እምየ ተዋሕዶ ሚዲያ - Emye Tewahedo Media
Open in Telegram
እሔ የቴሌግራም መንፈሳዊ ቻናላችን ስለ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሀይማኖታችን ምንማማርበት መንፈሳዊ መድረክ ነው። ለሌሎች ያጋሩ፣ አዳዲሶችም ተቀላቀሉ(join) አድርጉ።
Show more2 247
Subscribers
-124 hours
-47 days
+530 days
Data loading in progress...
Similar Channels
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+13
in 2 channels
August '26
+76
in 6 channels
Get PRO
July '26
+52
in 5 channels
Get PRO
June '26
+149
in 5 channels
Get PRO
May '26
+38
in 7 channels
Get PRO
April '26
+35
in 4 channels
Get PRO
March '26
+29
in 3 channels
Get PRO
February '26
+19
in 3 channels
Get PRO
January '26
+38
in 3 channels
Get PRO
December '25
+60
in 4 channels
Get PRO
November '25
+84
in 4 channels
Get PRO
October '25
+29
in 3 channels
Get PRO
September '25
+32
in 3 channels
Get PRO
August '25
+39
in 3 channels
Get PRO
July '25
+34
in 3 channels
Get PRO
June '25
+47
in 4 channels
Get PRO
May '25
+45
in 4 channels
Get PRO
April '25
+40
in 3 channels
Get PRO
March '25
+39
in 2 channels
Get PRO
February '25
+29
in 2 channels
Get PRO
January '25
+43
in 3 channels
Get PRO
December '24
+64
in 2 channels
Get PRO
November '24
+90
in 4 channels
Get PRO
October '24
+87
in 2 channels
Get PRO
September '24
+133
in 3 channels
Get PRO
August '24
+202
in 2 channels
Get PRO
July '24
+273
in 2 channels
Get PRO
June '24
+296
in 4 channels
Get PRO
May '24
+287
in 3 channels
Get PRO
April '24
+220
in 4 channels
Get PRO
March '24
+298
in 3 channels
Get PRO
February '24
+229
in 2 channels
Get PRO
January '24
+133
in 1 channels
Get PRO
December '23
+100
in 3 channels
Get PRO
November '23
+41
in 3 channels
Get PRO
October '23
+19
in 1 channels
Get PRO
September '23
+69
in 0 channels
Get PRO
August '23
+9
in 0 channels
Get PRO
July '23
+30
in 0 channels
Get PRO
June '23
+19
in 0 channels
Get PRO
