ተዘግቶ፣ በብሔራዊ ባህል ደረጃ ሊከበር የሚገባ ባህል (በዓል) መኖር የለበትም፣ አይገባም! ለኦሮሞ ወጣት አጭር ምክር አለኝ፣ ንቃ! እሽኮለሌ አታብዛ፣ የካሊጉላ አህመድ 'bread & circuses' ታክቲክ ሰለባ አትሁን፣ ይህ የሮማው ካሊጉላ የዛሬ 2 ሺህ አመት የተጠቀመው ማደናገሪያ ነው፣ በላቲን "panem et circenses" ይሉታል፣ በአበል (ዳቦ) ደንዝዘህ እሽኮለሌ አትበል፣ ኢሬቻ፣ ጎቤ፣ ሽኖዬ ወዘተ ሲልህ "ሰርከሱ የተባረከ ይሁን፣ ባህሌን በቀደመው መንገድ ራሴ አከብረዋለሁ፣ አንተ መንግስታዊ ኃላፊነትህን ተወጣ፣ ካንተ የምፈልገው ሰላም፣ ምቹ የስራ ቦታ፣ አሰሪ ህግ፣ መሰረተ ልማት፣ ደረጃውን የጠበቀ ትምህርትና የጤና አገልግሎት ወዘተ ነው" በለው፣ ሰርከስ እየሰሩ ወደ ቤት መግባት፣ ከዛም ሆድን ማከክ ከተመቸህ ምርጫው ያንተ ነው፣ *** በነገራችን ላይ ኤሊያስ መልካ የሞተው በኢሬቻ ምክንያት መንገድ በመዘጋቱና በሰዓቱ ሀኪም ጋር ባለመድረሱ እንደሆነ ጓደኞቹ ሲናገሩ ሰምቻለሁ፣ ካሳ አንበሳው

