en
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Open in Telegram
1 083
Subscribers
+924 hours
+207 days
+1530 days
Posts Archive
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ "ብቃት" የወጣቶች ስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ሁለተኛ ዙር ትግበራ ለወጣቶች  መሠረታዊ የኮምፕዩተር ስልጠና መስጠት ተጀመረ፤ እንደ ድሬዳዋ አስተዳደር በ2016 ዓ.ም እየተተገበረ የሚገኘው ሁለተኛው ዙር "ብቃት" የወጣቶች ስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም የ10 ቀን የህይወት ክህሎት ሰልጠና ወስደው ተግባራዊ የሥራ ላይ ልምምድ በተለያዩ በአስተዳደሩ የሚገኙ ኢንደስትሪዎች ላይ ስድስት ወራት የሚፈጀውን ውጤታማ ቆይታ እያደረጉ ለሚገኙ ወጣቶች መሰረታዊ የኮምፒውተር ስልጠና በመሰጠት ላይ ይገኛል፡፡ ይህንንም ስልጠና በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እየተከታተሉ የሚገኙ ወጣቶች በአጠቃላይ በፕሮግራሙ ተጠቃሚነታቸው በአመለካከት፣ በክህሎት እንዲሁም በዕውቀት ከዚህ በፊት ከነበሩበት የተሻለ ነገሮችን የመረዳትና የማድረግ አቅም እያዳበሩ እንደሚገኙ የተናገሩ ሲሆን መሠረታዊ የኮምፒውተር ስልጠናው በድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅም በተመሳሳይ ከነገ ጀምሮ የሚሰጥ ይሆናል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኑነት ሐምሌ 22/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ "ብቃት" የወጣቶች ስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ሁለተኛ ዙር ትግበራ ሦስተኛው ዙር የአቻ ለአቻ ውይይት ተደረገ፤      ወጣቶቹ  በየወሩ የአቻ ለአቻ  ውይይት  በማድረግ  በየጊዜው ያገኙትን እውቀት  የገጠማቸውን ችግሮች  ለይተው የተወያዩበት መድረክ  ሲሆን ይህ  ለሦስተኛ ጊዜ የተዘጋጀ  ውይይት የተደረገ ሲሆን የስራ ላይ ልምምዱን ሲያጠናቅቁ  በተቀጠሩበት ወይም በሚቀጠሩበት ድርጅቶች በሰለጠኑት ሞያ መሰረት ለማገልገል እራሳቸውን የሚያዘጋጁበትና እርስበርሳቸው የሚመካከሩበት ይሆናል፡፡      በዚህም ውይይት ላይ ተሳታፊ የሆኑ ወጣቶች በአጠቃላይ በፕሮግራሙ ተጠቃሚነታቸው በአመለካከት፣ በክህሎት እንዲሁም በዕውቀት ከዚህ በፊት ከነበሩበት የተሻለ ነገሮችን የመረዳትና የማድረግ አቅም እያዳበሩ እንደሚገኙ የተናገሩ ሲሆን በተለይ እርስ በዕርስ በመነጋገር ችግሮችን የፈቱበትና የተሻለ ዕውቀት የቀሰሙበት እንደነበር ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሐምሌ 20/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ "ብቃት" የወጣቶች ስራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ለወጣቶች በተከታታይ ሦስተኛው ዙር የአቻ ለአቻ ውይይት ተደረገ፤      ወጣቶቹ  በየወሩ የአቻ ለአቻ  ውይይት  በማድረግ  በየጊዜው ያገኙትን እውቀት  የገጠማቸውን ችግሮች  ለይተው የተወያዩበት መድረክ  ሲሆን ይህ  ለሦስተኛ ጊዜ የተዘጋጀ  ውይይት የተደረገ ሲሆን የስራ ላይ ልምምዱን ሲያጠናቅቁ  በተቀጠሩበት ወይም በሚቀጠሩበት ድርጅቶች በሰለጠኑት ሞያ መሰረት ለማገልገል እራሳቸውን የሚያዘጋጁበትና እርስበርሳቸው የሚመካከሩበት