May '23
+30
in 0 channels
Get PRO
April '23
+66
in 0 channels
Get PRO
March '23
+52
in 0 channels
Get PRO
February '23
+441
in 0 channels
Get PRO
January '23
+174
in 0 channels
Get PRO
December '22
+48
in 0 channels
Get PRO
November '22
+488
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 08 September | 0 | |||
| 07 September | +1 | |||
| 06 September | +2 | |||
| 05 September | +1 | |||
| 04 September | +3 | |||
| 03 September | +2 | |||
| 02 September | +3 | |||
| 01 September | +1 |
Channel Posts
በመላው ዓለም ለምትገኙ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አማኞች በሙሉ እንኳን ለታላቁ መልአክ ለቅዱስ ሩፋኤል ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ።
ጳጉሜን ሦስት ቀን የገናናው መልአክ የቅዱስ ሩፋኤል መታሰቢያ በዓል ነው። የፍርድ ቀንም መታሰቢያ ቀን ነው።
ቅዱስ ሩፋኤል ሰይጣን ቤተክርስቲያንን ዓሣ አንበሪውን እንዲንቀሳቀስ በማድረግ ቤተክርስቲያንን ለማስጠም ሲሞክር
ቅዱስ ሩፋኤል ቤተክርስቲያንን ከመስጠም ጥፋት የታደገበት ቀን ነው እንኳን አደረሳችሁ።
በቤተክርስቲያናችን ሥርዓትና ደንብ መሠረት ጳጉሜ ሦስት የታላላቅ አምላካዊና መንፈሳዊ ምስጢራት ማሰብያ ድንቅ በዓላት ይታሰባሉ።
በዚህች ዕለት የሚታሰቡትን አራት ዋና ዋና ታላላቅ ሁነቶች በቅዱስ መጽሐፍ፣ በሊቃውንቱ ድርሳናትና በቅዱስ ያሬድ ምስጋና ተደግፈው እንደሚከተለው በቀረቡ ነጥቦች እንመለከታቸዋለን።
፩ኛ/ ቅዱስ ሩፋኤልእና የቤተክርስቲያንን መታደግ
ታሪኩ በእስክንድርያ ደሴት ላይ በቅዱስ ሩፋኤል ስም የታነጸችውን ቤተክርስቲያን የሚያስታውስ ነው። ዲያብሎስ በዓሣ ነባሪው አካል አድሮ ቤተክርስቲያኗን በባሕር ውስጥ ለማስጠም በሞከረ ጊዜ፣ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል በተሰጠው ኃይል በጦሩ ዓሣ ነባሪውን ወግቶና ገሥጾ ቤተክርስቲያኗን ከጥፋት የታደገበት ቀን ነው።
ዛሬም የፖለቲካ ባሕሩን በማናወጥ ኢትዮጵያን እና ቤተክርስቲያንን የሚፈታተነውን ርኩስ መንፈስ ፣ ቅዱስ ሩፋኤል ይገስጽልን አሜን።
በጦቢት መጽሐፍ ላይ “ዓሣው ሊበላው በወደደ ጊዜ መልአኩ ቅዱስ ሩፋኤል ጦቢትን አጽናናው፤ ዓሣውንም ይዞ ያወጣው ዘንድ ረዳው” (መጽሐፈ ጦቢት ፮፥፪) ተብሎ እንደተጻፈ፣ መልአኩ የሰውን ልጅ ከአጋንንትና ከጥፋት የመታደግ አምላካዊ ተልእኮ አለው።
ድርሳነ ሩፋኤል እንደሚያስረዳው የባሕሩ ማዕበልና የዓሣ ነባሪው መንቀሳቀስ የዓለምን ፈተናና የዲያብሎስን ተንኮል ሲያመለክት፣ ቅዱስ ሩፋኤል ደግሞ የምሕረትና የመዳን መልእክተኛ ሆኖ ቤተክርስቲያንን ያጸናል።
ቤተክርስቲያን በዓለም ማዕበል አትናወጥም። ዲያብሎስ እሷን ለማስጠም የቱንም ያህል ቢጥር፣ በቅዱሳን መላእክት ተጠበቃ በክርስቶስ ደም የተመሠረተች ናትና አትጠፋም።
፪ኛ/ ነገረ ምጽአትና የመጨረሻው ፍርድ