በመላው ዓለም ለምትገኙ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አማኞች በሙሉ እንኳን ለታላቁ መልአክ ለቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። ጳጉሜን ሦስት ቀን የገናናው መልአክ የቅዱስ ሩፋኤል መታሰቢያ በዓል ነው። የፍርድ ቀንም መታሰቢያ ቀን ነው። ቅዱስ ሩፋኤል ሰይጣን ቤተክርስቲያንን ዓሣ አንበሪውን እንዲንቀሳቀስ በማድረግ ቤተክርስቲያንን ለማስጠም ሲሞክር ቅዱስ ሩፋኤል ቤተክርስቲያንን ከመስጠም ጥፋት የታደገበት ቀን ነው እንኳን አደረሳችሁ። ​በቤተክርስቲያናችን ሥርዓትና ደንብ መሠረት ጳጉሜ ሦስት የታላላቅ አምላካዊና መንፈሳዊ ምስጢራት ማሰብያ ድንቅ በዓላት ይታሰባሉ። በዚህች ዕለት የሚታሰቡትን አራት ዋና ዋና ታላላቅ ሁነቶች በቅዱስ መጽሐፍ፣ በሊቃውንቱ ድርሳናትና በቅዱስ ያሬድ ምስጋና ተደግፈው እንደሚከተለው በቀረቡ ነጥቦች እንመለከታቸዋለን። ​ ፩ኛ/ ቅዱስ ሩፋኤልእና የቤተክርስቲያንን መታደግ ​ታሪኩ በእስክንድርያ ደሴት ላይ በቅዱስ ሩፋኤል ስም የታነጸችውን ቤተክርስቲያን የሚያስታውስ ነው። ዲያብሎስ በዓሣ ነባሪው አካል አድሮ ቤተክርስቲያኗን በባሕር ውስጥ ለማስጠም በሞከረ ጊዜ፣ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል በተሰጠው ኃይል በጦሩ ዓሣ ነባሪውን ወግቶና ገሥጾ ቤተክርስቲያኗን ከጥፋት የታደገበት ቀን ነው። ዛሬም የፖለቲካ ባሕሩን በማናወጥ ኢትዮጵያን እና ቤተክርስቲያንን የሚፈታተነውን ርኩስ መንፈስ ፣ ቅዱስ ሩፋኤል ይገስጽልን አሜን። ​ በጦቢት መጽሐፍ ላይ “ዓሣው ሊበላው በወደደ ጊዜ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ጦቢትን አጽናናው፤ ዓሣውንም ይዞ ያወጣው ዘንድ ረዳው” (መጽሐፈ ጦቢት ፮፥፪) ተብሎ እንደተጻፈ፣ መልአኩ የሰውን ልጅ ከአጋንንትና ከጥፋት የመታደግ አምላካዊ ተልእኮ አለው። ​ ድርሳነ ሩፋኤል እንደሚያስረዳው የባሕሩ ማዕበልና የዓሣ ነባሪው መንቀሳቀስ የዓለምን ፈተናና የዲያብሎስን ተንኮል ሲያመለክት፣ ቅዱስ ሩፋኤል ደግሞ የምሕረትና የመዳን መልእክተኛ ሆኖ ቤተክርስቲያንን ያጸናል። ​ ቤተክርስቲያን በዓለም ማዕበል አትናወጥም። ዲያብሎስ እሷን ለማስጠም የቱንም ያህል ቢጥር፣ በቅዱሳን መላእክት ተጠበቃ በክርስቶስ ደም የተመሠረተች ናትና አትጠፋም። ​ ፪ኛ/ ነገረ ምጽአትና የመጨረሻው ፍርድ ​በዚች ዕለት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በኃይልና በታላቅ ምስጋና ለፍርድ የሚመጣበት ነገረ ምጽአቱ ይታሰባል። “የሰው ልጅ በክብሩ በሚመጣበት ጊዜ ከእርሱም ጋር ቅዱሳን መላእክቱ ሁሉ፣ በዚያን ጊዜ በክብሩ ዙፋን ይቀመጣል... ንጉሡም በቀኙ ያሉትን ይላቸዋል፦ እናንተ የአባቴ ቡሩካን፣ ኑ፤ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ... በግራው ያሉትን ደግሞ ይላቸዋል፦ እናንተ የተረገማችሁ፣ ለዲያብሎስና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ” (ማቴዎስ ፳፭፥፴፩-፵፩)። ​ ማኅሌታዩ ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓው ላይ፦ "ይመጽእ እግዚእ ውስተ ዓለም ወይፌድዮሙ ለጻድቃን በጽድቆሙ ወለኃጣንኒ በኃጢአቶሙ" (ጌታ ወደ ዓለም ይመጣል፤ ለጻድቃን እንደ ጽድቃቸው፣ ለኃጥአንም እንደ ኃጢአታቸው ዋጋቸውን ይከፍላቸዋል) በማለት የምጽአቱን አስፈሪነትና የጻድቃንን ክብር ዘምሯል። ​ ፫ኛ/ ርኅወተ ሰማይ (የሰማይ መከፈት) ​በዚህ ቀን ሰማያት እንደሚከፈቱ፣ የሰው ልጅ ጸሎትና መሥዋዕት በመላእክት አማካኝነት ወደ እግዚአብሔር መንበር የሚያርግበት ልዩ የጸሎትና የምሕረት ጊዜ እንደሆነ ይነገራል። ​“የመልአኩም እጅ የዕጣኑ ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር በእግዚአብሔር ፊት ወጣ” (የዮሐንስ ራእይ ፰፥፬) ተብሎ እንደተጻፈ፣ መላእክት የሰውን ልጅ ጸሎት ወደ ፈጣሪ ያደርሳሉ። ​መንፈሳዊ ምስጢር፦ ርኅወተ ሰማይ ማለት የሰው ልጅ ምድር ላይ ሆኖ የሚያቀርበው ንስሐና አምልኮ በሰማያዊው አምላክ ዘንድ ተተቀባይነትን የሚያገኝበት፣ በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ያለው ግንኙነት የሚታደስበት የጸጋ ወቅት ነው። ​ ፬ኛ/ ካህኑ መልከ ጼዴቅ /የክርስቶስ ምሳሌ ​የሳሌም ንጉሥና የእግዚአብሔር ካህን የሆነው መልከ ጼዴቅ በዚች ዕለት ይታሰባል። ​የመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት፦ “የሳሌም ንጉሥ መልከ ጼዴቅም እንጀራንና ወይንን አወጣ፤ እርሱም የእልልታ አምላክ ካህን ነበረ” (ዘፍጥረት ፲፬፥፲፰)። ቅዱስ ጳውሎስም በዕብራውያን መልእክቱ “እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ለዘላለም ካህን ነህ” (ዕብራውያን ፭፥፮) በማለት መልከ ጼዴቅ የመድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ የካህንነቱ ምሳሌ መሆኑን አብራርቷል። ​ መልከ ጼዴቅ የወይንና የእንጀራ መሥዋዕት እንደ አቀረበ፣ ክርስቶስም ሥጋውንና ደሙን እንጀራና ወይን አድርጎ ለዓለም ድኅነት ሰጥቷል። ​የቅዱስ ሩፋኤል ጥበቃና ረድኤት፣ የካህኑ መልከ ጼዴቅ በረከት አይለየን አሜን። ዘላለም ምስክር

ጳጉሜን 3 – ዐፄ ዘርአ ያዕቆብ (1426-1460 ዓ.ም) ጳጉሜን 3 የገናናው ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ (1400-1460 ዓ.ም) ዕረፍት የሚታሰብበት ቀን ነው፡፡ የንጉሡን የሥነ ጽሑፍና የታሪክ ሥራዎች ል
ጳጉሜን 3 – ዐፄ ዘርአ ያዕቆብ (1426-1460 ዓ.ም) ጳጉሜን 3 የገናናው ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ (1400-1460 ዓ.ም) ዕረፍት የሚታሰብበት ቀን ነው፡፡ የንጉሡን የሥነ ጽሑፍና የታሪክ ሥራዎች ልናስተዋውቅና ልንዘክረው ይገባል፡፡ እርሳቸው ለታሪክና ለሃይማኖት ጥናት ከፍተኛ ጠቀሜታ ያላቸውን ከዘጠኝ በላይ መጻሕፍት አበርክተውልናል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብን “ቅዱስ” ባትለውም፣ በመጽሐፈ ስንክሳር ግን ያበረከተውን አስተዋጽዖ እውቅና ለመስጠት በክብር ታስበዋለች፡፡ በ2018 ዓ.ም. ሆነን ስንዘክረው፣ ለቤተ ክርስቲያን የሚችለውን ፈጽሞ ካረፈ 558 ዓመታት አልፈዋል፡፡ በተለይ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ የሆኑ አንዳንድ ‘ታሪክ’ ጸሐፊዎች እና የትግራይ ብሔርተኞች ለዐፄ ዘርአ ያዕቆብ ያለስሙ ስም በመስጠት በሐሰት ስሙን አጠልሽተውታል፡፡ ስለዚህ በታሪክ ላይ የሚፈጸመውን ማዛነፍ ለማስተካከል መሥራት ይገባል፡፡ ንጉሡን ያለማስረጃ አናጋንን፤ እንዲሁም አናንኳስ። ይህ ኢትዮጵያዊ ንጉሥ ለሀገሩና ለቤተ ክርስቲያኑ ታላቅ ተጋድሎ ያደረገ መሪ ነው፤ አስተዋጽዖውም እጅግ ላቅ ያለ ነው፡፡ ወደፊት በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጳጉሜን 3ን መሠረት በማድረግ፣ ስለ ዐፄ ዘርአ ያዕቆብ ጥናታዊ ጽሑፍ የሚቀርብበትና ውይይት የሚካሄድበት መርሐ ግብር ቢዘጋጅ መልካም ነው፡፡