ይሆናል፡፡      በዚህም ውይይት ላይ ተሳታፊ የሆኑ ወጣቶች በአጠቃላይ በፕሮግራሙ ተጠቃሚነታቸው በአመለካከት፣ በክህሎት እንዲሁም በዕውቀት ከዚህ በፊት ከነበሩበት የተሻለ ነገሮችን የመረዳትና የማድረግ አቅም እያዳበሩ እንደሚገኙ የተናገሩ ሲሆን በተለይ እርስ በዕርስ በመነጋገር ችግሮችን የፈቱበትና የተሻለ ዕውቀት የቀሰሙበት እንደነበር ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሐምሌ 20/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

#ጥቆማ ኢትዮጵያ 5 ሚሊዮን #ኮደሮችን ለማሰልጠን ያለመ ፕሮጀክት አስጀምራለች። ለ3 ዓመታት ያህል የሚቆየው ይሄ ፕሮጀክት ከተባበሩት አረብ ኤሜሪትስ (UAE) ጋር በመተባባር የሚተገበር ነው ተብሏል
#ጥቆማ ኢትዮጵያ 5 ሚሊዮን #ኮደሮችን ለማሰልጠን ያለመ ፕሮጀክት አስጀምራለች። ለ3 ዓመታት ያህል የሚቆየው ይሄ ፕሮጀክት ከተባበሩት አረብ ኤሜሪትስ (UAE) ጋር በመተባባር የሚተገበር ነው ተብሏል። ምን መማር ይቻላል ? - Android Kotlin Development Fundamentals - Data Science Fundamentals - Programming Fundamentals ትምህርቱን እንዴት ማግኘት ይቻላል ? ስልጠናዎቹ በዩዳሲቲ (Udacity) በተሰኘው ኦላይን የትምህርት ፕላትፎርም ተዘጋጅተው የቀረቡ ናቸው። ሰልጣኞች ያለ አንዳች ክፍያ በነጻ ኮምፒውተራቸውን ወይም ስልካቸውን በመጠቀም መሰልጠን ይችላሉ። ስልጠናዎቹ 6-7 የሚሆኑ ሳምንታትን የሚፈጁ ሲሆን በማጠቃለያው ላይ ሞያዊ ሰርተፊኬት ይሰጣል። የስልጠናዎቹን ይዘት እንዲሁም ተጨማሪ መረጃዎች በተዘጋጀው ድረ-ገጽ ( https://ethiocoders.et/ ) ላይ መመልከት ይችላሉ።

የሐዘን መግለጫ --------------------- በቢሯችን የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት ከፍተኛ ባለሞያ አቶ ነጋሽ በላይነህ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቶናል። የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎት
የሐዘን መግለጫ --------------------- በቢሯችን የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት ከፍተኛ ባለሞያ አቶ ነጋሽ በላይነህ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቶናል። የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን እየገለፀ ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹና ለቢሮው ማህበረሰብ መፅናናትን ይመኛል::

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በአስተዳደሩ ስር ከሚገኙ የከተማ እና የገጠር አንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያ ማስተባበሪያ አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር  የ2017 በጀት ዓመት ለወረዳዎቹ የተሸነሸነ ዕቅድ ላይ ውይይት ተደረገ፡፡ በዚህም የውይይት መድረክ ላይ ማዕከላቱን የሚመለከቱ ሥራዎችን በመቁረስ በከተማና በገጠር ለሚገኙ አንድ ማዕከላት ማውረድ የተቻለ ሲሆን በቀጣይም በመናበብ የአስተዳደሩን ነዋሪ ተደራሽና ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎችን በተጨባጭ ለመስራት አስፈላጊውን ምችችት እንደሚደረግና የሚታይ ውጤትና ለውጥ ለማምጣት ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ የቢሮው ም/ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ገልጸዋል፡፡ ዕቅዱን ወደ ታች ሸንሽኖ ከማውረድ ስራው ጎንለጎን የሥራ ዕድል የማመቻቸት እና የመፍጠር አቅምማጎልበቻ ሰነድ ቀርቦ በቀጣይ በዋናነት በአገራዊና በዘርፉ አዲስ ዕሳቤዎች ላይ የጋራ ግንዛቤ ይዞ የተናበበና የተቀናጀ ሥራ መስራት እንደሚገባ በማመላከት በማጠቃለያው በክረምት በንቅናቄ እየተሰሩ ያሉ ሥራዎች በወረዳዎች ቀርበው ተገምግመዋል፡፡ የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሐምሌ 18/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በአስተዳደሩ ቀበሌ አስተዳደር ስር ከሚገኙ የከተማ እና የገጠር አንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ጣቢያ ማስተባበሪያ አመራሮችና ባለሙያዎች ጋር  የ2017 በጀት ዓመት ለወረዳዎቹ የተሸነሸነ ዕቅድ ላይ ውይይት ተደረገ፡፡ በዚህም የውይይት መድረክ ላይ ማዕከላቱን የሚመለከቱ ሥራዎችን በመቁረስ በከተማና በገጠር ለሚገኙ አንድ ማዕከላት ማውረድ የተቻለ ሲሆን በቀጣይም በመናበብ የአስተዳደሩን ነዋሪ ተደራሽና ተጠቃሚ የሚያደርጉ ሥራዎችን በተጨባጭ ለመስራት አስፈላጊውን ምችችት እንደሚደረግና የሚታይ ውጤትና ለውጥ ለማምጣት ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ የቢሮው ም/ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ገልጸዋል፡፡ ዕቅዱን ወደ ታች ሸንሽኖ ከማውረድ ስራው ጎንለጎን የሥራ ዕድል የማመቻቸት እና የመፍጠር አቅምማጎልበቻ ሰነድ ቀርቦ በቀጣይ በዋናነት በአገራዊና በዘርፉ አዲስ ዕሳቤዎች ላይ የጋራ ግንዛቤ ይዞ የተናበበና የተቀናጀ ሥራ መስራት እንደሚገባ በማመላከት በማጠቃለያው በክረምት በንቅናቄ እየተሰሩ ያሉ ሥራዎች በወረዳዎች ቀርበው ተገምግመዋል፡፡ የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሐምሌ 18/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

በሳዑዲዓረቢያ ተቀጥረው ለመሥራት የሠለጠኑ ሥራ ፈላጊዎች የቅድመ ጉዞ ስልጠና ተሰጣቸው!! በኢትዮጵያ እና ሳዑዲዓረቢያ መንግሥት ሥምምነት መሰረት ወደ ሳዑዲዓረቢያ ከሚሔዱ ሥራ ፈላጊ ዜጎች መካከል በድሬዳዋ  አስተዳደር በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ስልጠናቸውን ሲከታተሉ ለነበሩ 52 ሰልጣኞች ጉዞ ከማድረጋቸው በፊት አስፈላጊ  የሆነ ግንዛቤ እንዲፈጥሩ የሚያስቸላቸው ገለጻ በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የውጭ አገር ስራ ስምሪትና የሰራተኞች ጥበቃ ዳይሬክቶሬት ከፍተኛ ባሙያዎች ተደርጎላቸዋል። በዚህም ከሃገር ውጭ ለስራ ጉዞ ሲያደርጉ ቅድመ ጉዞ መደረግ እና ማሟላት የሚገባቸውን እንዲሁም በጉዞ ላይ እና ለስራ በሚሄዱበት አገር ሊገጥማቸው የሚችሉ ጉዳዮችን በተብራራ መልኩ ማግኘታቸው በቂ ግንዛቤ እንደፈጠረላቸው ሰልጣኞች ተናግረዋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሐምሌ 17/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

” የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱ ቆሟል” ቢሚል የሚሰራጨው መረጃ ከእውነታው የራቀ ነው! የሥራና ክህሎት ሚስቴር መቋቋሙን ተከትሎ የቅድሚያ ቅድሚያ ትኩረት ከሰጣቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ነው፡፡ ከዚህ ቀደም ስምሪቱ በርካታ ህገወጥ አሰራሮች በሰፊው የተንሰራፉበት ነበር፡፡ በመሆኑም ለተሻለ ህይወት እና ሥራ ወደ ተለያዩ ሀገራት የሚሄዱ ዜጎቻችን ላልተፈለገ ወጪ እና እንግልት ተዳርገዋል፡፡ ከዚህ በላይ በርካቶች ለሞት እና ለከፍተኛ አካል ጉዳት ሲዳረጉ ቆይቷል፡፡ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ፍልሰት አይቀሬ ነባራዊ ሁኔታ መሆኑን ከግምት በማስገባት የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ስርዓቱን ለማሻሻል የተለዩ የሪፎርም ሥራዎችን በትኩረት ሰርቷል፡፡ የሪፎርሙ አጠቃላይ መነሻና መዳረሻ የዜጎችን መብት፣ ደህንነትና ተጠቃሚነትን ማረጋገጥ ሲሆን ይህንን ዕውን ለማድረግ ሥራውን ጊዜውን በዋጁ ቴክኖሎጂዎች ለመደገፍ ከፍተኛ ሥራ ተሰርቷል፡፡ በውስጥ አቅም በልፅጎ ሥራ ላይ የዋለው የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ሥርዓት የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱን ከማዘመኑም በላይ ዜጎች ከመነሻ እስከ መዳረሻ ሀገራት ድረስ ይገጥማቸው የነበረውን አላስፈላጊ ወጪ እንዲቆምና የነበረው እንግልትም እንዲቀንስ   አድርጓል፡፡ ከመረጃ ጋር ተያይዞ እንደ ሀገር የነበረብንን መሰረታዊ ችግርንም ሙሉ ለሙሉ እንድንሻገር አስችሎናል፡፡ በውጭ ሀገር የሥራ ስምሪት ላይ ለመሳተፍ ለሚፈልጉ ዜጎቻችን ሥርዓተ-ትምህርት ተቀርጾ  በመላ ሀገሪቱ በሚገኙና በተመረጡ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት ስልጠና እንዲወስዱና ብቃታቸውንም በምዘና እንዲያረጋግጡ የሚያስችል ስርዓት ተዘርግቶ ተግባራዊ እየተደረገ  ይገኛል፡፡ ይህም  ዜጎች ከሙያ ባለፈ ስለሚሄዱበት ሀገር ባህል፣ ቋንቋና መሰል ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ጭምር በስነ-ልቦና ዝግጁ እንዲሆኑ የሚያደርግ ነው፡፡ ሳውዲ አረቢያ፣ የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ፣ ጆርዳን፣ ኳታር፣ ቤሩት እና ኩዌት የመዳረሻ ሀገራትን ለማስፋት በተደረገው ጥረት የሁለትዮሽ ስምምነት የተደረገባቸው ሀገራት ናቸው፡፡ መዳረሻ ሀገራቱን ለማስፋትም ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጋር በቅርበት እየተሰራ ነው፡፡ በ2016 በጀት ዓመት ብቻ ከ345 ሺህ ዜጎች በላይ ስምምነት ወደተገባባቸው ሀገራት ህጋዊ በሆነ መንገድ የሥራ ስምሪት አግኝተዋል፡፡ አሁንም በሁሉም መዳረሻ ሀገራት ያለው የሥራ ስምሪት ሥራ ካለምንም ችግር እንደቀጠለ ነው፡፡ በበጀት ዓመቱ በህጋዊ መንገድ የሥራ ሥምሪተ ያገኙት ዜጎቻችን በ2014 ዓ.ም ተመሳሳይ ወቅት ጋር ከነበረው አፈፃፀም ጋር ሲነፃፀር የ762 በመቶ በላይ እድገት አሳይቷል፡፡ በቀጣይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ የሰለጠነና በከፊል የሰለጠኑ ባለሙያዎችን ጨምሮ በርካታ ዜጎቻችን የዓለም የሥራ ገበያ በሚያመጣው ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ በትኩረት እየሰራ ይገኛል፡፡ ነገር ግን ሰሞኑን በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች “የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱ ቆሟል” የሚል ከእውነታው ፍፁም የሚቃረን መረጃ እየተዘዋወረ ይገኛል፡፡ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱ ከመቼውም ጊዜ በተሻለ ዘመኑን በዋጁ ቴክኖሎጂዎች በመታገዝ ከሰው ንክኪ ነፃ በሆነ እና ፍትሃዊነትን በሚያረጋግጥ መልኩ ተግባራዊ እየሆነ ይገኛል፡፡ በመሆኑም ህብረተሰቡ ይህንን ተገንዝቦ ህጋዊ በሆነው የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪቱ ላይ ማንኛውንም አይነት መረጃ ሲፈልግ አቅራቢያቸው ከሚገኙ ሥራውን ከሚያስተባብሩ ቢሮዎችና ጽ/ቤቶች እንዲሁም ከሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ማግኘት እንደሚችል እንገልፃለን፡፡

ናፍቆት የድሬደዋ ሳምንት ከሐምሌ 21 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ለ3ኛ ጊዜ በድምቀት ለሚካኼደው 'ናፍቆት የድሬዳዋ ሳምንት' በዓል ላይ የሚሳተፉ ወገኖች ወደድሬደዋ መግባት መጀመራቸውን አቶ ሮቤል ጌታ
ናፍቆት የድሬደዋ ሳምንት ከሐምሌ 21 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ለ3ኛ ጊዜ በድምቀት ለሚካኼደው 'ናፍቆት የድሬዳዋ ሳምንት' በዓል ላይ የሚሳተፉ ወገኖች ወደድሬደዋ መግባት መጀመራቸውን አቶ ሮቤል ጌታቸው የበዓሉ አቀባበልና መስተንግዶ ኮሚቴ ሰብሳቢ ተናገሩ። 3ኛው አመት 'ናፍቆት የድሬዳዋ ሳምንት' በዓል ከሐምሌ 21 እስከ 25 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ እንደሚከበር ታውቋል። በዓሉ የድሬደዋን ሕዝብ ባሳተፈ መልኩ በስፖርታዊ ውድድሮች፣ በኪነጥበባዊ ዝግጅቾች ለማክበር ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን አቶ ሮቤል ጠቅሰዋል። ለበዓሉ አከባበር በወጣው መርሐግብር መሰረት ሐምሌ 21 የሰላም እና የፍቅር ቀን ሐምሌ 22 የባህል እና የስፖርት ቀን ሐምሌ 23 የንግድ ቀን 'ኑ በድሬ እንነግድ' ሐምሌ 24 የቤተሰብ ቀን እንዲሁም ሐምሌ 25 የምስጋና እና የመዘከር ቀን በሚል መጠሪያ እንደሚከበሩም ተገልጿል። ከዚህ በተጨማሪ በሳምንቱ ቀናት፥ የበጎ ፈቃድ (በጤና፣ በትምህርት እና በማሕበራዊ ዘርፍ) አገልግሎት እንዲሁም ከአስተዳዳሩ ወጣቶች እና አመራሮች ጋር የሚደረግ የልምድ ልውውጥና፥ የዙም ሚቲንግን ጨምሮ የሽልማት መርሐ ግብር እንደሚኖር ታውቋል። Via በድሬቲዩብ

በዘንድሮ አመት የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና የተሳተፉ ፈታኞች እንዲሁም ተፈታኝ ተማሪዎች በጋራ በመሆን የአረንጓዴ አሻራ ማስቀመጥ መርሃ ግብር በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አከናወኑ፡፡ የዘንድሮ አመት
+8
በዘንድሮ አመት የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና የተሳተፉ ፈታኞች እንዲሁም ተፈታኝ ተማሪዎች በጋራ በመሆን የአረንጓዴ አሻራ ማስቀመጥ መርሃ ግብር በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አከናወኑ፡፡ የዘንድሮ አመት የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና በትናንትናው እለት በሰላም መጠናቀቁ የሚታወስ ሲሆን ከ520 በላይ ተፈታኝ ተማሪዎች በኮሌጁ ተመድበው በኮምፒውተር የታገዘ የፈተና ስርአት ፈተና መውሰዳቸው የሚታወስ ሲሆን እነዚህም ተፈታኝ ተማሪዎች ፈተናውን ተፈትነው