በዚች ዕለት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በኃይልና በታላቅ ምስጋና ለፍርድ የሚመጣበት ነገረ ምጽአቱ ይታሰባል።
“የሰው ልጅ በክብሩ በሚመጣበት ጊዜ ከእርሱም ጋር ቅዱሳን መላእክቱ ሁሉ፣ በዚያን ጊዜ በክብሩ ዙፋን ይቀመጣል... ንጉሡም በቀኙ ያሉትን ይላቸዋል፦ እናንተ የአባቴ ቡሩካን፣ ኑ፤ ዓለም ከተፈጠረ ጀምሮ የተዘጋጀላችሁን መንግሥት ውረሱ... በግራው ያሉትን ደግሞ ይላቸዋል፦ እናንተ የተረገማችሁ፣ ለዲያብሎስና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ” (ማቴዎስ ፳፭፥፴፩-፵፩)።
ማኅሌታዩ ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓው ላይ፦ "ይመጽእ እግዚእ ውስተ ዓለም ወይፌድዮሙ ለጻድቃን በጽድቆሙ ወለኃጣንኒ በኃጢአቶሙ" (ጌታ ወደ ዓለም ይመጣል፤ ለጻድቃን እንደ ጽድቃቸው፣ ለኃጥአንም እንደ ኃጢአታቸው ዋጋቸውን ይከፍላቸዋል) በማለት የምጽአቱን አስፈሪነትና የጻድቃንን ክብር ዘምሯል።
፫ኛ/ ርኅወተ ሰማይ (የሰማይ መከፈት)
በዚህ ቀን ሰማያት እንደሚከፈቱ፣ የሰው ልጅ ጸሎትና መሥዋዕት በመላእክት አማካኝነት ወደ እግዚአብሔር መንበር የሚያርግበት ልዩ የጸሎትና የምሕረት ጊዜ እንደሆነ ይነገራል።
“የመልአኩም እጅ የዕጣኑ ጢስ ከቅዱሳን ጸሎት ጋር በእግዚአብሔር ፊት ወጣ” (የዮሐንስ ራእይ ፰፥፬) ተብሎ እንደተጻፈ፣ መላእክት የሰውን ልጅ ጸሎት ወደ ፈጣሪ ያደርሳሉ።
መንፈሳዊ ምስጢር፦ ርኅወተ ሰማይ ማለት የሰው ልጅ ምድር ላይ ሆኖ የሚያቀርበው ንስሐና አምልኮ በሰማያዊው አምላክ ዘንድ ተተቀባይነትን የሚያገኝበት፣ በሰውና በእግዚአብሔር መካከል ያለው ግንኙነት የሚታደስበት የጸጋ ወቅት ነው።
፬ኛ/ ካህኑ መልከ ጼዴቅ /የክርስቶስ ምሳሌ
የሳሌም ንጉሥና የእግዚአብሔር ካህን የሆነው መልከ ጼዴቅ በዚች ዕለት ይታሰባል።
የመጽሐፍ ቅዱስ መሠረት፦ “የሳሌም ንጉሥ መልከ ጼዴቅም እንጀራንና ወይንን አወጣ፤ እርሱም የእልልታ አምላክ ካህን ነበረ” (ዘፍጥረት ፲፬፥፲፰)። ቅዱስ ጳውሎስም በዕብራውያን መልእክቱ “እንደ መልከ ጼዴቅ ሹመት ለዘላለም ካህን ነህ” (ዕብራውያን ፭፥፮) በማለት መልከ ጼዴቅ የመድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ የካህንነቱ ምሳሌ መሆኑን አብራርቷል።
መልከ ጼዴቅ የወይንና የእንጀራ መሥዋዕት እንደ አቀረበ፣ ክርስቶስም ሥጋውንና ደሙን እንጀራና ወይን አድርጎ ለዓለም ድኅነት ሰጥቷል።
የቅዱስ ሩፋኤል ጥበቃና ረድኤት፣ የካህኑ መልከ ጼዴቅ በረከት አይለየን አሜን።
ዘላለም ምስክር
| 2 | No text... | 114 |
| 3 | ጳጉሜን 3 – ዐፄ ዘርአ ያዕቆብ (1426-1460 ዓ.ም)
ጳጉሜን 3 የገናናው ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ (1400-1460 ዓ.ም) ዕረፍት የሚታሰብበት ቀን ነው፡፡ የንጉሡን የሥነ ጽሑፍና የታሪክ ሥራዎች ልናስተዋውቅና ልንዘክረው ይገባል፡፡ እርሳቸው ለታሪክና ለሃይማኖት ጥናት ከፍተኛ ጠቀሜታ ያላቸውን ከዘጠኝ በላይ መጻሕፍት አበርክተውልናል፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዐፄ ዘርዓ ያዕቆብን “ቅዱስ” ባትለውም፣ በመጽሐፈ ስንክሳር ግን ያበረከተውን አስተዋጽዖ እውቅና ለመስጠት በክብር ታስበዋለች፡፡ በ2018 ዓ.ም. ሆነን ስንዘክረው፣ ለቤተ ክርስቲያን የሚችለውን ፈጽሞ ካረፈ 558 ዓመታት አልፈዋል፡፡