በወለጋ መንግስታዊ ሽብር የአማራ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ነው ❗️ እንደ አለም አቀፍ ሚድያ first post ዘገባ ገዳ ኮማንዶ የተባለ በኦሮምያ የብልጽግና አገዛዝ ታጣቂዎች ንጹሀንን በግፍ ሲ***ገ*
በወለጋ መንግስታዊ ሽብር የአማራ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ነው ❗️ እንደ አለም አቀፍ ሚድያ first post ዘገባ ገዳ ኮማንዶ የተባለ በኦሮምያ የብልጽግና አገዛዝ ታጣቂዎች ንጹሀንን በግፍ ሲ***ገ*ሉ እና መኖርያ ቤት ሲያቃጥሉ መረጃዎች መውጣታቸውን ዘግበዋል:: እንደ ሚድያው ዘገባ ከ 50 በላይ ንጹሀን ማንነት በለየ ጥቃት መ*ደላቸውን ነገር ግን በሶሻል ሚድያ መረጃዎች ከ 250 በላይ የሚገመቱ ንጹሀን ነፍሳቸው ስለ መነጠቁ እየተገለጸ መሆኑን ዘግበዋል:: በወለጋ በጊዳ አያና እና በአከባቢው ማንነት ተኮር ጥቃት (የአማራ ትግራይ እና ሌሎች በሰፈራ ፕሮግራም በኦሮምያ የሚገኙ) አረጋውያን እና ካህናትን ጨምሮ ግያ እና አብያተ ክርስቲያናት ቃጠሎ መዘገቡ የሚታወስ ነው:: ይህ ግፍና በደል በገለልተኛ አካል ተጣርቶ ግፈኞች ለፍርድ ማግኘት ይገባቸዋል ❗️

በጊዜ ከእንቅልፏ የነቃች ነፍስ 🙏 እህታችን ለዘመናት በ«መልካም ወጣት ጉባኤ» በሚል ስም በሚንቀሳቀሰው ድርጅት ውስጥ ቆይታለች። አሁን ግን እውነተኛዋን ሃይማኖት ወደ ሆነችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ
+3
በጊዜ ከእንቅልፏ የነቃች ነፍስ 🙏 እህታችን ለዘመናት በ«መልካም ወጣት ጉባኤ» በሚል ስም በሚንቀሳቀሰው ድርጅት ውስጥ ቆይታለች። አሁን ግን እውነተኛዋን ሃይማኖት ወደ ሆነችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መጥታ፣ የቅድስት ሥላሴን ልጅነት አግኝታለች። 🙏⛪ +***+ እግዚአብሔር በእውነተኛው መንገድ ያጽናሽ፤ እኛንም ያጽናን። እንኳን ደህና መጣሽ! 🤍 እግዚአብሔር ይመስገን! 🙏 Ephram