እንደጨረሱ ከትምህርት ቢሮ ም/ኃላፊ እንዲሁም ከኮሌጁ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማ እና ከተለያዩ እንግዶች ጋር በመሆን በጋራ በኮሌጁ የአረንጓዴ አሻራ ማስቀመጥ መርሃ ግብር አከናውነዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምንኬሽን ሀምሌ12/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ለመፈተን በኮሌጁ የነበሩትን እንግዶች በዛሬው እለት የመሸኛ የምሳ ግብዣ አደረገ፡፡ ፈተና ለማስተባበር እንዲሁም ለመፈተን ከ
+4
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ለመፈተን በኮሌጁ የነበሩትን እንግዶች በዛሬው እለት የመሸኛ የምሳ ግብዣ አደረገ፡፡ ፈተና ለማስተባበር እንዲሁም ለመፈተን ከተለያዩ የአገራችን ክፍሎች የተውጣጡ ፈታኞች በኮሌጁ በነበራቸው ቆይታ በጣም ደስተኛ እንደነበሩና አጠቃላይ የኮሌጁ እንቅስቃሴም በአገር ደረጃ ተሞክሮ ሊወሰድበት የሚገባ ትልቅ ተቋም ነው  ስለዚህ በዚህ ኮሌጅ ውስጥ በቆየንባቸው ቀናቶች ውስጥ በኮሌጁ ያየናቸው ነገሮች እጅግ በጣም ጥሩ ናቸው እንዲሁም ይህን እንደ አገር ጥቂቶች ብቻ  የተወጡትን የፈተና ስርአት  ኮሌጁ በብቃት ያለምንም ችግር ተወጥቶታል ብለዋል፡፡ በዘንድሮ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና በወረቀትና በኮምፒውተር የታገዘ የፈተና ስርዓት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተና እንደሚወስዱ የሚታወቅ ሲሆን ከዚህም ውስጥ በኮሌጁ የተመደቡ የማህበረሰብ ሳይንስ ተማሪዎችና የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በአጠቃላይ ከ520 በላይ ተማሪዎች በኮምፒውተር የታገዘ የፈተና ስርዓት እንደተፈተኑ የሚታወስ ነው፡፡ የኮሌጁ ኮምንኬሽን ሀምሌ 11/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ለመፈተን በኮሌጁ የነበሩትን እንግዶች በዛሬው እለት የመሸኛ የምሳ ግብዣ አደረገ፡፡ ፈተና ለማስተባበር እንዲሁም ለመፈተን ከ
+4
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ለመፈተን በኮሌጁ የነበሩትን እንግዶች በዛሬው እለት የመሸኛ የምሳ ግብዣ አደረገ፡፡ ፈተና ለማስተባበር እንዲሁም ለመፈተን ከተለያዩ የአገራችን ክፍሎች የተውጣጡ ፈታኞች በኮሌጁ በነበራቸው ቆይታ በጣም ደስተኛ እንደነበሩና አጠቃላይ የኮሌጁ እንቅስቃሴም በአገር ደረጃ ተሞክሮ ሊወሰድበት የሚገባ ትልቅ ተቋም ነው ስለዚህ በዚህ ኮሌጅ ውስጥ በቆየንባቸው ቀናቶች ውስጥ በኮሌጁ ያየናቸው ነገሮች እጅግ በጣም ጥሩ ናቸው እንዲሁም ይህን እንደ አገር ጥቂቶች ብቻ የተወጡትን የፈተና ስርአት ኮሌጁ በብቃት ያለምንም ችግር ተወጥቶታል ብለዋል፡፡ በዘንድሮ የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና በወረቀትና በኮምፒውተር የታገዘ የፈተና ስርዓት የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተና እንደሚወስዱ የሚታወቅ ሲሆን ከዚህም ውስጥ በኮሌጁ የተመደቡ የማህበረሰብ ሳይንስ ተማሪዎችና የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በአጠቃላይ ከ520 በላይ ተማሪዎች በኮምፒውተር የታገዘ የፈተና ስርዓት እንደተፈተኑ የሚታወስ ሲሆን፡፡ የኮሌጁ ኮምንኬሽን ሀምሌ 11/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