በተለይ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ የሆኑ አንዳንድ ‘ታሪክ’ ጸሐፊዎች እና የትግራይ ብሔርተኞች ለዐፄ ዘርአ ያዕቆብ ያለስሙ ስም በመስጠት በሐሰት ስሙን አጠልሽተውታል፡፡ ስለዚህ በታሪክ ላይ የሚፈጸመውን ማዛነፍ ለማስተካከል መሥራት ይገባል፡፡ ንጉሡን ያለማስረጃ አናጋንን፤ እንዲሁም አናንኳስ። ይህ ኢትዮጵያዊ ንጉሥ ለሀገሩና ለቤተ ክርስቲያኑ ታላቅ ተጋድሎ ያደረገ መሪ ነው፤ አስተዋጽዖውም እጅግ ላቅ ያለ ነው፡፡
ወደፊት በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጳጉሜን 3ን መሠረት በማድረግ፣ ስለ ዐፄ ዘርአ ያዕቆብ ጥናታዊ ጽሑፍ የሚቀርብበትና ውይይት የሚካሄድበት መርሐ ግብር ቢዘጋጅ መልካም ነው፡፡ | 406 |
| 4 | No text... | 179 |
| 5 | በወለጋ መንግስታዊ ሽብር የአማራ ህዝብ ላይ እየተፈጸመ ነው ❗️
እንደ አለም አቀፍ ሚድያ first post ዘገባ ገዳ ኮማንዶ የተባለ በኦሮምያ የብልጽግና አገዛዝ ታጣቂዎች ንጹሀንን በግፍ ሲ***ገ*ሉ እና መኖርያ ቤት ሲያቃጥሉ መረጃዎች መውጣታቸውን ዘግበዋል::
እንደ ሚድያው ዘገባ ከ 50 በላይ ንጹሀን ማንነት በለየ ጥቃት መገ*ደላቸውን ነገር ግን በሶሻል ሚድያ መረጃዎች ከ 250 በላይ የሚገመቱ ንጹሀን ነፍሳቸው ስለ መነጠቁ እየተገለጸ መሆኑን ዘግበዋል::
በወለጋ በጊዳ አያና እና በአከባቢው ማንነት ተኮር ጥቃት (የአማራ ትግራይ እና ሌሎች በሰፈራ ፕሮግራም በኦሮምያ የሚገኙ) አረጋውያን እና ካህናትን ጨምሮ ግድያ እና አብያተ ክርስቲያናት ቃጠሎ መዘገቡ የሚታወስ ነው::
ይህ ግፍና በደል በገለልተኛ አካል ተጣርቶ ግፈኞች ለፍርድ ማግኘት ይገባቸዋል ❗️ | 167 |
| 6 | በጊዜ ከእንቅልፏ የነቃች ነፍስ 🙏
እህታችን ለዘመናት በ«መልካም ወጣት ጉባኤ» በሚል ስም በሚንቀሳቀሰው ድርጅት ውስጥ ቆይታለች። አሁን ግን እውነተኛዋን ሃይማኖት ወደ ሆነችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መጥታ፣ የቅድስት ሥላሴን ልጅነት አግኝታለች። 🙏⛪
+***+
እግዚአብሔር በእውነተኛው መንገድ ያጽናሽ፤
እኛንም ያጽናን።
እንኳን ደህና መጣሽ! 🤍
እግዚአብሔር ይመስገን! 🙏
Ephram | 184 |
| 7 | ♦መንግስታዊ መድሎ እና አሻጥር . . .
በመንግሥት የመገናኛ ብዙሃን እንደተገለጸው ”ሽኖዬ እና ጎቤ” የኦሮሞ ወጣቶች ባህላዊ ጭፈራ ፤ በአዲስ አበባ በአደባባይ በአሉን የማስተዋወቅ ዝግጅት ከፋተኛ የመንግስት አመራር በተገኙበት በይፋ እንደተጀመረ ተገልጿል ።
በኢትዮጵያ ውስጥ የተለያዩ ባህሎች ፣ ሐይማኖቶች እና ልማዶች እንዲሁም መሰል ባህሎች አሉ ። ሁሉም እንደየ-ፈርጁ በተከታዮቻቸው እየተከበረ ይገኛል ።
ይሁን እንጂ ፤ ከሁሉም ባህሎች እና ሐይማኖቶች መሰል ክንውኖች በተለይ መልኩ ፤ የኦሮሚያ ባህሎችና ልማዶች
ለማክበር እና ለማስተዋወቅ ፣ ከቤተመንግስቱ ጀምሮ እስከ ታች ቀበሌ ድረስ መንግስታዊ ማዋቀር የዕዝ ሰንሰለት ተዘርግቶለት ፣ እንዲሁም ከፍተኛ የመንግስት በጀት ተመድቦ እየተከበረ ይገኛል ፤ ይህ ለምንድነው ?!