♦መንግስታዊ መድሎ እና አሻጥር . . . በመንግሥት የመገናኛ ብዙሃን እንደተገለጸው ”ሽኖዬ እና ጎቤ” የኦሮሞ ወጣቶች ባህላዊ ጭፈራ ፤ በአዲስ አበባ በአደባባይ በአሉን የማስተዋወቅ ዝግጅት ከፋተኛ
+3
♦መንግስታዊ መድሎ እና አሻጥር . . . በመንግሥት የመገናኛ ብዙሃን እንደተገለጸው ”ሽኖዬ እና ጎቤ” የኦሮሞ ወጣቶች ባህላዊ ጭፈራ ፤ በአዲስ አበባ በአደባባይ በአሉን የማስተዋወቅ ዝግጅት ከፋተኛ የመንግስት አመራር በተገኙበት በይፋ እንደተጀመረ ተገልጿል ። በኢትዮጵያ ውስጥ የተለያዩ ባህሎች ፣ ሐይማኖቶች እና ልማዶች እንዲሁም መሰል ባህሎች አሉ ። ሁሉም እንደየ-ፈርጁ በተከታዮቻቸው እየተከበረ ይገኛል ። ይሁን እንጂ ፤ ከሁሉም ባህሎች እና ሐይማኖቶች መሰል ክንውኖች በተለይ መልኩ ፤ የኦሮሚያ ባህሎችና ልማዶች ለማክበር እና ለማስተዋወቅ ፣ ከቤተመንግስቱ ጀምሮ እስከ ታች ቀበሌ ድረስ መንግስታዊ ማዋቀር የዕዝ ሰንሰለት ተዘርግቶለት ፣ እንዲሁም ከፍተኛ የመንግስት በጀት ተመድቦ እየተከበረ ይገኛል ፤ ይህ ለምንድነው ?! አዲስ አበባ "የብሔር ብሔረሰቦች መዲና" የሁሉም ኢትዮጵያዊ መናገሻ ከተማ እንደመሆና መጠን ፤ ሁሉም ብሔረሰቦች በከተማቸው ላይ እኩል የመጠቀም እና መንግስታዊ ድጋፍ የማግኘት እንዲሁም በፈለጉት አልባሳት እና ቀለማት የማክበር መብት አላቸው ሆይ ?! ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ባለፉት ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከባድ ግፍና መከራ እያለፈች ትገኛለች። ታሪካዊቷ፣ የሰላምና የፍቅር አስተማሪዋ ቤተክርስቲያን ምዕመናኗ ማረፊያ፣ ታቦታቷ ማደሪያ የሚያጡበት እና በአደባባይ በዓላቷ ላይ እንኳን ጫና የሚበዛባት ደረጃ ላይ ደርሳለች ። ይድነቃቸው ከበደ

+1
🇪🇹 በአፍሪካ ትልቁ የገበያ ማዕከል እንደሆነ የሚነገርለት መርካቶ፣ በአሁኑ ሰዓት በእሳት እየተቃጠለ ይገኛል። እሳቱ የተነሳው፣ የጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አገዛዝ ከሰሞኑ በመርካቶ ማፍረስ በጀመረው፣ በመስኪዱ ዙሪያ፣ አካባቢ ነው። ቤቶቹ ጣልያን የገነባቸው የድንጋይ ቤቶች በመሆናቸው፣ ለአገዛዙ ለማፍረስ አስቸጋሪ ሆኖበት ሰንብቷል። በዚህ ዓይነት አፈራረስ ሌላውም ስለሚያስቸግረውና ኃይል እና ጉልበት ስለሚወስድበት፣ አገዛዙ በምትኩ እሳት መልቀቁን አማራጭ ያደረገው ይመስላል። አገዛዙም፣ ሲያፈርሰው እንደከረመው ከተማ፣ እሱም በቅርብ ጊዜ መፍረሱ አይቀርም የሚሉ ብዙ ናቸው።

ምን እንድትሰሙ ተጠበቁ። ማር 4፤24 በDMV ለምትኖሩ ኦርቶዶክሳውያን የተዋሕዶ ልጆች የተላለፈ ወቅታዊ መልዕክት።
ምን እንድትሰሙ ተጠበቁ። ማር 4፤24 በDMV ለምትኖሩ ኦርቶዶክሳውያን የተዋሕዶ ልጆች የተላለፈ ወቅታዊ መልዕክት።