አዲስ አበባ "የብሔር ብሔረሰቦች መዲና" የሁሉም ኢትዮጵያዊ መናገሻ ከተማ እንደመሆና መጠን ፤ ሁሉም ብሔረሰቦች በከተማቸው ላይ እኩል የመጠቀም እና መንግስታዊ ድጋፍ የማግኘት እንዲሁም በፈለጉት አልባሳት እና ቀለማት የማክበር መብት አላቸው ሆይ ?!
ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ባለፉት ስምንት ዓመታት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ከባድ ግፍና መከራ እያለፈች ትገኛለች። ታሪካዊቷ፣ የሰላምና የፍቅር አስተማሪዋ ቤተክርስቲያን ምዕመናኗ ማረፊያ፣ ታቦታቷ ማደሪያ የሚያጡበት እና በአደባባይ በዓላቷ ላይ እንኳን ጫና የሚበዛባት ደረጃ ላይ ደርሳለች ።
ይድነቃቸው ከበደ | 182 |
| 8 | 🇪🇹 በአፍሪካ ትልቁ የገበያ ማዕከል እንደሆነ የሚነገርለት መርካቶ፣ በአሁኑ ሰዓት በእሳት እየተቃጠለ ይገኛል።
እሳቱ የተነሳው፣ የጠቅላይ ሚኒስቴር አብይ አገዛዝ ከሰሞኑ በመርካቶ ማፍረስ በጀመረው፣ በመስኪዱ ዙሪያ፣ አካባቢ ነው።
ቤቶቹ ጣልያን የገነባቸው የድንጋይ ቤቶች በመሆናቸው፣ ለአገዛዙ ለማፍረስ አስቸጋሪ ሆኖበት ሰንብቷል።
በዚህ ዓይነት አፈራረስ ሌላውም ስለሚያስቸግረውና ኃይል እና ጉልበት ስለሚወስድበት፣ አገዛዙ በምትኩ እሳት መልቀቁን አማራጭ ያደረገው ይመስላል።
አገዛዙም፣ ሲያፈርሰው እንደከረመው ከተማ፣ እሱም በቅርብ ጊዜ መፍረሱ አይቀርም የሚሉ ብዙ ናቸው። | 195 |
| 9 | ምን እንድትሰሙ ተጠበቁ። ማር 4፤24
በDMV ለምትኖሩ ኦርቶዶክሳውያን
የተዋሕዶ ልጆች የተላለፈ ወቅታዊ መልዕክት። | 196 |
| 10 | የወንድሜ አብርሃም ኃይሉ ጥፋት ለፍቶ ማደሩ ብቻ ነው። አብርሽ በዘመኑ የፖለቲካ ሕመም ያልተለከፈ፣ መንደር ውስጥ የማይወሸቅ፣ የሰው ሕመም የሚያመው፣ ለተቸገሩት ደራሽ፣ ሰብአዊነት የሚሰማው ፍጹም የዋህ እና አዛኝ ሰው ነው። ሰው ችግር ላይ ከሆነ ጎጥ፣ መንደር፣ ቋንቋ እና ሌላ መለያ ጉዳዩ አይደለም፤ ሰውነት ለሚለው ተፈጥሮ ተገዥ የሆነ ወንድም ነው። ይህ ወንድም አንባቢ ትውልድ እንዲፈጠር የድርሻውን የሚወጣ፣ የማንበብ ፍላጎት እያላቸው አቅም ለሌላቸው በራሱ ወጭ መጻሕፍትን የሚለግስ ሰው ነው። አብርሽ በላቡ ጥሮ ግሮ መጽሐፍ ቸርችሮ የዕለት ጉርሱን የሚያገኝ ኦርቶዶክሳዊ ወጣት ነው።
ይህንን ኦርቶዶክሳዊ ወጣት ለምን መጽሐፍ ሸጥክ ብሎ ማሠር ዐይን ያወጣ ግፍ፣ ሥር የሰደደ በደል፣ የሚሠሩ ወጣቶችን የሚያሸማቅቅ ነውር ነው። አንድን ኦርቶዶክሳዊ መጽሐፍ ማከፋፈል ለምን ወንጀል ሆነ?!
ዲ/ን ታደለ ሲሳይ | 170 |
| 11 | የታሰሩበትን ቦታ በትክክል አረጋግጠናል።
በቀሲስ መንግሥቱ ጎበዜ (ዶ/ር) የተጻፈው "የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሦስት ሺሕ ዘመናት የታሪክ ጉዞ" የተሰኘው ዐዲስ መጽሐፍ በመሸጣቸው ምክንያት፣ መጽሐፉ በፖሊስ ተወርሶባቸው ያለአግባብ የታሰሩት የአርጋኖን መጻሕፍት መደብር ሥራ አስኪያጅ የሆኑትን ቅኑን አብርሃም ኃይሉን እና ወንድም ይልማን ዛሬ ከሰዓት በኋላ ጠይቀናቸዋል። የታሰሩት መገናኛ፣ 24 ቀበሌ ገቢዎች አካባቢ በሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ መሆኑን በትክክል አረጋግጠናል። ስለዚህ ለመጠየቅ የምትሄዱ ሰዎች እንዳትደክሙ፤ መገናኛ ደርሳችሁ ወደ ገርጂ ወይም አደይ አበባ በሚወስደው የታክሲ መያዣ በኩል ካለፋችሁ በኋላ፣ በፎቶው ላይ በሚታየው መንገድ ቁልቁል ቀጥታ ጥቂት እንደወረዳችሁ እስር ቤቱ ይገኛል።
እየሄድን እነዚህን በግፍ የታሰሩ ወገኖቻችንን እንጠይቃቸው።
በአሁኑ ወቅት "ዕውቀትን በዕውቀት መሞገት" የሚለው መርሕ አፈር በልቷል። በመጽሐፉ ውስጥ ባሉ ሐሳቦች ላይ ተገቢውን የጽሑፍ ኂስ በማቅረብ መከራከር ሲገባ፣ መጽሐፉ እንዳይነበብ በፖሊስ ኃይል ማስለቀም፣ ማገድና መጻሕፍት አከፋፋዮችን ማሰር ፈጽሞ የማይገባ ድርጊት ነው።
ዲ/ን ዮሴፍ | 165 |
| 12 | የዝች የሙስሊም እህታችንን ግጥም አድምጡት | 199 |
| 13 | በኦሮሚያ ያላችሁ ኦርቶዶክሳውያን ቋንቋ ዘር ቀለም ሳትለዩ ራሳችሁን ጠብቁ የከፋ መከራ እየመጣ ነውና | 186 |
| 14 | የመጀመሪያዎቹ ሙስሊሞች በቁራይሽ ጎሳዎች ከመካ ሲሳደዱ እጁን ዘርግቶ የተቀበላቸው የክርስቲያኗ ኢትዮጵያ ንጉሥ ክርስቲያን ንጉሥ ነበር። ለዚህ ጥርጥር የለውም። ውሃቢያዎች ግን ነጃሺ የሚል ስም ሰጥተውት የሰለመ ንጉሥ አስመስለው ትርክት መፍጠር ከጀመሩ ከራርመዋል። ይህ የቀሲስ መንግሥቱ ጎበዜ መጽሐፍ መሠረት አልባ ትርክታቸውን በማሥረጃ አስደግፎ እርቃን ያስቀራል።
ፖሊስ ያለ ፍር ቤት ማዘዣ ይህን መጽሐፍ ካሳታሚው አርጋኖን መጽሐፍ ቤትና ከሌሎች መጻሕፍት መደብሮች እየለቀመ መውሰድ ጀምሯል። | 236 |
| 15 | የታሰሩት 24 ቀበሌ ገቢዎች አካባቢ በሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ ነው።
በቀሲስ መንግሥቱ ጎበዜ (ዶ/ር) የተጻፈው "የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሦስት ሺሕ ዘመናት የታሪክ ጉዞ" የተሰኘው ዐዲስ መጽሐፍ በመሸጣቸው ምክንያት፣ መጽሐፉ በፖሊስ ተወርሶባቸው ያለአግባብ የታሰሩት እነ አብርሃም ኃይሉ ያሉበት ቦታ ፒያሳ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ዋና መሥሪያ ቤት በሚገኘው እስር ቤት አይደለም። በአሁኑ ወቅት የታሰሩት 24 ቀበሌ ገቢዎች አካባቢ በሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ ስለሆነ፣ እየሄድን እነዚህን የግፍ እስረኞች እንጠይቃቸው።