የወንድሜ አብርሃም ኃይሉ ጥፋት ለፍቶ ማደሩ ብቻ ነው። አብርሽ በዘመኑ የፖለቲካ ሕመም ያልተለከፈ፣ መንደር ውስጥ የማይወሸቅ፣ የሰው ሕመም የሚያመው፣ ለተቸገሩት ደራሽ፣ ሰብአዊነት የሚሰማው ፍጹም የ
የወንድሜ አብርሃም ኃይሉ ጥፋት ለፍቶ ማደሩ ብቻ ነው። አብርሽ በዘመኑ የፖለቲካ ሕመም ያልተለከፈ፣ መንደር ውስጥ የማይወሸቅ፣ የሰው ሕመም የሚያመው፣ ለተቸገሩት ደራሽ፣ ሰብአዊነት የሚሰማው ፍጹም የዋህ እና አዛኝ ሰው ነው። ሰው ችግር ላይ ከሆነ ጎጥ፣ መንደር፣ ቋንቋ እና ሌላ መለያ ጉዳዩ አይደለም፤ ሰውነት ለሚለው ተፈጥሮ ተገዥ የሆነ ወንድም ነው። ይህ ወንድም አንባቢ ትውልድ እንዲፈጠር የድርሻውን የሚወጣ፣ የማንበብ ፍላጎት እያላቸው አቅም ለሌላቸው በራሱ ወጭ መጻሕፍትን የሚለግስ ሰው ነው። አብርሽ በላቡ ጥሮ ግሮ መጽሐፍ ቸርችሮ የዕለት ጉርሱን የሚያገኝ ኦርቶዶክሳዊ ወጣት ነው። ይህንን ኦርቶዶክሳዊ ወጣት ለምን መጽሐፍ ሸጥክ ብሎ ማሠር ዐይን ያወጣ ግፍ፣ ሥር የሰደደ በደል፣ የሚሠሩ ወጣቶችን የሚያሸማቅቅ ነውር ነው። አንድን ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፍ ማከፋፈል ለምን ወንጀል ሆነ?! ዲ/ን ታደለ ሲሳይ

የታሰሩበትን ቦታ በትክክል አረጋግጠናል። በቀሲስ መንግሥቱ ጎበዜ (ዶ/ር) የተጻፈው "የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሦስት ሺሕ ዘመናት የታሪክ ጉዞ" የተሰኘው ዐዲስ መጽሐፍ በመሸጣቸ
የታሰሩበትን ቦታ በትክክል አረጋግጠናል። በቀሲስ መንግሥቱ ጎበዜ (ዶ/ር) የተጻፈው "የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሦስት ሺሕ ዘመናት የታሪክ ጉዞ" የተሰኘው ዐዲስ መጽሐፍ በመሸጣቸው ምክንያት፣ መጽሐፉ በፖሊስ ተወርሶባቸው ያለአግባብ የታሰሩት የአርጋኖን መጻሕፍት መደብር ሥራ አስኪያጅ የሆኑትን ቅኑን አብርሃም ኃይሉን እና ወንድም ይልማን ዛሬ ከሰዓት በኋላ ጠይቀናቸዋል። የታሰሩት መገናኛ፣ 24 ቀበሌ ገቢዎች አካባቢ በሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ መሆኑን በትክክል አረጋግጠናል። ስለዚህ ለመጠየቅ የምትሄዱ ሰዎች እንዳትደክሙ፤ መገናኛ ደርሳችሁ ወደ ገርጂ ወይም አደይ አበባ በሚወስደው የታክሲ መያዣ በኩል ካለፋችሁ በኋላ፣ በፎቶው ላይ በሚታየው መንገድ ቁልቁል ቀጥታ ጥቂት እንደወረዳችሁ እስር ቤቱ ይገኛል። እየሄድን እነዚህን በግፍ የታሰሩ ወገኖቻችንን እንጠይቃቸው። በአሁኑ ወቅት "ዕውቀትን በዕውቀት መሞገት" የሚለው መርሕ አፈር በልቷል። በመጽሐፉ ውስጥ ባሉ ሐሳቦች ላይ ተገቢውን የጽሑፍ ኂስ በማቅረብ መከራከር ሲገባ፣ መጽሐፉ እንዳይነበብ በፖሊስ ኃይል ማስለቀም፣ ማገድና መጻሕፍት አከፋፋዮችን ማሰር ፈጽሞ የማይገባ ድርጊት ነው። ዲ/ን ዮሴፍ