በአሁኑ ወቅት "ዕውቀትን በዕውቀት መሞገት" የሚለው መርሕ አፈር በልቷል። በመጽሐፉ ውስጥ ባሉ ሐሳቦች ላይ ተገቢውን የጽሑፍ ሒስ በማቅረብ መከራከር ሲገባ፣ መጽሐፉ እንዳይነበብ በፖሊስ ኃይል ማስለቀም፣ ማገድና መጻሕፍት አከፋፋዮችን ማሰር ፈጽሞ የማይገባ ድርጊት ነው። | 1 262 |
| 16 | A Global Campaign To Save The Ethiopian Orthodox Tewahedo | 183 |
| 17 | ለኦርቶዶክሳውያን በሙሉ
ከመስከረም 1 /2018ዓ.ም ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ በዞናችን፣በወረዳችን ና በቀበሌያችን የተፈጸሙ በኦርቶዶክሳውያን ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶችን(ሞት፣ስደት፣እገታ፣ዝርፊያ፣የቤተ ክርስቲያን ቃጠሎ ወዘተ...) መዝግባችሁ እንድትልኩልን።በዚህ የተሳተፉ ግለሰቦችን ስም ጨምራችሁ ላኩልን።የጊዜ ገዳይ ነው ገዳዮቻችንም ሆኑ አስገዳዮቻችን ለፍርድ ይቀርባሉ። | 176 |
| 18 | እነዚህ ልጆች ኦሮሚኛ ተናጋሪ ኦርቶዶክሳውያን ናቸው።የተወሰደበን የቤተ ክርስቲያን ህጋዊ ይዞታ ይመለስልን ነው ያሉት። በኦርቶዶክስ ጥላቻ ያበዱት ግን "ፋኖ ናቸው ጨፍጭፋችሁ አጥፏቸው"የሚል ጥሪ እያቀረቡ ይገኛሉ።
ከዚህ ምን እንማራለን?
ብሔሩ ኦሮሞም ይሁን አማራ ጉራጌም ይሁን ትግሬ ሃይማኖቱ ኦርቶዶክስ የሆነ ሁሉ "ፋኖ"የሚል ታርጋ ተለጥፎበት እንደሚገደል | 190 |
| 19 | በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን ኤጄርሳ ወረዳ ህጋዊ ካርታ ያለው ያለውን የቤተ ክርስቲያን ይዞታ ለ ሌሎች በመሰጠቱ ኦርቶዶክሳውያን ተቃውሟቸው ገልጸዋል። | 185 |
| 20 | ከመንግስት ጀርባ ያለው መንግስት ውሃቢያ
የመንግስት መዋቅር ተጠልፎ የዜጎች በሕግ ፊት የተረጋገጠ የመናገርና ሐሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት በመንፈግ በየማተሚያ ቤት እየዞሩ ዛቻና ማስፈራራት እየፈጸሙ ነው።
ከዚሁ ጋር ተያይዞ «የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሦስት ሺህ ዘመናት የታሪክ ጉዞ» መጽሃፍን ያሳተመው ማተሚያ ቤት ባለቤት ከነሰራተኞቹ በእስር ላይ ይገኛሉ።
ምንም እንኳን ማተሚያ ቤቱ የቅጂና ተዛማጅ መብት ባለቤትን ፈቃድ በመመልከትና መጽሐፉን መርምሮ ያሳተመው ቢሆንም የመንግስትን መዋቅር ጠልፈው ለራሳቸው ፍላጎት ያለይሉኝታ እየተጠቀሙ የሚገኙ ውሃቢያዎች እንዲታሰር ፈርደውበታል። የታሰረው እሱ ብቻ ሳይሆን ሰራተኞቹ እና መጻሕፍቱም ጭምር ናቸው።
ኦርቶዶክሳውያንን በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ መበደል ሕጋዊ እስኪመስል ሥርዓቱ ምን ዓይንት እርምጃ አይወስድም። እንደውም የተበደለውን ሳይሆን በዳዩን ይንከባከባል። ይህም በኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚደርሰው በደል በመንግስት መወቅር የሚደገፍ እንደሆነ ማሳያ ነው።
ስምዐ ተዋሕዶ | 236 |