የዝች የሙስሊም እህታችንን ግጥም አድምጡት

Repost from Eotc Task Force
በኦሮሚያ ያላችሁ ኦርቶዶክሳውያን ቋንቋ ዘር ቀለም ሳትለዩ ራሳችሁን ጠብቁ የከፋ መከራ እየመጣ ነውና
+1
በኦሮሚያ ያላችሁ ኦርቶዶክሳውያን ቋንቋ ዘር ቀለም ሳትለዩ ራሳችሁን ጠብቁ የከፋ መከራ እየመጣ ነውና

የመጀመሪያዎቹ ሙስሊሞች በቁራይሽ ጎሳዎች ከመካ ሲሳደዱ እጁን ዘርግቶ የተቀበላቸው የክርስቲያኗ ኢትዮጵያ ንጉሥ ክርስቲያን ንጉሥ ነበር። ለዚህ ጥርጥር የለውም። ውሃቢያዎች ግን ነጃሺ የሚል ስም ሰጥተ
የመጀመሪያዎቹ ሙስሊሞች በቁራይሽ ጎሳዎች ከመካ ሲሳደዱ እጁን ዘርግቶ የተቀበላቸው የክርስቲያኗ ኢትዮጵያ ንጉሥ ክርስቲያን ንጉሥ ነበር። ለዚህ ጥርጥር የለውም። ውሃቢያዎች ግን ነጃሺ የሚል ስም ሰጥተውት የሰለመ ንጉሥ አስመስለው ትርክት መፍጠር ከጀመሩ ከራርመዋል። ይህ የቀሲስ መንግሥቱ ጎበዜ መጽሐፍ መሠረት አልባ ትርክታቸውን በማሥረጃ አስደግፎ እርቃን ያስቀራል። ፖሊስ ያለ ፍር ቤት ማዘዣ ይህን መጽሐፍ ካሳታሚው አርጋኖን መጽሐፍ ቤትና ከሌሎች መጻሕፍት መደብሮች እየለቀመ መውሰድ ጀምሯል።

የታሰሩት 24 ቀበሌ ገቢዎች አካባቢ በሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ ነው። በቀሲስ መንግሥቱ ጎበዜ (ዶ/ር) የተጻፈው "የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሦስት ሺሕ ዘመናት የታሪክ ጉዞ" የተሰኘው
+1
የታሰሩት 24 ቀበሌ ገቢዎች አካባቢ በሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ ነው። በቀሲስ መንግሥቱ ጎበዜ (ዶ/ር) የተጻፈው "የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሦስት ሺሕ ዘመናት የታሪክ ጉዞ" የተሰኘው ዐዲስ መጽሐፍ በመሸጣቸው ምክንያት፣ መጽሐፉ በፖሊስ ተወርሶባቸው ያለአግባብ የታሰሩት እነ አብርሃም ኃይሉ ያሉበት ቦታ ፒያሳ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ዋና መሥሪያ ቤት በሚገኘው እስር ቤት አይደለም። በአሁኑ ወቅት የታሰሩት 24 ቀበሌ ገቢዎች አካባቢ በሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ ስለሆነ፣ እየሄድን እነዚህን የግፍ እስረኞች እንጠይቃቸው። በአሁኑ ወቅት "ዕውቀትን በዕውቀት መሞገት" የሚለው መርሕ አፈር በልቷል። በመጽሐፉ ውስጥ ባሉ ሐሳቦች ላይ ተገቢውን የጽሑፍ ሒስ በማቅረብ መከራከር ሲገባ፣ መጽሐፉ እንዳይነበብ በፖሊስ ኃይል ማስለቀም፣ ማገድና መጻሕፍት አከፋፋዮችን ማሰር ፈጽሞ የማይገባ ድርጊት ነው።